Telegram Web Link
#መድሐኒአለም_አባቴ
ዛሬም የወደድከኝ ተመስገን!

#የነፍሴ ንጉስ የህይወቴ ቤዛ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! #አመሰግንሃለሁ ። እኔን መውደድህ ይገርመኛል እንደሞተ ውሻ የምቆጠረውን #ማፍቀርህ ይደንቀኛል ። ኣምላኬ ሆይ ! ምኔን አይተህ ነው #የወደድከኝ ? ራሴን በጽሞና ሳየው ራሴን እንኳ መውደድ አቃተኝ ። አንተ ግን ህይወት ንጹህ ሳለህ እንደ ወንጀለኛ ተከሰስክልኝ ። የኔ አፍቃሪ ንጉስ #የማይገባኝን ልትሰጠኝ የማይገባህን መከራ ተቀበልክልኝ ።የምለው ባጣ እንዲሁ #ተመስገን ! እልሃለው ።በማላውቀው ጉዳይ እፈርዳለሁ አንተ ግን ብምታውቀው ጉዳይ ትምራለህ ። እባክህን እውቀትና ዕድሜ ያልለወጠኝን እባክህ አንተ #የልቤ ጌታ ለውጥልኝ ። እንደወደድከኝ መጠን ልወድህ #አልችልም ነገር እባክህን አቅም ስጠኝና እንደ አባቶቼ ቅዱሳን አብዝቼ #ልውደድህ! ዛሬም ተመስገን!

በማይቀየረው #ፍቅርህ በማይጠቁረው ፊትህ ለዘላለሙ አሜን !

#መልካም__ቀን🙏

የተለያዩ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇

@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
8🙏4
                       †                        

እንኳን ከዘመነ ፀደይ [ በጋ ] ወደ ዘመነ ክረምት የመሸጋገሪያ ዕለት በሰላም አደረሰን።

    🕊       ዘመነ ክረምት         🕊

" ሰማዩን በደመናት ይሸፍናል ለምድርም ዝናብን ያዘጋጃል ፤ ሣርን በተራሮች ላይ ያበቅላል ፤ ለምለሙንም ለሰው ልጆች ጥቅም።" [መዝ.፻፵፯፥፰]

🕊                        💖                     🕊


አራቱ አዝማናት [ ወቅቶች ] :-

፩. ዘመነ ክረምት [ ከሰኔ ፳፮ (26) እስከ መስከረም ፳፭ (25) ]
፪. ዘመነ መፀው [ ከመስከረም ፳፮ (26) እስከ ታኅሣሥ ፳፭ (25) ]
፫. ዘመነ ሐጋይ [ ከታኅሣሥ ፳፮ (26) እስከ መጋቢት ፳፭ (25) ]
፬. ዘመነ ፀደይ [ ከመጋቢት ፳፮ (26) እስከ ሰኔ ፳፭ (25) ] መሆናቸው ይታወቃል::

ዘመነ ፀደይን [ በጋን ] የባረከ አምላክ ዘመነ ክረምትን እንዲባርክልን : የንስሐ ጊዜም እንዲያደርግልን ቅዱስ ፈቃዱ ይሁን::

" የክረምት ጥቅሙ ይበልጥ የሚታወቀው ወራቱ ካለፈ በኋላ ነውና፡፡ የዚያን ጊዜ የአበባው ማበብ ፣ የአዝመራው ማፍራት ፣ ሌሎች ዕፅዋትም በቅጠላቸውና በፍሬያቸው በወርሐ ክረምት ያገኙትን ጥቅም ግልጽ አድርገው ይናገራሉና ! "

[  ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ  ]


🕊                        💖                     🕊
5
3
                       †                           

†    🕊  መንፈሳዊው መሰላል  🕊   †


           [   ክፍል  አርባ አራት  ]

▬▬▬▬▬▬   ♱    ▬▬▬▬▬▬

ይህችውም ሆድህ ናት .......

❝ ሕዋሳት ትእዛዛትን ከባድ ሆነው ሲያገኙዋቸው ፣ ይበልጥ ሰነፍ የሆኑት ራሳቸውን በጸሎት ማስጠመድ እንዲሻላቸው ይመርጣሉ፡፡ ሆኖም ቀላል የሆነውን ነገር በታዘዙ ጊዜ ግን ከእሳት እንደሚሸሽ ከጸሎት ይሸሻሉ፡፡ ወይም [ ይበልጥ ሰነፍ የሆኑ ትእዛዛትን ከባድ ቀላል የሆነውን ትእዛዝ ሆነው ሲያገኟቸው ፣ ጸሎት እንደሚሻላቸው ይመርጣሉ ፣ እንዲፈጽሙ ሲነገራቸው ግን ከእሳት እንደሚሸሽ ከጸሎት ይሸሻሉ ] ፡፡

አንዳንዶች አንድን የተለየ ተግባር ይፈጽማሉ ፤ ይሁን እንጂ ስለ አንድ ወንድም ይህንኑም ተዉት፡፡ አንዳንዶች በስንፍና ምክንያት ሕሊና ብለው በእርሱ ጥያቄ ይህንኑም ተግባሮቻቸውን ተዉ ፤ ሌሎች ግን ከውዳሴ ከንቱ የተነሣ ፣ ሌሎችም ከቀናኢነት የተነሣ ይህን አልተዉትም፡፡

ራስህን በግዴታዎች ካሰርክ ፣ ዓይነ ነፍስህም እንዳልጠራ ካሰብህ ፣ ትተወው ዘንድ ዕረፍትን አትጠይቅ፡፡ አማናዊ ነገሮች በየትም ስፍራ አማናዊ ናቸው ፣ የዚሁ ተቃራኒም እንዲሁ ነው። በዓለም ውስጥ ሐሜት ለብዙ መለያየቶች መንስኤ ሆኖዋል ፤ በማኅበር ግን በላተኝነት ውድቀቶችንና አለመታዘዝን ሁሉ ያመጣል፡፡

በእመቤትህ ላይ ከሰለጥንክባት [ ይህችውም ሆድህ ናት ] ፣ ማንኛውም የመኖሪያ ስፍራ ፈቃድን መተው [ መቲረ ፈቃድን ] ያጎናጽፍሃል ፣ እሷ ብትሰለጥንብህ ግን ከመቃብር ታወጣሃለች ፣ ከዚያም በየስፍራው ለአደጋ የተጋለጥህ ትሆናለህ፡፡ ❞

[ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ]


🕊                      💖                     🕊
1
2
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

🕊       [   ምክረ ቅዱሳን   ]        🕊


▷     "  እ ግ ዚ አ ብ ሔ ር አ ለ !  " 

💖 በብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ 💖  ]

[           🕊   ስብከት    🕊              ]

▬▬▬▬▬▬   ♱    ▬▬▬▬▬▬


❝ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እስኪገለጥ ድረስ ያለ እድፍና ያለ ነቀፋ ሆነህ ትእዛዙን ጠብቅ ፤ ያንም መገለጡን በራሱ ጊዜ ብፁዕና ብቻውን የሆነ ገዥ ፥ የነገሥታት ንጉሥና የጌቶች ጌታ ፥ ያሳያል።

እርሱ ብቻ የማይሞት ነው ፤ ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን ይኖራል ፤ አንድ ሰው እንኳ አላየውም ሊያይም አይቻለውም ፤ ለእርሱ ክብርና የዘላለም ኃይል ይሁን ፤ አሜን። ❞

[  ፩ጢሞ . ፮ ፥ ፲፬ - ፲፮  ]



🕊                       💖                   🕊
6🙏1
3
🕊

[ †  እንኩዋን ለስደተኛው ሊቀ ዻዻሳት "አባ ቴዎዶስዮስ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ  † ]

🕊   †  አባ ቴዎዶስዮስ   †   🕊

ጻድቁ ሊቀ ዻዻሳት ተወልዶ ያደገው በምድረ ግብጽ በ6ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው:: ከልጅነቱ መጻሕፍትን ተምሮ በመንኖ ጥሪት የሚኖር ደግ ሰው ነበር:: ያ ዘመን መለካውያንና ልዮናውያን [ክርስቶስን ፪ [2] ባሕርይ የሚሉ] የሰለጠኑበት ዘመን ነበር:: በአንጻሩ ደግሞ ተዋሕዶን የሚያምኑ ሊቃውንትና ምዕመናን ቁጥራቸው የተመናመነ ነበር::

ችግሩ ግን ይህ ብቻ አልነበረም:: በጊዜው ተዋሕዶን አምኖ መገኘት እስከ ሞት የሚደርስ ዋጋንም ያስከፍል ነበር:: ለዚሕም ነው ሮማውያን ሃይማኖትን በግድ ለማስለወጥ ከነገሥታቱ ጋር የተቆራኙት:: ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ጋግራ ደሴት ውስጥ ከተገደለ በሁዋላ በግብፅ የተሾሙ ሊቃነ ዻዻሳት አብዛኞቹ መከራና ስደትን ቀምሰዋል:: ትልቁን ቦታ ግን አባ ቴዎዶስዮስ ይወስዳል::

አባ ቴዎዶስዮስ ለእስክንድርያ [ግብፅ] ፴፫ [33] ኛ ፓትርያርክ ነው:: እረኝነት [ዽዽስና] እንዳሁኑ ዘመን ሠርግና ምላሽ አይደለምና ገና እንደ ተሾመ የቀረበለት ጥያቄ አንድ ነበር:: "ተዋሕዶን ትተህ መለካዊ ትሆናለህ ወይስ የሚከተልብህን ፍርድ ትቀበላለህ?" አሉት:: ይህንን ያሉት ከንጉሡ ዮስጢያኖስ የመጡ መልእክተኞች ነበሩ:: መልሱ ፈጣን ሆነባቸው:: "እኔንም ሆነ ሕዝቤን ከቀናችው እምነታችን በምንም ልትለዩን አትችሉም" አላቸው::

በዚህ ምክንያት በቀጥታ ግዞት [ስደት] ተፈረደበት:: ወደ በርሃ ሲያግዙት ካህናት : መምሕራንንና ምዕመናንን አደራ ብሏቸው ነው የሔደው:: መናፍቃኑ እሱን ካሰደዱ በሁዋላ ሕዝቡን ለመቀየር ብዙ ደክመዋል:: ግን ሊሳካላቸው አልቻለም:: ምክንያቱም አደርነትን የማይረሱ ደጋግ መምሕራን ነበሩና ነው::

በዚያ ላይ አባ ቴዎዶስዮስ ጦማር [መልእክት] በየጊዜው ይጽፍላቸው ነበር:: እጅግ ብዙ ከሆኑት መልእክቶቹ የተወሰኑት ዛሬም ድረስ ሃይማኖተ አበው መጽሐፍ ውስጥ ይገኛሉ::

በዚሕ አስቸጋሪ ዘመን መልካም ነገሮችም ነበሩ:: ቀዳሚው ማሕቶተ ተዋሕዶ ቅዱስ ያዕቆብ ዘእልበረዳይ ሲሆን ፪ [2] ኛው ደግሞ የንጉሡ ሚስት የተባረከችው ታኦድራ ናት::

አባ ቴዎዶስዮስ በግዞትና በስደት ሳለ ንግሥቲቱ ትራዳው : ምዕመናንንም ትንከባከብ ነበር:: ቅዱስ ያዕቆብ ከሊቀ ዻዻሱ ዘንድ ክህነትን ተቀብሎ ከሶርያ እስከ ምድረ ግብጽ ስለ ተዋሕዶ ሕልውና ተጋድሏል:: ምናልባትም ከሐዋርያው ቅዱስ ዻውሎስ በሁዋላ በፈሊጥ ክርስትናን በማስፋፋት ቀዳሚ አባት ነው:: [በነገራችን ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ማዕተብ ማሰርን ያስተማረ አባትም ነው]

፪ [2] ቱ [አባ ቴዎዶስዮስና ቅዱስ ያዕቆብ] ስለ ቀናች ሃይማኖት ብዙ ስለ ደከሙ የዘመኑ ምዕመናን በስማቸው "ያዕቆባውያን እና ቴዎዶስዮሳውያን" ተብለው ተጠርተዋል:: አባ ቴዎዶስዮስ ግን ሲታሠር ሲፈታ : ሲሰደድ ሲመለስ ብዙ ተሰቃየ::

ሕዝቡን ግን በመልካም እረኝነት ጠብቆ : ከተኩላ አፍ ታደገ:: በዚህች ቀንም ዐርፎ ተቀብሯል:: በፓትርያርክነት ያገለገለባቸው ዘመናት ፴፪ [32] ዓመታት ሲሆኑ ከእነዚህ ዓመታት ፳፰ [28] ቱ ያለቁት በስደትና በመከራ ነው::

እግዚአብሔር የአባቶቻችን ስደት አስቦ ከነፍስ ስደት ይሰውረን:: ከበረከታቸውም ያድለን::

🕊

[ † ሰኔ ፳፰ [ 28 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]

፩. አባ ቴዎዶስዮስ ሊቀ ዻዻሳት
፪. ቅዱስ ያዕቆብ ዘእልበረዳይ
፫. ቅዱስ ባስልዮስ
፬. ቅዱስ ባሊዲስ

[ †  ወርኀዊ በዓላት ]

፩. አማኑኤል ቸር አምላካችን
፪. ቅዱሳን አበው [አብርሃም: ይስሐቅና ያዕቆብ]
፫. ቅዱስ እንድራኒቆስና ሚስቱ ቅድስት አትናስያ
፬. ቅድስት ዓመተ ክክርስቶስ
፭. ቅዱስ ቴዎድሮስ ሮማዊ [ሰማዕት]

" ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብጹዓን ናቸው:: መንግስተ ሰማያት የእነርሱ ናትና:: ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዷችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብጹዓን ናችሁ:: ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ:: ሐሴትም አድርጉ:: ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳደዋቸዋልና:: " [ማቴ.፭፥፲] (5:10)

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖
5🙏1
3
ድል አለ በስምህ ድል አለ በቃልህ ተራራው ይናዳል #አማኑኤል ስልህ ባህር ይከፈላል መድሀኒአለም ስልህ የመኖራችን ትርጉም የቀራኒዮ ንጉስ የድንግል ማርያም ልጅ ቸሩ #አማኑኤል ከክፉ ሁሉ ይጠብቃችሁ #ሲከፍችሁ ክንዱን ዘርግቶ አለሁ ይበላችሁ 🙏 በያለንበት ሁላችንንም ይጠብቀን

                  
#ሰናይ__ቀን🙏

ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam  
@Enatachn_mareyam
8🙏2
🕊

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ:: አሜን::

🕊   †  ቅዱስ ያዕቆብ ዘእልበረዲ [ እል-በረዳይ ] [ St. Jacob baradaeus ]  †   🕊


[ በተለይ በሃገራችን የተዘነጋ የሚመስለው የምሥራቅ ኮከብ - ኮከበ ጽባሕ ]

🕊

"ያዕቆብ" ለሚል ስም ትርጉምን የሰጡ አበው በ2 መንገድ ያትቱታል::

፩. አኃዜ ሰኮና:: ነገሩ ከወልደ ይስሐቅ ወርብቃው ርዕሰ አበው ያዕቆብ ጋር የተያያዘ ቢሆንም አበው ግን ለትህትና ይተረጉሙታል::
፪. አእቃጺ / አሰናካይ:: ነገሩ ስድብ [ አሉታዊ ] ይምሰል እንጂ በዚህ ስም የተጠሩ አበው ሁሉ ለአጋንንትና ለመናፍቃን ትልቅ መሰናክል ሆነውባቸው ኑረዋልና አባባሉ ምስጋና እንጂ ነቀፋን አይወክልም::

የ፮ኛው መቶ ክ/ዘመን ምሥራቃዊ ኮከብ ቅዱስ ያዕቆብም ለመለካዊ መናፍቃንና ለተዋሕዶ ተገዳዳሪዎች ትልቅ መሰናክል ሆኖባቸዋል:: የቀናችውን ቀርነ ሃይማኖትንም አጽንቷል::

ብዙ ጊዜ "ዘ" - እልበረዲ መባሉን ይዘው በ"ዘ" ምክንያት እልበረዲን እንደ ሃገር የቆጠሯት አልጠፉም:: በረከታቸው ይድረሰንና ትጉሑ ዻዻስ አቡነ ጐርጐርዮስ ካልዕ ግን ለዚሁ መላምት "የለም!" ባይ ናቸው::
'የቤተ ክርስቲያን ታሪክ በዓለም መድረክ' በተሰኝ ተወዳጅ መጽሐፋቸው "እል-በረዲ" ማለትን በዓረብኛ ከሠጋር በቅሎ : ከሥሙር ሠረገላ ጋር አነጻጽረው አስቀምጠውታል:: ለምን ቢባል

- እንደ ሠረገላ በተፋጠነ አገልግሎቱ ወዳጅንም ጠላትንም አስደምሟልና::
+ቅዱስ ያዕቆብ የተወለደው በ፮ኛው መቶ ክ ዘመን መጀመሪያ [ በ፭፻ አካባቢ ] ሲሆን ያረፈው ደግሞ በ፭፻፸፰ ዓ/ም እንደሆነ ይታመናል:: ነገሩን ልብ ስንለው ቅዱስ ማኅሌታይ ያሬድን - ወዲህ በዘመን : ወዲያ ደግሞ በአገልግሎት ይመስለዋል::

እርግጥ ነው ለውለታው የሶርያ ቤተ ክርስቲያን "ያዕቆባዊት" ስትባል የእኛዋስ ምናለ "ያሬዳዊት" ብትባል የሚል ቁጭትን ያመጣል::
+ ጊዜው [ ፭ኛውና ፮ኛው መቶ ክ/ዘመን] ወዲህ ወርቃማ : ወዲያ ደግሞ ጨለማ ተብሎ ሊጠራ የሚችል ዘመን ነበር::
¤ በብርሃንነቱ በተለይ በምሥራቁ ዓለም ያበሩ አበው እነ ያዕቆብ ዘስሩግ : ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ : ያዕቆብ ዘእልበረዲን የመሰሉ አበው ተገኝተውበታል:: ሲያልፍ ደግሞ ዘይኑንና አንስጣስዮስን የመሰሉ ደጋግ ነገሥታት በዘመኑ መነሳታቸውን እናስባለን::

+ በተቃራኒው ግን ዘመኑ ቤተ ክርስቲያን ለ፪ የተከፈለችበት : መለካውያን የነገሥታቱ ደጀን አላቸውና ተዋሕዶ ሃይማኖትን ከሥሯ ነቅሎ ለማጥፋት ብዙ የሞከሩበት ዘመን ነውና ጨለማነቱ ይጐላብናል::
+ በእርግጥም ከመርቅያን እስከ ዮስጢኖስ ዳግማዊ ዘመን ድረስ ለ፻ ዓመታት መለካውያኑ የልዮን ልጆች ፪ ባሕርይ ማለትን ሊያሰፉ : ተዋሕዶንም ሊያጠፉ የከፈቱት ዘመቻ ሊሳካ ጫፍ የደረሰ ይመስል ነበር::

+ ግን አማናዊት ቤቱን የማይተው አማናዊው ጌታ መድኃኔ ዓለም አርመኖቹን ስቦ በ፬፻፺ዎቹ ወደ መንጋው ቀላቀለ:: በግብጽ አባ ቴዎዶስዮስን : በሶርያ ደግሞ ታላቁን ሊቅ ቅዱስ ሳዊሮስን አስነስቷል:: ከቤተ መንግስትም ስም አጠራሯ ያማረ ንግሥት ታኦድራን ማርኯል:: በእነዚህ ቅዱሳን ትጋት የለመለመችው ተዋሕዶ እንደ ቅዱስ ያዕቆብ ዘእልበረዲ ያለ አርበኛን ግን ያገኘችው በጭንቅ ቀን ነበር::

+ ሰው መሆን ሰው በጠፋባቸው ቀናት ነውና : በግብጽና በቁስጥንጥንያ በትምህርትና ምናኔ ላይ የነበረው ቅዱሱ ታጥቆ ለአገልግሎት የተሰለፈው በ፭፻፴ዎቹ አካባቢ ነበር::
+ ጊዜው ወዲህ አንበሳው ቅዱስ ሳዊሮስ ከሶርያ ወደ ግብጽ እንደተሰደደ ያረፈበት ነበር:: ወዲያ ደግሞ ሊቁ አባ ቴዎዶስዮስ የግብጹ ለግዞት የተዳረገበት ነበርና የተዋሕዶ ምዕመናን ያለ እረኛ ተቅበዘበዙ:: የቤተ መንግስቱ ተጽዕኖ ደግሞ ፪ ባሕርይ በማይሉት ላይ እሥራትና ግድያን ወደ ማወጅ ተሸጋግሯልና የምእመናን ቁጥር እጅጉን መመንመኑ ቀጠለ::
+ ይህ ዕረፍት የነሳው ቅዱስ ያዕቆብ በበኩሉ ነገሩን በዝምታ ሊያልፈው አልወደደምና አገልግሎቱን አሰፋ:: ሌሊቱን በጸሎት ያድራል:: ቀን በቤተ ክርስቲያን አካባቢ ማስተማር ባይችል በየቦታው እየዞረ ያስተምር ነበር::
+ ከትምህርቱ ጣዕምና ከመልእክቱ ሥምረት የተነሳም ምእመናን እንደገና ተነቃቁ:: እርሱም ከግብጽ እስከ ሶርያ : አልፎም እስከ ቁስጥንጥንያ ድረስ ያለ ዕረፍት ሲሰብክ ፵ ዘመናትን አሳለፈ:: በተለይ አዲስ አማኞችን ያጠምቅ ዘንድ በእሥረኛው ቅዱስ ቴዎዳስዮስ ኤዺስ ቆዾስነትን ተቀብሏል::

+ የሶርያ [ አንጾኪያ ] የፕትርክና መንበሩ ክፍት ሆኖ እርሱን ቢጠብቀውም እርሱ ግን የዚህ [ የስልጣን ] ፈላጊ አልነበረምና ሌሎች እንዲሾሙበት አድርጉዋል::
+ ቅዱስ ያዕቆብ በስብከት አገልግሎት ምሥራቁን ዓለም ሲያበራ የተባበሩት ደቀ መዛሙርት ቢኖሩም ያሳለፈው ድካምና መከራ ግን ተወዳዳሪ አልነበረውም:: በተለይ የወቅቱ የአንጾኪያ ኃያላን መኩዋንንትና ሹመኛ መናፍቃን ብዙ አሳደውታል::
+ እርሱ ግን በጥበብና በፈሊጥ እዚያው ደጃቸው ላይ የነበሩ ምዕመናንን በእረኝነት ጠብቁአል:: ለዚህ ሲባልም ራሱን እየቀያየረ የመሣፍንቱን አጥሮችና ቅጥሮች አልፏል:: ለቤተ ክርስቲያን ክብርም እንደ እብድ : እንደ ሴትም መስሎ የወንጌልን ዘር ዘርቷል::

¤ ከብዙ ፈተናና አገልግሎት በሁዋላም በተወለደ በ፸፰ ዓመቱ [ በ፭፻፸፰ ዓ/ም ] ዐርፎ በክብር ተቀብሯል::

¤ ትልቁ መታሰቢያው የሶርያ ቤተ ክርስቲያን "ያዕቆባዊት" : ምዕመኑ "ያዕቆባውያን" መባላቸው ሲሆን እኛ ደግሞ በአንገታችን ላይ እንድናስራት ባስተማረን ማዕተብ [ ማኅተም ] ዘወትር እናስበዋለን:: ለመጀመሪያ ጊዜ ማዕተብን በአንገት ላይ ስለ ማሰር ያስተማረ እርሱ ነውና::

¤ የምሥራቁን ኮከብ እል-በረዲ ያዕቆብን በየዓመቱ ሰኔ ፳፰ ቀን በነገረ ቅዱሳን መደበኛ ጉባኤ [ ጐንደር ] እናከብራለን:: ሶርያውያን ደግሞ July 31 [ ሐምሌ ፳፬ ቀን ] ያከብሩታል::

" እናንተ የምድር ጨው ናችሁ . . . እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ:: በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሠወር አይቻላትም:: መብራትንም አብርተው በዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያናሩታል:: በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል:: መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ:: " [ ማቴ. ፭ ፥ ፲፫ - ፲፮ ]

አምላከ ቅዱስ ያዕቆብ ተዋሕዶ ሃይማኖታችን ይጠብቅልን:: ከቅዱሱ በረከትም አይለየን::

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †

[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]


         †              †               †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖                   🕊                    💖
1🙏1
5
                       †                       

  [  🕊  ድምፀ ተዋሕዶ   🕊  ]  

🍒▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🍒               

[  ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ።  ]

[ ሳምንታዊ መርሐ-ግብር ]

🕊             

[    " ቅ ዱ ሳ ት   መ ጻ ሕ ፍ ት  "    ]
             
         [    የመጨረሻ ክፍል     ]

❝ ይህን በመጀመሪያ እወቁ ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም ፤ ትንቢት ከቶ በሰው ፈቃድ አልመጣምና ፥ ዳሩ ግን በእግዚአብሔር ተልከው ቅዱሳን ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተነድተው ተናገሩ። ❞ [ ፪ጴጥ.፩፥፳ ]

▬▬▬▬▬▬   ♱    ▬▬▬▬▬▬

       💖   ድንቅ ትምህርት  💖

[ በመምህራችን በቀሲስ ኅብረት የሺጥላ ]

የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል። ❞ [ ምሳ.፩፥፴፫ ]

         †              †               †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
                         👇
🙏1
2025/07/11 23:26:28
Back to Top
HTML Embed Code: