👏10
👍46🤬2
👍5👏3
ተማሪዎች ባሉባቸው ዩኒቨርስቲዎች የግብር ከፋይ መለያ ቁጥሩን እንዲያገኙ የሚደረግበትን አሰራር ለማመቻቸት እየተሰራ ነው ገቢዎች ሚንስቴር ።
በ2018 የትምህርት ዘመን ወደ መንግሥት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለሚገቡ ተማሪዎች፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) በሁሉም ቅርንጫፎች እየሰጠ መሆኑን የገቢዎች ሚኒስቴር ለአሐዱ አስታውቋል፡፡
በሚኒስቴሩ የታክስ ከፋዮች ምዝገባ እና አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ደረጄ ፋና፤ የከፍተኛ ትምህርት ወጪ መጋራትን በተመለከተ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ሲጨርሱ ክፍያ የመክፈል በሕግ የተቀመጠ ኃላፊነት እንዳለባቸው ገልጸዋል።
ይህንን የወጪ መጋራት ክፍያን ለመሰብሰብ እንዲያመች በአዋጁ መሠረት ለገቢዎች ሚኒስቴር በተሰጠው ኃላፊነት፤ በግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ተግባራዊ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡
አሰራሩ አዲስ አበባን ጨምሮ በክልል ከተሞች ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን አንስተው፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥሩን የፌዴራል ዋና ኦዲተር ተቋማት ወይም ቀጣሪዎችና ባለድርሻ አካላት የወጪ መጋራትን ከመሰብሰብ አንፃር የተሰራው ሥራ ክፍተት ያለበት ሆኖ በመገኘቱ ያለውን አሰራር ለማሻሻል ያለመ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ተማሪዎች የወጪ መጋራት ክፍያቸውን በግብር ከፋይ መለያ ቁጥር በቀላሉ መፈፈም እንዲችሉ ለማድረግም ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም መሠረት የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አዲስ እና ነባር ተማሪዎች በሙሉ የፋይዳ ቁጥር በመያዝ፤ በሁሉም የገቢዎች ቢሮ ቅርንጫፎች በመገኘት የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር በመውሰድ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
ተማሪዎች ባሉባቸው ዩኒቨርስቲዎች የግብር ከፋይ መለያ ቁጥሩን እንዲያገኙ የሚደረግበትን አሰራር ለማመቻቸት እየተሰራ ነው ተብሏል ።
አሐዱ ሬዲዮ
@DBU11
@DBU11
በ2018 የትምህርት ዘመን ወደ መንግሥት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለሚገቡ ተማሪዎች፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) በሁሉም ቅርንጫፎች እየሰጠ መሆኑን የገቢዎች ሚኒስቴር ለአሐዱ አስታውቋል፡፡
በሚኒስቴሩ የታክስ ከፋዮች ምዝገባ እና አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ደረጄ ፋና፤ የከፍተኛ ትምህርት ወጪ መጋራትን በተመለከተ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ሲጨርሱ ክፍያ የመክፈል በሕግ የተቀመጠ ኃላፊነት እንዳለባቸው ገልጸዋል።
ይህንን የወጪ መጋራት ክፍያን ለመሰብሰብ እንዲያመች በአዋጁ መሠረት ለገቢዎች ሚኒስቴር በተሰጠው ኃላፊነት፤ በግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ተግባራዊ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡
አሰራሩ አዲስ አበባን ጨምሮ በክልል ከተሞች ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን አንስተው፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥሩን የፌዴራል ዋና ኦዲተር ተቋማት ወይም ቀጣሪዎችና ባለድርሻ አካላት የወጪ መጋራትን ከመሰብሰብ አንፃር የተሰራው ሥራ ክፍተት ያለበት ሆኖ በመገኘቱ ያለውን አሰራር ለማሻሻል ያለመ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ተማሪዎች የወጪ መጋራት ክፍያቸውን በግብር ከፋይ መለያ ቁጥር በቀላሉ መፈፈም እንዲችሉ ለማድረግም ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም መሠረት የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አዲስ እና ነባር ተማሪዎች በሙሉ የፋይዳ ቁጥር በመያዝ፤ በሁሉም የገቢዎች ቢሮ ቅርንጫፎች በመገኘት የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር በመውሰድ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
ተማሪዎች ባሉባቸው ዩኒቨርስቲዎች የግብር ከፋይ መለያ ቁጥሩን እንዲያገኙ የሚደረግበትን አሰራር ለማመቻቸት እየተሰራ ነው ተብሏል ።
አሐዱ ሬዲዮ
@DBU11
@DBU11
👍6🤬1
የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ አዲስ የቃልኪዳን ቤተሰብ ምስረታ ስምምነት ፈራረመ
በመስከረም 8/2018 ዓ.ም፣ ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎች የቃልኪዳን ቤተሰብ ምስረታ የሁለትዮሽ የጋራ ስምምነት በተሳታፊ አካላት መካከል ተፈራረመ። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አስማረ መለሰ በመነሻ ንግግሩ የቃልኪዳን ቤተሰብ ምስረታ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተ መሆኑን አስታውቆ አሁን ላለው ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታ መፍትሄ ሰጭ መሆኑን ገልፀዋል።
የተማሪዎች ከቤተሰብ ርቀት የሚያስከትለውን የመነጠል ስሜት ለመቀነስ፣ በአካባቢው ባህልና ወግ ስምምነት በማድረግ ተማሪዎች እንደ ሁለተኛ ቤታቸው ደብረብርሃንን እንዲያውቁ የሚያበረታታ እና የተማሪ ህይወትን የሚያስተካክል አጋጣሚ ነው ተብሏል።
በፕሮግራሙ የሃይማኖት አባቶች፣ የከተማው ም/ል ከንቲባ፣ የክፍለ ከተማ አመራሮች፣ የዩኒቨርሲቲው ዳይሬክተሮችና ዲኖች ተሳትፎ ያደረጉበት ነው።
በመጨረሻ፣ የፕሮግራሙ መዝገበ ፊርማ በፕሬዚዳንት ዶ/ር አስማረ መለሰ እና የከተማው ም/ል ከንቲባ አቶ ወርቃለማሁ ኮስትሬ ተካሂዷ ፕሮግራሙ ተጠናቋል።
@DBU11
@DBU111
በመስከረም 8/2018 ዓ.ም፣ ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ ለተማሪዎች የቃልኪዳን ቤተሰብ ምስረታ የሁለትዮሽ የጋራ ስምምነት በተሳታፊ አካላት መካከል ተፈራረመ። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር አስማረ መለሰ በመነሻ ንግግሩ የቃልኪዳን ቤተሰብ ምስረታ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተ መሆኑን አስታውቆ አሁን ላለው ሀገራዊ ነባራዊ ሁኔታ መፍትሄ ሰጭ መሆኑን ገልፀዋል።
የተማሪዎች ከቤተሰብ ርቀት የሚያስከትለውን የመነጠል ስሜት ለመቀነስ፣ በአካባቢው ባህልና ወግ ስምምነት በማድረግ ተማሪዎች እንደ ሁለተኛ ቤታቸው ደብረብርሃንን እንዲያውቁ የሚያበረታታ እና የተማሪ ህይወትን የሚያስተካክል አጋጣሚ ነው ተብሏል።
በፕሮግራሙ የሃይማኖት አባቶች፣ የከተማው ም/ል ከንቲባ፣ የክፍለ ከተማ አመራሮች፣ የዩኒቨርሲቲው ዳይሬክተሮችና ዲኖች ተሳትፎ ያደረጉበት ነው።
በመጨረሻ፣ የፕሮግራሙ መዝገበ ፊርማ በፕሬዚዳንት ዶ/ር አስማረ መለሰ እና የከተማው ም/ል ከንቲባ አቶ ወርቃለማሁ ኮስትሬ ተካሂዷ ፕሮግራሙ ተጠናቋል።
@DBU11
@DBU111
🤔4👌3
