ትምህርት ተቋማት ከተማሪ ወላጆች ጋር በዋጋ ጭማሪ ዙሪያ ባቀረቡት የመነሻ ሃሳብ ላይ ተወያዩ፡፡
(ሰኔ 14 ቀን 2017ዓ.ም) በዛሬው ዕለት የተማሪ ወላጆች በዋጋ ጭማሪ ዙሪያ ውይይት ካደረጉት የትምህርት ተቋማት መካከል ካየናቸው ት/ቤቶች በአራዳ ክ/ከተማ የሚገኘው የራዲካል አካዳሚ ት/ቤት እና ወላጆች ባደረጉት ውይይት ት/ቤቱ የክፍያ ጭማሪ ፕሮፖዛሉን እና የክፍያ መጠኑን ለቤቱ በዝርዝር ያቀረበ ሲሆን ወላጆችም ሰፊ ሃሳቦችን አንስተው ተወያይተዋል፡፡
በዚህም ተቋሙ ጭማሪውን ያደረገበትን ዋና ዋና ሃሳብ ሲያስቀምጥ ለግብዓት ማሟያ፣የትምህርት ጥራት ስታንዳርዱን ለማጠበቅ፣ስቴሽሪ እቃዎችን ለማሟላት፣አስተዳደራዊ ወጪዎችን ለመሸፈን፣የመምህራን ደመወዝን ጭማሪ ለማድረግ፣የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን ለመጠቀም እንዲሁም ሌሎችንም በመዘርዘር ያቀረቡ ሲሆን ወላጆች በቀረበው የመነሻ ሃሳብ ላይ እንደተናገሩት እንደዚህ አይነት የውይይት መድረክ መኖሩ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው የነገ አገር ተረካቢ ልጆችን የምናስተምርበት ተቋም የተሻለ ቢሆንና የተሻለ ውጤት ቢኖረው የሚመኙ መሆናቸውን ጠቅሰው የዋጋ ጭማሪው ላይ ግን በተቋሙ ፕሮፖዛል ላይ የተቀመጠው ዝርዝር ሃሳብ ተግባራዊ እንዲሆኑ ወላጆች አሳስበዋል፡፡
(ሰኔ 14 ቀን 2017ዓ.ም) በዛሬው ዕለት የተማሪ ወላጆች በዋጋ ጭማሪ ዙሪያ ውይይት ካደረጉት የትምህርት ተቋማት መካከል ካየናቸው ት/ቤቶች በአራዳ ክ/ከተማ የሚገኘው የራዲካል አካዳሚ ት/ቤት እና ወላጆች ባደረጉት ውይይት ት/ቤቱ የክፍያ ጭማሪ ፕሮፖዛሉን እና የክፍያ መጠኑን ለቤቱ በዝርዝር ያቀረበ ሲሆን ወላጆችም ሰፊ ሃሳቦችን አንስተው ተወያይተዋል፡፡
በዚህም ተቋሙ ጭማሪውን ያደረገበትን ዋና ዋና ሃሳብ ሲያስቀምጥ ለግብዓት ማሟያ፣የትምህርት ጥራት ስታንዳርዱን ለማጠበቅ፣ስቴሽሪ እቃዎችን ለማሟላት፣አስተዳደራዊ ወጪዎችን ለመሸፈን፣የመምህራን ደመወዝን ጭማሪ ለማድረግ፣የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን ለመጠቀም እንዲሁም ሌሎችንም በመዘርዘር ያቀረቡ ሲሆን ወላጆች በቀረበው የመነሻ ሃሳብ ላይ እንደተናገሩት እንደዚህ አይነት የውይይት መድረክ መኖሩ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው የነገ አገር ተረካቢ ልጆችን የምናስተምርበት ተቋም የተሻለ ቢሆንና የተሻለ ውጤት ቢኖረው የሚመኙ መሆናቸውን ጠቅሰው የዋጋ ጭማሪው ላይ ግን በተቋሙ ፕሮፖዛል ላይ የተቀመጠው ዝርዝር ሃሳብ ተግባራዊ እንዲሆኑ ወላጆች አሳስበዋል፡፡
በሌላ በኩል በጉለሌ ክፍለ ከተማ የሚኘው የሊንደን ውድ አካዳሚ ላይ ተገኝተን ባደረግነው ምልከታ ወላጆች ትምህርት ቤቱ ባቀረበው ፕሮፖዛል መነሻነት በመወያየትና የራሳቸውንም ሃሳብ በማንጸባረቅ ከተወያዩና ድምጽ ከሰጡ በኋላ በመግባባት ውይይታቸውን አጠናቀዋል፡፡
ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅና የጥራት ዘርፍ ሃላፊ በውይይት መደረኮቹ ላይ በመገኘት ወላጆች ለሚያነሷቸው ግልጽነት ለሚስፈልጋቸው ሃሳቦች ግልጽነትን የፈጠሩና ሃሳቦችን ያብራሩ ሲሆን ወላጆችና የትምህርት ተቋማት በሚያደርጉት ውይይት መግባባት ላይ መድረስ ካልቻሉ ልዩነቱን ወደ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በማምጣት የመፍትሄ ውሳኔ ባለስልጣኑ እንደሚሰጥ የገለጹ ሲሆን ነገ እንዲሁም በቀጣይ ሳምንታት በሚኖሩ ውይይቶች በሚያደርጉ ተቋማት ላይ የሚገኙ ወላጆች በውይይቱ ላይ በመገኘትና የነቃ ተሳትፎና የበሰለ ውይይት በማድረግ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡
በተገኘንባቸው መድረኮች ላይ የባለስልጣኑ እና የቅ/ጽ/ቤት አመራሮች፣መድረኩን በታዛቢነት የሚከታተሉ ተወካዮች እንዲሁም የወተመህ ተወካዮች የተገኙ ሲሆን በነገው ዕለትም በሌሎች ተቋማት ላይ ውይይቱ የሚደረግ ይሆናል፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://www.tg-me.com/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅና የጥራት ዘርፍ ሃላፊ በውይይት መደረኮቹ ላይ በመገኘት ወላጆች ለሚያነሷቸው ግልጽነት ለሚስፈልጋቸው ሃሳቦች ግልጽነትን የፈጠሩና ሃሳቦችን ያብራሩ ሲሆን ወላጆችና የትምህርት ተቋማት በሚያደርጉት ውይይት መግባባት ላይ መድረስ ካልቻሉ ልዩነቱን ወደ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በማምጣት የመፍትሄ ውሳኔ ባለስልጣኑ እንደሚሰጥ የገለጹ ሲሆን ነገ እንዲሁም በቀጣይ ሳምንታት በሚኖሩ ውይይቶች በሚያደርጉ ተቋማት ላይ የሚገኙ ወላጆች በውይይቱ ላይ በመገኘትና የነቃ ተሳትፎና የበሰለ ውይይት በማድረግ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡
በተገኘንባቸው መድረኮች ላይ የባለስልጣኑ እና የቅ/ጽ/ቤት አመራሮች፣መድረኩን በታዛቢነት የሚከታተሉ ተወካዮች እንዲሁም የወተመህ ተወካዮች የተገኙ ሲሆን በነገው ዕለትም በሌሎች ተቋማት ላይ ውይይቱ የሚደረግ ይሆናል፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://www.tg-me.com/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
በትምህርት አገልግሎት የዋጋ ጭማሪ ክፍያ ላይ ትምህርት ቤቶች ከወላጆች ጋር ውይይት አደረጉ፡፡፡
(ሰኔ 15 ቀን 2017ዓ.ም) ከወላጆች ጋር ውይይት ካደረጉ ት/ቤቶች መካከል በዛሬው ዕለት በጉለሌ ክ/ከተማ በአሚጎንያ ት/ቤት በመገኘት ውይይቱን የተከታተልን ሲሆን ት/ቤቱ የክፍያ ጭማሪ ያደረገበትን ፕሮፖዛል እና የክፍያ መጠኑን ለወላጆች በዝርዝር ያቀረበ ሲሆን ወላጆችም ሀሳባቸውን በሰፊው አንስተው ተወያይተዋል፡፡
በዚህም ት/ቤቱ በቀጣይ ሶስት አመታት ጭማሪ የሚያደርግበትን ምክንያት ሲያስረዳ ለግብዓት ማሟያ፣የትምህርት ጥራት ስታንዳርዱን ለማጠበቅ፣ስቴሽሪ እቃዎችን ለማሟላት፣አስተዳደራዊ ወጪዎችን ለመሸፈን፣የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን ለመጠቀም እንዲሁም በዋናነት መምህራን ተረጋግተው ማስተማር እንዲችሉ የደመወዝ ጭማሪ ለማድረግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ወላጆች በቀረበው የመነሻ ሃሳብና በምክንያቱ ዙሪያ እንደተናገሩት ከሆነ ጭማሪው የወላጁንም አቅም ግምት ውሰጥ በማስገባት እንዲሆን ት/ቤቱም ቀጣይነት እንዲኖረው በሚያስችል መልኩ እንዲሆን ሃሳብ የሰጡ ሲሆን ከት/ቤቱ እና ከወላጅ በተነሱት ሃሳቦች ሰፊ ውይይትና ክርክር በማድረግ ድምጽ እንዲሰጥ ከተደረገ በኋላ መግባባት ላይ በመድረስ ውይይታቸውን ፈጽመዋል፡፡
በውይይቱ ላይ ያገኘናቸው አቶ ፍቅሩ ገቢሳ በትምርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ እንደገለጹት የትምህርት አገልግሎት ክፍያ አሠራር ሥርዓት ደንብ ቁጥር 194/2017 በከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ መጽደቁ ት/ቤቶች የዋጋ ጭማሪ ሲያደርጉ ደንቡን ተከትለው ጭማሪ እንዲያደርጉ እንዲሁም የዋጋ ጭማሪው በደረጃ በመሆኑ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የሚያግዝ ይሆናል ብለዋል፡፡
(ሰኔ 15 ቀን 2017ዓ.ም) ከወላጆች ጋር ውይይት ካደረጉ ት/ቤቶች መካከል በዛሬው ዕለት በጉለሌ ክ/ከተማ በአሚጎንያ ት/ቤት በመገኘት ውይይቱን የተከታተልን ሲሆን ት/ቤቱ የክፍያ ጭማሪ ያደረገበትን ፕሮፖዛል እና የክፍያ መጠኑን ለወላጆች በዝርዝር ያቀረበ ሲሆን ወላጆችም ሀሳባቸውን በሰፊው አንስተው ተወያይተዋል፡፡
በዚህም ት/ቤቱ በቀጣይ ሶስት አመታት ጭማሪ የሚያደርግበትን ምክንያት ሲያስረዳ ለግብዓት ማሟያ፣የትምህርት ጥራት ስታንዳርዱን ለማጠበቅ፣ስቴሽሪ እቃዎችን ለማሟላት፣አስተዳደራዊ ወጪዎችን ለመሸፈን፣የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን ለመጠቀም እንዲሁም በዋናነት መምህራን ተረጋግተው ማስተማር እንዲችሉ የደመወዝ ጭማሪ ለማድረግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ወላጆች በቀረበው የመነሻ ሃሳብና በምክንያቱ ዙሪያ እንደተናገሩት ከሆነ ጭማሪው የወላጁንም አቅም ግምት ውሰጥ በማስገባት እንዲሆን ት/ቤቱም ቀጣይነት እንዲኖረው በሚያስችል መልኩ እንዲሆን ሃሳብ የሰጡ ሲሆን ከት/ቤቱ እና ከወላጅ በተነሱት ሃሳቦች ሰፊ ውይይትና ክርክር በማድረግ ድምጽ እንዲሰጥ ከተደረገ በኋላ መግባባት ላይ በመድረስ ውይይታቸውን ፈጽመዋል፡፡
በውይይቱ ላይ ያገኘናቸው አቶ ፍቅሩ ገቢሳ በትምርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የጉለሌ ቅ/ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ እንደገለጹት የትምህርት አገልግሎት ክፍያ አሠራር ሥርዓት ደንብ ቁጥር 194/2017 በከተማ አስተዳደሩ ካቢኔ መጽደቁ ት/ቤቶች የዋጋ ጭማሪ ሲያደርጉ ደንቡን ተከትለው ጭማሪ እንዲያደርጉ እንዲሁም የዋጋ ጭማሪው በደረጃ በመሆኑ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ የሚያግዝ ይሆናል ብለዋል፡፡
አቶ ያሬድ ካሳ የባለስልጣኑ የእውቅና ፍቃድ እድሳት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በበኩላችው እንደተናገሩት ለትምህርት ጥራት ግብዓት አንዱ መነሻ ነው ግብአቱን ተጠቅሞ ወደ ሂደት በመቀየር ውጤትን በማምጣት የተሻለ ጥራት ያለው ትምህርት እንዲኖር ያስችላል፤ በመሆኑም ወላጆችና ት/ቤቱ በመስማማት የሚያደርጉት የዋጋ ጭማሪ ት/ቤቱ በአግባቡ በስራ ላይ ማዋሉን ባለስልጣኑ ክትትል እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡
በዛሬው ዕለት በተገኘንበት አሚጎንያ ት/ቤት የባለስልጣኑ እና የቅ/ጽ/ቤት አመራሮች፣መድረኩን በታዛቢነት የሚከታተሉ ተወካዮች እንዲሁም የወተመህ ተወካዮች የተገኙ ሲሆን በቀጣይ ሳምንትም ውይይቱ ባልተካሄደባቸው በሌሎች ት/ቤቶች ላይ ውይይት እንደሚከናወን ታውቋል፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://www.tg-me.com/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
በዛሬው ዕለት በተገኘንበት አሚጎንያ ት/ቤት የባለስልጣኑ እና የቅ/ጽ/ቤት አመራሮች፣መድረኩን በታዛቢነት የሚከታተሉ ተወካዮች እንዲሁም የወተመህ ተወካዮች የተገኙ ሲሆን በቀጣይ ሳምንትም ውይይቱ ባልተካሄደባቸው በሌሎች ት/ቤቶች ላይ ውይይት እንደሚከናወን ታውቋል፡፡
#ፌስቡክ;https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F
#ድረ_ገጽ; educoc.gov.et
#ቴሌግራም https://www.tg-me.com/AAEQOCAA
#ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@educationtraning2?_t=ZM-8u2f6smztvr&_r=1
#ነጻ_የጥቆማ_የስልክ_መስመር_9302
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
ባለስልጣኑ የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያና የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር አካሄደ፡፡
(ሰኔ 16 ቀን 2017ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አመራሮችና አጠቃላይ ሰራተኞች በተገኙበት የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተከናወነ፡፡
በዛሬው የወርቃማ ሰኞ ማለዳ መርሃ-ግብር ላይ አቶ ነብዩ ዳዊት የባለስልጣኑ የእቅድና በጀት ዝግጅትና ክትትል ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የ90 ቀናት የንቅናቄ ተግባራትን እቅድ በዝርዝር አቅርበዋል፡፡በዚህም የበጎ አድራጎት የኢኒሼቲቭ፣የአገልግሎት አሰጣጥና መልካም አስተዳደር፣የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ማጠቃለያ ግምገማ፣የአረንጓዴ አሻራ ሽፋን ማሳደግ፣ት/ት ለትውልድ ንቅናቄ፣ የፋይዳ ምዝገባ እና ኢትዮ ኮደርስ፣ተግባራትን በህዝብ ግንኙነት አግባብ ሽፋን መስጠት በሚሉ ሰባት ግቦች ያሉትና የአፈጻጸም አቅጣጫ እንዲሁም ስራውን የሚያከናውኑ ኮሚቴዎች የተዋቀሩበትን ዝርዝር የያዘ እቅድ ያቀረቡ ሲሆን ውይይትም ተደርጎበታል፡፡
አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ በመርሃ- ግብሩ ላይ እንደገለጹት በቀረበው በ90 ቀናት እቅድ የክረምት ዘላቂ ስራችንን አጠናክረን የአሰራር ግልጽነትን በመፍጠር፣ስራን ከብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ በማከናወንና የእቅዱ አካል ሆነን ከለውጥ ጋር በመጓዝ ለአፈጻጸማችን ውጤታማነት መትጋት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡
(ሰኔ 16 ቀን 2017ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አመራሮችና አጠቃላይ ሰራተኞች በተገኙበት የወርቃማ ሰኞ ማለዳ የማነቃቂያ የእውቀት ሽግግር መርሃ-ግብር ተከናወነ፡፡
በዛሬው የወርቃማ ሰኞ ማለዳ መርሃ-ግብር ላይ አቶ ነብዩ ዳዊት የባለስልጣኑ የእቅድና በጀት ዝግጅትና ክትትል ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የ90 ቀናት የንቅናቄ ተግባራትን እቅድ በዝርዝር አቅርበዋል፡፡በዚህም የበጎ አድራጎት የኢኒሼቲቭ፣የአገልግሎት አሰጣጥና መልካም አስተዳደር፣የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ማጠቃለያ ግምገማ፣የአረንጓዴ አሻራ ሽፋን ማሳደግ፣ት/ት ለትውልድ ንቅናቄ፣ የፋይዳ ምዝገባ እና ኢትዮ ኮደርስ፣ተግባራትን በህዝብ ግንኙነት አግባብ ሽፋን መስጠት በሚሉ ሰባት ግቦች ያሉትና የአፈጻጸም አቅጣጫ እንዲሁም ስራውን የሚያከናውኑ ኮሚቴዎች የተዋቀሩበትን ዝርዝር የያዘ እቅድ ያቀረቡ ሲሆን ውይይትም ተደርጎበታል፡፡
አቶ ኢዘዲን ሙስባህ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ በመርሃ- ግብሩ ላይ እንደገለጹት በቀረበው በ90 ቀናት እቅድ የክረምት ዘላቂ ስራችንን አጠናክረን የአሰራር ግልጽነትን በመፍጠር፣ስራን ከብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ በማከናወንና የእቅዱ አካል ሆነን ከለውጥ ጋር በመጓዝ ለአፈጻጸማችን ውጤታማነት መትጋት ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡