Telegram Web Link
2
                          †                          

      [   🕊    ማር ሚና      🕊   ]  

🍒▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🍒               

🕊 † ቅዱስ ሚናስ ምዕመን ሰማዕት † 🕊

❝ ጻድቃን ስለአንተ ታመሙ [ መከራን ተቀበሉ ] መከራቸውም ደስታ ሆነላቸው ፣ ክብር ይገባቸዋል ፣ በተጋድሎአቸው ሰማዕታት ፣ በትዕግስታቸውም መንግሥተ ሰማያትን ወረሱ። ❞

🕊

[  ቅዱስ ያሬድ   ]

†                       †                       †

የቅዱስ ሚናስ ምልጃና ጸሎቱ ከዘለዓለም እሳት ያድነን:: ጸጋ በረከቱ ይክፈለን::

🍒

†                       †                       †
💖                    🕊                    💖
2
1
                       †                       

  [  🕊  ድምፀ ተዋሕዶ   🕊  ]  

🍒▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🍒               

[  ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ።  ]

[ ሳምንታዊ መርሐ-ግብር ]

🕊             

[    " ቅ ዱ ሳ ት   መ ጻ ሕ ፍ ት  "    ]
             
             [     ክፍል ዘጠኝ     ]

❝ ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም ፤ ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና ፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ተናገሩ። ❞ [ ፪ጴጥ.፩፥፳ ]

▬▬▬▬▬▬   ♱    ▬▬▬▬▬▬

       💖   ድንቅ ትምህርት  💖

[ በመምህራችን በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ ]

የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል። ❞ [ ምሳ.፩፥፴፫ ]

         †              †               †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
                         👇
1
🕊

† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ †

❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖

❖ ሰኔ ፲፮ [ 16 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

🕊  † ቅዱስ አቡናፍር ገዳማዊ  †  🕊

ጻድቁ ተወልዶ ያደገው በ፭ [5] ኛው መቶ ክ/ዘመን በምድረ ግብፅ ነው:: ወቅቱ ሥርዓተ መነኮሳት የሚጠበቅበት:አበው ባሕታውያን እንደ ሰማይ ከዋክብት በዝተው የደመቁበት ነበር:: ታላቁ አቡናፍርም ከክርስቲያን ወላጆቹ ተወልዶ: በሥርዓት አድጎ: መጻሕፍትንም ተምሮ ገና በወጣትነቱ መንኗል::

ሥርዓተ መነኮሳትን ከአባ ኤስድሮስ ታላቁ አጥንቶ ገዳሙንና መምሕሩን እየረዳ ለብዙ ዓመታት በጾምና በጸሎት ኑሯል:: መነኮሳቱ ስለ ትሕትናውና ስለ ታዛዥነቱ ፈጽመው ያከብሩት ነበር::

ከዕለታት በአንዱ ቀን አረጋውያን መነኮሳት ጭው ባለ በርሃ ስለሚኖሩ ባሕታውያን ሲጨዋወቱ: ሲያደንቁዋቸውም ሰማ:: እርሱ በዛ ወቅት ባሕታውያን በበርሃ መኖራቸውን አያውቅም ነበርና ሒዶ መምሕሩን አባ ኤስድሮስን ጠየቃቸው:: እርሳቸውም "አዎ ልጄ! ከዚሕ በጣም ርቅው: ንጽሕናቸውን ጠብቀው: ከሰውና ከኃጢአት ተይለው የሚኖሩ ገዳማውያን አሉ" አሉት::

ቅዱስ አቡናፍር "በዚሕ ካሉት መነኮሳትና በበርሃ ካሉት ማን ይበልጣል?" ቢላቸው "እነርሱ በጣም ይበልጣሉ:: ዓለም እንኩዋ ከነ ክብሯ የእግራቸውን ሰኮና አታህልም" አሉት:: ይሕንን የሰማው ቅዱስ አባ አቡናፍር ጊዜ አላጠፋም::

ከመምሕሩ ቡራኬ ተቀብሎ ወደ በርሃ ሔደ:: ለብዙ ቀናት ከተጉዋዘ በኋላ አንድ ባሕታዊ አግኝቶ አብሯቸው ተቀመጠ:: ከእርሳቸው ዘንድም ሥርዓተ ባሕታውያንን ተምሮ እንደገና ወደ ዋናው በርሃ ጉዞውን ቀጠለ::

ከብዙ ቀናት መንገድ በኋላም አንድ ሠፊ ሜዳ ላይ ደረሰ:: አካባቢው የውሃ ጠብታ የማይገኝበት: ይቅርና መጠለያ ዛፍ የሣር ዘር እንኩዋ የሌለበት ወይም በልሳነ አበው "ዋዕየ ፀሐይ የጸናበት: ልምላሜ ሣዕር የሌለበት: ነቅዐ ማይ የማይገኝበት" ቦታ ነበር:: በዚህ ቦታ ይቅርና የሰው ልጅ አራዊትም አይኖሩበትም::

ለአባ አቡናፍር ግን ተመራጭ ቦታ ነበር:: ቅዱሳኑን ይሕ አያሳስባቸውም:: ምክንያቱም ለእነርሱ ምግባቸውም: ልብሳቸውም ፍቅረ ክርስቶስ ነውና:: አባ አቡናፍር ወደ ፈጣሪ ጸለዩ:: በእግዚአብሔር ቸርነት ከጎናቸው አንዲት ዘንባባ [በቀልት] በቀለች:: ከእግራቸው ሥርም ጽሩይ ማይ [ንጹሕ ምንጭ] ፈለቀች::

ጻድቁ ተጋድሏቸውን ቀጠሉ:: ዓመታት አለፉ:: ልብሳቸውን ፀሐይና ብርድ ጨርሶት ቅጠል ለበሱ:: በዚያ ቦታም የሰው ዘርን ሳያዩ ለ፷ [60] ዓመታት በተጋድሎ ኖሩ:: የሚያርፉበት ጊዜ ሲደርስ እግዚአብሔር አባ በፍኑትዮስን [የባሕታውያንን ዜና የጻፈ አባት ነው] ላከላቸው::

ቃለ እግዚአብሔርን እየተጨዋወቱ ሳለ የአባ አቡናፍር አካሉ ተለወጠ:: እንደ እሳትም ነደደ:: አባ በፍኑትዮስም ደነገጠ:: ታላቁ ገዳማዊ ግን እጆቻቸውን ዘርግተው ጸለዩ: ሰገዱና አማተቡ:: ነፍሳቸውም ከሥጋቸው በፍቅር ተለየች:: ቅዱሳን መላዕክትም በዝማሬና በማኅሌት አሳረጉዋት:: የሚገርመው ደግሞ አባ በፍኑትዮስ ይሕን ሲያይ ቆይቶ ዘወር ቢል ዛፏ ወድቃለች: ቅርንጯም ደርቃለች::

ዳግመኛ ይህች ዕለት የቅዱሳን አበው ባሕታውያን መታሠቢያ ናት::

ከሰው [ ከዓለም ] ርቀው: ንጽሕ ጠብቀው: ዕጸበ ገዳሙን: ግርማ አራዊቱን: ጸብዐ አጋንንትን ታግሠው የኖሩ: ስማቸውን የምናውቀውንም ሆነ የማናውቃቸውን እንድናከብራቸው ቤተ-ክርስቲያን ሥርዓትና በዓል ሠርታለች::

አምላካችን ከአበው ባሕታውያን ጸጋ በረከት ይክፈለን::

🕊

[ † ሰኔ ፲፮ [ 16 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]

፩. አባ አቡናፍር ገዳማዊ [ስም አጠራሩ የከበረ:
ሽምግልናው ያማረ አባት]
፪. አበው ቅዱሳን ባሕታውያን [ ዛሬ የሁሉም ቅዱሳን ባሕታውያን [በተለይም የስውራኑ] ዓመታዊ በዓል ነው::

- ከሰው: ከዓለምና ከኃጢአት ርቀው
- ንጽሕ ጠብቀው
- ዕጸበ ገዳሙን
- ድምጸ አራዊቱን
- ግርማ ሌሊቱን
- የሌሊቱን ቁር
- የመዓልቱን ሐሩር
- ረሐቡን: ጽሙን: መራቆቱን . . . ሁሉ
ስለ ፍቅረ-ክርስቶስ ሲሉ ታግሠውታልና::

"ዛሬም በየበርሃው የወደቁ: ስለ ዓለም ምሕረትን
የሚማጸኑ አሉ::"

አምላካቸው በረከታቸውን ያድለን።

፫. የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ በሕልም ከግብጽ እንዲመለስ የነገረበት [ተዝካረ ሚጠታ ለእግዝእትነ ማርያም]
፬. አፄ ይኩኖ አምላክ [ንጉሠ ኢትዮዽያ]

[ †  ወርኃዊ በዓላት ]

፩፡ ኪዳነ ምሕረት ማርያም
፪፡ ቅድስት ኤልሳቤጥ
፫፡ አባ ዳንኤል ገዳማዊ
፬፡ ቅዱስ አኖሬዎስ ንጉሠ ሮሜ
፭፡ አባ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ
፮፡ ቅዱስ ሐርቤ ንጉሠ ኢትዮጵያ

" . . . ሌሎችም መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ: ከዚሕም በላይ በእሥራትና በወኅኒ ተፈተኑ . . . ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ: እየተጨነቁ: የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ:: ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ: በዋሻና በምድር ጉድጉዋድ ተቅበዘበዙ:: ዕብ.፲፩፥፴፮] (11:36) "

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]

         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖
2
5
#ኪዳነምህረት_እናቴ 16 🙏🙏

#የብርሃን_እናቱ_ሆይ ካንቺ በነሳው ስጋ እኛነታችንን አከበረ፡ መዐዛሽ ስቦት አንችን በወደደ ጊዜ ድህነታችን ተሰራ #ድንግል_ሆይ እውነተኛው የህይወት እንጀራ : ጣፋጩን የነፍስ መጠጥ አማናዊው የፅድቅ ብርሀን የፈነጠቀብሽ ነሽና ከትውልድ መሀል #ብፅዕናሽን እንናገራለን ጥማችንን የቆረጠ ጥዑም ወይን ረሀባችንን ያጠፋ እውነተኛው መብል ካንቺ ወጥቶልናልና #እንወድሻለን ምስራቃዊት በራችን ሆይ ከሴቶች አንችን የሚመስል የለም፡ ባንቺ ላይ ስለተደረገልን ታላቅ ነገር ዛሬም ለዘላለምም ስምሽን እናገናለን፡፡

#ዝምተኛይቱ_ድንግል_ሆይ አንቺ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ የአይሁድ ሴቶች አይደለሽም በትሕትና ተልመሽ በንፅሕና አጊጠሽ የባህርያችንን መመኪያ ያስገኘሽልን የፅድቅ በራችን ነሽ።

#አንችን_ማመስገን የነፍስ ምግብ የህሊና እርካታ ነው #ስናመሰግንሽ እናርፋለን ስናርፍ #እናመሰግንሻለን። ክብርሽ ከሰማይ ምስጋናሽም ከአርያም ነውና አንችን ለማመስገን ልቦናችን ይብራ አሜን🙏

           #_ሰናይ__ቀን🙏

ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam  
@Enatachn_mareyam
10🙏2
🕊                      †                        🕊

[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

[   በቦታው ሁሉ ምሉ ነውና !  ]

🕊                    💖                       🕊


❝ ነፍሱን በሲኦል አልተወም ፥ ሥጋውም ሙስና መቃብርን አላየም። መለኮት ከሁለቱ [ ከነፍስ ከሥጋ ] አልተለየም ፤ ሁለንተናው ከነፍስ ጋር በሲኦል ነበረ። በሲኦልም ለጻድቃን የምሥራችን አበሠረ። ሁለንተናውም ከሥጋ ጋር በመቃብር ነበረ እንጂ። በቦታው ሁሉ ምሉ ነውና መለኮት በሕማም ድል አይነሣም ለሕማም አይገኝም። [ መዝ.፲፮ [፲፭]፥፲ ፤ ፹፰ [፹፯]፥፫-፮ ። ግብ ሐዋ.፪፥፳፯ ። ፩ጴጥ.፫፥፲፱ ና ፳ ]

ሌሎችም ባለማወቃቸው ቃል ሰው ስለመሆኑ ሲናገሩ 'ነፍስን ሥጋን አልነሣም እግዚአብሔር ቃል እንደ ዕሩቅ ብእሲ መርጦ አደረበት እንጂ' ይላሉ። ዳግመኛም ቃል በባሕርዩ እንደ ታመመ እንደ ሞተ  አብም እንደ አስነሣው ይናገራሉ ፥ ይህንን የሚናገሩ ሦስቱ ሞቱ እንዲያሰኝባቸው አያውቁም።

እግዚአብሔር ቃል በባሕርዩ ከሞተስ እነሆ አብም ዳግመኛ ሞተ እርሱ ራሱ [ ወልድ ] እኔ በአብ ህልው ነኝ አብም በእኔ ህልው ነው እኛ አንድ ነን ብሏልና።

ዳግመኛ እኔን ያየ አባቴን አየ ብሏልና ፤ ይህም እኔ የነገርኳችሁ ቃል እኔ ከራሴ አንቅቼ የነገርኳችሁ አይደለም ፤ በእኔ ህልውና ያለ አብ እርሱ ሥራውን ይሠራል እንጂ ብሏልና።

እኛ ግን ፦

ከእኛ ባሕርይ በነሣው ሥጋ እንደ ታመመ እንደ ሞተ እናምናለን
። እርሱ እግዚአብሔር ቃልም የተዋሐደውን ሥጋ ከሙታን ለይቶ እንዳስነሣው ፤ ያስነሣውም ሌላ እንዳይደለ እናምናለን ፤ ቅዱሳን አባቶቻችን ያስተማሩትን ትምህርት ትተው ክርስቶስ ፈጽሞ እንዳልታመመ እንዳልሞተ እንዳልተነሣ የሚናገሩ አሉ ፤ ይህንንም በመናገራቸው መለኮት ያጻፋቸውን መጻሕፍት ሁሉ ይለውጣሉ ፤ ሐሰትም ያደርጓቸዋል። [ ፪ጴጥ.፪፥፫-፲፮ ]

ለእኛ ግን ፦

እግዚአብሔር ያጻፋቸው ቅዱሳት መጻሕፍት ትምህርታችን ናቸው። መንፈስ ቅዱስም ክርስቶስ የማይታመም ፍጹም አምላክ ፤ የሚታመም ፍጹም ሰው ያለመለየትም አንድ አካል አንድ ባሕርይ ነው ብሎ በሐዋርያት አድሮ ተናገረ ፤ በሊቃውንት አድሮ አስተማረ ፤ ካልታመመ ካልሞተ ፤ ካልተነሣ ሌሎችን እንደምን ያስነሣል ?
[ ፩ቆሮ.፲፪፥፫ ፤ ፩ጴጥ.፩፥፲፩ ]

አልሞተም አልተነሣም የሚሉ ግን መለኮት ያጻፋቸው መጻሕፍትን ሐሰተኞች ያደርጓቸዋል ፤ ባለማወቃቸውም አምላክ የለም ፤ ትንሣኤም ቢሆን ፤ መንግሥተ ሰማያትም ቢሆን ወቀሳም ቢሆን ፍርድም ሲሆን የለም ይላሉ እርሱ ግን እንደ ከሀሊነቱ የወደደውን ሁሉ ያደርጋል። ❞

[    🕊   ቅዱስ ቄርሎስ   🕊     ]

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።


†                         †                         †
💖                     🕊                      💖
4
1
                         †                         


እግዚአብሔር ያጽናናሽ ቅድስት ቤተክርስቲያን !

▬▬▬▬▬▬   †    ▬▬▬▬▬▬

❝ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ የፈሰሰው የነቢያት ሁሉ ደም ፥ ከአቤል ደም ጀምሮ በመሠዊያውና በቤተ መቅደስ መካከል እስከ ጠፋው እስከ [ ካህኑ ] ዘካርያስ ደም ድረስ ፥ ከዚህ ትውልድ እንዲፈለግ አዎን እላችኋለሁ ፥ ከዚህ ትውልድ ይፈለጋል። ❞

[ ሉቃ.፲፩፥፶ ]

         †              †               †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
😢7
😢13
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

🕊     ም ክ ረ     ቅ ዱ ሳ ን     🕊

▷  " ሦስቱ የቅዱሳን ማዕረጋት ! "

[   " በሶርያ ቅዱሳን አባቶች ... ! "   ]

[                        🕊                        ]
-----------------------------------------------

-▷ የእግዚአብሔር ፍቅር ብልጭታ
-▷ ነፍስን መቀደስ
-▷ ተመሥጦና ፍጹም ደስታ


❝ እንግዲህ ፥ ወዳጆች ሆይ ፥ የዚህ ተስፋ ቃል ካለን ፥ በእግዚአብሔር ፍርሃት ቅድስናን ፍጹም እያደረግን ሥጋንና መንፈስን ከሚያረክስ ሁሉ ራሳችንን እናንጻ። ❞ [ ፪ቆሮ . ፯ ፥ ፩ ]


🕊                        💖                     🕊
                             👇
4
ሰው ከእግዚአብሔር ሲለይ ፦ 
ዓይኑ ያልተፈቀደውን ሁሉ ያያል።
ምላሱ ሰውን አራጅና አዋራጅ ትሆናለች።
ጀሮው የሰውን ኃጢአትና ገመና ሰሚ ይሆናል።
እጆቹ የሰውን ንብረትና አካል ዘራፊ ይሆናሉ።
እግሮቹ ነፍስንና ስጋን ወደሚያበላሹ ቦታዎች ይሮጣሉ።
ስጋው የዝሙት ፈረስ ይሆናል።
ልቡ የፍርሀትና የጭንከት ከበሮ ይመታል።
አእምሮው የአጋንንትና የሰይጣናት መስሪያ ቤት  ይሆናሉ።

          
#_ሰናይ__ቀን🙏

ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam  
@Enatachn_mareyam
🙏75😢1
2025/07/11 23:23:39
Back to Top
HTML Embed Code: