This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
†
❝ እኔ ብቻዬንና ችግረኛ ነኝና ፊትህን ወደ እኔ አድርግ ማረኝም።
የልቤ ችግር ብዙ ነው ፤ ከጭንቀቴ አውጣኝ። ድካሜንና መከራዬን እይ ፥ ኃጢአቴንም ሁሉ ይቅር በለኝ። ❞
[ መዝ . ፳፭ ፥ ፲፮ ]
† † †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
❝ እኔ ብቻዬንና ችግረኛ ነኝና ፊትህን ወደ እኔ አድርግ ማረኝም።
የልቤ ችግር ብዙ ነው ፤ ከጭንቀቴ አውጣኝ። ድካሜንና መከራዬን እይ ፥ ኃጢአቴንም ሁሉ ይቅር በለኝ። ❞
[ መዝ . ፳፭ ፥ ፲፮ ]
† † †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
❤6🙏2
🕊
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞
[ ✞ እንኳን ለአባቶቻችን ቅዱሳን ፲፪ [ 12 ] ቱ ደቂቀ ነቢያት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞ ]
🕊 ✞ ፲፪ [12] ቱ ቅዱሳን ደቂቀ ነቢያት ✞ 🕊
ነቢይ ማለት ከእግዚብሔር ተመርጦ ኃላፍያትን [አልፎ የተሠወረውን] : መጻዕያትን [ለወደፊቱ የሚደረገውን] የሚያውቁ ሰዎች ሲሆኑ ሕዝቡን እንዲመሩ: እንዲገስጹም ይላካሉ:: ሕይወታቸውም በቅድስና የተለበጠ ነው:: ነቢያትን በቁጥር መግለጽ ከባድ ቢሆንም ቤተ ክርስቲያን እንድንረዳቸው እንዲህ ትከፍላቸዋለች::
=> በኩረ ነቢያት አዳም
=> ሊቀ ነቢያት ሙሴ
=> ርዕሰ ነቢያት ኤልያስ
=> ልበ አምላክ ዳዊት
=> ፲፭ [15] ቱ ነቢያት [ከአዳም ጀምሮ እስከ ሳሙኤል]
=> ፬ [4] ቱ ዐበይት ነቢያት [ኢሳይያስ: ኤርምያስ: ሕዝቅኤልና ዳንኤል]
፲፪ [12] ቱ ደቂቀ ነቢያት ደግሞ ከሆሴዕ እስከ ሚልክያስ ያሉት ናቸው:: በዚህች ቀን ታዲያ ፲፪ [12] ቱ ቅዱሳን ደቂቀ ነቢያት በአንድነት ይታሠባሉ:: እነዚህም :-
፩. ቅዱስ ሆሴዕ [ኦዝያ]
፪. ቅዱስ አሞጽ
፫. ቅዱስ ሚክያስ
፬. ቅዱስ ኢዩኤል
፭. ቅዱስ አብድዩ
፮. ቅዱስ ዮናስ
፯. ቅዱስ ናሆም
፰. ቅዱስ እንባቆም
፱. ቅዱስ ሶፎንያስ
፲. ቅዱስ ሐጌ
፲፩. ቅዱስ ዘካርያስ እና
፲፪. ቅዱስ ሚልክያስ ናቸው::
ቅዱሳኑ ደቂቀ ነቢያት የተባሉት
፩. የነቢያት ልጆች በመሆናቸው
፪. የጻፏቸው ሐረገ ትንቢቶች በንጽጽር ከዐበይቱ [ከነኢሳይያስ] ስለሚያንስ ነው::
በምግባር: በትሩፋት: በአገልግሎት ግን ያው ናቸው:: ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እሊህን ነቢያት "እለ አውኀዙ ተነብዮ በእንተ ስመ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ" ይሏቸዋል:: [ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መውረድ: መወለድና የማዳን ሥራ የትንቢት ጐርፍን ያፈሰሱ እንደ ማለት ነው ::]
ቅዱሳኑ ከክርስቶስ የማዳን ሥራ ባሻገር ዓለማችን ላይ ከነበሩበት ዘመን እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሊደረጉ ያላቸውን ነገሮችም ተናግረዋል:: የነበሩበት ዘመን በአማካኝ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ ከ፱ መቶ [900] እስከ ፭ [500] ነው:: በትንቢት ደረጃም እንደነ ሆሴዕና ዘካርያስ ፲፬ [14] ምዕራፎችን: እንደነ አብድዩም አንዲት ምዕራፍ ብቻም የጻፉ አሉ::
በሕይወታቸው ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ያሻቸው ናቸውና በየጊዜው ከእግዚአብሔር ጋር እየተነጋገሩ የእርሱን ድምጽ ለእሥራኤል [አንዳንዴም ለአሕዛብ] ያደርሱ ነበር:: ፊት አይተው የማያዳሉ ናቸውና ሕዝቡንም ሆነ ነገሥታቱን ስለ ኃጢአታቸው ይገሰጹ ነበር:: በዚህም ምክንያት ከነገሥታቱና ከሕዝቡ አለቆች መከራ ደርሶባቸዋል:: አልፎም ያለ አበሳቸው ሕዝቡ በኃጢአቱ ሲማረክ አብረውት ወርደዋል::
በመጨረሻ ሕይወታቸውም አንዳንዶቹን ክፉዎች ሲገድሏቸው አንዳንዶቹ ደግሞ በመልካም ሽምግልና ዐርፈዋል:: ዛሬ ነቢያት ከእነርሱ ባሕርይ በተገኘችና ብዙ ትንቢትን በተናገሩላት በእመቤታችን ምክንያት ክርስቶስ ድኅነትን ፈጽሞላቸው በተድላ ገነት ይኖራሉ:: ስለ እኛም ይማልዳሉ::
" ናጥሪ እንከ ትሕትና ዘምስለ ንጽሕና"
[ እንግዲህ እንደ ነቢያት ትሕትናን ከንጽሕና ጋር ገንዘብ እናድርግ ]
"እስመ በአንጽሖ መንፈስ ርዕይዎ ነቢያት ለእግዚአብሔር: ወተናጸሩ ገጸ በገጽ"
[ ነቢያት መንፈስን ንጹሕ በማድረግ እግዚአብሔርን አይተውታልና: ፊት ለፊትም ተያይተዋልና ]
/ቅዳሴ ማርያም/
ከአባቶቻችን ቅዱሳን ነቢያት በረከት ይክፈለን::
🕊
[ † ሐምሌ ፬ [ 4 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. "12ቱ" ቅዱሳን ደቂቀ ነቢያት
፪. ቅዱስ ሶፎንያስ ነቢይ [ዕረፍቱ]
፫. ቅዱሳን ሰማዕታት አቡቂርና ዮሐንስ [ቅዳሴ ቤታቸው]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጉዋድ [ወንጌላዊው]
፪. ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ
፫. ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
፬. ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ [ሰማዕት]
" ለእናንተም ስለሚሰጠው ጸጋ ትንቢት የተናገሩት ነቢያት ስለዚህ መዳን ተግተው እየፈለጉ መረመሩት:: በእነርሱም የነበረ የክርስቶስ መንፈስ ስለ ክርስቶስ መከራ ከእርሱም በሁዋላ ስለሚመጣው ክብር አስቀድሞ እየመሠከረ በምን ወይም እንዴት ባለ ዘመን እንዳመለከተ ይመረምሩ ነበር:: " [፩ዼጥ.፩፥፲]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞
[ ✞ እንኳን ለአባቶቻችን ቅዱሳን ፲፪ [ 12 ] ቱ ደቂቀ ነቢያት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞ ]
🕊 ✞ ፲፪ [12] ቱ ቅዱሳን ደቂቀ ነቢያት ✞ 🕊
ነቢይ ማለት ከእግዚብሔር ተመርጦ ኃላፍያትን [አልፎ የተሠወረውን] : መጻዕያትን [ለወደፊቱ የሚደረገውን] የሚያውቁ ሰዎች ሲሆኑ ሕዝቡን እንዲመሩ: እንዲገስጹም ይላካሉ:: ሕይወታቸውም በቅድስና የተለበጠ ነው:: ነቢያትን በቁጥር መግለጽ ከባድ ቢሆንም ቤተ ክርስቲያን እንድንረዳቸው እንዲህ ትከፍላቸዋለች::
=> በኩረ ነቢያት አዳም
=> ሊቀ ነቢያት ሙሴ
=> ርዕሰ ነቢያት ኤልያስ
=> ልበ አምላክ ዳዊት
=> ፲፭ [15] ቱ ነቢያት [ከአዳም ጀምሮ እስከ ሳሙኤል]
=> ፬ [4] ቱ ዐበይት ነቢያት [ኢሳይያስ: ኤርምያስ: ሕዝቅኤልና ዳንኤል]
፲፪ [12] ቱ ደቂቀ ነቢያት ደግሞ ከሆሴዕ እስከ ሚልክያስ ያሉት ናቸው:: በዚህች ቀን ታዲያ ፲፪ [12] ቱ ቅዱሳን ደቂቀ ነቢያት በአንድነት ይታሠባሉ:: እነዚህም :-
፩. ቅዱስ ሆሴዕ [ኦዝያ]
፪. ቅዱስ አሞጽ
፫. ቅዱስ ሚክያስ
፬. ቅዱስ ኢዩኤል
፭. ቅዱስ አብድዩ
፮. ቅዱስ ዮናስ
፯. ቅዱስ ናሆም
፰. ቅዱስ እንባቆም
፱. ቅዱስ ሶፎንያስ
፲. ቅዱስ ሐጌ
፲፩. ቅዱስ ዘካርያስ እና
፲፪. ቅዱስ ሚልክያስ ናቸው::
ቅዱሳኑ ደቂቀ ነቢያት የተባሉት
፩. የነቢያት ልጆች በመሆናቸው
፪. የጻፏቸው ሐረገ ትንቢቶች በንጽጽር ከዐበይቱ [ከነኢሳይያስ] ስለሚያንስ ነው::
በምግባር: በትሩፋት: በአገልግሎት ግን ያው ናቸው:: ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እሊህን ነቢያት "እለ አውኀዙ ተነብዮ በእንተ ስመ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ" ይሏቸዋል:: [ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መውረድ: መወለድና የማዳን ሥራ የትንቢት ጐርፍን ያፈሰሱ እንደ ማለት ነው ::]
ቅዱሳኑ ከክርስቶስ የማዳን ሥራ ባሻገር ዓለማችን ላይ ከነበሩበት ዘመን እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሊደረጉ ያላቸውን ነገሮችም ተናግረዋል:: የነበሩበት ዘመን በአማካኝ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ ከ፱ መቶ [900] እስከ ፭ [500] ነው:: በትንቢት ደረጃም እንደነ ሆሴዕና ዘካርያስ ፲፬ [14] ምዕራፎችን: እንደነ አብድዩም አንዲት ምዕራፍ ብቻም የጻፉ አሉ::
በሕይወታቸው ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ያሻቸው ናቸውና በየጊዜው ከእግዚአብሔር ጋር እየተነጋገሩ የእርሱን ድምጽ ለእሥራኤል [አንዳንዴም ለአሕዛብ] ያደርሱ ነበር:: ፊት አይተው የማያዳሉ ናቸውና ሕዝቡንም ሆነ ነገሥታቱን ስለ ኃጢአታቸው ይገሰጹ ነበር:: በዚህም ምክንያት ከነገሥታቱና ከሕዝቡ አለቆች መከራ ደርሶባቸዋል:: አልፎም ያለ አበሳቸው ሕዝቡ በኃጢአቱ ሲማረክ አብረውት ወርደዋል::
በመጨረሻ ሕይወታቸውም አንዳንዶቹን ክፉዎች ሲገድሏቸው አንዳንዶቹ ደግሞ በመልካም ሽምግልና ዐርፈዋል:: ዛሬ ነቢያት ከእነርሱ ባሕርይ በተገኘችና ብዙ ትንቢትን በተናገሩላት በእመቤታችን ምክንያት ክርስቶስ ድኅነትን ፈጽሞላቸው በተድላ ገነት ይኖራሉ:: ስለ እኛም ይማልዳሉ::
" ናጥሪ እንከ ትሕትና ዘምስለ ንጽሕና"
[ እንግዲህ እንደ ነቢያት ትሕትናን ከንጽሕና ጋር ገንዘብ እናድርግ ]
"እስመ በአንጽሖ መንፈስ ርዕይዎ ነቢያት ለእግዚአብሔር: ወተናጸሩ ገጸ በገጽ"
[ ነቢያት መንፈስን ንጹሕ በማድረግ እግዚአብሔርን አይተውታልና: ፊት ለፊትም ተያይተዋልና ]
/ቅዳሴ ማርያም/
ከአባቶቻችን ቅዱሳን ነቢያት በረከት ይክፈለን::
🕊
[ † ሐምሌ ፬ [ 4 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. "12ቱ" ቅዱሳን ደቂቀ ነቢያት
፪. ቅዱስ ሶፎንያስ ነቢይ [ዕረፍቱ]
፫. ቅዱሳን ሰማዕታት አቡቂርና ዮሐንስ [ቅዳሴ ቤታቸው]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጉዋድ [ወንጌላዊው]
፪. ቅዱስ እንድርያስ ሐዋርያ
፫. ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት
፬. ቅዱስ ዮሐንስ ዘሐራቅሊ [ሰማዕት]
" ለእናንተም ስለሚሰጠው ጸጋ ትንቢት የተናገሩት ነቢያት ስለዚህ መዳን ተግተው እየፈለጉ መረመሩት:: በእነርሱም የነበረ የክርስቶስ መንፈስ ስለ ክርስቶስ መከራ ከእርሱም በሁዋላ ስለሚመጣው ክብር አስቀድሞ እየመሠከረ በምን ወይም እንዴት ባለ ዘመን እንዳመለከተ ይመረምሩ ነበር:: " [፩ዼጥ.፩፥፲]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
❤1👍1🙏1
#ወዳጆቼ
#ይህ_ብርድ አንድ ታላቅ ውለታ አያስታውስህም
ብርድ ሲበርድህ የብርድ መከላከያ ነገር ትፈልጋለህ (ብርድ ልብስ) #ለስጋህ እንዲህ አደረክ
#ነፍስህ ስትበረድስ ምን ታለብሳት?
አዳምና ሔዋን #በኀጢአት ብርድ በወደቁ ጊዜ ክርስቶስ ስጋን ለብሶ #የኀጢአት_ብርድን አስወገደላቸው።
ታዲያ ወዳጄ በነፍስ ተበርደህ ከሆነ መፍትሄው #ክርስቶስን መልበስ ነው
"፤ ነገር ግን ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን #ልበሱት፤ ምኞቱንም እንዲፈጽም #ለሥጋ አታስቡ።
(ወደ ሮሜ ሰዎች 13: 14)
#መልካም__ቀን 🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
#ይህ_ብርድ አንድ ታላቅ ውለታ አያስታውስህም
ብርድ ሲበርድህ የብርድ መከላከያ ነገር ትፈልጋለህ (ብርድ ልብስ) #ለስጋህ እንዲህ አደረክ
#ነፍስህ ስትበረድስ ምን ታለብሳት?
አዳምና ሔዋን #በኀጢአት ብርድ በወደቁ ጊዜ ክርስቶስ ስጋን ለብሶ #የኀጢአት_ብርድን አስወገደላቸው።
ታዲያ ወዳጄ በነፍስ ተበርደህ ከሆነ መፍትሄው #ክርስቶስን መልበስ ነው
"፤ ነገር ግን ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን #ልበሱት፤ ምኞቱንም እንዲፈጽም #ለሥጋ አታስቡ።
(ወደ ሮሜ ሰዎች 13: 14)
#መልካም__ቀን 🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤12🙏5
†
🕊 💖 ዼጥሮስ ወዻውሎስ 💖 🕊
🕊
[ እንኩዋን ለብርሃናተ ዓለም ቅዱሳን ዼጥሮስ ወዻውሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ]
❝ ስማቸው ጴጥሮስና እንድርያስ ፣ ያዕቆብና ዮሐንስ ፣ ፊልጶስና በርተሎሜዎስ ፣ ቶማስና ማቴዎስ ፣ ታዴዎስና ናትናኤል ፣ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብና ማትያን በመባል ለሚጠሩ ለ ፲፪ ቱ የመድኅን ሐዋርያት ሰላምታ ይገባል። ❞
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
❝ አቤቱ በስምኽ የሰበኩ ፤ በታላቅ መከራ በረኀብና በጥም ፤ በብርድና በመራቆት ፤ በመውዛትና በመድከም ፤ ከነገሥታትና ከመኳንንት ዘንድ ተፈርዶባቸው መከራን በመቀበል በምድር ኹሉ ውስጥ የቃልኽን መዝገብ ስለዘሩ ስለነዚኽ ደቀ መዛሙርትኽ ብለኽ በምሕረትኽ ዐስበኝ ፤ በእሳት በመከራ የተቀበለ አለ ፤ በጦርም የተወጋ አለ ፤ በሰይፍም የተቆረጠ አለ ፤ በመንኰራኲርም የተፈጨ አለ ፤ በደንጊያም የተወገረ ፤ በበትርም የተቀጠቀጠ አለ ፤ ስለነርሱ ብለኽ ማረኝ አስበኝም ፤ ስለሥቃያቸው ስለመቸገራቸውና ስለደማቸው ብለኽ የእኔን የአገልጋይኽን የዕዳ መጽሐፌን ቅደድ ፤ አሜን። ❞
[ ተአምኆ ቅዱሳን ]
ሕዝብ ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡራን አዕማደ ቤተክርስቲያን ፣
ሰመየ ስሞሙ ደቂቀ ብርሃን ጴጥሮስ ወጳውሎስ።
† 🕊 እንኳን አደረሰን 🕊 †
🕊 💖 🕊
🕊 💖 ዼጥሮስ ወዻውሎስ 💖 🕊
🕊
[ እንኩዋን ለብርሃናተ ዓለም ቅዱሳን ዼጥሮስ ወዻውሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ]
❝ ስማቸው ጴጥሮስና እንድርያስ ፣ ያዕቆብና ዮሐንስ ፣ ፊልጶስና በርተሎሜዎስ ፣ ቶማስና ማቴዎስ ፣ ታዴዎስና ናትናኤል ፣ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብና ማትያን በመባል ለሚጠሩ ለ ፲፪ ቱ የመድኅን ሐዋርያት ሰላምታ ይገባል። ❞
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
❝ አቤቱ በስምኽ የሰበኩ ፤ በታላቅ መከራ በረኀብና በጥም ፤ በብርድና በመራቆት ፤ በመውዛትና በመድከም ፤ ከነገሥታትና ከመኳንንት ዘንድ ተፈርዶባቸው መከራን በመቀበል በምድር ኹሉ ውስጥ የቃልኽን መዝገብ ስለዘሩ ስለነዚኽ ደቀ መዛሙርትኽ ብለኽ በምሕረትኽ ዐስበኝ ፤ በእሳት በመከራ የተቀበለ አለ ፤ በጦርም የተወጋ አለ ፤ በሰይፍም የተቆረጠ አለ ፤ በመንኰራኲርም የተፈጨ አለ ፤ በደንጊያም የተወገረ ፤ በበትርም የተቀጠቀጠ አለ ፤ ስለነርሱ ብለኽ ማረኝ አስበኝም ፤ ስለሥቃያቸው ስለመቸገራቸውና ስለደማቸው ብለኽ የእኔን የአገልጋይኽን የዕዳ መጽሐፌን ቅደድ ፤ አሜን። ❞
[ ተአምኆ ቅዱሳን ]
ሕዝብ ቅዱሳን ሐዋርያት ክቡራን አዕማደ ቤተክርስቲያን ፣
ሰመየ ስሞሙ ደቂቀ ብርሃን ጴጥሮስ ወጳውሎስ።
† 🕊 እንኳን አደረሰን 🕊 †
🕊 💖 🕊
🙏1