Telegram Web Link
አድዋ፡ የመጨረሻው ውጊያ

« ከዚህ ቀጥሎ አጼ ምኒልክ ጦራቸውን ወደ አድዋ በመምራት የአድዋ ሸለቆ ከሚታይበት ከፍታ ላይ ሰፈሩ። ራስ መኮንን፣ ራስ መንገሻ እና ራስ ሚካኤልን ከመሃል ወራሪ፤ እራሳቸውን እና እቴጌን ከመካከል፣ ንጉሥ ተክለሃይማኖትን በስተቀኛቸው፣ ራስ አሉላን በስተግራ አደረጓቸው።

ጀነራል ባራቴሪ ከቅርብ ርቀት ላይ ቢሆንም የስንቅ እና ቁሳቁሶች እጥረት እየገጠመው ነበር። ስለዚህ በጥር ወር የምኒልክም ጦር ስንቅ እስኪያልቅ ጣልያኖች እንዲጠብቁ አዞ ነበር። ነገር ግን የጣልያን መንግሥት እርምጃ ውሰድ ዝምብለህ ከምትጠብቅ የሚል ትእዛዝ ስለላከ ሊተገብረው አልቻለም።

በየካቲት 23 ጥዋት ላይ ሊያጠቃ የነበረው ባራቴሪ ሦስት ሻለቃ ጦሮችን አሰለፈ። ጀነራል አልበርቶን በስተግራ፣ ጀነራል ዳቦርሚዳ በስተቀኝ እና ጀነራል አሪሞንዲ ከመካከል አድርጎ ደጀን ላይ ደግሞ ጀነራል ኢሌናን አስቀመጠ። አልበርቶን ራሱን ኪዳነምሕረት በምትባል ከፍታ ላይ አስቀምጦ የኢትዮጵያውያኑን እንቅስቃሴ ለመከታተል አስቦ ነበር።

ነገር ግን እሱ እንዳቀደው ሳይሆን ጀነራል አልበርቶን ዘው ብሎ ራስ አሉላ በሠፈሩበት አካባቢ ገባ። ሯጮች አጼ ምኒልክ ጋር ገስግሰው ጣልያን በጠዋት እንዳጠቃ ነገሯቸው። ዘበኞች ውጊያ ጀምረው ነበር። 25 ሺህ ሰዎችን ሲልኩላቸው አሪሞንዲን ከነበረበት ነቅለው እንዲሸሽ አደረጉት። 12 ሰዓት ላይ አልበርቶንን እና አስካሪዎቹን ወደ አሪሞንዲ ጦር ገፍተው አልበርቶንን ምርኮኛ ያዙት። የዳቦሪሚዳ ጦር እንኳን አልበርቶንን ሊያድን እራሱ ሳያስበው በራስ ሚካኤል ሰፈር ውስጥ ገብቶ ስለተከበበ ተደመሰሰ። የቀሩት የባራቴሪ ጦረኞች በንጉሥ ተክለሃይማኖት ተቆርጠው ተገደሉ። ቀን 6 ሰዓት ሲሆን በምኒልክ ሥር የዘመቱት የጦር መሪዎች በጦር ሜዳው ተሳትፈው ራሳቸውን አስመስክረዋል። የተረፉት ጣልያኖች ወደ ኤርትራ እግሬ አውጪኝ ሸሹ። እነሱም በኢትዮጵያ ገበሬዎች እየተጠቁ ኤርትራ የገቡት በጣም ጥቂቶቹ ናቸው።

የአድዋ ጦርነት እንዲህ ተፈጸመ። ከ4 እስከ 5 ሺህ ኢትዮጵያውያን ሞተው ወደ 8 ሺህ ያህል ቆስለዋል። ጀነራል አልበርቶን እና 3ሺህ ጣልያናውያን ምርኮኛ ተወሰዱ። ከእነዚህ 200 የሚሆኑት በቁስሎቻቸው ምክንያት ሲሞቱ ወደ 800 አስካሪዎች ግራ እግራቸውን እና ቀኝ እጃቸውን ተቆረጡ። ከጠላት ጋር አብራችኋል በማለት። ጣልያኖች ወደ 7ሺህ ሰዎች ሲሞቱባቸው፣ 1500 ያህል ቆስሏል። 11 ሺህ ጠመንጃዎቻቸውም ተማርከዋል። »

ከፀሐይ ብርሃነሥላሴ፡ ኢትዮጵያዊ ጦረኝነት Ethiopian Warriorhood
ገጽ 234
ሰላም ጤና ይስጥልኝ ጦብያዎች

እመት ገነት አየለ ከዚህ በፊት በሁለት ቅጽ ከፈረንሳይኛ የተረጎመችው የዳባዲ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ተራራዎች ቆይታዬ መጽሐፍ ሦስተኛ ክፍሉ ሰሞኑን ተመርቋል። አብሶ ከአጼ ቴዎድሮስ መነሳት በፊት ስለነበረው 19ኛ ክ/ዘ ኢትዮጵያ ማወቅ ለምትፈልጉ ጠቃሚ የታሪክ ሰነድ ነው።

የመጽሐፉ ምርቃት የካቲት 15 ቀን ነበረ ግን ዛሬ ገና ነው እኔም ያየሁት። ባይሆን ዋልያ መጻሕፍት ዩትዩብ ላይ ውይይቱን ሊያወጣው ይችላል

[መረጃውን ለሰጠን አባ በዝብዝ እናመሰግናለን ፡)]
ሌላ አዲስ መጽሐፍ ለማስተዋወቅ ያህል፡ Africa as Method: A Handbook of Sources and Epistemologies

ከሥር አያይዤዋለሁኝ።
ሰላም ጤና፡

ሁለት የተለያዩ ዌቢናሮችን ለማስተዋወቅ ያህል ነው።

1. March 24 እና 25 የሚካሄድ Unpacking Mixedness for an Inclusive History of the Red Sea, 1800s-2000s የተባለ ዝግጅት አለ። ለተጨማሪ መረጃ እዚህ ተመልከቱ፡ https://unifind.unito.it/resource/project/FUSV_HEU_ERC_COG_24_01
ለመመዝገብ እዚህ ሂዱ፡ https://docs.google.com/forms/d/1PdkwFtY60Lr2agORVDR0Kq9NGjGJ9OSxxoZYjSqTMZ4/viewform?edit_requested=true

2. April 2 እና 3 የሚካሄድ “The Black Indian Ocean: Slavery, Religion, and Expressive Cultures (1400-1700),” የተባለ ሌላ ፕሮግራም ነው። የሱን ማስታወቂያ ከሥር አያይዤ ልኬላችኋለሁ። ማስታወቂያው መጨረሻ ላይ ሁለት QR Codeኦች አሉ። በነሱ ነው የምትመዘገቡት/ፕሮግራሙን የምታዩት።

መልካም ዐርብ
ሌላ ማስታወቂያ፡

ቀኃሥ ያረፉበትን እና የኢትዮጵያ ንጉሣዊ ሥርዓት ያበቃበትን 50ኛ ዓመት በማስመልከት Africa የተባለው ጆርናል ከ May 31, 2025 በፊት ስለ ንጉሠ ነገሥቱ ታሪካዊ ጽሑፎችን ማቅረብ ለሚችሉ ጥሪ አቅርቧል። ጽሑፉ 10ሺህ ቃላት መሆን አለበት -- ረዘም ያለ አርቲክል ነው የሚፈለገው።

የጆርናሉ ድረገጽ፡ https://www.viella.it/riviste/testata/15 ይሄ ነው።
ለቅዳሜያችሁ፡

የአንድርያስ እሸቴ ቃለመጠይቅ ከዳግማዊ ዉብሸት ጋር።
ዐቢይ ተክለማርያም "አደናጋሪው ምሑር" ብሎ ስለ ፕሮፍ አንድርያስ እሸቴ የጻፈው የአዲስ ነገር ጽሑፍ ያለው ሰው አለ? ለሥራ ፈልገነው አጥተነው ነው።

አመሰግናለሁ
«ሰው መሆን አለ እንጂ»

ሰሞኑን የጋሽ አለማየሁ ፈንታን፣ ዛሬ ደግሞ የጋሽ መርአዊ ስጦትን እና የፕሮፌሰር ኤልሳቤጥ ወ/ጊዮርጊስን በሞት መለየት ዜና ሰማን።

የኢትዮጵያ ጥናት ማዕከል አካባቢ ላላችሁ ፕሮፍ ኤልሳቤጥን በአካል ባይሆን እንኳን ወይ በስም ወይ በዝና ልታውቋት ትችሉ ይሆናል። የማዕከሉ ዳይሬክተር ነበረች ከተወሰነ ዓመታት በፊት። በቅርብ Modernist Art in Ethiopia የሚል መጽሐፏን አሳትማ ነበር።

ሁሉንም ነፍስ ይማርልን።
አዲስ መጽሐፍ ስለማስተዋወቅ፡ History of Women in Ethiopia
ሰላም ጤና ወገን፡

ይሄን ማመልከቻ እስቲ እዩ። ፕሮጀክቱ ስለ ሴቶች ነው። WomAtWork represents the first comparative investigation into the history of female urban popular professions in in five African countries – Kenya, Ethiopia, Ghana/Gold Coast, Sudan, and Tanganyika/Tanzania – over the course of fifty years (1919-1970). Not only is this topic under-studied in African history, but these professions (i.e. midwives, beauticians, market vendors, craftswomen, wedding or ritual singers) are also characterised by fascinating and unsettling aspects. For example, notions such as a set price for a service and fixed working times or workplace did not apply to many of such professions.

https://euraxess.ec.europa.eu/jobs/314857
ብርሃንና ሰላም ጋዜጣ 1ኛ ዓመት ቁጥር 4 (ጥር 14 ቀን 1917 ዓ.ም.)

ጋዜጣው በዚህ ዘመን 4 ገጾች ነው ርዝመቱ። የሚያበቃው ታድያ ከጃንሜዳ ሽቅድድም ማሕበር በወጣ ማስታወቂያ ነው።

አጭር ማስታወቂያ ነው። Striking ነገሮች አሉት፡ በዛን ዘመን ማኅበርተኞች ጋዜጣ ማንበባቸው ታውቆ ማስታወቂያ መለቀቁ በጋዜጣ፣ ወራት በፈረንሳይኛ ቀናት ደግሞ በግእዝ ቁጥር መጻፋቸው፣ ማስታወቂያውን የጻፈው ደግሞ ኮምት ጀ ኮሊ የተባለ ሰው መሆኑ (ፈረንሳይኛ ተናጋሪ ፈረንጅ ይሆን?) ወዘተ። በዘመኑ ለፈረንሳይኛ እናዳላ ነበር መሰል ግን ስዋሰዉም ለየት ይላል አይደል? በደንብ ባያችሁት ቁጥር ጸሐፊው አማርኛን ተወልዶበት አድጎበት ሳይሆን እንደተጨማሪ ቋንቋ የተማረ ይሆን ያስብላል። «መሰብሰብ» የሚለው ቃል ነው እንዲህ ያስባለኝ

-- ይኸው ለማንኛውም፡ እራሳችሁ እዩት
2025/10/25 06:31:51
Back to Top
HTML Embed Code: