Telegram Web Link
42🥰6
ታላቁ ማዲህ ሸይኽ ሙሀመድ ሁሴን ወደ አኼራ ተሻግረዋል
.................................
ለዘመናት ነብያችንን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም በማወደስ የሚታወቁት ሸይኽ ሙሐመድ ሁሴን ዛሬ ጠዋት አዲስአበባ ላይ ያለፉ ሲሆን ረፋድ ላይ ታላላቅ ዑለማዎች እና ወዳጆቻቸው ተሰባስበው ጀናዛቸው ወደ ሚያርፍበት ኮምቦልቻ ሸኝተዋል ።

ሐሪማ ቴሌቪዥን በኚህ ታላቅ አሊም እና ማዲህ ህልፈት የተሰማውን ሃዘን እየገለፀ ህዝበ ሙስሊሙ ዱአ እንዲያደርግ መልእክቱን ያስተላልፋል።
😢48😭486🤯1
ሐገራዊውን “መንዙማ” በዕውቀትና በሥርዓት፣ በተዋበ ድምጽና ወግ በጠበቀ ቅኝት ለትውልድ በማሸጋገር ለአርባዎቹ ዓመታት የላቀ ሚና ያበረከቱት ማዲህ ሸህ ሙሐመድ ሑሴን በ63 ዓመታቸው በዛሬው ዕለት አርፈዋል።

ውልደት እና ዕድገታቸው ደቡብ ወሎ ኮምቦልቻ አካባቢ ነበር። የዒልም(ዕውቀት)፣ የአዳብ(ሥርዓት)፣ የመንፈሳዊ እነጻ ዝግጅታቸውን ያጠናቀቁት በ“ዛውዮች” በ“ኡላኡላ” በ“መጅት” የዕውቀትና መንፈሳዊ ማዕከላት ነው። በዋነኝነት የዳግማዊ መጅት(ሸህ ሰዒድ ቡሽራ) ምሩቅ ናቸው።

ለመንፈሳዊ መምህራቸው ለዳግማዊ መጅት የላቀ ፍቅር፣ አክብሮት እና አገልግሎት(ኺድሚያ) ነበራቸው። ሦስት ጊዜ መካ-መዲና አብሮ የመጓዝ ወርቃማ ዕድል አግኝተዋል። ዱዓ እና ምርቃትም ተችረዋል።

ሸህ ሙሐመድ ሑሴን ለነቢ ሙሐመድ(ሶ.ዓ.ዎ.) የከበረ ፍቅር፣ ናፍቆት፣ ተከታይነት ነበራቸው። ለሃያ ጊዜ ያክል መካ-መዲናን የመዘየራቸው ሚስጥር፣ ለአርባዎቹ ዓመታት በመድህ(መወድሰ ነቢ) የማገልገላቸው ቀመር ከዚያ የሚመነጭ ነው።

በኢማምነት፣ በመልካም ጸባይ ታግዘው ግብረ ገባዊ ምክርና ታሪክ በመለገስ፣ ሐገርን ሰርክ በጸሎት/ዱዓ በማሰብ ይታዎቃሉ። በወሎ በአዲስ አበባ ቀጥተኛ ተፅዕኖ አላቸው። የመንዙማ አበርክቷቸው በመላ ኢትዮጵያ ዕውቅና አለው። እንዲሁም ከዐስራ አምስት በላይ ዕውቅ ተተኪ ማዲሆችን አፍርተዋል። በትዳር ሕይዎታቸውም አምስት ልጆችን ወልደዋል።

በአዲስ አበባ በዛሬው ዕለት ሙፍቲ ሐጂ ዑመርን ጨምሮ በርካታ ዓሊሞች(ሊቃውንት)፣ ምሁራን እና ምእመናን መንፈሳዊ ሽኝት አድርገውላቸዋል። የቀብር ሥነ ስርዓታቸው በነገው ዕለት በኮምቦልቻ ከተማ ይፈጸማል።

(በኸድር ታጁ)
😢59😭4119
40🥰11👍4🔥2
52👍8
🥰2819👏4
29👍4
ዛሬ ምሽት
2፡30 ጀምሮ
ከንቃተ ህሊና እስከ ነብያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ልቅና
👍3025
ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን

ታላቁ የተፍሲር ሊቅ ሸይኽ ሀምዛ አብራር ወደ አኼራ ተሻግረዋል
.................
ከልጅነታቸው ጀምሮ ለ አራት አስርተ-አመታት  ጨካ፣ ሸይኽ ወዴ ፣ቃሉ ሸይኽ አሊ ላይ ተፍሲር ፣ሸይኽ ገበሮ ላይ እንዲሁም አዲስአበባ በሐጅ መሀመድ ራፊእ  በሌሎች አንጋፋ ሀሪማዎች ኢልምን ሲቀስሙ ቆይተዋል ።

ከ 2003 ጀምሮ ለአርባ አመት የሰበሰቡትን ኢልም በወለቴ በሁነይን መስጅድ በማስተማር እና ቁርአንን በመፈሰር ላይ ቆይተው በዛሬው እለት ወደ አኼራ ተሻግረዋል ።


ሐሪማ ቴሌቭዥን በሸይኽ ሀምዛ አብራር ህልፈት የተሰማንን ሀዘን እየገለፅን ሙስሊሙ ማህበረሰብ በዱአ እንዲያስታውሳቸው መልእክቱን ያስተላልፋል ።
😢81😭41💔1711👍2
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ቅዳሜ ቀን 8:00 ጀምሮ
24👏5
50🥰5👍4
21❤‍🔥1
2025/10/20 15:55:27
Back to Top
HTML Embed Code: