Telegram Web Link
Forwarded from 【Naty.B】
አስራት ወልደየስ ካምፓስ
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ

@dbu11
@dbu_entertain
ባዶ ጄሪካኖችን በጨረታ ለሽያጭ ቀርበዋል።

ባለ 3

ባለ 5

ባለ 20 አለ ተብላችኃል

@DBU11
@DBU11
ለድህረምርቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ

ወደ ዩኒቨርሲቲው ዌብ ፔጅ ለመግባት ይህን ይጫኑ


@DBU11
የመውጫ ፈተና ለምትወስዱ ኤክስቴንሽን ተማሪዎች በሙሉ


@DBU11
@DBU_ENTERTAIN
ለሁለተኛ ዓመት ተማሪዎች ሁሉ እንኳን ለሃፍ ላይፍ አደረሳችሁ እያልን

ዕለቱን ምክኒያት በማድረግ በልዩ ቅናሽ
በሚፈልጉት የቲሸርት ኳሊቲ እና የህትመት አይነት ፈጣን የህትመት ስራዎችን እኛ ጋር ያገኛሉ።

ከነፃ ዴሊቨርሲ አገልግሎት ጋር በልዩ መስተንግዶ እንቀበሎታለን።
ይደውሉ
0940219376
0918908467
ወይም @natiTg2 ላይ ያናግሩን

@DBU11
@DBU_ENTERTAIN
የኢኮኖሚ ድጋፍ ተጠቃሚ የሆናችው ሴት ተማሪዎች ነገ ማለትም ሐሙስ 6-10-2016ዓ.ም ከቀኑ 7:30 ጀምሮ በ PR አዳራሽ እንድትገኙ ሲል የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ጥሪ አስተላልፏል ።

@DBU_ENTERTAINMENT
@DBU11
#ይነበብ

የፕሬዝዳንሻል ሜንተርሺፕ ስልጠና ተሳታፊ የነበራችሁ የሴት ተማሪዎች በሙሉ የምርቃት መዝጊያ መርሃ ግብር በአዲስአበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ስለሆነ በነገው ዕለት ማለትም አርብ 07-10-16 ዓ.ም ከቀኑ 6 ሰዓት በዩኒቨርስቲው አስተዳደር ህንፃ ስር የትራንስፖርት አገልግሎት ስለተዘጋጀ በሰዓቱ ተገኝቻችሁ እንድጓዙ እናሳስባለን።

የሴ/ህ/ወ ዳይሬክቶሬት
@dbu_entertain
@dbu11
የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ እየተሰጠ ይገኛል።

ከሰኔ 3-10/2016 ዓ.ም ይሰጣል ተብሎ የተጠበቀው የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና በደብረ ብርሃን ዩኒቨርስቲ በጥሩ አፈፃፀም እየተሰጠ ይገኛል።

የማህበራዊ ሳይንስ  ተማሪዎች የመጨረሻ ፈተናቸውን ዛሬ የሚወስዱ ሲሆን በአንፃሩ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተናቸውን ዛሬ ጀምረዋል።

በዩንቨርስቲአችን  ያገኘናቸዉ  የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች  ለፈተናው ከየካቲት አጋማሽ ጀምሮ  የነበሩ ወራቶችን ሲዘጋጁ እንደነበር ገልፀውልናል።

ተፈታኞቹም በጥራት መዘጋጀታቸውን ጠቁመው  በመጨረሻም ጥሩ ውጤት እንደሚጠብቁ dbudaily ያነጋገራቸው ተማሪዎች ገልፀዋል።

እንደሚታወቀው የሬሜዲያል ፈተና በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ብቻ የሚሰጥ ሲሆን፤ ተቋማቱ ለፈተናው ትኩረት ሰተው እየሰሩ መሆኑን ተመልክተናል።

ዘንድሮ 78 ሺህ የሪሚዲያል ተማሪዎች ከባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ውጪ በሁሉም የ መንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን ከታህሳስ ወር ጀምሮ ሲከታተሉ ቆይተዋል፡፡

@dbu11
ክሪፕቶ ከረንሲ ምንድነው

ዲጂታል ወይም ቨርቹዋል የሚባል ደህንነቱ የተጠበቀ ብሎክ ቼይን (Block chain) የባንክ ሲስተም ነው።

ዲ-ሴንትራላይዝድ በሆነ ኮምፒውተር ሲስተም የታገዘ ማለትም ይህን እንቅስቃሴ የሚቆጣጠረው ራሱ ሲስተሙ እንጂ ማንነቱ የተወሰነለት አካል አይደለም።

ይህም ከብሎክቼይን ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ለደህንነት ስጋት እንደማይፈጥር የዘርፉ ምሁራን ይገልፃሉ።

This decentralized structure allows cryptocurrencies to exist outside the control of governments and central authorities

የዚህም ግብይት  ሂደት online ብቻ የሚደረግ ይሆናል። እሱም እስካሁን ከኖርንበት የገንዘብ ዝውውር ጋር የራሱን ምንዛሬ በቀንና በሰዓት ያሳውቃል። በዚህም ሰዎች የራሳቸውን ኮይን ይሸጣሉ። ይገዛሉ።

ይህን ሲስተም በሙሉ እና በከፊል ህጋዊ አድርገው የተቀበሉ ሃገራት ብዙ ሲሆኑ እንደምሳሌም
- El Salvador
- European Union
- United States
- Canada
- Japan
- South Africa ጥቂቶቹ ናቸው።

በአንፃሩም በሃገራቸው ላይ በከፊልም ሙሉ በሙሉ እገዳ ከታሉ ሃገራት መካከል ጥቂቶቹ
Algeria
- Egypt
- Morocco
- Nigeria
- Bolivia
- Afghanistan
- Bangladesh
ይገኙበታል።

በሃገራችን ዲጂታል ከረንሲ መፈቀዱ ሙሉ በሙሉ ያልተረጋገጠ ሲሆን ነገር ግን የዚህ አካል የሆነው የካፒታል ማርኬት ስርዓት ህጋዊ ሆኖ እንዲቀጥል በቅርቡ ይፋ ተደርጓል።(በባንክ ስርዓት ውስጥ ባይገባም እግድ አልተጣለበትም።

ዝርዝር ነገር ከፈለጋችሁ በኮሜንት ስር አሳውቁኝ።

ይቀጥላል...

@DBU11
@DBU_ENTERTAIN
የቀጣይ አመት በጀት 1.03 ቢሊዮን ብር ለ ደብረ ብርሀን ዩኒቨርሲቲ ተመደበ።

ከ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ከተመደበላቸው ዩኒቨርሲቲዎች መካከል ደብረ ብርሀን ዩኒቨርሲቲ  13 ደረጃ ይገኛል ።

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 1.9 ቢሊዮን ብር በጀት የመጀመሪያው ደረጃ ላይ ይገኛል ። በሁለተኛ ደረጃ ባህርዳር :ጎንደር :ጂማ :ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በቅደም ተከተል ተቀምጠዋል።

ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ በ1.03ቢሊዮን ብር በጀት 13ተኛ ደረጃ ይገኛል ።

የተመደበው በጀት በዩኒቨርስቲዎች እቅድ መሠረት ነው ።

@DBU11
@DBU11
ማስታወቂያ

በ ሰላም ሚኒስትር እና በ ትምህርት ሚኒስተር  ትብብር  የ በጎ አድራጎት ስልጠና  ስትከታተሉ ቆይታችሁ ዛሬ ስልጠናውን የ ጨረሰችሁ ተማሪዎች ከላይ በምስሉ በተቀመጠው የስም ዝርዝር መሰረት  የመረጃ ጉድለት ያለባችሁ ነገ(አርብ) ጧት ከ 1:00_2:00 ድረስ ብቻ በማሰልጠኛ  ቦታችሁ በአካል መታችሁ እንድታስተካክሉ እናሳስባለን።

አስተባባሪዎች


@DBU11
በሀኪም ግዛው ሆስፒታል የተመላላሽ ህክምና ፋርማሲ በአዲስ መልኩ አገልግሎት መስጠት ጀመረ
----------------------------------------------------------------------
የደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ሀኪም ግዛው ሆስፒታል የተመላላሽ ህክምና ፋርማሲ በአዲስ መልኩ አገልግሎቱን በስፋትና በጥራት መስጠት ጀመረ፡፡

ማዕከሉ የተገልጋዮቹን ምቾት በጠበቀ መልኩ አገልግሎቱን መስጠት የሚያስችል ሰፊ ማረፊያ ቦታ ያለው፣ በልዩ ሁኔታ የምክር አገልግሎት አግኝተው የሚስተናገዱ ባለጉዳዮች የሚስተናገዱበት ክፍል ያለው፣ አላስፈላጊ እንግልቶችን የሚያስቀርና ሁሉንም አገልግሎቶች በአንድ ቦታ እንዲያገኙ ታስቦ በAPTS (Auditable Pharmacy Transactions and Services) ስታንዳርድ የተደራጀ ነው፡፡
በዘርፉ በቂ ባለሙያዎች ተመድበው ፈጣንና ግልፅነት ያለው አገልግሎት የሚሰጥበት፣ ተጠያቂነትን ያሰፈነ የአሰራር ስርዓት ተዘርግቷል፡፡ በተጨማሪም ከወረቀት ነፃ የዲጂታል አሰራርን በመዘረጋት የተቀላጠፈና የተገልጋዮቹን እንግልት በሚቀንስ መልኩ አገልግሎት እየሰጠ ነው፡፡

በሆስፒታሉ በተመላላሽና ተኝቶ ህክምና እንዲሁም በድንገተኛ ህክምና የሚታከሙ ታካሚዎች በሀኪሞቻቸው ከሚታዘዙላቸው መድሃኒቶች ከ95 በመቶ በላይ የሚሆነውን መድሃኒት በሆስፒታሉ ውስጥ ባሉ ፋርማሲዎች እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡ ለዚህም የደብረብርሃን ዩኒቨርስቲ አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ እና ሀኪም ግዛው ሆስፒታል አመራሮች በሆስፒታሉ ውስጥ የመድሃኒትና መሰል የግብዓት አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛሉ፡፡

በቀጣይም የከተማውና አካባቢውን ማህበረሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ መድሃኒቶችን የሚያገኝበት የማህበረሰብ አገልግሎት መስጫ ፋርማሲ ለማደራጀት የህንፃ ግንባታው ተጠናቶ አገልግሎቱን የሚሰጡ ባለሙያዎችን ማሟላት፣ የመድሃኒት ግዢና አቅርቦት ቅድመ ዝግጅት ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ ይገኛሉ

@DBU11
የሰው ልጅ ትዕዛዝ የተማረበት
ፈጣሪ በፍጡሮቹ እንደማይጨክን ያሳየበት
ታላቅ በዓል !
ለእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ  እንኳን ለኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

@DBU11
@DBU_ENTERTAINMENT
የፕሬዘደንሻል ሜንቶርሺፕ የምረቃ ስነ-ስርአት በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ አዳራሽ ተካሂዷል።

ሰኔ 8-2016 ዓ.ም የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በተገኙበት የፕሬዘደንሻል ሜንቶርሺፕ የምረቃ ስነ-ስርአት በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ አዳራሽ ተካሂዷል።

የፕሬዚደንሻል ሜንቶርሺፕ ፕሮግራም ሴቶች በራስ መተማመናቸውን የሚያሳድግና አቅማቸውን የሚያጎለብት መሆኑን የኢፌደሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገልፀዋል።

በመርሀ ግብሩ ፕሬዝደንት ሳህለወርቅ ዘውዴን ጨምሮ በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሸኔ፣ የአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ደረጄ እንግዳ ፣ እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።

በፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ሀሳብ አመንጪነት በቢል ኤንድ ሜሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ድጋፍ የተዘጋጀው ይህ ስልጠና እስካሁን ለ1ሺህ 500 ሴት ተማሪዎች በአምስት የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲማሩ መደረጉ ተመላክቷል።

የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ፣ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ፣ የሀሮማያ ዩኒቨርሲቲና ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የመርሀ ግብሩ ተጠቃሚ እንደነበሩ ተገልጿል።

የፕሮግራሙ አላማ ሴት ተማሪዎች ትምህርት ጨርሰው ወደ ስራ ከመሰማራታቸው በፊት ለስራው አለም ክህሎት እንዲጨብጡ እንዲሁም ባሉበት መስክ ላይ ተመራጭ እንዲሆኑ ማስቻል መሆኑ ተገልጿል።

ተመራቂዎቹ በቆይታቸው 40 ችግር ፈቺ ፕሮጀክቶችን ቀርጸው ተግባራዊ እንዲሆኑ ማድረጋቸው ተገልጿል።

ፕሮግራሙ የዳበረ የህይወት ልምድ ያላቸው ሴቶች ለተማሪዎቸ ልምዳቸውን በማካፈል አቅማቸውን የሚያሳድጉበት መሆኑ ተመላክቷል።

በግቢያችን ደብረብርሃንም ከመቶ በላይ ሴት ተማሪዎች የመርሃ ግብሩ ተጠቃሚ ነበሩ።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት

@DBU_ENTERTAINMENT
@DBU11
2024/06/16 08:33:54
Back to Top
HTML Embed Code: