አል-ፋሽጋ ዳግም በኢትዮጵያውያን እጅ ገባ
ለዘመናት የኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች የእርሻና የኑሮ መሰረት የነበረው ለም መሬት፣ አል-ፋሽጋ፣ ዳግም ወደ ህጋዊ ባለቤቶቹ ተመልሷል።
የሱዳን ጦር የኢትዮጵያን የውስጥ ችግር እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠር፣ በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎንደር ዞን የሚገኙትን የመተማና የቋራ ወረዳ ለም መሬቶችን በኃይል ተቆጣጥሮ ነበር።
በወቅቱ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በቅርብ ርቀት ላይ ሆኖ ሁኔታውን በትዕግስት ሲከታተል የነበረ ሲሆን፣ መንግሥትም ችግሩን በዲፕሎማሲና በውይይት ለመፍታት ያለውን ፍላጎት በተደጋጋሚ መግለጹ ይታወሳል፡፡
በዚህ የሱዳን ወረራ ወቅት ኢትዮጵያውያን ገበሬዎች ከእርሻቸው ከመፈናቀላቸውም በላይ ከፍተኛ የሆነ የሰብልና የንብረት ውድመት እንደደረሰባቸው አይዘነጋም፡፡
የሱዳን ባለሥልጣናት ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ታጣቂዎች በአገሪቱ መከላከያ ሠራዊት በመታገዝ የአማራ ክልል አዋሳኝ ወደኾኑ የሱዳን ለም መሬቶች በመስፋፋት ላይ ናቸው ሲሉ መክሰሳቸው ተዘግቦ ነበር፡፡
ለዘመናት የኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች የእርሻና የኑሮ መሰረት የነበረው ለም መሬት፣ አል-ፋሽጋ፣ ዳግም ወደ ህጋዊ ባለቤቶቹ ተመልሷል።
የሱዳን ጦር የኢትዮጵያን የውስጥ ችግር እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠር፣ በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎንደር ዞን የሚገኙትን የመተማና የቋራ ወረዳ ለም መሬቶችን በኃይል ተቆጣጥሮ ነበር።
በወቅቱ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በቅርብ ርቀት ላይ ሆኖ ሁኔታውን በትዕግስት ሲከታተል የነበረ ሲሆን፣ መንግሥትም ችግሩን በዲፕሎማሲና በውይይት ለመፍታት ያለውን ፍላጎት በተደጋጋሚ መግለጹ ይታወሳል፡፡
በዚህ የሱዳን ወረራ ወቅት ኢትዮጵያውያን ገበሬዎች ከእርሻቸው ከመፈናቀላቸውም በላይ ከፍተኛ የሆነ የሰብልና የንብረት ውድመት እንደደረሰባቸው አይዘነጋም፡፡
የሱዳን ባለሥልጣናት ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ታጣቂዎች በአገሪቱ መከላከያ ሠራዊት በመታገዝ የአማራ ክልል አዋሳኝ ወደኾኑ የሱዳን ለም መሬቶች በመስፋፋት ላይ ናቸው ሲሉ መክሰሳቸው ተዘግቦ ነበር፡፡
የሰነደ መዋዕለ ንዋዮች ገበያ በሚቀጥለው ሳምንት ይፋዊ ግብይት ሊጀምር ነው
ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረው የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋዮች ( ስቶክ ገበያ) በሚቀጥለው ሳምንት ሥራ ሊጀምር መሆኑ ተሰምቷል። ይህ እርምጃ ለአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ ታውቋል።
ገበያዉ በኖቬምበር 2023 በተደረገ የካፒታል ማሰባሰቢያ ዘመቻ 1.5 ቢሊዮን ብር በማሰባሰብ ከታሰበው ግብ በ631% በልጧል። ይህ ገንዘብ ከ48 የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ተቋማት የተገኘ መሆኑ ይታወቃል።
በሕዝብና በግል ሽርክና የሚሰራው አዲሱ የበይነመረብ ንግድ ልዉዉጥ መድረክን መንግሥት 25%፣ የግል ዘርፍ ደግሞ 75% ድርሻ አላቸዉ። አሁን ላይ ገዳ ባንክ አ.ማ. እና ወጋገን ካፒታል ኢንቨስትመንት ባንክ አ.ማ. በገበያው ላይ ከተመዘገቡት ኩባንያዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
የሰነደ መዋዕለ ንዋይ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ውስጥ እስከ 50 ኩባንያዎችን፣ በአሥር ዓመታት ውስጥ ደግሞ ከ90 በላይ ንግዶችን ለማካተት አቅዷል። ይህ ልውውጥ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለማዘመን፣ ግልጽነትን ለማሳደግ እና ለንግዶች ካፒታል ማሰባሰቢያ አዳዲስ አማራጮችን ለመስጠት ያለመ ሲሆን፣ የኢኮኖሚ ዕድገትን እንደሚያነቃቃም ይጠበቃል።
ዝርዝሩን ያንብቡ
ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረው የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋዮች ( ስቶክ ገበያ) በሚቀጥለው ሳምንት ሥራ ሊጀምር መሆኑ ተሰምቷል። ይህ እርምጃ ለአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ ታውቋል።
ገበያዉ በኖቬምበር 2023 በተደረገ የካፒታል ማሰባሰቢያ ዘመቻ 1.5 ቢሊዮን ብር በማሰባሰብ ከታሰበው ግብ በ631% በልጧል። ይህ ገንዘብ ከ48 የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ተቋማት የተገኘ መሆኑ ይታወቃል።
በሕዝብና በግል ሽርክና የሚሰራው አዲሱ የበይነመረብ ንግድ ልዉዉጥ መድረክን መንግሥት 25%፣ የግል ዘርፍ ደግሞ 75% ድርሻ አላቸዉ። አሁን ላይ ገዳ ባንክ አ.ማ. እና ወጋገን ካፒታል ኢንቨስትመንት ባንክ አ.ማ. በገበያው ላይ ከተመዘገቡት ኩባንያዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
የሰነደ መዋዕለ ንዋይ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ውስጥ እስከ 50 ኩባንያዎችን፣ በአሥር ዓመታት ውስጥ ደግሞ ከ90 በላይ ንግዶችን ለማካተት አቅዷል። ይህ ልውውጥ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለማዘመን፣ ግልጽነትን ለማሳደግ እና ለንግዶች ካፒታል ማሰባሰቢያ አዳዲስ አማራጮችን ለመስጠት ያለመ ሲሆን፣ የኢኮኖሚ ዕድገትን እንደሚያነቃቃም ይጠበቃል።
ዝርዝሩን ያንብቡ
በህዳሴው ግድብ ምርቃት ላይ ፕሬዝደንት ፑቲን ሊጋበዙ ነው
የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን በመጪው መስከረም ወር በሚደረገው የህዳሴ ግድብ ምርቃት ስነስርአት እንዲገኙ ግብዣ ሊላክላቸው መሆኑ ተሰማ፡፡
ስፑትኒክ የተሰኘው የሩሲያ ሚዲያ ዛሬ እንደዘገበው በግድቡ መክፈቻ ስነስርአት ላይ ፑቲን እንዲገኙ የኢትዮጵያ መንግስት ግብዣ ሊላክላቸው ይችላል፡፡ ይሁንና ግብዣው ቢላክ ፕሬዝደንቱ ለመገኘት ፈቃደኛ ስለመሆንና አለመሆናቸው ያለው ነገር የለም፡፡ የሩሲያው ፕሬዝደንት ፑቲን በአለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት በቀረበባቸው ክስ የእስር ማዘዣ የተቆረጠባቸው መሆኑ ይታወቃል፡፡
በአሁኑ ወቅት በብራዚል እየተካሄደ ባለው የብሪክስ የመሪዎች ስብሰባ ላይ በአካል ያልተገኙትም ለዚህ ነው፡፡ ስለጉዳዩ የተጠየቁት የክሬሚሊን አማካሪ ዩሪ ኡሻኮቭ ‹‹ከአይሲሲ ሁኔታዎች ጋር በተያያዘ ፕሬዝደንት ፑቲን በአካል ብራዚል ለመገኘት አይችሉም›› ሲሉ ባለፈው ሳምንት ተናግረው ነበር፡፡
በመሆኑም በስብሰባው ላይ በቪዲዮ ኮንፈረንስ እንደሚሳተፉ ማስታወቃቸው አይዘነጋም፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ኢትዮጵያ የአለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት(አይሲሲ) አባል አይደለችም፡፡ በሮም ፍርድ ቤቱን በተመለከተ የተፈረመውን ስምምነት ባለመፈረሟ የፍርድ ቤቱን ትእዛዝ የማስፈፀም ግዴታ እንደሌለባት ዘገባዎች ገልፀዋል፡፡
የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን በመጪው መስከረም ወር በሚደረገው የህዳሴ ግድብ ምርቃት ስነስርአት እንዲገኙ ግብዣ ሊላክላቸው መሆኑ ተሰማ፡፡
ስፑትኒክ የተሰኘው የሩሲያ ሚዲያ ዛሬ እንደዘገበው በግድቡ መክፈቻ ስነስርአት ላይ ፑቲን እንዲገኙ የኢትዮጵያ መንግስት ግብዣ ሊላክላቸው ይችላል፡፡ ይሁንና ግብዣው ቢላክ ፕሬዝደንቱ ለመገኘት ፈቃደኛ ስለመሆንና አለመሆናቸው ያለው ነገር የለም፡፡ የሩሲያው ፕሬዝደንት ፑቲን በአለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት በቀረበባቸው ክስ የእስር ማዘዣ የተቆረጠባቸው መሆኑ ይታወቃል፡፡
በአሁኑ ወቅት በብራዚል እየተካሄደ ባለው የብሪክስ የመሪዎች ስብሰባ ላይ በአካል ያልተገኙትም ለዚህ ነው፡፡ ስለጉዳዩ የተጠየቁት የክሬሚሊን አማካሪ ዩሪ ኡሻኮቭ ‹‹ከአይሲሲ ሁኔታዎች ጋር በተያያዘ ፕሬዝደንት ፑቲን በአካል ብራዚል ለመገኘት አይችሉም›› ሲሉ ባለፈው ሳምንት ተናግረው ነበር፡፡
በመሆኑም በስብሰባው ላይ በቪዲዮ ኮንፈረንስ እንደሚሳተፉ ማስታወቃቸው አይዘነጋም፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ኢትዮጵያ የአለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት(አይሲሲ) አባል አይደለችም፡፡ በሮም ፍርድ ቤቱን በተመለከተ የተፈረመውን ስምምነት ባለመፈረሟ የፍርድ ቤቱን ትእዛዝ የማስፈፀም ግዴታ እንደሌለባት ዘገባዎች ገልፀዋል፡፡