ሰላም የችግሮች አለመኖር ሳይሆን በፈተናዎች ውስጥ ከእግዚአብሔር ጋር የመሆን ውጤት ነው።
እግዚአብሔር የሚሰጠውን ሰላም የትኛውም ኃይል ሊወስደው አይችልም!
እግዚአብሔር የሚሰጠውን ሰላም የትኛውም ኃይል ሊወስደው አይችልም!
+++ ቅዱስ ሉቃስ እና ቅዱስ ኤፍሬም በቀዶ ጥገና ክፍል ውስጥ +++
X. P. ሲል ስሙን በምሕጻር ያስቀመጠ አንድ የ46 ዓመት ጎልማሳ በቅዱሳኑ የተደረገለትን ተአምር እንዲህ ያወጋናል።
"ስሜ X. P. ይባላል። እድሜዬ አርባ ስድስት ዓመት ሲሆን በሰሜናዊው የግሪክ ክፍል ነዋሪ ነኝ። እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2004 ዓ.ም ናላዬ ላይ በተፈጠረ እጢ (Brain tumor) አማካኝነት የቀዶ ሕክምና አድርጌ ነበር። ነገር ግን ይህ ከሆነ ከሦስት ዓመት ከስድስት ወር በኋላ እንደገና እጢው በናላዬ ላይ ታየ። በዚህም ምክንያት ብዙ ዶክተሮች ጋር የሄድኩ ቢሆንም አንዳቸውም ግን ቀዶ ጥገና ሊያደርጉልኝ ፈቃደኛ አልነበሩም። በዚህም ተበሳጭቼ እና ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ገብቼ ነበር።
በመጨረሻም ይህን አስቸጋሪ ቀዶ ጥገና ለማድረግ የተስማማ አንድ ሐኪም አገኘሁ። አንዳንድ የቅርብ ዘመዶቼም የታመሙትን የሚረዳ ባለመድኃኒት የሆነውን ቅዱስ ሉቃስን እንዳከብረው እና ሌሎች ሕሙማንን እንደረዳ እኔንም ይረዳኝ ዘንድ እንድማጸነው ነገሩኝ። እኔም በሁኔታው ተሰማምቼ ቅዱሱን ለማክበርና ለመማጸን ሕንጻ መቅደሱ ወዳለበት የግሪክ ከተማ ተጓዝኩኝ። በዚያም እጅግ የዋህና ትሁት የሆነ አንድ ካህን አገኘሁ (የእርሱንም ስም በምሕጻር Fr. K ይለዋል)።
እርሱ ጥንካሬና ብርታትን ሰጠኝ ፣ ጸሎትም አደረገልኝ። እኔም ኃጢአቴን ተናዝዤ ሥጋ ወደሙን ተቀብዬ ፤ የቀዶ ጥገናው ቀን በመቃረቡ ወደ መጣሁበት ተመለስኩ። ከእለታት በአንደኛው ምሽት በሕልሜ ቅዱስ ኤፍሬምን አየሁት። እርሱም እንዳልረበሽና ነገሮችም በጥሩ ሁኔታ እንደሚሄዱ ነገረኝ።
በመጋቢት 13 ፣ 2007 ዓ.ም ቀዶ ጥገና ወደሚደረግበት ክፍል ገባሁ። ምንም በመድኃኒት የደነዘዝኩ ብሆንም እንኳን ፤ ከቅዱስ ሉቃስና ከቅዱስ ኤፍሬም ጋር ሆነው ቀዶ ጥገናውን የሚያደርጉትን ፤ ትንንሽ ክብ መነጽር ያደረጉና ስለቶች በእጃቸው የያዙ ሐኪሞችን ማየት እችል ነበር። ቅዱስ ኤፍሬም እንዳልፈራ እየነገረኝ እጄን ይዞታል ፤ በግራ እጁ ደግሞ ራሴ አካባቢ የሚያበራ መብራት ይዞ ነበር።
ቀዶ ጥገናው እንደተጠናቀቀም ወደ ከፍተኛ ክትትል ክፍል ወሰዱኝ። በዚያም ድጋሚ ቅዱስ ሉቃስ መጥቶ "በቀዶ ጥገናው ክፍል ውስጥ አብሬህ ነበርኩ" አለኝ። እኔም "አውቃለሁ" ብዬ መለስኩለት። አስቀድሞ ከቀዶ ጥገናው ክፍል ስወጣ ሐኪሙ "እንዲህ ዓይነት ሕመም ሆኖ ነገር ግን ቀላል ቀዶ ጥገና ሳደርግ የመጀመሪያዬ ነው።" እያለ ሲነግረኝ ሰምቼዋለሁ።
ከዚህ በፊት ስለ እነዚህ ሁለት ቅዱሳን ምንም የማውቀው ነገር አልነበረም። አሁን ግን በዙሪያዬ የሚከቡኝ ጠባቂዎቼ ሆነዋል።
Source : http://www.pravoslavie.ru/english/75865.htm
ትርጉም : ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
X. P. ሲል ስሙን በምሕጻር ያስቀመጠ አንድ የ46 ዓመት ጎልማሳ በቅዱሳኑ የተደረገለትን ተአምር እንዲህ ያወጋናል።
"ስሜ X. P. ይባላል። እድሜዬ አርባ ስድስት ዓመት ሲሆን በሰሜናዊው የግሪክ ክፍል ነዋሪ ነኝ። እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2004 ዓ.ም ናላዬ ላይ በተፈጠረ እጢ (Brain tumor) አማካኝነት የቀዶ ሕክምና አድርጌ ነበር። ነገር ግን ይህ ከሆነ ከሦስት ዓመት ከስድስት ወር በኋላ እንደገና እጢው በናላዬ ላይ ታየ። በዚህም ምክንያት ብዙ ዶክተሮች ጋር የሄድኩ ቢሆንም አንዳቸውም ግን ቀዶ ጥገና ሊያደርጉልኝ ፈቃደኛ አልነበሩም። በዚህም ተበሳጭቼ እና ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ገብቼ ነበር።
በመጨረሻም ይህን አስቸጋሪ ቀዶ ጥገና ለማድረግ የተስማማ አንድ ሐኪም አገኘሁ። አንዳንድ የቅርብ ዘመዶቼም የታመሙትን የሚረዳ ባለመድኃኒት የሆነውን ቅዱስ ሉቃስን እንዳከብረው እና ሌሎች ሕሙማንን እንደረዳ እኔንም ይረዳኝ ዘንድ እንድማጸነው ነገሩኝ። እኔም በሁኔታው ተሰማምቼ ቅዱሱን ለማክበርና ለመማጸን ሕንጻ መቅደሱ ወዳለበት የግሪክ ከተማ ተጓዝኩኝ። በዚያም እጅግ የዋህና ትሁት የሆነ አንድ ካህን አገኘሁ (የእርሱንም ስም በምሕጻር Fr. K ይለዋል)።
እርሱ ጥንካሬና ብርታትን ሰጠኝ ፣ ጸሎትም አደረገልኝ። እኔም ኃጢአቴን ተናዝዤ ሥጋ ወደሙን ተቀብዬ ፤ የቀዶ ጥገናው ቀን በመቃረቡ ወደ መጣሁበት ተመለስኩ። ከእለታት በአንደኛው ምሽት በሕልሜ ቅዱስ ኤፍሬምን አየሁት። እርሱም እንዳልረበሽና ነገሮችም በጥሩ ሁኔታ እንደሚሄዱ ነገረኝ።
በመጋቢት 13 ፣ 2007 ዓ.ም ቀዶ ጥገና ወደሚደረግበት ክፍል ገባሁ። ምንም በመድኃኒት የደነዘዝኩ ብሆንም እንኳን ፤ ከቅዱስ ሉቃስና ከቅዱስ ኤፍሬም ጋር ሆነው ቀዶ ጥገናውን የሚያደርጉትን ፤ ትንንሽ ክብ መነጽር ያደረጉና ስለቶች በእጃቸው የያዙ ሐኪሞችን ማየት እችል ነበር። ቅዱስ ኤፍሬም እንዳልፈራ እየነገረኝ እጄን ይዞታል ፤ በግራ እጁ ደግሞ ራሴ አካባቢ የሚያበራ መብራት ይዞ ነበር።
ቀዶ ጥገናው እንደተጠናቀቀም ወደ ከፍተኛ ክትትል ክፍል ወሰዱኝ። በዚያም ድጋሚ ቅዱስ ሉቃስ መጥቶ "በቀዶ ጥገናው ክፍል ውስጥ አብሬህ ነበርኩ" አለኝ። እኔም "አውቃለሁ" ብዬ መለስኩለት። አስቀድሞ ከቀዶ ጥገናው ክፍል ስወጣ ሐኪሙ "እንዲህ ዓይነት ሕመም ሆኖ ነገር ግን ቀላል ቀዶ ጥገና ሳደርግ የመጀመሪያዬ ነው።" እያለ ሲነግረኝ ሰምቼዋለሁ።
ከዚህ በፊት ስለ እነዚህ ሁለት ቅዱሳን ምንም የማውቀው ነገር አልነበረም። አሁን ግን በዙሪያዬ የሚከቡኝ ጠባቂዎቼ ሆነዋል።
Source : http://www.pravoslavie.ru/english/75865.htm
ትርጉም : ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
Orthodox Christianity
St. Luke the Surgeon and St. Ephraim in the Operating Room
In 2004, I was operated on for a brain tumor. After three and a half years, it appeared again. I visited plenty of doctors, but none would agree to operate on me.
+++የሚጠብቅ ሕግ+++
እንደ ጎርጎርዮሳውያኑ አቆጣጠር በ1847 ዓ.ም. በኦስትሪያ ቬና ውስጥ በሚገኝ በአንድ ሆስፒታል ዕውቁ የማኅፀን ሐኪም የነበረው ኢግናዝ ሴሞቫይስ (Ignaz Semmelweis) በዳይሬክተርነት ይሠራ ነበር፡፡ እርሱም በሚመራው የሕክምና ክፍል (ward) ብዙ በእርግዝና ያሉ ሴቶች እየመጡ የጤና ክትትል ያደርጋሉ፡፡ በአጠቃላይ ከሚመጡት እርጉዝ ሴቶች መካከል ከስድስቱ አንዷ በዚያ ክፍል ምርመራ የተደረገላት ሴት በኃይለኛ ንዳድ ተይዛ ትሞት ነበር፡፡ የእነዚህም ሟች ሴቶች አስከሬን ሲመረመር ከቆዳቸው በታች ባለው የሰውነት ክፍላቸው፣ ደረታቸው አካባቢ ባለው ክፍት ቦታ እና የዓይኖቻቸው ኳሶች በተቀመጡባቸው ሰርጓዳ ክፍሎች ውስጥ መግል ይታይ ነበር፡፡ ሴሞቫይስም እርሱ በሚመራው የሆስፒታሉ ዋርድ ሆነ በአጠቃላይ በአውሮፓ ውስጥ በሚገኙት ሆስፒታሎች ውስጥ እየታየ ባለው የእናቶች ሞት እጅግ ተጨነቀ፡፡
አንዲት ያረገዘች ሴት ለዚህ ሥራ ብቻ በተመደበች አዋላጅ አማክኝነት ስትወልድ የሞቱ መጠን ወደ 3% የሚቀንስ ሲሆን፣ የዚያች እርጉዝ ሴት ምርጫ የተሻለ ልምድና ዕውቀት ባላቸው እና በቀን ብዙ ታካሚ በሚጎበኙ ሐኪሞች እጅ መውለድ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ የሞቱ መጠን ወደ 18% ያሻቅብ ነበር፡፡
ዶ/ር ሴሞቫይስ ይህ ባረገዙ ሴቶች ላይ እየደረሰ ያለውን እልቂት ለመግታት ብዙ ጥረት ቢያደርግም የሞታቸውን ቁጥር ግን ሊቀንስ አልቻለም፡፡ እንደውም ቢጨንቀው በአካባቢው ሌሊት ወደ መቅደሱ ሲገባ ካህኑ የሚደውለው የቤተ ክርስቲያን ደወል እያስደነገጣቸው ይሆናል የሚታመሙት ብሎ በማሰብ ካህኑን በጸጥታ ወደ መቅደስ እንዲገባ አድርጎም እንደ ነበር ተጽፏል፡፡ ይሁን እንጂ ነገሩ አንድም መፍትሔ ጠብ አላደረገም፡፡
ታዲያ ዶክተሩ በዚህ አጣብቂኝ መካከል ሆኖ ሲያሰላስል ሳለ አንድ ነገር ተመለከተ፡፡ ይኸውም በሆስፒታሉ ውስጥ ያሉ ወጣት የሕክምና ተማሪዎች የተለመደውን የእለት ክንውናቸውን፣ ማለትም የሞቱትን እናቶች አስከሬን መመርመር፣ ቀጥለውም በጎድጓዳ ሳህን ውስጥ ባለ በደም በደፈረሰ ውኃ እጆቻቸውን በመለቅለቅ የጋራ በሆነ ፎጣ አድርቀው በቀጥታ ለሕክምና የመጣችን ሴት የአካል ምርመራ ሲያደርጉ አየ። በርግጥ ይህን የመሰለው ተግባር pathologyን ለተረዳ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ለሚገኝ ሰው በጣም እንግዳ ሊሆንበት እና “እንዴት?!” ሊያስብል ይችላል፡፡ ‹በጤነኛ አእምሮው ያለ አንድ ሐኪም የሞተን አካል በነካ እጁ ምንም ዓይነት የንጽሕና መጠበቂያ ጥንቃቄ ሳያደርግ እንዴት በሕይወት ያለችን ሴት ሰውነት መልሶ ይመረምራል?› ብሎ መጠየቁም አይቀርም፡፡ ነገር ግን በአውሮፓው ዓለም በአሥራ ዘጠነኛው ምእት ዓመት አጋማሽ "ጀርም" የሚባለው በሽታ አምጪ ስውር ሕዋስ የማይታወቅ እንግዳ ሐሳብ ነበር፡፡ በማጉያ መሳሪያም አይተውት አያውቁም፡፡ ከፍተኛ ጥፋት የማምጣት ኃይሉንም ገና በሚገባ አልተገነዘቡም ነበር፡፡
ዶ/ር ሴሞቫይስም እርሱ ባለበት ዋርድ የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች ሁሉ ማናቸውንም አካላዊ ምርመራ ከማድረጋቸው በፊትም ሆነ ካደረጉ በኋላ እጃቸውን በክሎሪን ውሕድ እንዲታጠቡ ጥብቅ ትእዛዝ አወጣ፡፡ ይህ በሆነ በሦስት ወራት ውስጥም የእናቶች ሞት መጠን ከ18% ወደ 1% ወረደ፡፡ ሐኪሙ ሴሞቫይስ የAntiseptic ጉዳይ ወደ ሕክምናው ትግበራ እንዲገባ በማድረግ የብዙ እናቶችን ሕይወት በመታደጉ በዚህ አስደናቂ ግኝቱ እስከ ዛሬ ድረስ በታሪክ ሲመሰገን ይኖራል፡፡
ይሁን እንጂ መጽሐፍ ቅዱስን ለሚያነብ ሰው ግን ይህ ነገር በዶክተር ሴሞቫይስ የተገኘ ሳይሆን፣ ከ3300 ዓመታት በፊት እግዚአብሔር በሙሴ በኩል የሰጠው ትእዛዝ እንደ ሆነ ይረዳል፡፡ ትእዛዙም ‹‹የሞተውን ሰው በድን የሚነካ ሰባት ቀን ርኩስ ይሆናል፡፡ በዚህም ውኃ በሦስተኛውና በሰባተኛው ቀን ሁለመናውን ያጠራል፡፡ ንጹሕም ይሆናል፡፡ ነገር ግን በሦስተኛውና በሰባተኛው ቀን ሁለመናውን ባያጠራ ንጹሕ አይሆንም›› የሚል ነበር። (ዘኁል. 19፤11-12) ዓለም ፈጽማ ስለ በሽታ አምጪ ተሕዋስያን ዕውቀቱ ባልነበራት ጊዜ እግዚአብሔር ሕዝቡን በቃሉ ይጠብቅ ነበር። አሁንም ወደ መጽሐፍ ቅዱስ እንመለስ፣ እንመርምረው፣ የጥበቦች መጀመሪያ ሆኖ እናገኘዋለን። እርሱም በነፍስ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሲመራን፣ በሥጋ ደግሞ የሚጠቅመንንም ምክር አያስቀርብንም። ሕጉ የተሰጠን እንድንጠብቀው ብቻ ሳይሆን ሊጠብቀንም ጭምር ነው።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
እንደ ጎርጎርዮሳውያኑ አቆጣጠር በ1847 ዓ.ም. በኦስትሪያ ቬና ውስጥ በሚገኝ በአንድ ሆስፒታል ዕውቁ የማኅፀን ሐኪም የነበረው ኢግናዝ ሴሞቫይስ (Ignaz Semmelweis) በዳይሬክተርነት ይሠራ ነበር፡፡ እርሱም በሚመራው የሕክምና ክፍል (ward) ብዙ በእርግዝና ያሉ ሴቶች እየመጡ የጤና ክትትል ያደርጋሉ፡፡ በአጠቃላይ ከሚመጡት እርጉዝ ሴቶች መካከል ከስድስቱ አንዷ በዚያ ክፍል ምርመራ የተደረገላት ሴት በኃይለኛ ንዳድ ተይዛ ትሞት ነበር፡፡ የእነዚህም ሟች ሴቶች አስከሬን ሲመረመር ከቆዳቸው በታች ባለው የሰውነት ክፍላቸው፣ ደረታቸው አካባቢ ባለው ክፍት ቦታ እና የዓይኖቻቸው ኳሶች በተቀመጡባቸው ሰርጓዳ ክፍሎች ውስጥ መግል ይታይ ነበር፡፡ ሴሞቫይስም እርሱ በሚመራው የሆስፒታሉ ዋርድ ሆነ በአጠቃላይ በአውሮፓ ውስጥ በሚገኙት ሆስፒታሎች ውስጥ እየታየ ባለው የእናቶች ሞት እጅግ ተጨነቀ፡፡
አንዲት ያረገዘች ሴት ለዚህ ሥራ ብቻ በተመደበች አዋላጅ አማክኝነት ስትወልድ የሞቱ መጠን ወደ 3% የሚቀንስ ሲሆን፣ የዚያች እርጉዝ ሴት ምርጫ የተሻለ ልምድና ዕውቀት ባላቸው እና በቀን ብዙ ታካሚ በሚጎበኙ ሐኪሞች እጅ መውለድ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ የሞቱ መጠን ወደ 18% ያሻቅብ ነበር፡፡
ዶ/ር ሴሞቫይስ ይህ ባረገዙ ሴቶች ላይ እየደረሰ ያለውን እልቂት ለመግታት ብዙ ጥረት ቢያደርግም የሞታቸውን ቁጥር ግን ሊቀንስ አልቻለም፡፡ እንደውም ቢጨንቀው በአካባቢው ሌሊት ወደ መቅደሱ ሲገባ ካህኑ የሚደውለው የቤተ ክርስቲያን ደወል እያስደነገጣቸው ይሆናል የሚታመሙት ብሎ በማሰብ ካህኑን በጸጥታ ወደ መቅደስ እንዲገባ አድርጎም እንደ ነበር ተጽፏል፡፡ ይሁን እንጂ ነገሩ አንድም መፍትሔ ጠብ አላደረገም፡፡
ታዲያ ዶክተሩ በዚህ አጣብቂኝ መካከል ሆኖ ሲያሰላስል ሳለ አንድ ነገር ተመለከተ፡፡ ይኸውም በሆስፒታሉ ውስጥ ያሉ ወጣት የሕክምና ተማሪዎች የተለመደውን የእለት ክንውናቸውን፣ ማለትም የሞቱትን እናቶች አስከሬን መመርመር፣ ቀጥለውም በጎድጓዳ ሳህን ውስጥ ባለ በደም በደፈረሰ ውኃ እጆቻቸውን በመለቅለቅ የጋራ በሆነ ፎጣ አድርቀው በቀጥታ ለሕክምና የመጣችን ሴት የአካል ምርመራ ሲያደርጉ አየ። በርግጥ ይህን የመሰለው ተግባር pathologyን ለተረዳ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ለሚገኝ ሰው በጣም እንግዳ ሊሆንበት እና “እንዴት?!” ሊያስብል ይችላል፡፡ ‹በጤነኛ አእምሮው ያለ አንድ ሐኪም የሞተን አካል በነካ እጁ ምንም ዓይነት የንጽሕና መጠበቂያ ጥንቃቄ ሳያደርግ እንዴት በሕይወት ያለችን ሴት ሰውነት መልሶ ይመረምራል?› ብሎ መጠየቁም አይቀርም፡፡ ነገር ግን በአውሮፓው ዓለም በአሥራ ዘጠነኛው ምእት ዓመት አጋማሽ "ጀርም" የሚባለው በሽታ አምጪ ስውር ሕዋስ የማይታወቅ እንግዳ ሐሳብ ነበር፡፡ በማጉያ መሳሪያም አይተውት አያውቁም፡፡ ከፍተኛ ጥፋት የማምጣት ኃይሉንም ገና በሚገባ አልተገነዘቡም ነበር፡፡
ዶ/ር ሴሞቫይስም እርሱ ባለበት ዋርድ የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች ሁሉ ማናቸውንም አካላዊ ምርመራ ከማድረጋቸው በፊትም ሆነ ካደረጉ በኋላ እጃቸውን በክሎሪን ውሕድ እንዲታጠቡ ጥብቅ ትእዛዝ አወጣ፡፡ ይህ በሆነ በሦስት ወራት ውስጥም የእናቶች ሞት መጠን ከ18% ወደ 1% ወረደ፡፡ ሐኪሙ ሴሞቫይስ የAntiseptic ጉዳይ ወደ ሕክምናው ትግበራ እንዲገባ በማድረግ የብዙ እናቶችን ሕይወት በመታደጉ በዚህ አስደናቂ ግኝቱ እስከ ዛሬ ድረስ በታሪክ ሲመሰገን ይኖራል፡፡
ይሁን እንጂ መጽሐፍ ቅዱስን ለሚያነብ ሰው ግን ይህ ነገር በዶክተር ሴሞቫይስ የተገኘ ሳይሆን፣ ከ3300 ዓመታት በፊት እግዚአብሔር በሙሴ በኩል የሰጠው ትእዛዝ እንደ ሆነ ይረዳል፡፡ ትእዛዙም ‹‹የሞተውን ሰው በድን የሚነካ ሰባት ቀን ርኩስ ይሆናል፡፡ በዚህም ውኃ በሦስተኛውና በሰባተኛው ቀን ሁለመናውን ያጠራል፡፡ ንጹሕም ይሆናል፡፡ ነገር ግን በሦስተኛውና በሰባተኛው ቀን ሁለመናውን ባያጠራ ንጹሕ አይሆንም›› የሚል ነበር። (ዘኁል. 19፤11-12) ዓለም ፈጽማ ስለ በሽታ አምጪ ተሕዋስያን ዕውቀቱ ባልነበራት ጊዜ እግዚአብሔር ሕዝቡን በቃሉ ይጠብቅ ነበር። አሁንም ወደ መጽሐፍ ቅዱስ እንመለስ፣ እንመርምረው፣ የጥበቦች መጀመሪያ ሆኖ እናገኘዋለን። እርሱም በነፍስ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሲመራን፣ በሥጋ ደግሞ የሚጠቅመንንም ምክር አያስቀርብንም። ሕጉ የተሰጠን እንድንጠብቀው ብቻ ሳይሆን ሊጠብቀንም ጭምር ነው።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
እነሆ ከመላእክት አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ!
እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል አደረሰን!!!
መልአኩ የእኛን መቸገር አይቶ ሊረዳን ፈጥኖ ወደ እኛ ይምጣልን!!!
እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል አደረሰን!!!
መልአኩ የእኛን መቸገር አይቶ ሊረዳን ፈጥኖ ወደ እኛ ይምጣልን!!!
በውጭው ካሉት ይልቅ በአንተ ውስጥ የሚገኙት ፍትወታት ጠንካራ ጠላቶችህ ናቸው። ልክ ያልተሠራለት ምኞት ከባቢሎን እሳት ይልቅ ያቃጥላል። አልጠግብ ባይነትም ከጥፉት ውኃ ይልቅ ያሰጥማል። ያልተገራ ፍላጎት ማንነትን አስጥሎ የሰይጣን ባሪያ ያደርጋል። ራስን መግዛት የሰው ልጆች ጌጥ ነው። ዮሴፍ ግብጽን ከፈርዖን ሁለተኛ ሆኖ ከገዛበት ታላቅ ሥልጣን ይልቅ፣ በጌታው ሚስት ፊት ያሳየው ራስን መግዛት ይበልጥ ይደነቃል። ጠቢቡ "በመንፈሱ ላይ የሚገዛ ከተማ ከሚወስዱ (ከሚገዙ) ይበልጣል" እንዳለ።(ምሳ 16፥32)
ራስህን ነጻ ማውጣት ትፈልጋለህ? እንግዲያውስ ከውስጥህ ጀምር። ሁል ጊዜ ካልበላሁ የሚለው ሆድህ ስስት አስለምዶ በወንድምህ ላይ ጨካኝ እንዳያደርግህ ለሰውነትህ ጾም አስተምረው። "ነገ እሞታለሁና ልብላ ልጠጣ" የሚለውን የዐሣማ ፍልስፍናህን (Pig philosophy) ተውና አንተ በፈቃድህ እየተራብህ (እየጾምህ) ያለ ፈቃዱ የተራበው ወንድምህን በምጽዋት አጥግበው።
ጌታ ወደ ገሊላ የተመለሰው ሄሮድስ ከሞተ በኋላ ነበር።(ማቴ 2፥20) አንተ ውስጥ ያለውን ሄሮድስ የተባለ ክፉ ምኞት እንዲሞት ካላደረግኸው በቀር የተሰደደው ክርስቶስ ወደ አንተ ሊመለስ አይችልም። ይህ ክርስቶስን ከልብህ የሚያሳድድብህን ሄሮድስ እንዴት ልትገድለው ትችላለህ? እርሱንስ ወግተህ የምትጥልበት የብረት ካስማ ምን ይሆን? ለዚህስ ከጾም እና ከጸሎት የሚበረታ ምንም ዓይነት የጦር ዕቃ አታገኝም። በል እነዚህን ይዘህ ዝመትበት።
መልካም የነቢያት ጾም ይሁንልን!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
አዲስ አበባ
ቴሌግራም
https://www.tg-me.com/Dnabel
ራስህን ነጻ ማውጣት ትፈልጋለህ? እንግዲያውስ ከውስጥህ ጀምር። ሁል ጊዜ ካልበላሁ የሚለው ሆድህ ስስት አስለምዶ በወንድምህ ላይ ጨካኝ እንዳያደርግህ ለሰውነትህ ጾም አስተምረው። "ነገ እሞታለሁና ልብላ ልጠጣ" የሚለውን የዐሣማ ፍልስፍናህን (Pig philosophy) ተውና አንተ በፈቃድህ እየተራብህ (እየጾምህ) ያለ ፈቃዱ የተራበው ወንድምህን በምጽዋት አጥግበው።
ጌታ ወደ ገሊላ የተመለሰው ሄሮድስ ከሞተ በኋላ ነበር።(ማቴ 2፥20) አንተ ውስጥ ያለውን ሄሮድስ የተባለ ክፉ ምኞት እንዲሞት ካላደረግኸው በቀር የተሰደደው ክርስቶስ ወደ አንተ ሊመለስ አይችልም። ይህ ክርስቶስን ከልብህ የሚያሳድድብህን ሄሮድስ እንዴት ልትገድለው ትችላለህ? እርሱንስ ወግተህ የምትጥልበት የብረት ካስማ ምን ይሆን? ለዚህስ ከጾም እና ከጸሎት የሚበረታ ምንም ዓይነት የጦር ዕቃ አታገኝም። በል እነዚህን ይዘህ ዝመትበት።
መልካም የነቢያት ጾም ይሁንልን!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
አዲስ አበባ
ቴሌግራም
https://www.tg-me.com/Dnabel
Telegram
Dn Abel Kassahun Mekuria
ይህ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ የተለያዩ ትምህርቶችን የሚያገኙበት በባለቤቱ የተከፈተ ቻነል ነው።
ይወዳጁን
ለፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/AbelKassahunMekuria12?mibextid=ZbWKwL
ለyoutube
https://youtu.be/s6Cn-jMYjrk?si=Tw7lXr62xkGQtL9_
ለInstagram
https://www.instagram.com/abelkassahunm?igsh=OW
ይወዳጁን
ለፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/AbelKassahunMekuria12?mibextid=ZbWKwL
ለyoutube
https://youtu.be/s6Cn-jMYjrk?si=Tw7lXr62xkGQtL9_
ለInstagram
https://www.instagram.com/abelkassahunm?igsh=OW
ዛሬ የተከበረውን የቅዱሱን ፍልሰረ አጽም በዓሉን በማስመልከት ይህን እጅግ ግሩም የሆነ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ መዝሙር ልጋብዛችሁ።
መዘምራኑ “መምህር ወመገስፅ ዘኢያደሉ ለገጽ” እያሉ ፊት አይቶ ማድላት የሌለበት የቅዱሱን አገልግሎት ያዘክሩናል።
ሰናይ ሌሊት!
https://youtu.be/MBKSklYDrmk?si=S1XD6WCKyG3_UWTk
መዘምራኑ “መምህር ወመገስፅ ዘኢያደሉ ለገጽ” እያሉ ፊት አይቶ ማድላት የሌለበት የቅዱሱን አገልግሎት ያዘክሩናል።
ሰናይ ሌሊት!
https://youtu.be/MBKSklYDrmk?si=S1XD6WCKyG3_UWTk
YouTube
"ዘኢያደሉ ለገጽ" የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አዲስ ዝማሬ በፍኖተ አፈወርቅ
ገቢው ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ኦቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት በራያ ቆቦ ወረዳ የኤፍራታ (የአረቋቱ) ደብረ መዊዕ ቅዱስ ቂርቆስ እና ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አንድነት ገዳም የሚውል
ኃጢአት ጸሎት የማቋረጥ ውጤት ነው። እውነተኛ ጸሎት ኃጢአትን የማቆም ምልክት ነው። ሰው ኃጢአትን ልምዱ ካላደረገ በቀር እየጸለየ የሚበድል፣ ከአምላኩ ጋር እየተነጋገረ የሚያምጽ የለም። አዳም እጸ በለስን የቆረጠው ከአምላኩ ጋር የነበረውን ንግግር (ጸሎቱን) በማቋረጡ ነው። ይኸውም አዳምን ጠርቶ "ወዴት ነህ?" ባለው በፈላጊው ድምጽ ተረጋግጧል።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
https://www.tg-me.com/Dnabel
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
https://www.tg-me.com/Dnabel
አባ መቃሪ በአንድ ወቅት ስለ ትሕትና ሲያስተምር ‹አንድ ባለጠጋ የነበረ ንጉሥ ያለውን ሀብት በአደራ መልክ ከአንድ ደሃ ዘንድ ቢያኖር ፤ ያ ደሃ በእነዚያ ብሮች እና ወርቆች ሊመካ ይችላልን? እንደ ራሱ ንብረትስ በመቁጠር የባለቤትነት ስሜት ሊሰማው ይገባል?› ሲል ይጠይቃል፡፡ በዚህ ቅዱስ አባት ምሳሌ መሠረት ያ ባለጠጋ ንጉሥ እግዚአብሔር ነው፡፡ አደራ ተቀባዩ ነዳይ ደግሞ እኛ ነን፡፡ አደራውም በእጃችን ያሉ በጎ ነገሮች ሁሉ ናቸው፡፡ ያሉንን መልካም ነገሮች እንደ ራስ ንብረት መቁጠርና በሌላው ላይ መኩራራት አደራ ተቀባይነትን እንደ መርሳት ነው፡፡ ሰው ባልፈጠረው በጎነት እንዴት ይኩራራል?
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
"ማርያም ሆይ፣ የሐናን ጡት እየጠባሽ ወደ ቤተ መቅደስ በገባሽ ጊዜ ያገኘሽ ያለ እናት ማደግ ያሳዝነኛል፤ ዳግመኛም በደመና የሚጫን የእሳት አበባ የለበሰ ፋኑኤል እንደ አባት ከመላእክት ጋር መናን እየመገበሽ በቅድስና የማደግሽ ምሥጢር ያስደስተኛል"
አባ ጽጌ ድንግል
እንኳን ለእመቤታችን ወደ መቅደስ የመግባት በዓል በሰላም አደረሰን!!!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
አዲስ አበባ
https://www.tg-me.com/Dnabel
አባ ጽጌ ድንግል
እንኳን ለእመቤታችን ወደ መቅደስ የመግባት በዓል በሰላም አደረሰን!!!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
አዲስ አበባ
https://www.tg-me.com/Dnabel