የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት የታሊባን መሪዎች ላይ የእስር ማዘዣ አወጣ
የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ዛሬ ማክሰኞ በሁለት የታሊባን ላይ መሪዎች የእስር ማዘዣ አውጥቷል ሲል ሲ ኤን ኤን ዘግቧል።
ፍርድ ቤቱ ባለሥልጣናቱ ላይ የእስር ማዘዣ ያወጣው በአፍጋኒስታን በሴቶች እና ልጃገረዶች ላይ ተከታታይ የጭቆና ያደርሳሉ በሚል መሆኑ ተነግሯል።
የአይሲሲ ዋና አቃቤ ህግ እንደገለፀው፣ ሂበቱላህ አክሁንዘዳህ የታሊባን የበላይ መሪ እና አብዱልሀኪም ሃቃኒ የጀማአቱል ኢስላሚያ ዋና ዳኛ በስርዓተ ፆታ ላይ የተመሰረተ በሴቶች እና በልጃገረዶች ላይ ጭቆና ያደርሳሉ በሚል ከኦገስት 15 2021 ጀምሮ በመፈጸም “በወንጀል ተጠያቂ” ናቸው ብሏል።
ታሊባን አፍጋኒስታንን ከተቆጣጠረ ጀምሮ በሴቶች እና ልጃገረዶች ላይ ተከታታይ የጭቆና እርምጃዎችን ተግባራዊ አድርጓል ሲልም ወቅሷል።
"ታሊባን በአጠቃላይ በህዝቡ ላይ የተወሰኑ ህጎችን እና ክልከላዎችን ቢያደርግም በተለይ ልጃገረዶችን እና ሴቶችን በፆታቸው ምክንያት መሰረታዊ መብቶችን እና ነፃነቶችን ገፏል" ሲል አይሲሲ ተናግሯል ብሏል።
የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ዛሬ ማክሰኞ በሁለት የታሊባን ላይ መሪዎች የእስር ማዘዣ አውጥቷል ሲል ሲ ኤን ኤን ዘግቧል።
ፍርድ ቤቱ ባለሥልጣናቱ ላይ የእስር ማዘዣ ያወጣው በአፍጋኒስታን በሴቶች እና ልጃገረዶች ላይ ተከታታይ የጭቆና ያደርሳሉ በሚል መሆኑ ተነግሯል።
የአይሲሲ ዋና አቃቤ ህግ እንደገለፀው፣ ሂበቱላህ አክሁንዘዳህ የታሊባን የበላይ መሪ እና አብዱልሀኪም ሃቃኒ የጀማአቱል ኢስላሚያ ዋና ዳኛ በስርዓተ ፆታ ላይ የተመሰረተ በሴቶች እና በልጃገረዶች ላይ ጭቆና ያደርሳሉ በሚል ከኦገስት 15 2021 ጀምሮ በመፈጸም “በወንጀል ተጠያቂ” ናቸው ብሏል።
ታሊባን አፍጋኒስታንን ከተቆጣጠረ ጀምሮ በሴቶች እና ልጃገረዶች ላይ ተከታታይ የጭቆና እርምጃዎችን ተግባራዊ አድርጓል ሲልም ወቅሷል።
"ታሊባን በአጠቃላይ በህዝቡ ላይ የተወሰኑ ህጎችን እና ክልከላዎችን ቢያደርግም በተለይ ልጃገረዶችን እና ሴቶችን በፆታቸው ምክንያት መሰረታዊ መብቶችን እና ነፃነቶችን ገፏል" ሲል አይሲሲ ተናግሯል ብሏል።
ግብጽ በድጋሚ የቀይ ባህር ደህንነት ላይ ትኩረት አደርጋለች፣ ከሶማሊያ ጋር ጠንካራ ወታደራዊ ግንኙነት ለመመስረት ቃል ገብታለች!
የግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ ኤል ሲሲ አሁንም በድጋሚ በቀይ ባህር ደህንነት ላይ ያተኮረ መልዕክት ሰኔ 29 ቀን 2017 ዓ.ም አስተላልፈዋል፤ የቀይ ባህርን ደህንነት ለማስጠበቅ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ግብጽ ለሶማሊያ የምታደርገውን ወታደራዊ ድጋፍ አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉም ቃል ገብተዋል።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን መልዕክት በድጋሚ ያስተላለፉት የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድን በግብፅ የባህር ጠረፍ ከተማ ኤል አላሜይን ሰኔ 29 ቀን 2017 ዓ.ም ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት ነው፤ በአፍሪካ ቀንድ ውጥረት እየጨመረ ባለበት በአሁኑ ወቅት ሁለቱ መሪዎች በውይይታቸው ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን ለማስቀጠል ቃል ገብተዋል ተብሏል።
ሁለቱ መሪዎች ያደረጉትን ውይይት ተከትሎ በግብጽ በኩል የወጣው መግለጫ አንደሚያትተው መሪዎቹ የሁለቱን ሀገራት ሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ተስማምተዋል፣ በተለይም በሶማሊያ ደህንነት እና መረጋጋት ዙሪያ በዝርዝር ተነጋግረዋል ብሏል።
ፕሬዝዳንት አልሲሲ በተደጋጋሚ በአፍሪካ ቀንድ እንዲሁም በቀይ ባህር ደህንነት እና መረጋጋት ዙሪያ አስተያየት ሰጡ ወይንም ተወያዩ የሚሉ አገላለጾች መሰማት የጀመሩት ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2024 መጀመሪያ ላይ ከሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረመች በኋላ ነው።
በኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ መካከል በተፈረመው የመግባቢያ ሰነድ ዙሪያ ከሁለቱም ወገኖች ምንም አይነት ድምጽ እየተሰማ ባይሆንም ኢትዮጵያውያ በቀጥታ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት አሁንም ከግብፅም ሆነ ከሶማሊያ በኩል በጥርጣሬ እና በስጋት የሚታይ ነው።
Via AS
የግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ ኤል ሲሲ አሁንም በድጋሚ በቀይ ባህር ደህንነት ላይ ያተኮረ መልዕክት ሰኔ 29 ቀን 2017 ዓ.ም አስተላልፈዋል፤ የቀይ ባህርን ደህንነት ለማስጠበቅ እንደሚሰሩ ገልጸዋል። ግብጽ ለሶማሊያ የምታደርገውን ወታደራዊ ድጋፍ አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉም ቃል ገብተዋል።
ፕሬዝዳንቱ ይህንን መልዕክት በድጋሚ ያስተላለፉት የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድን በግብፅ የባህር ጠረፍ ከተማ ኤል አላሜይን ሰኔ 29 ቀን 2017 ዓ.ም ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት ነው፤ በአፍሪካ ቀንድ ውጥረት እየጨመረ ባለበት በአሁኑ ወቅት ሁለቱ መሪዎች በውይይታቸው ስትራቴጂካዊ አጋርነታቸውን ለማስቀጠል ቃል ገብተዋል ተብሏል።
ሁለቱ መሪዎች ያደረጉትን ውይይት ተከትሎ በግብጽ በኩል የወጣው መግለጫ አንደሚያትተው መሪዎቹ የሁለቱን ሀገራት ሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ተስማምተዋል፣ በተለይም በሶማሊያ ደህንነት እና መረጋጋት ዙሪያ በዝርዝር ተነጋግረዋል ብሏል።
ፕሬዝዳንት አልሲሲ በተደጋጋሚ በአፍሪካ ቀንድ እንዲሁም በቀይ ባህር ደህንነት እና መረጋጋት ዙሪያ አስተያየት ሰጡ ወይንም ተወያዩ የሚሉ አገላለጾች መሰማት የጀመሩት ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2024 መጀመሪያ ላይ ከሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረመች በኋላ ነው።
በኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ መካከል በተፈረመው የመግባቢያ ሰነድ ዙሪያ ከሁለቱም ወገኖች ምንም አይነት ድምጽ እየተሰማ ባይሆንም ኢትዮጵያውያ በቀጥታ የባህር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት አሁንም ከግብፅም ሆነ ከሶማሊያ በኩል በጥርጣሬ እና በስጋት የሚታይ ነው።
Via AS
አዲስ የግብር አወሳሰን ለአከራዮች እና የሙያ አገልግሎት ሰጪዎች ይፋ ተደረገ
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የ2017 የግብር ዘመን አዲስ የአወሳሰን ስርዓት ከሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን ማድረጉን አስታወቀ። ይህ አዲስ መመሪያ የመኖሪያ ቤት አከራዮችን፣ የሙያ አገልግሎት ሰጪዎችን፣ እንዲሁም አንዳንድ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎችን ይመለከታል።
የንግድ ስራ ያልሆነ ገቢ ያላቸው የመኖሪያ ቤት አከራዮች እና የንግድ ፍቃድ ሳይኖራቸው በሙያ ፍቃድ ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ ግለሰቦች (እንደ ጠበቆችና ኢንሹራንስ ወኪሎች ያሉ) ከጠቅላላ ገቢያቸው 35 በመቶው እንደ ወጪ የሚቀነስ ሲሆን፣ ቀሪው 65 በመቶው ብቻ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ይሆናል።
ይህ አሰራር የሂሳብ መዝገብ ማቅረብ ግዴታ ሳይኖርባቸው በግምት ገቢያቸው የሚሰላላቸውን ግብር ከፋዮች ጫና ለመቀነስ እና የግብር አሰባሰቡን ፍትሃዊ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ካፒታል ከመመሪያው ለመረዳት ችሏል።
ከዚህ በተጨማሪ በህግ ደረሰኝ የመጠቀም ግዴታ የሌለባቸው የከተማ ውስጥ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች እንዲሁም በግል ኮድ 02 እና በንግድ ኮድ 03 የተመዘገቡ ተሽከርካሪ የኪራይ አገልግሎት ሰጪዎች ላይም አዲሱ መመሪያ ተፈፃሚ ይሆናል። ለእነዚህ ዘርፎች ግብሩ የሚሰላው በሰንጠረዥ "ሐ" መሰረት መሆኑን ተገልጿል።
ከእነዚህ ዘርፎች ውጭ የሆኑ እና የሂሳብ መግለጫ የማቅረብ ግዴታቸውን ያልተወጡ ግብር ከፋዮች ግን ግብር ለመሸሽ በሚደረግ ተግባር እንደሚወገዱ ቢሮው አስጠንቅቋል። በዚህም መሰረት፣ የታክስ ጉዳቱ 40 በመቶ እና የታክሱ እጥፍ ቅጣት ሳይነሳ ገቢው እንደሚሰበሰብ ተገልጿል።
Capital Newspaper
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የ2017 የግብር ዘመን አዲስ የአወሳሰን ስርዓት ከሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን ማድረጉን አስታወቀ። ይህ አዲስ መመሪያ የመኖሪያ ቤት አከራዮችን፣ የሙያ አገልግሎት ሰጪዎችን፣ እንዲሁም አንዳንድ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎችን ይመለከታል።
የንግድ ስራ ያልሆነ ገቢ ያላቸው የመኖሪያ ቤት አከራዮች እና የንግድ ፍቃድ ሳይኖራቸው በሙያ ፍቃድ ብቻ አገልግሎት የሚሰጡ ግለሰቦች (እንደ ጠበቆችና ኢንሹራንስ ወኪሎች ያሉ) ከጠቅላላ ገቢያቸው 35 በመቶው እንደ ወጪ የሚቀነስ ሲሆን፣ ቀሪው 65 በመቶው ብቻ ግብር የሚከፈልበት ገቢ ይሆናል።
ይህ አሰራር የሂሳብ መዝገብ ማቅረብ ግዴታ ሳይኖርባቸው በግምት ገቢያቸው የሚሰላላቸውን ግብር ከፋዮች ጫና ለመቀነስ እና የግብር አሰባሰቡን ፍትሃዊ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ካፒታል ከመመሪያው ለመረዳት ችሏል።
ከዚህ በተጨማሪ በህግ ደረሰኝ የመጠቀም ግዴታ የሌለባቸው የከተማ ውስጥ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች እንዲሁም በግል ኮድ 02 እና በንግድ ኮድ 03 የተመዘገቡ ተሽከርካሪ የኪራይ አገልግሎት ሰጪዎች ላይም አዲሱ መመሪያ ተፈፃሚ ይሆናል። ለእነዚህ ዘርፎች ግብሩ የሚሰላው በሰንጠረዥ "ሐ" መሰረት መሆኑን ተገልጿል።
ከእነዚህ ዘርፎች ውጭ የሆኑ እና የሂሳብ መግለጫ የማቅረብ ግዴታቸውን ያልተወጡ ግብር ከፋዮች ግን ግብር ለመሸሽ በሚደረግ ተግባር እንደሚወገዱ ቢሮው አስጠንቅቋል። በዚህም መሰረት፣ የታክስ ጉዳቱ 40 በመቶ እና የታክሱ እጥፍ ቅጣት ሳይነሳ ገቢው እንደሚሰበሰብ ተገልጿል።
Capital Newspaper