ተአምረ ማርያም ላይ መናፍቃን ጥያቄዎች አንዱ

☞ ጥያቄ. ነፍሳትን በበላው በበላኤ ሰብ ታሪክ ላይ።
☞ መልስ፦ የብላዔ ሰብዕ 78 ነፍስ አጥፍቶ መማሩ በማቴ10:42
"በደቀ መዝሙር ስም ቀዝቃዛ ዉሃ ቢጠጣ እውነት እላችኋለሁ
ዋጋው አይጠፋበትም" በሚለው አምላካዊ ቃል መሰረት ነው::
ተአምረ ማርያም እንደሚነግረን ስምዖን የተባለው ይህ ሰው ብዙ ነፍስ ካጠፋ በሗላ ንስሓ ገባ ተጸጸተ ልክ በቀኝ እንደተሰቀለው ወንበዴ::
በወንጌሉ መሰረት ለድሀ ከደቀመዛሙርት ሁሉ ከፍጥረት
ሁሉ በከበረችው በእመቤታችን ስም ቀዝቃዛ ዉሀ ለድሀ አጠጣ:: እመቤታችም በወንጌሉ መሰረት ማርለኝ አለችው ማረላት:: በቀኝ የተሰቀለ ከብላዔ ሰብዕ (ከዚህ ሰብ በላ) የበለጠ ይሥራ አይሥራ እኛ አናዉቅም::
ቃል ኪዳን ሲሰጥ ክርስቶስ ገደብ አላስቀመጠም (ይህንን ያህል
የገደለ አልምርም የሚል የለ)::
በደቀ መዝሙር ስም ያጠጣ አለ እንጂ:: ስለዚህ የወንበዴውን መዳንም እየተጠራጠሩ በወንጌል አምናለሁ ማለት አይቻልም:: በወንጌል ተጽፎ ነው እንጂ በቀኝ የተሰቀለው ታሪክ በተአምረ
ማርያም ቢጻፍ ኖሮ አይቀበሉትም ነበር::
በመጨረሻም መናፍቃን ከተለያዩ ገድላት፣ድርሳናት፣ተአምራት በመጥቀስ ምዕመንን ለማሰናከል ይኳትናሉና።
በተቻለ መጠን አይታለሉላቸው። ምንም እንኳን ገድሉ ተአምሩ ለማመን ከባድ ቢሆንም ክርስቲያኖች ነንና ከዚህም በላይ እንደሚደረግ እንወቅ!
ጌታ ያለውም ይህንኑ ነው።በእኔ የሚያምን ከዚህ በላይ ያደርጋል
ተብሎ ተፅፋልና!!!..... ሌሎች ጥያቄዎችን እንመለስበታለን  ይቆየን
@And_Haymanot
@And_Haymanot
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#ገድል_ያወጣል_ከገደል
የገድላት ምንነትና አስፈላጊነት እንዲሁም በገድላት ዙርያ የሚጠየቁ ጥያቄዎችን የምንዳስስበት ተከታታይ ትምህርት ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡ ሼር በማድረግ ምዕመናንን የመዳን ሥራ አብረን እንስራ
ክፍል ፩
በዲ/ን ቴዎድሮስ ዘለቀ
@Konobyos
@And_Haymanot
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#ገድል_ያወጣል_ከገደል
ክፍል ፪
@And_Haymanot
ሼር በማድረግ ምዕመናንን የመዳን ሥራ አብረን እንስራ

በዲ/ን ቴዎድሮስ ዘለቀ
@Konobyos
@And_Haymanot
​​ሃያል ነህ አንተ

ሃያል ነህ አንተ ሃያል
ደጉ መልአክ ገብርኤል /2/
ይውደቅ ይሸነፍ ጠላት
አንተ ተራዳን በእውነት /2/
በዱራ ሜዳ ላይ........ገብርኤል
ጣዎት ተዘጋጅቶ.......ገብርኤል
ሊያመልኩት ወደዱ.......ገብርኤል
አዲስ አዋጅ ወጥቶ.......ገብርኤል
ሲድራቅና ሚሳቅ አብናጎም ፀኑ
ጣዎቱን እረግጠው በእግዚአብሔር አመኑ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡እዝ፡፡፡፡፡፡
ተቆጣ ንጉሡ.......ገብርኤል
በሶስቱ ሕፃናት .......ገብርኤል
ጨምሯቸው አለ.......ገብርኤል
ወደ እቶን እሳት.......ገብርኤል
ከሰማይ ተልኮ ደረሰ መልአኩ
ከሞት አዳናቸው እሳት ሳይነኩ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡እዝ፡፡፡፡፡፡
እቶኑ ስር ሆነው........ገብርኤል
ዝማሬ ተሞሉ........ገብርኤል
ገፍተው የጣሏቸው.......ገብርኤል
በእሳቱ ሲበሉ.......ገብርኤል
አልተቃጠለችም የራሳቸው ፀጉር
አዩ መኳንንቱ የእግዚአብሔር ክብር
፡፡፡፡፡፡፡፡፡እዝ፡፡፡፡፡፡
ናቡከደነጾር........ገብርኤል
እጁን በአፋ ጫነ.......ገብርኤል
ሠለስቱ ደቂቅን........ገብርኤል
ከእሳት ስላዳነ.......ገብርኤል
ይክበር ጌታ አለ የላከው መልአኩን
ሊያመልከው ወደደ ስላየ ማዳኑን.
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እንኳን አደረሳችሁ
ገድለ ተክለ ሃይማኖት ፩

@And_Haymanot
ጥያቄ ፩
ገድለ ተክለ ሃይማኖትላይ ‘ሰይጣንን አጠመቁት’ ይላል እያሉ የተሐድሶ መናፍቃን ይተቻሉ፡፡ እውን ግን ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት በቁሙ ሰይጣንን አጥምቀዋልን?

መልስ፡- በቀድሞ መጻሕፍት ሥጋ ለበስ የሆኑ አጋንንት ታሪክ የታወቀ ነው፡፡ እነዚህ ሥጋ ለበስ አጋንንት የአጋንንትን ሥራ የሚሠሩ ቢሆኑም
የሚዳሰስ ሥጋ ግን አላቸው፡፡ ለምሳሌ ድርሳነ ሚካኤል ዘጥር ላይ እንደ ተገለጠው እነዚህ በሽታዎችን ሁሉ የሚያመጡ ሥጋ ለበስ አጋንንት
እንደ ሰው ሁሉ ይታመማሉ፤ ይራባሉ፤ ይሞታሉም፡፡ አንዳንድ ጊዜ በበረሐ ውስጥ አንዳንድ ጊዜም በውኃ ውስጥ ይኖራሉ፡፡

+ በገድለ ተክለ ሃይማኖትና በልደተ አበው ላይ እንዲህ ይላል “አቡነ ተክለ ሃይማኖት በእነዚህ አውራጃዎች ሲመላለስ አንድ ቀን በውኃ ዳር ዐረፍ አለ፡፡ ጋኔንም ከውኃው ወጣና ደቀ መዛሙሩን ያዘው፡፡ አሳመመውም፡፡ እርሱም ጋኔን መሆኑን ዐወቀ፡፡ በረድኡ ላይም በመስቀል ምልክት አማተበበት፡፡ ጋኔኑም ፈጥኖ ወጣ ሸሸ፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም በእጁ ያዘው፡፡ ሥራዩንም አወጣበት፡፡ ያን ጊዜም ለሁሉ ታየ፡፡ እርሱም “ማነው ስምህ?” አለው፡፡ ጋኔኑም “ባሕር አልቀም” አለው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም “ከኔ ጋር ትኖራለህን?” አለው፡፡ እርሱም ገዘረውና ወደ ታላቁ የቤተ ክርስቲያን ምሥጢረ ጥምቀት አገባው፡፡ ስሙንም ክርስቶስ ኀረዮ(ክርስቶስ መረጠው ማለት ነው) አለው፡፡ ረድእም አደረገው፡፡ ወደ በኣቱም አስገባው፡፡ እርሷም አስቦ ናት፡፡ እርሱም እግዚአብሔርን የሚወድና ወንድሞቹንም ሁሉ የሚያስደስት ሆነ፡፡” (ገድለ ተክለ ሃይማኖት፤ነሐሴ 1989 ዓ.ም፤ ምዕራፍ ፶፩፤ ገጽ. 177-178፤ Getachew Haile, Geneaology, P.11&12)

+ በጥንታውያን ሰዎች ዘንድ በአጋንንት አሠራር ተጠምደው የሚኖሩ ጣዖት አምላኪ ሰዎችን ባደሩባቸው አጋንንት ስም መጥራት የተለመደ ነው፡፡ ሰው በውስጡ ባለው ነገር ይጠራልና፡፡ ልክ ጌታ ጴጥሮስን “አንተ ሰይጣን ከኋላየ ሒድ” (ማቴ.16፡23) እንዳለው ማለት ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ታሪኮች በብዙ ጥንታውያን መጻሕፍት አሉ፡፡ ሥጋ ለበስ አጋንንት የሚሏቸው እነርሱን ነው፡፡ የተለያዩ የምትሐት ነገሮችን ይሠራሉ፡፡ በባሕር ይኖራሉ፣ በእሳት ውስጥም ገብተው በደኅና ይወጣሉ፡፡ ዋሊስ ባጅ ባሰተመው የደብረ ሊባኖስ ገድለ ተክለ ሃይማኖት ላይ ጸሐፊው ከሌሎቹ የአካባቢው ቅጅዎች ለየት ብሎ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ያጠመቁት ክፉ መንፈስ ያለበትን ሰው እንጂ መንፈስ የሆነውን ሰይጣን አለመሆኑን በቅዱሳት መጻሕፍት ማስረጃዎች ያብራራል፡፡ (E.A.W. Budge, The Life and Miracles of Takla Hay-manot, (London,1906), P. 80).
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ገድለ ተክለ ሃይማኖት ፪


-------ጥያቄ ፪-------
‘የተክለ ሃይማኖት ተቅማጥ ከክርስቶስ ደም ጋር እኩል ነው’ ይላል ይላሉ፡፡ በውኑ ይላልን?

መልስ፡- ሙሉ ገጸ ንባቡ “ክቡር አባታችንም ጌታዬ ወደ ሰማዕትነት ዐደባባይ ሄጄ በስምህ እንድሞት እዘዘኝ አለው፤ ጌታም መጋደልስ ፈጸምክ ከሞት በቀር ምንም አልቀረህም፡፡” አለው ነው የሚለው፡፡ [ገድለ ተክለ ሃይማኖት፤ነሐሴ 1989 ዓ.ም፤ ምዕራፍ ፶፯፤ ገጽ. 195] ከዚህም በኋላ፡- “ወናሁ ትመውት በሕማመ ብድብድ በእኩይ ሞት ወእሬሲ ለከ ኪያሃ ከመ ስቅለትየ በከመ ደመ ሰማዕት እለ እምቅድሜከ አኮ ለባሕቲትከ አላ ደቂቅከኒ እለ ይመውቱ በሕማመ ብድብድ በውስተ ዛቲ ገዳም እኌልቆሙ ምስለ ሰማዕታት ወአወፍዮሙ ለከ በመንግሥተ ሰማያት፡፡”[ዝኒ ከማሁ] ነው ያለው፡፡

+ የቃሉ የግእዝ ትርጒም ሕማመ ብድብድ ማለት ቸነፈር ማለት ነው፡፡ ጻድቁ ተክለ ሃይማኖት የሞቱት በቸነፈር በሽታ ነው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በዕለተ ዐርብ እንደ ተቀበልኩት መከራ መስቀል አደርግልሃለሁ ያለው፤ ገድላቸውንና በደዌ የተቀበሉትን መከራ ነው፡፡ በመልክዐ ጊዮርጊስ ላይም እንዲህ የሚል አብነት ይገኛል፡፡ ሰላም ለሰኳንዊከ ምስለ ክልኤሆን መከየድ፡፡ ለአጻብዒከ ሰላም ወለአጽፋረ እግርከ አምሳለ መረግድ፡፡ ገባሬ መንክራት ጊዮርጊስ በአቊጽሎ ይቡስ ዐምድ፡፡ አድኅነኒ በጸሎትከ እምነ መከራ ክቡድ፡፡ እስመ እምኔሁ ይወጽእ ቀታሊ ብድብድ፡፡ (መልክዐ ጊዮርጊስ) ትርጓሜውም፡- ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ በሁለቱ ተረከዞችህ ጋር ለጫሞችህ ሰላም እላለሁ፡፡ እንደ ከበረ ዕንቊ ለሚያበሩት ለእግር ጽፍሮችህና ጣቶችህም ሰላም እላለሁ፡፡ ተአምር አድራጊው ሰማዕት ሆይ! ደረቁን ምሰሶ ለምለም ተአምራትህን ገልጸሃልና፡፡ ከጽኑ መከራ በጸሎትህ አድነኝ፡፡ ሰውስ ለሥቃይ የሚዳርጉ ረኀብ ቸነፈር ከእሱ ይፈልቃሉና፡፡ ማለት ነው፡፡ ስለሆነም "ብድብድ" የሚለው ረኀብ፤ ቸነፈር ተብሎ ይተረጎማል፡፡

+ የተሐድሶ መናፍቃኑ እንደ ሚሉት ‘ተቅማጥህ እንደ ስቅላቴ ደም ነው’ የሚል ሐረግም ከገድሉ ላይ አይገኝም፡፡ “… እሷንም እንደ ስቅላቴና ካንተ በፊት እንደ ነበሩ ሰማዕታት ደም እቆጥርልሃለሁ፤” [ዝኒ ከማሁ(Ibid)] ነው ያለው፡፡ ይህም ማለት የተክለ ሃይማኖት ሕማም ከሰማዕታት ደም ጋር እኩል እንደሆነ እንጂ ከክርስቶስ ደም ጋር እኩል እንደሆነ አያስረዳም፡፡
ይህም የሆነበት ምክንያት ከገድሉ ላይ እንደምንረዳው መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አባ ተክለ ሃይማኖት ብዙ ተጋድለሃል ከእንግዲህ ይበቃሃል ነፍስህ ከመከራ ተለይታ ወደ እረፍት መሄጃህ ጊዜ ደርሷል ባላቸው ጊዜ አባ ተክለ
ሃይማኖት በሰማዕትነት እንድሞት አድርገኝ ብለው ስለለመኑት ነው፡፡ + በሚሞቱበት ጊዜ የሚደርስባቸውን ሕማም እንደ ራሱ መከራና በጦር ተወግተው በስለት ተቆርጠው ደማቸው እንደ ፈሰሰው ሰማዕታት ደም ሲቆጠርላቸው ነው፡፡ ሰማዕታት ለክርስቶስ ሲሉ በጦር ተወግተው በስለት ተቆርጠው ደማቸው እንደሚፈስ አባ ተክለ ሃይማኖትም ለክርስቶስ ሲሉ ሃገር ለሃገር ጫካ ለጫካ ሲንከራተቱ ሕማመ ብድብድን (ቸነፈርን) በጦር ተወግተው ደማቸው እንደፈሰሰው ሰማዕታት ቆጠረላቸው፡፡ ስለዚህ የአባ ተክለ ሃይማኖት ሕማመ ብድብድ (ቸነፈር) እንደ ሰማዕታት ደም ሆኖ ቢቆጠር ሃይማኖት ላለውና ለሚያስተውል ሰው አያደንቅም፡፡
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
​​ገድሉ ተአምራቱ

@And_Haymanot

ገድሉ ተአምራቱ እጅግ ብዙ ነው 
ጣኦትን አዋርዶ የተሸለመው 
የተዋሕዶ ኮከብ ተክለሐዋርያ 
አባ ተክለ ሃይማኖት ዘኢትዮጵያ 
አዝ ------------------ 
ዳግማዊ ዮሐንስ ጠፈር የታጠቀ 
ንጹሕ ባህታዊ ጠላት ያስጨነቀ 
የጸጋ ዘአብ ፍሬ ዛፍ ሆኖ በቀለ 
በደብረ ሊባኖስ መናኝ አስከተለ 
አዝ --------------------- 
ደካማ መስሏቸው በአንድ እግሩ ቢያዩት 
ባላስድስት ክንፉ ጻድቁ የእኔ አባት 
እርሱስ አንበሳ ነው ትናገር ደብረ አስቦ 
ሌጌዎን ሲዋረድ እፍረት ተከናንቦ 
አዝ ----------- 
ከካህናት መካከል ኅሩይ ነው አቡዬ 
መጣው ከገዳምህ ልሳለለምህ ብዬ 
ኢትዮጵያዊው ቅዱስ አባ ተክለሃይማኖት 
ወልድ ዋሕድ ብለህ ምድሪቱን ቀደስካት 
አዝ ----------------- 
የባረከው ውኃ የረገጥከው መሬት 
ጥላህ ያረፈበት ሆንዋል ጸበል እምነት 
ኑና ተመልከቱ ድውያን ሲፈቱ 
ይሰብካል ተክለአብ ዛሬም እንደጥንቱ 
አዝ ------------------
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ገድለ ተክለሃይማኖት ፫


@And_Haymanot
ጥያቄ ፫
፫. “ከሩቅም ከቅርብም ቢመጣ ወደ መቃብርህ የሄደውን እኔ ወደ መቃብሬ ኢየሩሳሌም እንደ ሄደ አደርገዋለሁ፤ በመታሰቢያህ ቀን ሥጋውን ደሙን የተቀበለውንም ስማቸው ከተጠራው ገድላቸው ከተነገረው ልጆችህ ጋራ እኔ እቈጥረዋለሁ፡፡” [ገድለ ተክለ ሃይማኖት፤ነሐሴ 1989 ዓ.ም፤ ምዕራፍ ፶፯፤ ገጽ. 193] ማለት ምን ማለት ነው?

+ መልስ፡- ወደ መቃብርህ የመጣውን ወደ መቃብሬ እንደመጣ አደርገዋለሁ ማለት በአንተ አማላጅነት በእኔ በርነት ወደ መንግሥተ ሰማያት ይገባል ማለት ነው፡፡ ይህም እናንተን የተቀበለ
እኔን ተቀበለ ያለው የወንጌል ቃል በተግባር ሲተረጎም ነው፡፡ + በተክለ ሃይማኖት በመቃብር ላይ በተክለ ሃይማኖት ስም በተሠራው የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ወደ ሚገኝበት በመምጣት በመጸለይ ወደ መንግሥተ ሰማያት መግባት ነው፡፡ የእግዚአብሔር በረከት ወደሚገኝበት ቦታ በመሄድ ዋጋ እንደሚገኝም መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምረናል፡፡ 2ኛ.ነገ.5፡1፤
ዕብ. 11፡23፤ ሩት. 1፡16-18፡፡

+ “በመታሰቢያህ ቀን ሥጋውን ደሙን
የተቀበለውንም ስማቸው ከተጠራው ገድላቸው ከተጻፈው ልጆችህ ጋር እኔ አኖራቸዋለሁ፡፡” የሚለውም ቃል የኢየሱስ ክርስቶስን መግቢያ
በርነት የበለጠ ያስተምራል እንጂ

አያስቀርም፡፡ በአንተ መታሰቢያ
ዕለት የእኔን ሥጋና ደም ተቀብሎ በአንተ አስተማሪነት በእኔ በርነት ወደ መንግሥተ ሰማያት ይገባል ማለት ነው፡፡

፬ የመናፍቃን ጥያቄ ከገድለ ተክለሐይማኖት ውስጥ: "እባብን የገደለ ይጽድቃል" ይላል፡፡ ስለዚህ ሰዎች ሁሉ እባብን እየፈለጉ ለመጽደቅ እባብን መግደል አለባቸው ወይ የሚል ነው። አይ ይህቺ የመናፍቃን ጭንቅላት ትንሽ ብትሰፋ! ወገኖቼ መጸሐፍ ቅዱስ እውርን እውር ቢመራው ተያይዞ ገደል መግባት ነው ይላል:: አንዱ ብርሃን መሆን አለበት:: ዛሬ ብዙ ሰዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ታውረዋል፡፡ አባታችን ተክለ ሐይማኖት ይፈውሱዋቸው አሜን :: ወገኖቼ እባብን የገደለ ይጸድቃል ማለት እባብ የተባለ ዲያቢሎስ ነው:: ለምሳሌ ያህል በመዝሙር ምህራፍ 73 ቁጥር 14 እንዲህ ይላል “አንተም የዘንዶውን እራስ ቀጠቀጥክ ለኢትዮጵያ ሰዎችም ምግባቸውን ሰጠሃቸው፤” ይላል :: ታዲያ አንተ የዘንዶውን እራስ ቀጠቀጥክ
ሲል ታዲያ እግዚአብሔር ዘንዶ ያለበትን እየሔደ እራስ እራሱን ቀጠቀጠው ማለት ነውን? አይደለም :: ዘንዶ የተባለው ሰይጣን ነው:: ሰይጣንን ደግሞ እግዚአብሔር በመስቀሉ
ቀጥቅጦታል :: እንዲሁም ገድለ ተክለ ሐይማኖት ላይም እባብን የገደለ ይጽድቃል ሲል ሰይጣንን የገደለ ይጸድቃል ማለቱ ነው :: ሰይጣንን የምንገለው ደግሞ በጾም በጸሎት እና በስግደት ነው:: በነዚህ እባብ (ዲያቢሎስን ) መግደል እንችላለን:: በተጨማሪም ደግሞ ራእይ ዮሐንስ ምህራፍ 12 ቁጥር 7 እንዲህ ይላል፡- “በሰማይም ሰልፍ ሆነ ሚካኤልና ሰራዊቱ ዘንዶውን ተዋጉት :: ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋር ተዋጋ አልቻላቸውም፤ ከዚያም ወዲያ በሰማይ ስፍራ አልተገኘላቸውም:: ዓለሙን ሁሉ የሚያስት ዲያቢሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፡፡ ወደ ምድርም ተጣለ፤ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ፤” ይላል:: ታዲያ ሚካኤልና ቅዱሳን መላእክቱ ከዘንዶው ጋር ተዋጉ ሲል ከእንስሳ ጋር ተዋጉ ማለት ነውን? አይደለም፡፡ ዘንዶ የተባለው የቀደመው ሰይጣን እርሱ ዲያቢሎስ ነው ይለናል:፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
---------ልቦናን ያድልልን -----------
ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡
Join
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
የአበው ሃይማኖት አትታደስም፡፡
እንኳን ለ ለብርሃነ ልደቱ ፤ በሰላም አደረሳችሁ።

"በጎል ሰከበ አፅርቅት ተጠብለለ 
ቤዛ ኩሉ ዓለም ዮም ተወልደ"
በበረት ተኛ በጨርቅ ተጠቅለለ፡
የዓለም መድኃኒት ዛሬ ተወለደ
   🕯🕯📖📖🕯🕯
        📖📖📖
" ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።"
(ኢሳ 7: 14)
       📖📖📖
" እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፥ ትርጓሜውም፦ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል ነው።"
(ማቴ 1: 23)
     📖📖📖
" ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና  አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል ስሙም ድንቅ መካር" ኃያል "አምላክ" የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።"
(ኢሳ 9: 6)
መልካም የገና በአል ይሁንላችሁ:)
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ኃጢአትን ለንስሓ አባት/ለካህን መናዘዝ/

@And_Haymanot

ተወዳጆች የተሀድሶ መናፍቃን ምዕመናንን ከንስሃ ህይወት ለማራቅ ሃጢአትን ለንስሃ አባት መናዘዝ አያሥፈልግም በማለት ሀጢአትን ለካህን መናዘዝን ይቃወማሉ፡፡ እናት ቤተክርስቲያናችን መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት አድርጋ እንዲህ ታሥተምራለች
@And_Haymanot
ካህን የእግዚአብሔር ምሥጢራት አስፈፃሚ ስለሆነ ኃጢአትህን ንገረው ። ይህን ቅዱስ ጳውሎስም አስረግጦ ጽፎልሃል ። " እንዲሁ ሰው እኛን እንደ እግዚአብሔር ምሥጢር መጋቢዎች ይቁጠር ።" 1ቆሮ 4*1
አስቀድሞም በነቢዩ ሚኪያስ ያደረው እግዚአብሔር ሲናገር "ካህኑ የሠራዊት ጌታ የእግዚአብሔር መልእክተኛ ነው "ይላል ።

ኃጢአትህን ለካህን በምትነግርበት ጊዜ የሚሰማህን ኃፍረት መሸማቀቅ ሁሉ ችለህ የመመለስን ምሥጢር እንዲያስፈጽምልህ ስትጥር እግዚአብሔር ደግሞ ይህን ድርጊትህን እንደ ታላቅ መሥዋእትነት ቆጥሮልህ ኃጢአትህን ሁሉ ይደመስስልሃል ።/ ዩሐ 20*21*23/ ማቴ 18*18

ካህኑ ክርስቶስ በሰጠው በዚህ ሥልጣን መሠረት ከኃጢአት እሥራት መፈታትህን ያረጋግጥልሀል ። ሕይወት ለሚሆነው ሥጋና ደሙ እንድትበቃም ያደርግሃል ።/1ቆሮ 11*27/

በሕይወትህ ውስጥ የሚታዩትን ጉድለቶች (መንፈሳዊ ድክመቶች )እየተመለከተም እንዴት አሸናፊ መሆን እንደምትችል የሚመክርህ መንፈሳዊ መሪህ ካህን የንስሓ አባት መሆኑንም አትዘንጋ ።

ለካህን ኃጢአትን መናዘዝህ በራሱ የሚያተርፍልህ ነገር አለው ። ኃጢአትን መልሰህ ስትናገረው ለአንተ ለራስህ ምን ያህል አሳፋሪ እንደሆነ ይሰማሃል ። ይህም ዳግም እንዳትመለስበት ታላቅ ትምህርት ይሰጥሀል ። መጽሐፍ ቅዱስም የሚለው ይህንኑ ነው ። " እርስ በእርሳችሁ ኃጢአታችሁን ተናዘዙ ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ሰው ስለሌለው ይጸልይ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች ።" /ያዕ 5*16 /

ምንጭ @pope_shenouda
@pope_shenouda
___፩ ሃይማኖት_______
ላልደረሳቸው እናዳርስ
@And_Haymanot
ቤተክርስቲያን ባህረ ጥበባት አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት የሲኦል ደጆች አይችሏትም ቤተክርስቲያን
@And_Haymanot
#______አትታደስም______!
የሐዋርያት ጉባኤ ስለሆነች ስለአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰላም እንማልዳለን! (መጽሐፈ ሚስጢር)
@And_Haymanot
ኦርቶዶክስ መልስ አላት
@And_Haymanot
============================
፩ ጌታ
፩ ሃይማኖት
፩ ጥምቀት ኤፌ4:5
ሰበር ዜና

ቅዱስ ሲኖዶስ መንግስት የቤተ ክርስቲያኒቱን መብት የማያስከብር ከሆነ ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጀምሮ መላው ኦርቶዶክሳውያን የሚሳተፉበት ሰላማዊ ሰልፍ በመጥራት በደሉን ለዓለምዓቀፉ ማኅበረሰብ እንደሚገልጽ አስታወቀ።
@And_Haymanot
Channel photo updated
የፍርሃት ምንጩ ጠላትን ማተለቅ ሲሆን
የእምነት ምንጩ
የእግዚአብሔርን ታላቅነት ማየት ነው🙏 ከነገሮች በላይ አምላካችን ታላቅ ነው!😊🙏
@And_Haymanot
#እናስተውል

በሆነው እና በሚሆነው በጎ ነገር ሁሉ እግዚአብሔርን ከማመስገን በቀር "እኛ እኮ እንዲህ ነን!" የሚል ግብዝነት ክርስቲያናዊ አይደለምና 'ራሳችንን እናርቅ!!
#እግዚአብሔር_ይመስገን!!
©Yared Shumete - ያሬድ ሹመቴ
ከእንግዲህ ቤተ ክርስቲያን ችግር ሲገጥማት ጠብቀን የምንሰበሰብባት ስፍራ አትሆንም !!! በጊዜውም ያለ ጊዜውም በደጇ እንፅና !!!ሊያጠፏት የሚፈልጉ ጠላቶች እንዳሏት ካወቅን የኛ ድርሻ ከደጇ ባለመጥፋትም ፣ በፀሎትም ፣ በአንድነትም ፣ በመናበብም ፣ ባለመዘናጋትም ፥ ተጠናክከረን ከአጥፊዎቿ ተሽሎ መገኘት ነው።
©Belay
@And_Haymanot
"ወዳጄ ሆይ! ክርስቲያን ነህን? እንኪያስ በፍጹም ወንድምህን አትናቀው፡፡ እኅትህን አትናቃት፡፡
ምንም ይኹን ምን ሰውን አትናቅ፡፡ ይህ የምትንቀው ወንድም በተለይ ክርስቲያን ከኾነ ክርስቶስን እየሰደብከው እንደኾነ አስተውል፡፡ እንዴት? ያልከኝ እንደኾነ ይህ የምትንቀው ወንድምህ የክርስቶስ ሕዋስ (ብልት) ኾኗል፡፡ የክርስቶስ ሕዋስ ከኾነ ደግሞ እርሱን ናቅኸው ማለት
ክርስቶስን ናቅኸው ማለት ነውና ወንድምህን የምትንቅ ከኾነ በጲላጦስ አደባባይ ጌታን ከገረፉት፣ ዕራቁቱን ከሰቀሉት፣ሐሞትን ቀላቅለው ካጠጡት፣ በፊቱ ላይ ከተፉበት ሰዎች በምንም አትተናነስም፡፡ ስለዚህ ወንድምህን እኅትህን ከመናቅ ተጠንቀቅ፡፡”
~ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፥ ሰማዕትነት አያምልጣችሁ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
ሰኞ
ሰሙነ ሕማማት የመጀመርያው ዕለት
@And_Haymanot
ማክሰኞ
ሰሙነ ሕማማት ሁለተኛው ዕለት
@And_Haymanot
እንኳን ደስ አለህ መምህራችን
2024/05/23 13:56:12
Back to Top
HTML Embed Code: