የኃጢአት ሸክም ያጎበጠህ፣ በሁሉ የተናቅህ፣ አላፊ አግዳሚው ምራቁን ጢቅ እያለ ስድብ የሚያዋጣብህ ጎስቋላ ትሆናለህ። ሌሎች እነርሱን ስላልመሰልክ ይንቁህና ያንቋሽሹህ ይሆናል። ነገር ግን በፈጣሪህ ዘንድ ያለህን ተፈላጊነት ሰዎች በሚያሳዩህ ዝቅ ያለ አመለካከት አትለካ። ዛሬ የሚሰድቡህና የሚያዋርዱህ ሰዎች በአንተ መፈጠርና ሰው ሆኖ መኖር ላይ ምንም ዓይነት አስተዋጽዖ የላቸውም። የሕያውነት እስትንፋስ አልሰጡህም ሞተህ እንዳትቀር ስለ አንተ አልተሰቀሉልህም። ላንተ ሲሉ የከፈሉት ዋጋ ስለሌለ ለእነርሱ ከቁስ ያነስክ ልትሆን ትችላለህ።
ነገር ግን በእጁ የለወሰህ፣ ቁርበትና ሥጋ ያለበሰህ፣ በአጥንትና በጅማት ያጠረህ ሕይወት ሰጥቶ ሰው ያደረገህ እግዚአብሔር ከአንተ የሚበልጥበት ሀብት የለውም። በፀሐይና በጨረቃ በሌሎች ብርሃናት ሁሉ ያላስቀመጠው በአንተ ውስጥ ብቻ የቀረጸውን መልኩን ፈጽሞ ሊረሳ የማይችል አምላክ ይፈልግሃል። ጥበቡን አፍስሶ ስለ ፈጠረህ ስትጠፋ ዝም አይልም። ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ ደሙን ስላፈሰሰልህ ፈጽሞ አይተውህም።
የሆሣዕና በዓል በሰዎች ፊት እንደ ምናምንቴ ለሆንን ለእኔ እና ለአንተ ነው። ጌታ ከኢያሪኮ ወደ ቤተ መቅደስ ይዟቸው የመጣው እንደ በርጤሜዎስ ያሉ የተናቁ ነዳያንን፣ እንደ ዘኬዎስ ያሉ የተጠሉ ኃጢአተኞችን ነበር። "ሆሣዕና በአርያም" የሚለው መዝሙራቸውም እንደዚያ ያማረው በመገፋት እና በመጠላት ልባቸው የቆሰሉትን በፍቅርና በምሕረቱ ፈውሶ መድኃኒትነቱን ስላቀመሳቸው ነው።
ለጌታ እናስፈልገዋለን!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
https://youtube.com/channel/UCRvatZyeFOJtXnAjZSOdrZg
ነገር ግን በእጁ የለወሰህ፣ ቁርበትና ሥጋ ያለበሰህ፣ በአጥንትና በጅማት ያጠረህ ሕይወት ሰጥቶ ሰው ያደረገህ እግዚአብሔር ከአንተ የሚበልጥበት ሀብት የለውም። በፀሐይና በጨረቃ በሌሎች ብርሃናት ሁሉ ያላስቀመጠው በአንተ ውስጥ ብቻ የቀረጸውን መልኩን ፈጽሞ ሊረሳ የማይችል አምላክ ይፈልግሃል። ጥበቡን አፍስሶ ስለ ፈጠረህ ስትጠፋ ዝም አይልም። ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ ደሙን ስላፈሰሰልህ ፈጽሞ አይተውህም።
የሆሣዕና በዓል በሰዎች ፊት እንደ ምናምንቴ ለሆንን ለእኔ እና ለአንተ ነው። ጌታ ከኢያሪኮ ወደ ቤተ መቅደስ ይዟቸው የመጣው እንደ በርጤሜዎስ ያሉ የተናቁ ነዳያንን፣ እንደ ዘኬዎስ ያሉ የተጠሉ ኃጢአተኞችን ነበር። "ሆሣዕና በአርያም" የሚለው መዝሙራቸውም እንደዚያ ያማረው በመገፋት እና በመጠላት ልባቸው የቆሰሉትን በፍቅርና በምሕረቱ ፈውሶ መድኃኒትነቱን ስላቀመሳቸው ነው።
ለጌታ እናስፈልገዋለን!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
https://youtube.com/channel/UCRvatZyeFOJtXnAjZSOdrZg
❤103👍18❤🔥8🙏5🥰1
ላትሞት ነው የምትፈታው?
(የሆሣዕና ፍትሐት)
ቤተ ክርስቲያናችን በበዓለ ሆሣዕና ቀን ከምታከናውናቸው ነገሮች መካከል አንዱ ለክርስተኢያኖች ሁሉ ፍትሐት ማድረግ ነው። ይኸውም ከሆሳዕና ቀጥሎ ባሉት ቀናት ሌሎቹን አገልግሎት ሁሉ ለጊዜው አቁማ ልክ እንደ ሰጎን ዕንቁላል ከክርስቶስ ሕማም እና ሞት ላይ ዓይኗን ስለማታነሣ፣ በዚህ ሳምንት የሚያንቀላፋ ቢኖሩ ቀድማ በዕለተ ሆሳዕና ፍትሐት ታደርግለታለች።
ይሁን እንጂ የፍትሐቱ ዋናው ምሥጢር ያለው ግን እዚህ ላይ ነው። ክርስቶስ የተቀበለው መከራ እና ሞቱ በሚታሰብበት በመጪው ሳምንት ልጆቿ ምእመናን የሥጋ ፈቃዳቸውን በመስቀል ሰቅለው ስለ እነርሱ ሲል ለሞተው አምላክ፣ እነርሱም ለዚህ ዓለም ፍትወት የሞቱ ሆነው እንዲያሳልፉ ለማሳሰብ ነው። ስለዚህም ክርስቲያኖችን ሁሉ በቁማቸው ሳሉ እንደ መነኮሳቱ (ለዓለሙ ፈቃድ እንደ ሞቱት) ፍትሐት ታደርግላቸዋለች። ታዲያ በሆሣዕና ሰንበት ወደ ቤተ ክርስቲያን ለፍትሐት ስትመጣ ለራስህ ፈቃድ ሙት ሆነህ ለክርስቶስ ለመኖር ወስነህ ነው? ወይስ ላትሞት ነው ለመፈታት የምትሄደው?
“በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ”
2ኛ ቆሮ 5:15
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
(የሆሣዕና ፍትሐት)
ቤተ ክርስቲያናችን በበዓለ ሆሣዕና ቀን ከምታከናውናቸው ነገሮች መካከል አንዱ ለክርስተኢያኖች ሁሉ ፍትሐት ማድረግ ነው። ይኸውም ከሆሳዕና ቀጥሎ ባሉት ቀናት ሌሎቹን አገልግሎት ሁሉ ለጊዜው አቁማ ልክ እንደ ሰጎን ዕንቁላል ከክርስቶስ ሕማም እና ሞት ላይ ዓይኗን ስለማታነሣ፣ በዚህ ሳምንት የሚያንቀላፋ ቢኖሩ ቀድማ በዕለተ ሆሳዕና ፍትሐት ታደርግለታለች።
ይሁን እንጂ የፍትሐቱ ዋናው ምሥጢር ያለው ግን እዚህ ላይ ነው። ክርስቶስ የተቀበለው መከራ እና ሞቱ በሚታሰብበት በመጪው ሳምንት ልጆቿ ምእመናን የሥጋ ፈቃዳቸውን በመስቀል ሰቅለው ስለ እነርሱ ሲል ለሞተው አምላክ፣ እነርሱም ለዚህ ዓለም ፍትወት የሞቱ ሆነው እንዲያሳልፉ ለማሳሰብ ነው። ስለዚህም ክርስቲያኖችን ሁሉ በቁማቸው ሳሉ እንደ መነኮሳቱ (ለዓለሙ ፈቃድ እንደ ሞቱት) ፍትሐት ታደርግላቸዋለች። ታዲያ በሆሣዕና ሰንበት ወደ ቤተ ክርስቲያን ለፍትሐት ስትመጣ ለራስህ ፈቃድ ሙት ሆነህ ለክርስቶስ ለመኖር ወስነህ ነው? ወይስ ላትሞት ነው ለመፈታት የምትሄደው?
“በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ”
2ኛ ቆሮ 5:15
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
❤174👍24🙏11🥰4👌3
ክርስቶስ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የአይሁድ ፋሲካ ሊደርስ አምስት ቀናት ብቻ ቀርተውት ነበር። በእርግጥ አምስት ቀናት የቀሩት እስራኤል ከግብጽ ባርነት መውጣታቸውን ለሚያስቡበት እና የፋሲካውን በግ ለሚያርዱበት በዓል ብቻ ሳይሆን፣ ዓለም ሁሉ ግብጽ ከተባለ ሲዖል ነጻ ለሚወጣበት እና የእግዚአብሔር በግ ኢየሱስ ክርስቶስ ተሠውቶ አማናዊው ፋሲካ ለሚደረግበትም የሥርየት ዕለት ነበር። ስለዚህ ሰውን ሁሉ ከሲዖል ወደ ገነት፣ ከባርነት ወደ ነጻነት የሚያሻግረው የፋሲካው በግ ክርስቶስ ወደሚሠዋባት ኢየሩሳሌም በገባ ጊዜ ሕዝቡ በደስታ ተቀበለው። መድኃኒትነቱን ተጠምቶ በናፍቆት ሲጠባበቀው የነበረ ነፍስ ሁሉም “አቤቱ እባክህ አሁን አድን” እያለ ዘንባባ ይዞ ዘመረለት።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
❤139👍19🙏8😍5
በእስራኤል ታሪክ አህያ ይጠብቅ እና በእርሱም ይጓጓዝ የነበረ እንደ ሳኦል ያለ ሰው ነግሥዋል። ይሁን እንጂ የሹመት ዘውድ ከደፋ በኋላ ግን ሳኦል በፈረስ እና በሠረገላ እንጂ በአህያ ዳግም አልተጫነም። ንጉሠ ሰላም ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ኢየሩሳሌም በገባ ጊዜ ሐዋርያቱን ፈረስ ወይም በቅሎ እንዲያዘጋጁለት አላዘዘም። ትሑት ሆኖ በአህያ ላይ ለመጫን አህያይቱን ከነግልገሏ ፈተው እንዲያመጡለት ላካቸው እንጂ። ምናልባት በፈረስ የተጫነ በሠረገላ የተፈናጠጠ ንጉሥ ይፈራ ይሆናል፣ ነገር ግን በአህያ ላይ ትሑት ሆኖ እንደ ተሳፈረ ንጉሥ ግን ሊወደድ እና ልብስ ሊነጠፍለት አይችልም። ክርስቶስ አስፈራርቶ ሳይሆን ተወዶ የሚገዛ ንጉሥ መሆኑን ያሳየው በዚህች በሆሳዕና ዕለት ነው። ሕዝቡ ለዚህ ትሑት አምላክ የጎበጠውን መሬት ማቅናት መደልደል፣ ቆሻሻውንም ማጽዳት ባይችሉ የለበሱትን ልብስ ትቢያ ላይ አንጥፈው “በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው” እያሉ አዳኛቸውን ተቀበሉ።
መሰናበቻ!
እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃማ ወድካም አመ ከመ ዮም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ ለብርሃነ ትንሣኤሁ እግዚአብሔር በፍስሓ ወበሰላም፥
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
መሰናበቻ!
እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃማ ወድካም አመ ከመ ዮም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ ለብርሃነ ትንሣኤሁ እግዚአብሔር በፍስሓ ወበሰላም፥
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
❤146🙏24👍15👏2😱1
ንጹሕ ሆነን የረከሰ ምራቅን አለመጠየፍ እንዴት ይቻለናል? ያለ በደል የሚደረግ ውንጀላ እና ግፍንስ "በቃ" አለማለት እንዴት ይሆናልናል?
ያለ ጥፋት የሚመጣብንን ምን ያህል ጥፊዎች እንታገሳለን? ስንት ጅራፎችንስ እንቀበላለን? ስንት ውርደቶችንስ እንሸከማለን? መድኃኔዓለም ይህን ሁሉ ነገር የተቀበለው ስለ እኛ መዳን ነው።
እኔ ግን ስለ ራሴ መዳን በጀርባህ ላይ ካረፉት ጅራፎች የአንዲቱን ሰንበር ያህል እንኳን መከራ ለመቀበል ትዕግስቱ የለኝም።
"ተሰሃለኒ እግዚኦ በከመ ዕበየ ሳህልከ" - "አቤቱ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝ" መዝ 50፥1
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
ያለ ጥፋት የሚመጣብንን ምን ያህል ጥፊዎች እንታገሳለን? ስንት ጅራፎችንስ እንቀበላለን? ስንት ውርደቶችንስ እንሸከማለን? መድኃኔዓለም ይህን ሁሉ ነገር የተቀበለው ስለ እኛ መዳን ነው።
እኔ ግን ስለ ራሴ መዳን በጀርባህ ላይ ካረፉት ጅራፎች የአንዲቱን ሰንበር ያህል እንኳን መከራ ለመቀበል ትዕግስቱ የለኝም።
"ተሰሃለኒ እግዚኦ በከመ ዕበየ ሳህልከ" - "አቤቱ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝ" መዝ 50፥1
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
❤199😢75👍27😭14🙏10
ይስሐቅ በሞሪያ ተራራ ሊሠዋ ሲሄድ የምትወደው እና እንደ ዓይኗ የምትሳሳለት እናቱ ከእርሱ ጋር አልነበረችም። አብርሃምም ኀዘኗን ማየት ስለ ፈራ ከእግዚአብሔር ስለ ተቀበለው ከባድ ትእዛዝ ለሣራ አልነገራትም። የይስሐቅ ቤዛው ክርስቶስ ግን ያ ሁሉ ጅራፍ ሲወርድበት፣ ደሙ በየመንገዱ እንደ ውኃ ሲፈስ፣ በገመድ አስረው እየጎተቱ ሲጥሉትና ምራቃቸውን እየተፉ ሲዘባበቱበት እናቱ ድንግል ማርያም አይታለች። አንድ ልጇ ላይ ብዙ የሆኑ አይሁድ እና ሮማውያን ተባብረው ሲጨክኑበት በዓይኗ በብረቱ ተመልክታለች። ወደ መሬት ወድቆ በረገጡት ጊዜ በስቃይ ከሚቃትት ልጇ ጋር ዓይን ለዓይን ተያይታለች።
ለልጅም ለእናቱም ቢሆን ከዚህ ዕለት በላይ የሚከብድ ምን ዓይነት የኀዘን ቀን ሊኖር ይችላል?
በዚህ ምድር እንደ አምላካችን ክርስቶስ የሰቃየ እንደ እመቤታችን ማርያምም ያዘነ ማንም የለም!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
ለልጅም ለእናቱም ቢሆን ከዚህ ዕለት በላይ የሚከብድ ምን ዓይነት የኀዘን ቀን ሊኖር ይችላል?
በዚህ ምድር እንደ አምላካችን ክርስቶስ የሰቃየ እንደ እመቤታችን ማርያምም ያዘነ ማንም የለም!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
❤279😢99💔27😭15👍12💯6
+++‹‹በለምጻሙ ስምዖን ቤት ሳለ›› ማቴ 26፥6+++
አይሁድ በሊቀ ካህናቱ በቀያፋ ግቢ ውስጥ ተሰብስበው በጌታ ሞት ላይ ሲመክሩ፣ መድኃኒታችን ግን በቢታንያ በስምዖን ቤት እራት ግብዣ ተቀምጦ ነበር፡፡ ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ጌታ እራት የተጠራበት ቤት ባለቤት ‹ለምጻሙ ስምዖን› እንደ ሆነ ይናገራል፡፡ ጸሐፊው ስለ ምን ይህንን ሰው ስምዖን ብቻ ብሎ አልጠራውም? ‹ለምጻሙ› የሚለው ገላጭ ቃል መጠቀም ለምን አስፈለገው? በርግጥ ስምዖን በለምጽ ንዳድ የተያዘና በአይሁድ ዘንድም እንደ ረከሰ እና በደለኛ ተቆጥሮ የሚገለል ብቸኛ ሰው ነበር፡፡ ይሁን እንጂ አሁን ግን ጌታ ከሐዋርያቱ ጋር ሆኖ በእርሱ ቤት ለእራት በተቀመጠ ጊዜ፣ ቅዱስ ጄሮም እንደሚናገረው ይህ ሰው ካለበት ለምጽ ሁሉ ነጽቶ ነበር፡፡ ታዲያ ወንጌላዊው ስለ ምን ከለምጹ የነጻውን ስምዖን ‹‹ለምጻሙ›› ሲል ጠራው?
ይህ ያለ ምክንያት አልሆነም፡፡ ጌታችን በስምዖን ቤት ለእራት ተቀምጦ ሳለ የሚፈጸም ቀጣይ ወሳኝ ታሪክ ስላለ፣ ‹ለምጻሙ› የሚለው ገላጭ ለዚያ መግቢያ የሚሆን ወሳኝ ቃል ነበር፡፡ ቀጥሎ የምናገኘው ታሪክም አንዲት በኃጢአት የተመረረችና ነፍሷ የጎሰቆለባት ሴት፣ መንፈሳዊውን ምሕረት ፈልጋ ጌታችን ወዳለበት መምጣቷና የያዘችውን እጅግ ውድ የሆነውን ሽቱ ከፍታ በጌታ በራሱና በእግሮቹ ላይ ማፍሰሷን የሚናገር ነው፡፡ ይህች ሴት ቀድሞ በዝሙት ትኖር ነበረች ብትሆንም ዛሬ ግን የሽቱና የእንባን መባ ይዛ ወደ ክርስቶስ ቀርባለች፡፡ በዘመኑ ብዙዎች ያስጨንቃቸውና የክርስቶስን መድኃኒትነት ይፈልጉት የነበረው ለሥጋዊ ሕመማቸው ነበር፡፡ ምንም የሥጋ ሕመም የሌለባት ይህች ሴት ግን ባልተለመደ ሁኔታ የነፍሷን ሕመም (ኃጢአት) በምሕረቱ መድኃኒትነት ለመሻር ወደ ጌታችን ስትሮጥ መጣች፡፡ ይህም ሥራዋ እጅግ በጣም የምትደነቅ መንፈሳዊት ሴት ያደርጋታል፡፡
በዚህ ወንጌል የተጠቀሰችው ባለ ታሪክ ትሠራ የነበረው ሥራ በሁሉ ዘንድ አስነዋሪ የነበረውን፣ እንኳን በአምላክ ፊት ቀርቶ በሰው ፊት እንኳን ቀና ብሎ የማያስቆመውን ዝሙት ነበር፡፡ ታዲያ ወደ ክርስቶስ ለመምጣት ድፍረት የሰጣት ነገር ምንድር ነው? እንዴት ወደ መድኃኔዓለም ቀርባ ‹‹ማረኝ›› ለማለት በቃች? ካልን መልሱ ቀላል ነው፤ ጌታ ‹በለምጻሙ ስምዖን› ቤት እንደ ተገኘ አይታ ነው፡፡ ክርስቶስ ራሳቸውን ከሚያመጻድቁ ፈሪሳውያን መካከል በአንዱ ቤት ተገኝቶ ቢሆን ኖሮ ባለ ሽቱዋ ማርያም ድፍረት አግኝታ ወደ እርሱ ባልመጣች ነበር፡፡ ነገር ግን አሁን ሰዎች እንደ ርኩስና በደለኛ ቆጥረው ያገሉት በነበረው ስምዖን ቤት ነውሩን ሁሉ አስወግዶለት አብሮት ለእራት እንደ ተቀመጠ ስላየች፣ የሚበዛው ድካሜን አይቶ የበለጠ ይራራልኝ እንደ ሆነ እንጂ ለእርሱ ያደረገውን ቸርነት ለእኔ አይነሳኝም ብላ በተስፋ ወደ ፈጣሪዋ ገሰገሰች፡፡ እጅግ የሚያስደንቅ ተስፋ ነው!!!
ዛሬም መድኃኔዓለም ክርስቶስ በለምጻሙ ስምዖን ቤት አለ፡፡ ስለዚህ ‹አይሰማኝ ይሆን› የሚለውን ጥርጣሬያችንን ትተን ወገባችንን ያጎበጠውን ኃጢአት በንስሐ ከእግሩ ስር ለማራገፍ ፈጥነን ወደ እርሱ እንቅረብ፡፡ በለምጻሙ ስምዖን ቤት ለእራት የተቀመጠ አምላክ በፍጹም ጸጸት ብንመለስ የእኛንም ቤት (ሰውነት) አይንቅም፡፡ ይልቅ ሳይረፍድ ቶሎ ሄደን ከእግሮቹ ስር እንውደቅ!!!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
አዲስ አበባ
2015 ዓ.ም.
አይሁድ በሊቀ ካህናቱ በቀያፋ ግቢ ውስጥ ተሰብስበው በጌታ ሞት ላይ ሲመክሩ፣ መድኃኒታችን ግን በቢታንያ በስምዖን ቤት እራት ግብዣ ተቀምጦ ነበር፡፡ ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ጌታ እራት የተጠራበት ቤት ባለቤት ‹ለምጻሙ ስምዖን› እንደ ሆነ ይናገራል፡፡ ጸሐፊው ስለ ምን ይህንን ሰው ስምዖን ብቻ ብሎ አልጠራውም? ‹ለምጻሙ› የሚለው ገላጭ ቃል መጠቀም ለምን አስፈለገው? በርግጥ ስምዖን በለምጽ ንዳድ የተያዘና በአይሁድ ዘንድም እንደ ረከሰ እና በደለኛ ተቆጥሮ የሚገለል ብቸኛ ሰው ነበር፡፡ ይሁን እንጂ አሁን ግን ጌታ ከሐዋርያቱ ጋር ሆኖ በእርሱ ቤት ለእራት በተቀመጠ ጊዜ፣ ቅዱስ ጄሮም እንደሚናገረው ይህ ሰው ካለበት ለምጽ ሁሉ ነጽቶ ነበር፡፡ ታዲያ ወንጌላዊው ስለ ምን ከለምጹ የነጻውን ስምዖን ‹‹ለምጻሙ›› ሲል ጠራው?
ይህ ያለ ምክንያት አልሆነም፡፡ ጌታችን በስምዖን ቤት ለእራት ተቀምጦ ሳለ የሚፈጸም ቀጣይ ወሳኝ ታሪክ ስላለ፣ ‹ለምጻሙ› የሚለው ገላጭ ለዚያ መግቢያ የሚሆን ወሳኝ ቃል ነበር፡፡ ቀጥሎ የምናገኘው ታሪክም አንዲት በኃጢአት የተመረረችና ነፍሷ የጎሰቆለባት ሴት፣ መንፈሳዊውን ምሕረት ፈልጋ ጌታችን ወዳለበት መምጣቷና የያዘችውን እጅግ ውድ የሆነውን ሽቱ ከፍታ በጌታ በራሱና በእግሮቹ ላይ ማፍሰሷን የሚናገር ነው፡፡ ይህች ሴት ቀድሞ በዝሙት ትኖር ነበረች ብትሆንም ዛሬ ግን የሽቱና የእንባን መባ ይዛ ወደ ክርስቶስ ቀርባለች፡፡ በዘመኑ ብዙዎች ያስጨንቃቸውና የክርስቶስን መድኃኒትነት ይፈልጉት የነበረው ለሥጋዊ ሕመማቸው ነበር፡፡ ምንም የሥጋ ሕመም የሌለባት ይህች ሴት ግን ባልተለመደ ሁኔታ የነፍሷን ሕመም (ኃጢአት) በምሕረቱ መድኃኒትነት ለመሻር ወደ ጌታችን ስትሮጥ መጣች፡፡ ይህም ሥራዋ እጅግ በጣም የምትደነቅ መንፈሳዊት ሴት ያደርጋታል፡፡
በዚህ ወንጌል የተጠቀሰችው ባለ ታሪክ ትሠራ የነበረው ሥራ በሁሉ ዘንድ አስነዋሪ የነበረውን፣ እንኳን በአምላክ ፊት ቀርቶ በሰው ፊት እንኳን ቀና ብሎ የማያስቆመውን ዝሙት ነበር፡፡ ታዲያ ወደ ክርስቶስ ለመምጣት ድፍረት የሰጣት ነገር ምንድር ነው? እንዴት ወደ መድኃኔዓለም ቀርባ ‹‹ማረኝ›› ለማለት በቃች? ካልን መልሱ ቀላል ነው፤ ጌታ ‹በለምጻሙ ስምዖን› ቤት እንደ ተገኘ አይታ ነው፡፡ ክርስቶስ ራሳቸውን ከሚያመጻድቁ ፈሪሳውያን መካከል በአንዱ ቤት ተገኝቶ ቢሆን ኖሮ ባለ ሽቱዋ ማርያም ድፍረት አግኝታ ወደ እርሱ ባልመጣች ነበር፡፡ ነገር ግን አሁን ሰዎች እንደ ርኩስና በደለኛ ቆጥረው ያገሉት በነበረው ስምዖን ቤት ነውሩን ሁሉ አስወግዶለት አብሮት ለእራት እንደ ተቀመጠ ስላየች፣ የሚበዛው ድካሜን አይቶ የበለጠ ይራራልኝ እንደ ሆነ እንጂ ለእርሱ ያደረገውን ቸርነት ለእኔ አይነሳኝም ብላ በተስፋ ወደ ፈጣሪዋ ገሰገሰች፡፡ እጅግ የሚያስደንቅ ተስፋ ነው!!!
ዛሬም መድኃኔዓለም ክርስቶስ በለምጻሙ ስምዖን ቤት አለ፡፡ ስለዚህ ‹አይሰማኝ ይሆን› የሚለውን ጥርጣሬያችንን ትተን ወገባችንን ያጎበጠውን ኃጢአት በንስሐ ከእግሩ ስር ለማራገፍ ፈጥነን ወደ እርሱ እንቅረብ፡፡ በለምጻሙ ስምዖን ቤት ለእራት የተቀመጠ አምላክ በፍጹም ጸጸት ብንመለስ የእኛንም ቤት (ሰውነት) አይንቅም፡፡ ይልቅ ሳይረፍድ ቶሎ ሄደን ከእግሮቹ ስር እንውደቅ!!!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
አዲስ አበባ
2015 ዓ.ም.
❤217👍38🙏27😢7🔥3
“የወደዳቸውን እስከ መጨረሻ ወደዳቸው” ዮሐንስ 13:1
ሲወድድ ምክንያት አልነበረውም። ያለ ምክንያት የወደዳቸውን ግን እስከ መጨረሻው ወደዳቸው!
ጸጥ፤ ዝም የሚያሰኝ ቃል!!!
ለመወደድ የሚያበቃ ምንም ምክንያት የለኝም። እርሱ ግን እስከ መጨረሻው ወድዶኛል!!!
ሲወድድ ምክንያት አልነበረውም። ያለ ምክንያት የወደዳቸውን ግን እስከ መጨረሻው ወደዳቸው!
ጸጥ፤ ዝም የሚያሰኝ ቃል!!!
ለመወደድ የሚያበቃ ምንም ምክንያት የለኝም። እርሱ ግን እስከ መጨረሻው ወድዶኛል!!!
❤285🙏14👍12
ፍቅር ምን እንዳደረገው ተመልከቱ፤
በአርያም ካለው ከእሳት አዳራሹ ስቦ በቤተልሔም ዋሻ በከብቶች በግርግም አስተኛው።
ብርሃንን እንደ ልብስ የሚጎናጸፈው እርሱን በበለሳን ቅጠል እንዲጠቀለል አደረገው።
ዘመን የማይቆጠርለትን አምላክ ጽንስ፣ ሕፃን፣ ልጅ፣ ጎልማሳ አደረገው።
ፍቅር...
በአባቱ የሚወደደውን አንድያ ልጅ በአይሁድ ዘንድ የተጠላ አደረገው።
በመላእክት የሚመሰገነውን ጌታ በፈሪሳውያን መሪር አንደበት እንዲሰደብ አደረገው።
ፈታሒውን ዳኛ እጆቹን ታስሮ የሰውን ፍርድ ፍለጋ እንዲንከራተት አደረገው።
ፍቅር በኩሩቤል ጀርባ ለሚቀመጠው አምላክ የመስቀል ዙፋን አበጀለት። የመቃብር አልጋም አዘጋጀለት።
ፍቅር የእግዚአብሔርን ልጅ ሐፍረትን ንቆ በፊቱ ስላለው የምእመናን ደስታ እርቃኑን እንዲሰቀል አደረገው!
መድኃኒት በምትሆን ሕማሙ ከኃጢአት በሽታ ሁላችንንም ይፈውሰን!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
https://youtube.com/channel/UCRvatZyeFOJtXnAjZSOdrZg
በአርያም ካለው ከእሳት አዳራሹ ስቦ በቤተልሔም ዋሻ በከብቶች በግርግም አስተኛው።
ብርሃንን እንደ ልብስ የሚጎናጸፈው እርሱን በበለሳን ቅጠል እንዲጠቀለል አደረገው።
ዘመን የማይቆጠርለትን አምላክ ጽንስ፣ ሕፃን፣ ልጅ፣ ጎልማሳ አደረገው።
ፍቅር...
በአባቱ የሚወደደውን አንድያ ልጅ በአይሁድ ዘንድ የተጠላ አደረገው።
በመላእክት የሚመሰገነውን ጌታ በፈሪሳውያን መሪር አንደበት እንዲሰደብ አደረገው።
ፈታሒውን ዳኛ እጆቹን ታስሮ የሰውን ፍርድ ፍለጋ እንዲንከራተት አደረገው።
ፍቅር በኩሩቤል ጀርባ ለሚቀመጠው አምላክ የመስቀል ዙፋን አበጀለት። የመቃብር አልጋም አዘጋጀለት።
ፍቅር የእግዚአብሔርን ልጅ ሐፍረትን ንቆ በፊቱ ስላለው የምእመናን ደስታ እርቃኑን እንዲሰቀል አደረገው!
መድኃኒት በምትሆን ሕማሙ ከኃጢአት በሽታ ሁላችንንም ይፈውሰን!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
https://youtube.com/channel/UCRvatZyeFOJtXnAjZSOdrZg
❤217😭40🙏17👍11😢8🥰6
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
“እንደ ውኃ ፈሰስሁ፤ አጥንቶቼም ሁሉ ተለያዩ፤ ልቤ እንደ ሰም ሆነ፥ በአንጀቴም መካከል ቀለጠ። ኃይሌ እንደ ገል ደረቀ፥ በጕሮሮዬም ምላሴ ተጣጋ”
መዝሙር 22:14-15
መዝሙር 22:14-15
💔115😭38❤18🙏8👍5😢4❤🔥2
ሰላም ክቡራን፣
እንኳን አደረሳችሁ። የዛሬው የክፍል 7 የዕብራውያን መልእክት ሐተታ ትምህርታችንን በYouTube ለቀነዋል። ትምህርቱን ለዛሬ ድካማችንን ባገናዘበ መንገድ አጠር አድርገን ነው ያቀረብነው። እግዚአብሔር ቢፈቅድ ቀጣይ ሳምንት በተለመደው ሰዓት እንገናኛለን።
https://youtu.be/fnbrIW4MEI0?si=lHa-Hl9vggYvkEe9
እንኳን አደረሳችሁ። የዛሬው የክፍል 7 የዕብራውያን መልእክት ሐተታ ትምህርታችንን በYouTube ለቀነዋል። ትምህርቱን ለዛሬ ድካማችንን ባገናዘበ መንገድ አጠር አድርገን ነው ያቀረብነው። እግዚአብሔር ቢፈቅድ ቀጣይ ሳምንት በተለመደው ሰዓት እንገናኛለን።
https://youtu.be/fnbrIW4MEI0?si=lHa-Hl9vggYvkEe9
YouTube
የዕብራውያን መልእክት ሐተታ ክፍል 7 I Orthodox Bible study - @Dnabelkassahun
#biblestudy #share
❤71🙏11👍3👏1
የጠሉህን ሳትወድድ፣ መከራ ያከበዱብህን ተቀይመህ፣ ስለ አሳዳጆችህ ሳትጸልይ እንዴት ጣቶችህን አመሳቅለህ የመስቀል ምልክት ትሠራለህ? በጣቶችህ ያለው መስቀል ጠላት የተወደደበት፣ ለሰቃልያን በቃል የማይነገር ትዕግስት የታየበት፣ ተሳዳቢ የተመረቀበት፣ ለሚወጉ ምሕረት የተደረገበት የፍቅር አውድማ ነው። ሰውን ለመወንጀል በቀሰርከው ጣትህ እንዴት መልሰህ የይቅርባነት ምልክት የሆነውን መስቀል ለመሥራት ሌላው ጣትህን አግድም ታስተኛለህ?
እያማተብህ አትጥላ፣ እያማተብህ አትፍረድ፣ እያማተብህ አትቀየም፣ እያማተብህ አትርገም።
"ገብረ ሰላመ በደመ መስቀሉ" - "በመስቀሉ ደም ሰላምን አደረገ"
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
[email protected]
እያማተብህ አትጥላ፣ እያማተብህ አትፍረድ፣ እያማተብህ አትቀየም፣ እያማተብህ አትርገም።
"ገብረ ሰላመ በደመ መስቀሉ" - "በመስቀሉ ደም ሰላምን አደረገ"
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
[email protected]
❤173👍20🙏13😢8🥰2
ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ እና ዮሐንስ ዘደማስቆ ሐዋርያው ጴጥሮስ ጌታ በዐረገ በዓመቱ (34 ዓ.ም.) ቅዱሱን እሳት በመቃብሩ ስፍራ ማየቱን ጽፈዋል። ይህ ተአምር አሁን እስካለንበት ዘመን የቀጠለ ሲሆን፣ ሁል ጊዜም በትንሣኤ በዓል ዋዜማ ቅዳሜ ቀን ይታያል። ስለዚህ የሚያስደንቅ ተአምር ብዙ የማያምኑ ሰዎች በራሳቸው መንገድ ለማጣራት ሞክረዋል። እስኪ ከእነዚህ ውስጥ አንዱን ታሪክ ላጫውታችሁ።
በአንድ ወቅት እንዲህ ሆነ…
ዕለቱ ቅዳሜ ጠዋት 4 ሰዓት የትንሣኤ ዋዜማ ነው። የእስራኤል አይሁድ ፖሊሶች እና የከተማዋ ከንቲባ ይህ እሳት ይፈልቅበታል የተባለውን የጌታን መቃብር እውነትነት ማረጋገጥ ስለ ፈለጉ በውስጡ ለእሳቱ መነሣት ምክንያት የሚሆኑ ተቀጣጣይ ነገሮች ካሉ በሚል ለሁለት ሰዓታት ያህል ሦስት ጊዜ ጥብቅ ፍተሻ አደረጉ። ግን ምንም ሊያገኙ አልቻሉም። ቀጥሎም ሁለት መቃብሩን የሚጠብቁ ሙስሊሞችን በማምጣት ልክ የቀድሞዎቹ አይሁድ የጌታን መቃብር እንዳተሙ እነርሱም መቃብሩን ዘግተው በሰም እንዲያትሙት አደረጉ።
ይህንም ተከትሎ በቦታው የነበሩ አረብ ክርስቲያኖች ቱርክ እስራኤልን በተቆጣጠረችበት በ13ኛው ክፍለ ዘመን ከቤተ ክርስቲያን ውጭ በየትኛውም ቦታ ቢሆን እንዳይዘምሩ የተከለከሉትን ቆየት ያለ ዝማሬ በኅብረት ከፍ ባለ ድምፅ መዘመር ጀመሩ። መዝሙሩም:-
“እኛ ክርስቲያኖች ነን። ለብዙ መቶ ክፍለ ዘመናትም ክርስቲያኖች ነበርን። እስከ ዘላለምም እንዲሁ እንሆናለን፣ አሜን!” የሚል ነበር።
እኩለ ቀንም ሲሆን የግሪኩና የአርሜንያው ፓትርያርክ፣ የግብፁ ሜትሮፖሊታንት እንዲሁም ቀሳውስት እና ዲያቆናት ወደ ታተመው የክርስቶስ መቃብር መጡ። ከብዙ ጸሎት እና ምስጋናም በኋላ የታተመው የክርስቶስ መቃብር እንዲከፈት አደረጉ። ፓትርያርኩም ሞጣህቱን ብቻ አስቀርተው ከላይ የለበሱትን ልብሰ ተክህኖ በማውለቅ በክርስቶስ የዕድሜ ቁጥር ልክ ሦስት 33 ያልበሩ ሻማዎችን ይዘው ጨለማ ወደ ነበረው መቃብር ገቡ። ምእመናኑም ከውጭ ሆነው በአንድ ድምፅ ኪርዬሌይሶን (አቤቱ ይቅር በለን) እያሉ በመዘመር ይጠባበቁ ጀመር። ወደ ቅዱሱ መቃብር ገብተው የነበሩትም የግሪኩ ፓትርያርክ ያን በሰው ያልተቀጣጠለ እና የክርሰቶስን የትንሣኤ ብርሃን የሚያበሥረውን አምላካዊ እሳት ይዘው ብቅ አሉ። ይህን ጊዜ ጎልጎታ በእልልታ ተሞላች የቤተ ክርስቲያኑም ደወል በሐሴት ይደወል ጀመር።
ትንሣኤከ ለእለ አመነ
ብርሃነከ ፈኑ ዲቤነ
እንኳን አደረሰን!!!
https://youtu.be/OGyzCFZO0VY?si=2ptLkHV_WD5rYRvY
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
በአንድ ወቅት እንዲህ ሆነ…
ዕለቱ ቅዳሜ ጠዋት 4 ሰዓት የትንሣኤ ዋዜማ ነው። የእስራኤል አይሁድ ፖሊሶች እና የከተማዋ ከንቲባ ይህ እሳት ይፈልቅበታል የተባለውን የጌታን መቃብር እውነትነት ማረጋገጥ ስለ ፈለጉ በውስጡ ለእሳቱ መነሣት ምክንያት የሚሆኑ ተቀጣጣይ ነገሮች ካሉ በሚል ለሁለት ሰዓታት ያህል ሦስት ጊዜ ጥብቅ ፍተሻ አደረጉ። ግን ምንም ሊያገኙ አልቻሉም። ቀጥሎም ሁለት መቃብሩን የሚጠብቁ ሙስሊሞችን በማምጣት ልክ የቀድሞዎቹ አይሁድ የጌታን መቃብር እንዳተሙ እነርሱም መቃብሩን ዘግተው በሰም እንዲያትሙት አደረጉ።
ይህንም ተከትሎ በቦታው የነበሩ አረብ ክርስቲያኖች ቱርክ እስራኤልን በተቆጣጠረችበት በ13ኛው ክፍለ ዘመን ከቤተ ክርስቲያን ውጭ በየትኛውም ቦታ ቢሆን እንዳይዘምሩ የተከለከሉትን ቆየት ያለ ዝማሬ በኅብረት ከፍ ባለ ድምፅ መዘመር ጀመሩ። መዝሙሩም:-
“እኛ ክርስቲያኖች ነን። ለብዙ መቶ ክፍለ ዘመናትም ክርስቲያኖች ነበርን። እስከ ዘላለምም እንዲሁ እንሆናለን፣ አሜን!” የሚል ነበር።
እኩለ ቀንም ሲሆን የግሪኩና የአርሜንያው ፓትርያርክ፣ የግብፁ ሜትሮፖሊታንት እንዲሁም ቀሳውስት እና ዲያቆናት ወደ ታተመው የክርስቶስ መቃብር መጡ። ከብዙ ጸሎት እና ምስጋናም በኋላ የታተመው የክርስቶስ መቃብር እንዲከፈት አደረጉ። ፓትርያርኩም ሞጣህቱን ብቻ አስቀርተው ከላይ የለበሱትን ልብሰ ተክህኖ በማውለቅ በክርስቶስ የዕድሜ ቁጥር ልክ ሦስት 33 ያልበሩ ሻማዎችን ይዘው ጨለማ ወደ ነበረው መቃብር ገቡ። ምእመናኑም ከውጭ ሆነው በአንድ ድምፅ ኪርዬሌይሶን (አቤቱ ይቅር በለን) እያሉ በመዘመር ይጠባበቁ ጀመር። ወደ ቅዱሱ መቃብር ገብተው የነበሩትም የግሪኩ ፓትርያርክ ያን በሰው ያልተቀጣጠለ እና የክርሰቶስን የትንሣኤ ብርሃን የሚያበሥረውን አምላካዊ እሳት ይዘው ብቅ አሉ። ይህን ጊዜ ጎልጎታ በእልልታ ተሞላች የቤተ ክርስቲያኑም ደወል በሐሴት ይደወል ጀመር።
ትንሣኤከ ለእለ አመነ
ብርሃነከ ፈኑ ዲቤነ
እንኳን አደረሰን!!!
https://youtu.be/OGyzCFZO0VY?si=2ptLkHV_WD5rYRvY
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
YouTube
🔥 The Holy Fire, Miracle, or Myth? 🕯️🕊️ Documentary #holyfire #holylight #jerusalem #النور_المقدس
Curious if the Holy Fire ceremony is truly a miracle or just a myth? 🌟 Want to delve into the historical and scientific evidence surrounding this annual event witnessed by thousands? Ever wondered about the secrets behind Jerusalem's Church of the Holy Sepulcher?…
❤89👍11❤🔥3
+++የእስክንድር እንቁላሎች+++
ሕፃኑ እስክንድር እክል ካለበት ሰውነት ጋር የተወለደ ሲሆን፣ መለስተኛ የሆነ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ችግርም ነበረበት፡፡ እስክንድር ዕድሜው አሥራ ሁለት ዓመት ይሁን እንጂ በጊዜው ገና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ነበር፡፡ ካለበት የጤና እክልም የተነሣ መማር ይቸግረው ነበር፡፡ ታስተምረው የነበረች ሴት መምህርቱም በልዩ እንክብካቤ ያለና በእነርሱ የትምህርት ሥርዓት ውስጥ አብሮ መጓዝ እንደማይችል ተረድታዋለች፡፡ ይሁን እንጂ ጥሩ አስተማሪና እውነተኛ ክርስቲያን ስለነበረች ተማሪዋ እስክንድርን በትኩረት ትከታተለው ነበር፡፡ የፀደይ ወቅት በመድረሱ እንዲሁም የፋሲካም በዓል ከፊታቸው እየመጣ ስለሆነ ከእስክንድር ጋር የሚማሩት ሕፃናት ተማሪዎች በተደሰቱበት በአንዱ ቀን እንዲህ ሆነ፡፡
መምህርቷ ለተማሪዎቿ ሁሉ ትላልቅ የፕላስቲክ እንቁላል በመስጠት ‹ይህን የፕላስቲክ እንቁላል ወደ ቤታችሁ ወስዳችሁ ነገ መልሳችሁ እንድታመጡት እፈልጋለሁ፡፡ ነገር ግን ስታመጡ በውስጡ አዲስ ሕይወትን ሊያሳይ የሚችል ነገር ማስቀመጣችሁን እንዳትረሱ› ብላ ነገረቻቸው፡፡
በቀጣዩ ቀን ጠዋት ላይ ሕፃናት ተማሪዎቹ የተሰጣቸውን የፕላስቲክ እንቁላል ይዘው ወደ ትምህርት ቤት መጡ፡፡ እየተሳሳቁ እና እየተጫወቱ በክፍላቸው ውስጥ መምህርታቸው ወዳዘጋጀችው ትልቅ ቅርጫት እንቁላሎቻቸውን ወረወሩ፡፡ ከዚያም እንቁላሎቹ ተከፍተው የሚታዩበት ጊዜ ሲደርስ አስተማሪያቸው አንድ በአንድ ከቅርጫቱ ማውጣት ጀመረች፡፡
የመጀመሪያውን እንቁላል ስትከፍተው በውስጡ አበባ አገኘች፡፡ ለሕፃናቱም “በትክክል፤ በርግጥም አበባ የአዲስ ሕይወት ምልክት ነው!” ስትል ግርምቷን ገለጸች፡፡ የዚህ እንቁላል ባለቤት የሆነችውም ተማሪ እጇን በማውጣት የእርሷ መሆኑን ስትገልጽ “ጥሩ አድርገሻል!” ብላ አመሰገነቻት፡፡ በቀጣይ ያነሣችው እንቁላልም በውስጡ ቢራቢሮ ነበረው፡፡ መምህርቷም እንቁላሉን ወደ ላይ ከፍ በማድረግ “አባ ጨጓሬ መሳዩ (ካተርፒለር) ነገር በመቀየር ወደ ውብ ቢራቢሮነት እንደሚሸጋገር እናውቃለን፡፡ በእውነትም ይህም አዲስ ሕይወት ነው” አለች፡፡
ቀጥላም ሦስተኛውን እንቁላል ከፈተችው፡፡ በውስጡ ግን ምንም የሌለው ባዶ ነበር፡፡ በእርግጠኝነት የእስክንድር እንቁላል መሆኑን አሰበች፡፡ በጊዜው የተናገረችውን ነገር በደንብ ስላልተረዳ ይህን ያደረገ መሰላት፡፡ ልትረብሸውም ስላልፈለገች እንቁላሉን ቀስ ብላ በማስቀመጥ ሌላኛውን ከቅርጫት ሳበች፡፡ ነገር ግን በሁኔታው የተደነቀው እስክንድር በድንገት “መምህርት፣ ስላመጣሁት እንቁላል ምንም አትይም እንዴ?” ሲል ጠየቃት፡፡ መምህርቷም ፊቷ ላይ የመረበሽ ምልክት እየታየባት ‹”እስክንድር፣ ግን እኮ እንቁላልህ ባዶ ነው” አለችው፡፡ እርሱም ዓይን ዓይኗን እያየ ለስለስ ባለ ድምፅ “አዎ መምህርት፤ የክርስቶስ መቃብርም እኮ እንዲሁ ባዶ ነበር” አላት፡፡
አስተማሪዋ የቀሩትን እንቁላሎች ለተማሪዎቹ አሳይታ ስትጨርስ ወደ እስክንድር በመሄድ “ለመሆኑ መቃብሩ ለምን ባዶ እንደሆነ ታውቃለህ?” አለችው፡፡ እርሱም “አዎ፤ ክርስቶስ ተገድሎ በዚያ ውስጥ ተቀብሮ ነበር፡፡ ነገር ግን እርሱ ከሞት ተነሣ፡፡ ታዲያ ይህ ነገር አዲስ ሕይወትን አያሳይምን?” ብሎ መለሰላት፡፡ ያቺም መምህርት በነገሩ ልቧ ተነክቶ ፊቷን ሸፍና አነባች፡፡
ይህም ነገር ከሆነ ከሦስት ወራት በኋላ ተማሪው እስክንድር አረፈ፡፡ የቀብር ሥርዓቱንም ለመከታተል የተሰበሰቡት ሰዎች አንድ እንግዳ ነገር በመቀበሪያው ሳጥኑ ውስጥ ተመለከቱ፡፡ ይኸውም የተከማቹ ሃያ እንቁላሎች ነበሩ፡፡ በክርስቶስ ትንሣኤ ምክንያት ባዶ እንደ ነበረው መቃብር ሃያዎቹ እንቁላሎችም ባዶ ነበሩ፡፡
Source : ‹The Eggs of Alexander› - Orthodox Parables and Stories /ከመለስተኛ ማሻሻያ ጋር
ትርጉም ፡ ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
ሕፃኑ እስክንድር እክል ካለበት ሰውነት ጋር የተወለደ ሲሆን፣ መለስተኛ የሆነ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ችግርም ነበረበት፡፡ እስክንድር ዕድሜው አሥራ ሁለት ዓመት ይሁን እንጂ በጊዜው ገና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ነበር፡፡ ካለበት የጤና እክልም የተነሣ መማር ይቸግረው ነበር፡፡ ታስተምረው የነበረች ሴት መምህርቱም በልዩ እንክብካቤ ያለና በእነርሱ የትምህርት ሥርዓት ውስጥ አብሮ መጓዝ እንደማይችል ተረድታዋለች፡፡ ይሁን እንጂ ጥሩ አስተማሪና እውነተኛ ክርስቲያን ስለነበረች ተማሪዋ እስክንድርን በትኩረት ትከታተለው ነበር፡፡ የፀደይ ወቅት በመድረሱ እንዲሁም የፋሲካም በዓል ከፊታቸው እየመጣ ስለሆነ ከእስክንድር ጋር የሚማሩት ሕፃናት ተማሪዎች በተደሰቱበት በአንዱ ቀን እንዲህ ሆነ፡፡
መምህርቷ ለተማሪዎቿ ሁሉ ትላልቅ የፕላስቲክ እንቁላል በመስጠት ‹ይህን የፕላስቲክ እንቁላል ወደ ቤታችሁ ወስዳችሁ ነገ መልሳችሁ እንድታመጡት እፈልጋለሁ፡፡ ነገር ግን ስታመጡ በውስጡ አዲስ ሕይወትን ሊያሳይ የሚችል ነገር ማስቀመጣችሁን እንዳትረሱ› ብላ ነገረቻቸው፡፡
በቀጣዩ ቀን ጠዋት ላይ ሕፃናት ተማሪዎቹ የተሰጣቸውን የፕላስቲክ እንቁላል ይዘው ወደ ትምህርት ቤት መጡ፡፡ እየተሳሳቁ እና እየተጫወቱ በክፍላቸው ውስጥ መምህርታቸው ወዳዘጋጀችው ትልቅ ቅርጫት እንቁላሎቻቸውን ወረወሩ፡፡ ከዚያም እንቁላሎቹ ተከፍተው የሚታዩበት ጊዜ ሲደርስ አስተማሪያቸው አንድ በአንድ ከቅርጫቱ ማውጣት ጀመረች፡፡
የመጀመሪያውን እንቁላል ስትከፍተው በውስጡ አበባ አገኘች፡፡ ለሕፃናቱም “በትክክል፤ በርግጥም አበባ የአዲስ ሕይወት ምልክት ነው!” ስትል ግርምቷን ገለጸች፡፡ የዚህ እንቁላል ባለቤት የሆነችውም ተማሪ እጇን በማውጣት የእርሷ መሆኑን ስትገልጽ “ጥሩ አድርገሻል!” ብላ አመሰገነቻት፡፡ በቀጣይ ያነሣችው እንቁላልም በውስጡ ቢራቢሮ ነበረው፡፡ መምህርቷም እንቁላሉን ወደ ላይ ከፍ በማድረግ “አባ ጨጓሬ መሳዩ (ካተርፒለር) ነገር በመቀየር ወደ ውብ ቢራቢሮነት እንደሚሸጋገር እናውቃለን፡፡ በእውነትም ይህም አዲስ ሕይወት ነው” አለች፡፡
ቀጥላም ሦስተኛውን እንቁላል ከፈተችው፡፡ በውስጡ ግን ምንም የሌለው ባዶ ነበር፡፡ በእርግጠኝነት የእስክንድር እንቁላል መሆኑን አሰበች፡፡ በጊዜው የተናገረችውን ነገር በደንብ ስላልተረዳ ይህን ያደረገ መሰላት፡፡ ልትረብሸውም ስላልፈለገች እንቁላሉን ቀስ ብላ በማስቀመጥ ሌላኛውን ከቅርጫት ሳበች፡፡ ነገር ግን በሁኔታው የተደነቀው እስክንድር በድንገት “መምህርት፣ ስላመጣሁት እንቁላል ምንም አትይም እንዴ?” ሲል ጠየቃት፡፡ መምህርቷም ፊቷ ላይ የመረበሽ ምልክት እየታየባት ‹”እስክንድር፣ ግን እኮ እንቁላልህ ባዶ ነው” አለችው፡፡ እርሱም ዓይን ዓይኗን እያየ ለስለስ ባለ ድምፅ “አዎ መምህርት፤ የክርስቶስ መቃብርም እኮ እንዲሁ ባዶ ነበር” አላት፡፡
አስተማሪዋ የቀሩትን እንቁላሎች ለተማሪዎቹ አሳይታ ስትጨርስ ወደ እስክንድር በመሄድ “ለመሆኑ መቃብሩ ለምን ባዶ እንደሆነ ታውቃለህ?” አለችው፡፡ እርሱም “አዎ፤ ክርስቶስ ተገድሎ በዚያ ውስጥ ተቀብሮ ነበር፡፡ ነገር ግን እርሱ ከሞት ተነሣ፡፡ ታዲያ ይህ ነገር አዲስ ሕይወትን አያሳይምን?” ብሎ መለሰላት፡፡ ያቺም መምህርት በነገሩ ልቧ ተነክቶ ፊቷን ሸፍና አነባች፡፡
ይህም ነገር ከሆነ ከሦስት ወራት በኋላ ተማሪው እስክንድር አረፈ፡፡ የቀብር ሥርዓቱንም ለመከታተል የተሰበሰቡት ሰዎች አንድ እንግዳ ነገር በመቀበሪያው ሳጥኑ ውስጥ ተመለከቱ፡፡ ይኸውም የተከማቹ ሃያ እንቁላሎች ነበሩ፡፡ በክርስቶስ ትንሣኤ ምክንያት ባዶ እንደ ነበረው መቃብር ሃያዎቹ እንቁላሎችም ባዶ ነበሩ፡፡
Source : ‹The Eggs of Alexander› - Orthodox Parables and Stories /ከመለስተኛ ማሻሻያ ጋር
ትርጉም ፡ ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
❤107👍29🥰7🙏6🔥5😍3