❤️❤️🔥💔የልቤን ብታዪ❤️❤️🔥💔
አይኔ እንደ ቆራጥ አንቺን ባያይሽም
ሞልቶት ትንሽ ኩራት
አፌም ጀነን ብሎ አሻፈረኝ ቢልም
ስምሽን ለመጥራት
ጆሮዬም ቢያስመስል ከቶ እንደማይሰማ
አንቺን የሚል ወሬ
በሄድሽበት መሄድ ሁሌ መከተሉን
ባይሞክረው እግሬ
በይ ልንገርሽ ዛሬ
ሞኝ ልብ እንዳለኝ ማያውቅ ማስመሰል
ጠዋትና ማታ ስራው አድርጎታል
አንቺን ማሰላሰል።
📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝
✍️ @BEGITIMENAWGA
@getem
@getem
@getem
አይኔ እንደ ቆራጥ አንቺን ባያይሽም
ሞልቶት ትንሽ ኩራት
አፌም ጀነን ብሎ አሻፈረኝ ቢልም
ስምሽን ለመጥራት
ጆሮዬም ቢያስመስል ከቶ እንደማይሰማ
አንቺን የሚል ወሬ
በሄድሽበት መሄድ ሁሌ መከተሉን
ባይሞክረው እግሬ
በይ ልንገርሽ ዛሬ
ሞኝ ልብ እንዳለኝ ማያውቅ ማስመሰል
ጠዋትና ማታ ስራው አድርጎታል
አንቺን ማሰላሰል።
📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝
✍️ @BEGITIMENAWGA
@getem
@getem
@getem
ቂቤሽ ጭፍ እያለ
ቅጫማም ፀጉርሽን እንዳልደባበስኩኝ
እናትዬ ብዬ
ግንባርሽን ስሜ ሻሽ እንዳላሰርኩኝ
ድንገት ብንገናኝ ሳልፍ በመንገድሽ
አላስቀምጥ አለኝ ግልምጫ ንቀትሽ
.
ከአንቺም ብሶ ደግሞ
ወይራ እንደ ተጠገበ እንደ ጠላ በርሜል
ጭሰኛ ብብትሽ የአፍንጫ ጋንኤል
መሆኑን ባውቅ እንኳን ጎንሽ ተኝቻለው
ከስሜት ህዋሴ አንዱን ሰውቻለው
.
እናም ይኸው ዛሬ
የሀብታም መንጋጋ መንጭቆ ቢያወጣሽ
ያሳለፍነው ሁሉ ቀልድ ሆኖ ተረሳሽ
ሀር ፀጉሬን ንቀሽ መላጣ መርጠሻል
ከእኔ ደረት ይልቅ ቦርጩ ተስማምቶሻል
እሱን እያሻሸሽ እለቢው እንደ ላም
ስለ አንቺ ባወራ ጊዜውም አይበቃም
.
ለዛም ተመኘውኝ ደግ ደጉን ላንቺ
ቅጫምሽን ትተሽ
አረተፊሻል ዉጊውን ማንጠልጠሉን በርቺ
By በኪሩቤል አሰፋ @Ebuh_bhr
@getem
@getem
@getem
ቅጫማም ፀጉርሽን እንዳልደባበስኩኝ
እናትዬ ብዬ
ግንባርሽን ስሜ ሻሽ እንዳላሰርኩኝ
ድንገት ብንገናኝ ሳልፍ በመንገድሽ
አላስቀምጥ አለኝ ግልምጫ ንቀትሽ
.
ከአንቺም ብሶ ደግሞ
ወይራ እንደ ተጠገበ እንደ ጠላ በርሜል
ጭሰኛ ብብትሽ የአፍንጫ ጋንኤል
መሆኑን ባውቅ እንኳን ጎንሽ ተኝቻለው
ከስሜት ህዋሴ አንዱን ሰውቻለው
.
እናም ይኸው ዛሬ
የሀብታም መንጋጋ መንጭቆ ቢያወጣሽ
ያሳለፍነው ሁሉ ቀልድ ሆኖ ተረሳሽ
ሀር ፀጉሬን ንቀሽ መላጣ መርጠሻል
ከእኔ ደረት ይልቅ ቦርጩ ተስማምቶሻል
እሱን እያሻሸሽ እለቢው እንደ ላም
ስለ አንቺ ባወራ ጊዜውም አይበቃም
.
ለዛም ተመኘውኝ ደግ ደጉን ላንቺ
ቅጫምሽን ትተሽ
አረተፊሻል ዉጊውን ማንጠልጠሉን በርቺ
By በኪሩቤል አሰፋ @Ebuh_bhr
@getem
@getem
@getem
🥲ትናንት እና ዛሬ🥲
አላወቅሺም እንጂ አፍቅሬሽ ነበረ
ዳሩ ምን ያረጋል
ሌላው ይዞሽ ሲሄድ ልቤ ተሰበረ።
የሆነው ሆነና እንዳሰብኩት ሳይሆን
ከጎኔ ባጣሽም
በትናንት ሀዘኔ የዛሬው ህይወቴን
ከቶ አላበላሽም።
📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝
✍️ @BEGITIMENAWGA
@getem
@getem
@getem
አላወቅሺም እንጂ አፍቅሬሽ ነበረ
ዳሩ ምን ያረጋል
ሌላው ይዞሽ ሲሄድ ልቤ ተሰበረ።
የሆነው ሆነና እንዳሰብኩት ሳይሆን
ከጎኔ ባጣሽም
በትናንት ሀዘኔ የዛሬው ህይወቴን
ከቶ አላበላሽም።
📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝
✍️ @BEGITIMENAWGA
@getem
@getem
@getem
አምና ያንቺ ሱሰኛ ነበርኩ ሱሰኛሽ ያዉም በደስታ
መሽቶ መንጋቱን ማላምን ካለአይኖችሽ እይታ
ከራስ ፀጉሬ እስከ እግር ጣቴ ካላንቺ ድምፅ የማይፈታ
ሌት ተቀን ምኖር አብሬሽ ማልጠፋ ከጎንሽ ለአፍታ
ቃልሽን ሕጌ አድረጌው አኑሬሽ ከአማልክት ቦታ
ዘላለም ባገለግልሽ ለቅፅበት ማላመነታ
ነበርኩኝ ታማኝ አገልጋይ
ካላንቺ ሌሎች አምላኮች ማላይ
ምድር ሸሽታ ብትሄድ ቢገለባበጥ ሰማይ
አሁን ግን ምስጋና ላንቺ ዋልሽልኝ ታላቅ ዉለታ
አሳየሽኝ ሱስ እንደሚያረክስ እንደሚያወጣ ከሰዎች ተርታ
ዘረ-ሠናይ
@Prince_Zeresenay
@getem
@getem
@getem
መሽቶ መንጋቱን ማላምን ካለአይኖችሽ እይታ
ከራስ ፀጉሬ እስከ እግር ጣቴ ካላንቺ ድምፅ የማይፈታ
ሌት ተቀን ምኖር አብሬሽ ማልጠፋ ከጎንሽ ለአፍታ
ቃልሽን ሕጌ አድረጌው አኑሬሽ ከአማልክት ቦታ
ዘላለም ባገለግልሽ ለቅፅበት ማላመነታ
ነበርኩኝ ታማኝ አገልጋይ
ካላንቺ ሌሎች አምላኮች ማላይ
ምድር ሸሽታ ብትሄድ ቢገለባበጥ ሰማይ
አሁን ግን ምስጋና ላንቺ ዋልሽልኝ ታላቅ ዉለታ
አሳየሽኝ ሱስ እንደሚያረክስ እንደሚያወጣ ከሰዎች ተርታ
ዘረ-ሠናይ
@Prince_Zeresenay
@getem
@getem
@getem
🙄አልታይሽም ወይ👀
አቃለው እንዳልሆንኩ በምድር ምነፍስ
የንፋስ ሽውታ
መኖረ ሚታወቅ ቅጠል ሳንቀሳቅስ
ወይ ደግሞ በሽታ
ታዲያ እንዴት ሆኖ በዋልሽበት ውዬ
ሳንዣብብ በዙሪያሽ
እስከዛሬ ድረስ አይኖችሽ ያላዩኝ
ገብቼ ከእይታሽ።
አልታይሽም ወይ????
📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝
✍️ @BEGITIMENAWGA
@getem
@getem
@getem
አቃለው እንዳልሆንኩ በምድር ምነፍስ
የንፋስ ሽውታ
መኖረ ሚታወቅ ቅጠል ሳንቀሳቅስ
ወይ ደግሞ በሽታ
ታዲያ እንዴት ሆኖ በዋልሽበት ውዬ
ሳንዣብብ በዙሪያሽ
እስከዛሬ ድረስ አይኖችሽ ያላዩኝ
ገብቼ ከእይታሽ።
አልታይሽም ወይ????
📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝
✍️ @BEGITIMENAWGA
@getem
@getem
@getem
#የማይነቃ_ውሸት
እንደተወዛዋዥ ግንባር
በየምሶሶው የለጠፍሽው
"አለ" የምትል አድባር
ሰርክ መዳንን ብቻ አስለምደሽው
ሰርክ መኖርን ብቻ አስለምደሽው
ይረሳዋል እንደሚሞት ካልነገርሽው
ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu
@Getem
@Getem
እንደተወዛዋዥ ግንባር
በየምሶሶው የለጠፍሽው
"አለ" የምትል አድባር
ሰርክ መዳንን ብቻ አስለምደሽው
ሰርክ መኖርን ብቻ አስለምደሽው
ይረሳዋል እንደሚሞት ካልነገርሽው
ሳሙኤል አለሙ
@Samuelalemuu
@Getem
@Getem
✍️ድንቄም ገጣሚ✍️
ሳያዘጋጅ ብእር
ሃሳብ ሳይደረድር
ስላሰኘው ብቻ ለመግጠም ሲሞክር
አልሳካ ቢለው
በሰከነ መንፈስ ደግሞ ሳያስበው
የማይመስል ስንኝ ፅፎ እያሰፈረ
ካለበቂ እውቀት ለመግጠም እየጣረ
ቤት መታለው በሚል ቤት ማፍረስ ጀመረ::
:
:
:
ከሰማ ንገሩት
ቤት አታፍርስ በሉት::
<><><><><><><><><><><><><><><>
📌 ወቅቱን ታሳቢ አድርጌ ነው በድጋሚ አሻሽዬ ያዘጋጀሁት።
✍️ @BegitimEnawga
@getem
@getem
@getem
ሳያዘጋጅ ብእር
ሃሳብ ሳይደረድር
ስላሰኘው ብቻ ለመግጠም ሲሞክር
አልሳካ ቢለው
በሰከነ መንፈስ ደግሞ ሳያስበው
የማይመስል ስንኝ ፅፎ እያሰፈረ
ካለበቂ እውቀት ለመግጠም እየጣረ
ቤት መታለው በሚል ቤት ማፍረስ ጀመረ::
:
:
:
ከሰማ ንገሩት
ቤት አታፍርስ በሉት::
<><><><><><><><><><><><><><><>
📌 ወቅቱን ታሳቢ አድርጌ ነው በድጋሚ አሻሽዬ ያዘጋጀሁት።
✍️ @BegitimEnawga
@getem
@getem
@getem
😔😢ድብቅ ነው😢😔
ከንፈሬ ተገልጦ ጥርሶቼን ባይሸፍን
ቢያለብሰኝ ፈገግታ
የውስጤን መከፋት የልቤን ጠባሳ
ሸሸገው ከእይታ።
:
እውነታው ግን
:
ከሰው ተሸሽጌ ከጎጆዬ ስሆን
ለብቻዬ ስቀር
ብሶቴ ተነስቶ እምባዬ ይፈሳል
ከአይኔ ሲንደረደር።
የሚፈሰኝ እምባ አካሌን እያራሰው
መውረዱን ባይተውም
ውስጤ ሚነደውን የልቤ ውስጥ እሳት
ሊያጠፋው አይችልም።
<><><><><><><><><><><><><><><>
✍️ @BegitimEnawga
@getem
@getem
@getem
ከንፈሬ ተገልጦ ጥርሶቼን ባይሸፍን
ቢያለብሰኝ ፈገግታ
የውስጤን መከፋት የልቤን ጠባሳ
ሸሸገው ከእይታ።
:
እውነታው ግን
:
ከሰው ተሸሽጌ ከጎጆዬ ስሆን
ለብቻዬ ስቀር
ብሶቴ ተነስቶ እምባዬ ይፈሳል
ከአይኔ ሲንደረደር።
የሚፈሰኝ እምባ አካሌን እያራሰው
መውረዱን ባይተውም
ውስጤ ሚነደውን የልቤ ውስጥ እሳት
ሊያጠፋው አይችልም።
<><><><><><><><><><><><><><><>
✍️ @BegitimEnawga
@getem
@getem
@getem
/ ለምን ጠላሻለሁ/
መቼ ተለወጥኩኝ እንደዛው ነኝ እኔ
ተለዉጧል እርሱ አይደለም እንደ ያኔ፤
እያልሽ የሌለኝን ማንነት አትስጪኝ
ከመሬት አንስተሽ ከሰው አፍ አታውጪኝ፤
ደሞስ መች ሊጨክን ልቤስ ሊደነድን
በሕይወት ሳለሁኝ ከቶ ሳልሆን በድን፤
የኔ የዋነቴን የልቤንም አይተሽ
ዛሬ ምን ሲል ታየሽ ያኔ የሄድሽው ትተሽ፤
እርግጥ ሰው ባጠፋው ፀፀቱ ባይቀርም
ወደሽኝ ቢሆን ኖሮ በኔና አንቺ አይከርም፤
ታዲያ መች እንደዛ ሆኖ ያንቺ ቀረቤታ
ፌዝ አዘል ነበረ የጥርስሽ ፈገግታ፤
ያኔ ማፍቀርን ጠግቤው መፈቀር ቢርበኝ
ያንቺ ልብ በፍቅር መች አምኖ ቀረበኝ፤
አሁን ላይ ጥያቄሽ ለይቅር ከሆነ
ጥፋት እንዳጠፋሽ ልብሽ ይህን ካመነ፤
በሰው ቂም አሊዝም ይቅር ብዬሻለሁ
ዳግም ባልወድሽም ለምን ጠላሻለሁ;
#መሳይ ግርማ
@getem
@getem
@getem
መቼ ተለወጥኩኝ እንደዛው ነኝ እኔ
ተለዉጧል እርሱ አይደለም እንደ ያኔ፤
እያልሽ የሌለኝን ማንነት አትስጪኝ
ከመሬት አንስተሽ ከሰው አፍ አታውጪኝ፤
ደሞስ መች ሊጨክን ልቤስ ሊደነድን
በሕይወት ሳለሁኝ ከቶ ሳልሆን በድን፤
የኔ የዋነቴን የልቤንም አይተሽ
ዛሬ ምን ሲል ታየሽ ያኔ የሄድሽው ትተሽ፤
እርግጥ ሰው ባጠፋው ፀፀቱ ባይቀርም
ወደሽኝ ቢሆን ኖሮ በኔና አንቺ አይከርም፤
ታዲያ መች እንደዛ ሆኖ ያንቺ ቀረቤታ
ፌዝ አዘል ነበረ የጥርስሽ ፈገግታ፤
ያኔ ማፍቀርን ጠግቤው መፈቀር ቢርበኝ
ያንቺ ልብ በፍቅር መች አምኖ ቀረበኝ፤
አሁን ላይ ጥያቄሽ ለይቅር ከሆነ
ጥፋት እንዳጠፋሽ ልብሽ ይህን ካመነ፤
በሰው ቂም አሊዝም ይቅር ብዬሻለሁ
ዳግም ባልወድሽም ለምን ጠላሻለሁ;
#መሳይ ግርማ
@getem
@getem
@getem
▪️የዛን ቀን▪️
እግሬ አስጠልቶኛል
አንቺ ካለሽበት የዛን ቀን ወስዶኛል።
አይኔን ማይበትን ጠልቻለው ከቶ
የዛን ቀን ከሰዎች ስላየሽ ለይቶ።
ጆሮዬንም ቢሆን አልወደው እኔማ
የዛን ቀን ያንችን ድምፅ መርጦ ስለሰማ።
እውነታው ግን
እግሬና አይኖቼን አልያም ጆሮዬን
ለመጥላት አስቤ
ካለሽበት ሄዱ አዩሽ ሰሙሽ በሚል
ምክኒያት አሳብቤ
አጥፍተዋል ብልም እውነታውን ሳስብ
ሀሳቤን ሰብስቤ
ለካስ ጉድ የሰራኝ አንቺን መውደዱ ነው
የዛን ለታ ልቤ።
እናማ
የኔ ላላረግሽ ካጠገቤ ላጣሽ
ልቤ በወደደሽ ሆንኩኝ ሌላን ወቃሽ።
📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝
✍️ @BEGITIMENAWGA
@getem
@getem
@getem
እግሬ አስጠልቶኛል
አንቺ ካለሽበት የዛን ቀን ወስዶኛል።
አይኔን ማይበትን ጠልቻለው ከቶ
የዛን ቀን ከሰዎች ስላየሽ ለይቶ።
ጆሮዬንም ቢሆን አልወደው እኔማ
የዛን ቀን ያንችን ድምፅ መርጦ ስለሰማ።
እውነታው ግን
እግሬና አይኖቼን አልያም ጆሮዬን
ለመጥላት አስቤ
ካለሽበት ሄዱ አዩሽ ሰሙሽ በሚል
ምክኒያት አሳብቤ
አጥፍተዋል ብልም እውነታውን ሳስብ
ሀሳቤን ሰብስቤ
ለካስ ጉድ የሰራኝ አንቺን መውደዱ ነው
የዛን ለታ ልቤ።
እናማ
የኔ ላላረግሽ ካጠገቤ ላጣሽ
ልቤ በወደደሽ ሆንኩኝ ሌላን ወቃሽ።
📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝
✍️ @BEGITIMENAWGA
@getem
@getem
@getem
አይ ገላ አባ ወረት
በምናብ ሸራ ላይ ፥ በሐሳቤ ሰሌዳ
በምኞቴ ጓዳ ፥ በፍትወቴ ሜዳ
ውብ ሰውነትሽን፥ አየሁ ተቀይዳ
በስጋ እሳት ላንቃ ፥ በቁም እስር ርዳ።
የአይኖችሽን ጨረር ፥ የከንፈርሽን ማር
የአንገትሽን መርዘም ፥ የእግሮችሽን ማማር
የዳሌሽን ደጀን ፥የሽንጥሽን ጅረት
በስጋዬ አሰስኩት ፥በገላ ዳበስኩት
አወይ ገላ ግፉ፥ አይ ስጋ አባ ወረት
የጉንጭሽ ላይ ስንቡክ ፥ የአንገትሽ ስር ከርቤ
ቀመስኩት ሁሉንም ፥ መች ቀረሁ ተርቤ
የቤትኾቨን ኖታ ፥ የሞዛርት ሙዚቃ
መች ይስተካከላል ፥ ከአንደበትሽ ሲቃ
አወይ ገላ ግፉ ፥ አይ ስጋ አባ ወረት
ይገኝ ይመስለዋል ፥ ለነብስ ህመም ደዌ
አንድ የስጋ መድኅን ፥ አንድ የስጋ ሽረት።
አይጥመኝ ሐር ልብ ፥ ለስላሳ የተባለ
ከሐር ጠጉርሽ በቀር ፥ ከአለንጋ ጣቶችሽ
አላውቅም በአለም ፥ ላይ የተስተካከለ።
ይፈሳል እንደ አዋሽ ፥ ሳቅሽ እንደ መልካው
እጅ እግር አጠረኝ ፥ ነብስሽን በየት ልንካው
ሁሉን ስዳስሰው ፥ ጠጉርሽን ስለብሰው
እንደ ጠበል ጠዲቅ ፥ ከንፈርሽን ስቀምሰው
ጣፋጭ እሳትሽን፥ እንደ ኩዳድ ሳርሰው
ገላን በገላ አቅም ፥ ስትጠግቢኝ ስጠግብሽ
ንገሪኝ አንችዬ ፣
ለዚህ ጥያቄዬ ፥ ምን መለሰ ልብሽ?
አወይ ገላ ግፉ፥ አይ ገላ አባ ወረት
ምኞት ሙሉ ሜዳ ፥ ምኞት ሙሉ በረት
በአፍ እንደወደድሽኝ ፥በአይን እንደዳበሽኝ
መአት ረግረግሽ ውስጥ ፥ያኔ እንዳሰጠምሽኝ
መዘንጋት የማያውቅ ፥ ፍቅሬ እሱን ለግሽኝ
ገል አፈሩ ይቅርብኝ ፥
ገል አፈሩ ይብቃኝ፣
ነብስሽና ነብሴ ሁለቱ ይጣመሩ፥
ፍቅር እንደዚያ እንዲቃኝ።
By ©እስራኤል
(@isrik)
@getem
@getem
@getem
በምናብ ሸራ ላይ ፥ በሐሳቤ ሰሌዳ
በምኞቴ ጓዳ ፥ በፍትወቴ ሜዳ
ውብ ሰውነትሽን፥ አየሁ ተቀይዳ
በስጋ እሳት ላንቃ ፥ በቁም እስር ርዳ።
የአይኖችሽን ጨረር ፥ የከንፈርሽን ማር
የአንገትሽን መርዘም ፥ የእግሮችሽን ማማር
የዳሌሽን ደጀን ፥የሽንጥሽን ጅረት
በስጋዬ አሰስኩት ፥በገላ ዳበስኩት
አወይ ገላ ግፉ፥ አይ ስጋ አባ ወረት
የጉንጭሽ ላይ ስንቡክ ፥ የአንገትሽ ስር ከርቤ
ቀመስኩት ሁሉንም ፥ መች ቀረሁ ተርቤ
የቤትኾቨን ኖታ ፥ የሞዛርት ሙዚቃ
መች ይስተካከላል ፥ ከአንደበትሽ ሲቃ
አወይ ገላ ግፉ ፥ አይ ስጋ አባ ወረት
ይገኝ ይመስለዋል ፥ ለነብስ ህመም ደዌ
አንድ የስጋ መድኅን ፥ አንድ የስጋ ሽረት።
አይጥመኝ ሐር ልብ ፥ ለስላሳ የተባለ
ከሐር ጠጉርሽ በቀር ፥ ከአለንጋ ጣቶችሽ
አላውቅም በአለም ፥ ላይ የተስተካከለ።
ይፈሳል እንደ አዋሽ ፥ ሳቅሽ እንደ መልካው
እጅ እግር አጠረኝ ፥ ነብስሽን በየት ልንካው
ሁሉን ስዳስሰው ፥ ጠጉርሽን ስለብሰው
እንደ ጠበል ጠዲቅ ፥ ከንፈርሽን ስቀምሰው
ጣፋጭ እሳትሽን፥ እንደ ኩዳድ ሳርሰው
ገላን በገላ አቅም ፥ ስትጠግቢኝ ስጠግብሽ
ንገሪኝ አንችዬ ፣
ለዚህ ጥያቄዬ ፥ ምን መለሰ ልብሽ?
አወይ ገላ ግፉ፥ አይ ገላ አባ ወረት
ምኞት ሙሉ ሜዳ ፥ ምኞት ሙሉ በረት
በአፍ እንደወደድሽኝ ፥በአይን እንደዳበሽኝ
መአት ረግረግሽ ውስጥ ፥ያኔ እንዳሰጠምሽኝ
መዘንጋት የማያውቅ ፥ ፍቅሬ እሱን ለግሽኝ
ገል አፈሩ ይቅርብኝ ፥
ገል አፈሩ ይብቃኝ፣
ነብስሽና ነብሴ ሁለቱ ይጣመሩ፥
ፍቅር እንደዚያ እንዲቃኝ።
By ©እስራኤል
(@isrik)
@getem
@getem
@getem
🔥🔥እሳትና ውሀ🌊🌊
የታፈነ ውሀ በብረት ድስት ገብቶ
በጭቆና ሲኖር ነፃነቱን አጥቶ
ስንት ስቃይ አይቶ
ታጋሽ ሆኖ ሳለ
አንድ ጉልበተኛ እሳት የተባለ
ብረት ድስቱን ሊያግል እየተቀጣጠለ
ነበልባል ተላብሶ ድንገት ከተፍ አለ::
:
:
ቃጠሎ ንዳዱ ውሀው ሲበዛበት
የስቃዩ ማብቂያ ጊዜው ሲረዝምበት
ትግስቱ ተሟጦ የሚገነፍል ለት
የእሳቱ ግለት
ምን ያክል ቢከፋ
የታፈነው ውሀ በምሬት ሲደፋ
ሀያሉም ነበልባል አብሮት ነው ሚጠፋ::
▪️ ነገሮችን በትግዕስት ማለፍ ተገቢ ነው ግን ሁሉም ነገር ገደብ አለው። ይሄ ግጥም ገደብ እንዳለው ላልተረዱ ይድረስልኝ።
📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝
✍️ @BEGITIMENAWGA
@getem
@getem
@getem
የታፈነ ውሀ በብረት ድስት ገብቶ
በጭቆና ሲኖር ነፃነቱን አጥቶ
ስንት ስቃይ አይቶ
ታጋሽ ሆኖ ሳለ
አንድ ጉልበተኛ እሳት የተባለ
ብረት ድስቱን ሊያግል እየተቀጣጠለ
ነበልባል ተላብሶ ድንገት ከተፍ አለ::
:
:
ቃጠሎ ንዳዱ ውሀው ሲበዛበት
የስቃዩ ማብቂያ ጊዜው ሲረዝምበት
ትግስቱ ተሟጦ የሚገነፍል ለት
የእሳቱ ግለት
ምን ያክል ቢከፋ
የታፈነው ውሀ በምሬት ሲደፋ
ሀያሉም ነበልባል አብሮት ነው ሚጠፋ::
▪️ ነገሮችን በትግዕስት ማለፍ ተገቢ ነው ግን ሁሉም ነገር ገደብ አለው። ይሄ ግጥም ገደብ እንዳለው ላልተረዱ ይድረስልኝ።
📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝📝
✍️ @BEGITIMENAWGA
@getem
@getem
@getem
...ንገረኝ በሞቴ
ንገረኝ በሞቴ ምንህ ይሻለኛል
ዘንድሮን በጠና ሆድ ሆዴን በልቶኛል
ስለዚ ንገረኝ ምንህ ይሻለኛል
እህትህም መሆን ዛሬ አሰኝቶኛል
ፍቅረኛህ እንድሆን ደሞ ተሰምቶኛል
ብቻ እንዳታረገኝ ምስኪኖ እናትህን
በስስት ምታይህ የምትሞትልህን
አንተን ቀና ብለህ ያጎነበሰችን
ውስጣን እየከፋት የሳቀችልህን
ብቻ እንዳታረገኝ ምስኪኖ እናትህን
By
@Hanipia
@getem
@getem
@Hanipiagetem
ንገረኝ በሞቴ ምንህ ይሻለኛል
ዘንድሮን በጠና ሆድ ሆዴን በልቶኛል
ስለዚ ንገረኝ ምንህ ይሻለኛል
እህትህም መሆን ዛሬ አሰኝቶኛል
ፍቅረኛህ እንድሆን ደሞ ተሰምቶኛል
ብቻ እንዳታረገኝ ምስኪኖ እናትህን
በስስት ምታይህ የምትሞትልህን
አንተን ቀና ብለህ ያጎነበሰችን
ውስጣን እየከፋት የሳቀችልህን
ብቻ እንዳታረገኝ ምስኪኖ እናትህን
By
@Hanipia
@getem
@getem
@Hanipiagetem
/ይቀጥላል ፍቅር/
ሳላገኝሽ በፊት ሳትሆኚ በቅርቤ
በገሃድም ሳይሆን ሳለሽ በአሳቤ፤
የዛኔ የሆንኩት አንቺን ላገኝ ብዬ
ሙሾ ያስወረደኝ ያስባለኝ እዬዬ፤
ያ ፍቅርሽ ብዙ ጉድ ያሳየኝ
ጊዜው ደርሶ ዛሬ ካንቺ ቢያቆራኘኝ፤
አጣጥሜ በቅጡ ሳልቀምሰው
ልኖር ካንቺ ቤቴን ሳልቀልሰው፤
በጅምሩ በፍቅራችን ንጋት
የመውደድን ፅዋ አብረን ሳንጋት፤
" ዛሬላይ"
እስክረሳው ያንቺ ወደኔ መምጣት
እስክል ድረስ ለምን አፈቀርኳት፤
አርጎኝ የነበረው ላንቺ እንድረታ
ሰከን ያላረገኝ እንዳላስብ ላፍታ፤
የከለለኝ እሱ እንዳላይ ጋርዶብኝ
ፍቅርሽ አይደለም ሆይ ያረገኝ ባንቺሞኝ፤
ግን የሚገርመው የኔ ፅኑ አቋም
ይቀጥላል ፍቅር እንዴት ባንቺ ሊቆም:
#መሳይ ግርማ
@getem
@getem
@getem
ሳላገኝሽ በፊት ሳትሆኚ በቅርቤ
በገሃድም ሳይሆን ሳለሽ በአሳቤ፤
የዛኔ የሆንኩት አንቺን ላገኝ ብዬ
ሙሾ ያስወረደኝ ያስባለኝ እዬዬ፤
ያ ፍቅርሽ ብዙ ጉድ ያሳየኝ
ጊዜው ደርሶ ዛሬ ካንቺ ቢያቆራኘኝ፤
አጣጥሜ በቅጡ ሳልቀምሰው
ልኖር ካንቺ ቤቴን ሳልቀልሰው፤
በጅምሩ በፍቅራችን ንጋት
የመውደድን ፅዋ አብረን ሳንጋት፤
" ዛሬላይ"
እስክረሳው ያንቺ ወደኔ መምጣት
እስክል ድረስ ለምን አፈቀርኳት፤
አርጎኝ የነበረው ላንቺ እንድረታ
ሰከን ያላረገኝ እንዳላስብ ላፍታ፤
የከለለኝ እሱ እንዳላይ ጋርዶብኝ
ፍቅርሽ አይደለም ሆይ ያረገኝ ባንቺሞኝ፤
ግን የሚገርመው የኔ ፅኑ አቋም
ይቀጥላል ፍቅር እንዴት ባንቺ ሊቆም:
#መሳይ ግርማ
@getem
@getem
@getem
አንቺን እንዲያስረሳኝ እግዜርን ለመንኩኝ
ፍቅርሽ እንዲተወኝ ከአላህ ተማፀንኩኝ
እጣኑን ዘቢቡን ልሰዋ ከሰሙኝ
ለዓመት ደጁ ላልቀር ድባቡን ተሳልኩኝ
ግን እያደር ሳየው ናፍቆት ሆድ ሲያስብሰኝ
እግዜር እና አላህን መጠበቅ ሲሳነኝ
የ መርሳት ጉጉቴ ሆድ ሆዴን ቢያባባኝ
በአምላኮች መንገድ ተስፋዬን ቆረጥኩኝ
የእነሱን ቻይነት ሳልጠረጥር ባምንም
የእኔን ስለማውቀው ሚሆን አይመስለኝም
እና የአምላክ ነገር አልሳካ ቢለኝ
ተዋረስኩ ከአጋንንት ትዝታሽ ቢለቀኝ
አንቺን ከረሳሁኝ እንዳሻው እንዲያደርገኝ
ስጋዬን በቀብድ ለሰይጣን አስያዝኩኝ
ይቺ ብኩን ነፍሴን ሲዖል ወረወርኩኝ
ሠይጣን በዓለም እንጂ በፍቅር መች ይፈርዳል ይህም አልሆነልኝ
ስንቱን ልጥቀስልሽ አንዱ እንኳ አልቀረኝ
ሰንደሌን ለኩሼ ጠንቋይም አልተውኩኝ
እንዲያስረሳኝ ብዬ ስንቱን ዶሮ አረድኩኝ
እልፍ አዕላፍ ኡቃቤ ባንቺ ተማፀንኩኝ
ውቅያኖስ ናፍቆትሽን ከጠብታ አርቅቀው
ዓለም ትዝታሽን ከሀገር አሳንሰው
ያንቺን መውደድ ክብደት አቅለው ቢያሳዩኝ
እኔም እውነት መስሎኝ "አሜን" ልርሳት አልጉኝ
ወራት ቢቆጠሩ ቀናቶች ቢነጉዱ ፈገግ ስል ቢያዩኝ
"ከራማችን ፈርዷል ስለትህን አስገባ ረስተሃታል" አሉኝ
የናፍቆትሽን ፀባይ የፍቅርሽን አመል እኔ መች አጣሁኝ
ይኸው ትናንትና ድምፅሽን ብሰማ ዳግም ተነሣብኝ
ዘረ-ሠናይ
@Prince_Zeresenay
@getem
@getem
@paappii
ፍቅርሽ እንዲተወኝ ከአላህ ተማፀንኩኝ
እጣኑን ዘቢቡን ልሰዋ ከሰሙኝ
ለዓመት ደጁ ላልቀር ድባቡን ተሳልኩኝ
ግን እያደር ሳየው ናፍቆት ሆድ ሲያስብሰኝ
እግዜር እና አላህን መጠበቅ ሲሳነኝ
የ መርሳት ጉጉቴ ሆድ ሆዴን ቢያባባኝ
በአምላኮች መንገድ ተስፋዬን ቆረጥኩኝ
የእነሱን ቻይነት ሳልጠረጥር ባምንም
የእኔን ስለማውቀው ሚሆን አይመስለኝም
እና የአምላክ ነገር አልሳካ ቢለኝ
ተዋረስኩ ከአጋንንት ትዝታሽ ቢለቀኝ
አንቺን ከረሳሁኝ እንዳሻው እንዲያደርገኝ
ስጋዬን በቀብድ ለሰይጣን አስያዝኩኝ
ይቺ ብኩን ነፍሴን ሲዖል ወረወርኩኝ
ሠይጣን በዓለም እንጂ በፍቅር መች ይፈርዳል ይህም አልሆነልኝ
ስንቱን ልጥቀስልሽ አንዱ እንኳ አልቀረኝ
ሰንደሌን ለኩሼ ጠንቋይም አልተውኩኝ
እንዲያስረሳኝ ብዬ ስንቱን ዶሮ አረድኩኝ
እልፍ አዕላፍ ኡቃቤ ባንቺ ተማፀንኩኝ
ውቅያኖስ ናፍቆትሽን ከጠብታ አርቅቀው
ዓለም ትዝታሽን ከሀገር አሳንሰው
ያንቺን መውደድ ክብደት አቅለው ቢያሳዩኝ
እኔም እውነት መስሎኝ "አሜን" ልርሳት አልጉኝ
ወራት ቢቆጠሩ ቀናቶች ቢነጉዱ ፈገግ ስል ቢያዩኝ
"ከራማችን ፈርዷል ስለትህን አስገባ ረስተሃታል" አሉኝ
የናፍቆትሽን ፀባይ የፍቅርሽን አመል እኔ መች አጣሁኝ
ይኸው ትናንትና ድምፅሽን ብሰማ ዳግም ተነሣብኝ
ዘረ-ሠናይ
@Prince_Zeresenay
@getem
@getem
@paappii
.....ስድስት እና ስድስት
ተገጣጠሙና ወርና አመታት
ስድስት የጥላቻ ስድስቱ የናፍቆት
ማልቀስ ሳይቀር ማንባት
መቁሰል ነበር መድማት
እነዛን አመታት
ዛሬ ተቀይሮ አመታት በወር ላይ
አልውልም ትላለህ አይኖችሽን ሳላይ
የልቤ ደረሰ አንተን ሰጠኝ ከላይ
ወደድከኝ አለሜ ህይወትን ሠጠኸኝ
እሠየው አበጀህ እንካን አፈቀርከኝ
ስድስቱን አመታት በስድስት ወር ካስከኝ
4/8/2016
By
@Hanipia
@getem
@Hanipiagetem
@getem
ተገጣጠሙና ወርና አመታት
ስድስት የጥላቻ ስድስቱ የናፍቆት
ማልቀስ ሳይቀር ማንባት
መቁሰል ነበር መድማት
እነዛን አመታት
ዛሬ ተቀይሮ አመታት በወር ላይ
አልውልም ትላለህ አይኖችሽን ሳላይ
የልቤ ደረሰ አንተን ሰጠኝ ከላይ
ወደድከኝ አለሜ ህይወትን ሠጠኸኝ
እሠየው አበጀህ እንካን አፈቀርከኝ
ስድስቱን አመታት በስድስት ወር ካስከኝ
4/8/2016
By
@Hanipia
@getem
@Hanipiagetem
@getem