Telegram Web Link
ለሀገሪቱ የሀይል መቆራረጥ 47 በመቶ ምክንያት ሆነዋል የተባሉት ዛፎችን የመቁረጥ ስራ መጀመሩን አገልግሎቱ አስታወቀ

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ስራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው እንደገለጹት፣ 47 በመቶ የኤሌክትሪክ መቆራረጥ የሚከሰተው በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ በሚወድቁ ዛፎች እና ቅርንጫፎች ምክንያት ነዉ ሲሉ ተደምጠዋል።

ይህንን ችግር ለመፍታት ተቋሙ ከሁለት ወራት በፊት በመላ ሀገሪቱ በመስመሮች አካባቢ የሚገኙ ዛፎችን የመቁረጥ እና የማጽዳት ስራ መጀመሩን አረጋግጧል።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ብሩክ ታዬ በበኩላቸው እንደገለጹት፣ ምክንያታዊ ያልሆነ የኃይል መቆራረጥ እንደማይታገሱ አስታዉቀዋል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትን ጨምሮ በአጠቃላይ ከ 2ዐ በላይ መንግስታዊ የልማት ድርጅቶችን በስሩ እያስተዳደረ የሚገኘዉ የኢንቨስትመንት ሆልዲንግ በሀገሪቱ የሀይል መቆራረጦች በርካታ ምክንያቶች እንዳሉ የጠቆመ ሲሆን እነሱም የመሠረተ ልማት እጥረት፣ የቴክኒክ ችግሮች እና ሌሎች ብዛታዊ ምክንያቶች ናቸው ብሏል።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ባለፉት ስድስት ወራት በችግሩ ላይ ጥናት ተካሂዷል፣ እና ከኦፕሬሽን ጋር በተያያዘ ምክንያታዊ ያልሆነ የሀይል መቆራረጥ ለመቀነስ የመካከለኛ ጊዜ እቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ መግባቱ አስረድተዋል።

Capital
የግሪክ ኮሚኒቲ ትምህርት ቤት ቦታው ለኦሮሚያ ክልል ፕሬዝደንት ፅ/ቤት ማስፋፊያ ስለሚፈለግ እንዲነሳ ታዘዘ።

እድሜ ጠገቡ የግሪክ ኮሚኒቲ ትምህርት ቤት እና የግሪክ ክበብ አሁን ላይ የሚገኙበት ቦታ ለኦሮሚያ ክልል ፕሬዝደንት ፅ/ቤት ማስፋፊያነት ስለሚፈለግ እንዲነሱ እንደተነገራቸው ማረጋገጥ ችለናል።

የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 የመሬት ልማት እና አስተዳደር ፅ/ቤት በቅርቡ ለትምህርት ቤቱ እና ክበቡ በፃፈው ደብዳቤ ይዞታው ከኦሮሚያ ክልል ፕሬዝደንት ፅ/ቤት ማስፋፊያነት እንደሚፈለግ ገልጿል።

ትምህርት ቤቱ ደብዳቤው እንደደረሰው ለቦርዱ እንዲሁም ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ለትምህርት ሚኒስቴር እና ሌሎች ለሚመለከታቸው አካላት ማሳወቁን እና መልካም ምላሽ እየጠበቀ መሆኑን መሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ ይጠቁማል።

ከአንድ አመት ተኩል በፊት የግሪክ ኮሚኒቲ ት/ቤት ከፍርድ ቤት የእግድ ትዕዛዝ ውጪ ግቢው በፖሊስ እንደተያዘበት ለህዝብ አሳውቆ ነበር። በወቅቱ ጉዳዩን ሰምተው ለማብረድ ወደ ስፍራው ያቀኑት በኢትዮጵያ የግሪክ አምባሳደር እንደተገፈተሩ እና ከግቢው ለቀው እንዲወጡ እንደተደረጉ ይታወሳል።

"አምና ትምህርት ቤቱ ላይ ያ ሁሉ ወከባ እና የስም ማጥፋት ሲደርስ ለምን እንደነበር የገባን አሁን ነው፣ መሬቱን ለመንጠቅ የተጠነሰሰ ሴራ ነበር" በማለት አስተያየታቸውን የሰጡ አንድ ጉዳዩን የሚከታተሉ የኮሚኒቲው አባል ደብዳቤው ለብዙዎች አስደንጋጭ እንደሆነ ጨምረው ተናግረዋል።

የግሪክ ኮሚኒቲ ትምህርት ቤት ለበርካታ አስርት አመታት ተማሪዎችን ተቀብሎ ሲያስተምር የቆየ ሲሆን የግሪክ ኮሚኒቲ በኢትዮጵያ ያለውን ከ200 አመት በላይ ታሪክ ይዞ የቆየ መሆኑ ይነገርለታል።

መረት ሚዲያ
👍1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሀብተጊዮርጊስ ድልድይ አካባቢ በመኖሪያ እና ንግድ ቤቶች ላይ የእሳት አደጋ ደርሷል

በአዲስ ከተማ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 7 ሀብተጊዮርጊስ ድልድይ አካባቢ በመኖሪያ እና ንግድ ቤቶች ላይ የእሳት አደጋ ደርሷል።

አደጋው ትላንት ከሌሊቱ 10:35 ሰዓት መከሰቱ ተነግሯል።

የደረሰዉን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር  ሰፊ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የአዲስ አበባ እሳት እና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ  ተናግረዋል።
Via :-AMN
የአሜሪካ ማስጠንቀቂያ የጠ/ሚ አብይ የሶማሊያ ጉዞ በኃላ አሜሪካ ማስጠንቀቂያ ሰጠች

ትናንት በሶማሊያ ሞቃዲሾ አየር ማረፊያ የሞርታር ጥቃት መፈፀሙን ተከትሎ አሜሪካ የጉዞ ማስጠንቀቂያ አወጣች፡፡

በኬንያ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ባወጣው የጉዞ ማስጠንቀቂያ በትናንትናው እለት በሞቃዲሾ በሚገኘው አደን አዲ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተደጋጋሚ ጥቃት የተፈፀመበት መሆኑን ገልፆ አሜሪካዊያን በዚያ አየር ማረፊያ እንዳይጓዙ አስጠንቅቋል፡፡

ሌላ ማስታወቂያ እስከሚወጣ ድረስ በሱማሊያ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በአየር ማረፊያው ከመጠቀም እንዲቆጠብም አሳስቧል፡፡

በትናንትናው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድን የያዘው አውሮፕላን ሞቃዲሾ ከመድረሱ በፊት አየር መንገዱ አካባቢ 11 ጊዜ የሞርታር ጥቃት መፈፀሙንና አንዱ ኤርፖርቱ ውስጥ ማረፉን፣ከቱርክና ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ውጪ በረራ መከልከሉንና በርካታ የሞቃዲሾ መንገዶች መዘጋታቸውን መዘገባችን ይታወሳል።
ለ129ኛው የአድዋ ድል በዓል አከባበር ለተሽከርካሪዎች ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን አዲስ አበባ ፖሊስ ይፋ አድርጓል።

129ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓል የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ/ም ፒያሳ አካባቢ በሚገኘው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ይከበራል።

የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ለበዓሉ መከበር አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን አስታውቋል፡፡

በዓሉ በሚከበር ዕለት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥም እና አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ እንደሚሆኑም የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

በዚህም መሰረት፡-

• በቸርችል ጎዳና በቴዎድሮስ አደባባይ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ባንኮ ዲሮማ መብራት

• ከአራት ኪሎ በራስ መኮንን ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ራስ መኮንን ድልድይ

• ከመነን አካባቢ እና የካቲት 12 ሆስፒታል በአፍንጮ በር ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ አፍንጮ በር

• ከእሪ በከንቱ በኤሌክትሪክ ህንፃ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ደጎል አደባባይ

• ከአዲሱ ገበያ በሰሜን ሆቴል ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ሰሜን መብራት

• ከመርካቶ በአቡነ ጴጥሮስ ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ደጃዝማች ሀብተጊዮርጊስ ድልድይ

• ከእንቁላል ፋብሪካ በቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ዮሐንስ መብራት የሚወስዱት መንገዶች ከየካቲት 22 ቀን 2017 ዓ/ም ከምሽቱ 6፡00 ሠዓት ጀምሮ እስከ የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 7፡00 ሠዓት ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ ስለሚሆኑ አሽከርካሪዎች ይህንን ተገንዝበው አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ እና የትራፊክ ፖሊሶች የሚጠቁሟቸውን አማራጭ አቅጣጫዎችን በመጠቀም አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ህብረተሰቡም ማንኛውም አጠራጣሪ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ በ 011-1-11-01-11 ወይም በነፃ ስልክ መስመር 991 መጠቀም የሚቻል መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ይገልፃል።
#ሳኡዲ አረቢያ ታላቁ የረመዳን ጾም ነገ ቅዳሜ እንደሚጀምር አስታወቀች።

በሳኡዲ አረቢያ የቴሌስኮፕ ባለሙያዎች አዲስ የረመዳን ጨረቃ ማየታቸውን ገልጸዋል።

በዚህም በዛሬው ዕለት የተራዊህ ሶላት የሚጀመር ሲሆን በነገው ዕለት የረመዳን ጾም የሚጀመር ይሆናል።

¤ሀሩን ሚዲያ ለመላው ሙስሊም ማህበረሰብ እንኳን ለ1446ኛው ዓመተ ሂጅራ የረመዳን ጾም አደረሳችሁ ሲል መልካም ምኞቱን ይገልጻል።
👍4
የአሜሪካ የልማት እርዳታ ድርጅት በሺዎች የሚቆጠሩ ፕሮጀክቶችን ሲያቋርጥ፣ የሰብዓዊ ቀውስ ተባብሷል

በቀድሞው የትራምፕ አስተዳደር ትዕዛዝ፣ የአሜሪካ የልማት እርዳታ ድርጅት (USAID) በሺዎች የሚቆጠሩ የገንዘብ ድጋፍ ፕሮጀክቶችን አቋርጧል። ይህ ድርጊት የድርጅቱን 90% ስራዎች ያቋረጠ ሲሆን፣ ለተለያዩ አጋሮች የተላኩት የማቋረጫ ደብዳቤዎችም ከፍተኛ ቁጣን አስከትለዋል።

ብዙዎቹ ደብዳቤዎች "ውድ አጋር" በሚል የጀመሩ ሲሆን፣ "ከ USAID ጋር ስለሰሩ እና እግዚአብሔር አሜሪካን ይባርክ" በሚል ተጠናቀዋል። ይህ አጻጻፍ የተቋረጡት ፕሮጀክቶች ተጠቃሚዎችን እና አጋሮችን የበለጠ አሳዝኗል።

አንዳንድ አጋሮች ስራቸውን እንዲቀጥሉ ከ USAID ልዩ ፈቃድ አግኝተው የነበረ ቢሆንም፣ ባልተጠበቀ ሁኔታ የማቋረጫ ደብዳቤ ደርሷቸዋል። ይህ ድርጊት ከፍተኛ የስሜት መረበሽን ከመፍጠሩም በላይ፣ በእውነተኛ ህይወት ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አሳድሯል።

ለምሳሌ፣ "አላይት" የተባለው ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት በጦርነት በፈራረሰው ሱዳን ውስጥ ስድስት የህክምና ክሊኒኮችን ይደግፋል። ሰራተኞቹ በረሃብ አፋፍ ላይ ያሉ ህጻናትን ለማዳን የደም ሥር ፈሳሽ፣ ኦክስጅን እና ድንገተኛ ምግብ ይሰጣሉ።

የአላይት ዋና ስራ አስፈጻሚ ጆሴሊን ዋያት እንደገለጹት፣ በእነዚህ ማረጋጊያ ማዕከላት ውስጥ ከ15 እስከ 30 የሚደርሱ ህጻናት እና ሕፃናት በየጊዜው ይገኛሉ። እንክብካቤ ካላገኙ በ4 እስከ 8 ሰዓታት ውስጥ ህይወታቸውን ያጣሉ።

ጥፋቱ በሱዳን ብቻ የተወሰነ አይደለም። በዋሽንግተን ዲሲ፣ ከ USAID ትልልቅ አጋሮች አንዱ የሆነው ኬሞኒክስ፣ በድርጅቱ የገንዘብ ድጋፍ የሚደረግላቸው ሁሉም ፕሮግራሞቹ ተቋርጠዋል።

አንድ ምንጭ እንደገለጸው፣ የ USAID የ9.5 ቢሊዮን ዶላር ዓለም አቀፍ የጤና አቅርቦት ሰንሰለት ፕሮግራም ዋና ክፍሎች፣ የወባ፣ የእናቶች፣ የህጻናት እና የመራቢያ ጤና ጋር የተያያዙ እቃዎችን ማቅረብን ጨምሮ ተቋርጠዋል።

ስሙ እንዳይገለጽ የጠየቁ አንድ ዓለም አቀፍ የጤና መሪ እንደተናገሩት፣ "ዓላማው የእርዳታውን ዘርፍ ማፈን ነው። ተንኮል አዘልም ይሁን ብቃት በሌለው መንገድ ገንዘብ እንዳያገኝ ከከለከልነው፣ ያለው የአተገባበር መሠረተ ልማት ሁሉ ይሞታል።"

ማጠቃለያ፡

ይህ የ USAID ውሳኔ በአለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ የሆነ የሰብዓዊ ቀውስ እንደሚያስከትል እየተነገረ ነው። በተለይ በጦርነት እና በድህነት ለተጎዱ ሀገራት እርዳታው መቋረጡ ከፍተኛ ጉዳት ያስከትላል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዲስ ህግ

ከየካቲት 17 ጀምሮ ከንግድ ባንክ ስራ አስኪያጅ በተላከው ደብዳቤ መሰረት የባንኩ ቴለሮች/ገንዘብ ከፋዮች/ የባንኩን ደንበኞች ተቀማጭ ቀሪ ገንዘብ መጠን ማየት እንደማይችሉ ምንጮች ገልጸዋል።

ከዚህ ቀደም ውስጥ ለውስጥ እንደማይቻል እና ይወራ የነበረ ህግ ነበር አሁን መፅደቁን ሰምተናል።

የደንበኞችን ቀሪ ሂሳብ ማየት የሚችሉት ከፍተኛ ማኔጅሮች ብቻ ናቸው።

ባንኩ ይህን እርምጃ የወሰደው እየተንሰራፋ የሄደውን የገንዘብ ማጭበርበር ለከት ለማስያዝ እንደሆነ ተጠቁሟል።

Via: Ethiopian banking information
👍1
በአሜሪካ ውስጥ 616 የኢትዮጵያ ሬስቶራንቶች እንደሚገኙ አንድ ጥናት ገልጿል፡

በዚህ ጥናት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሬስቶራንቶች የሚገኙት በካሊፎርኒያ ግዛት ሲሆን ከሎስ አንጀለስ እስከ ቤይ ኤርያ ድረስ ባሉ ቦታዎች 88 የኢትዮጵያ ሬስቶራንቶች እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡

ይሁንና በርካታ ኢትዮጵያዊያን በሚኖሩበት ዋሽንግተን ዲሲ ያሉት ሬስቶራንቶች 33 መሆናቸውን ያስረዳው ጥናቱ ነገር ግን በቨርጂኒያ ሀምሳ እንዲሁም በሜሪላንድ አርባ ሬስቶራንቶች መኖራቸውን አስረድቷል፡፡

በቴክሳስ 55፣ በዋሽንግተን ግዛት 43፣ በጆርጂያና በኒውዮርክ 31 እንዲሁም በሚኒሶታ ደግሞ 30 የኢትዮጵያ ሬስቶራንቶች እንደሚገኙም አስታውቋል፡፡

በአሜሪካ ውስጥ የኢትዮጵያ ሬስቶራንቶች ከሌሉባቸው ግዛቶች መካከል ደግሞ አርካንሳስ፣ ዴላዌር፣ ኒው ሀምሻየር፣ ሮድ አይላንድና ሞንታና እንደሚገኙበት ጥናቱ አስረድቷል፡፡
የብሪታንያ መንግሥት፣ የዓለማቀፍ ዕርዳታ በጀቱን በከፍተኛ መጠን ሊቀንስ መኾኑን አስታውቋል

ብሪታንያ የውጭ ዕርዳታ በጀቷን ለመቀነስ የወሰነችው፣ የመከላከያ በጀቷን መጨመሯን ተከትሎ ነው። በአውሮፓዊያን 2023 ከአፍሪካ የብሪታንያን ከፍተኛ የውጭ እርዳታ በመቀበል ቀዳሚ ነበረች።

ኢትዮጵያ በተጠቀሰው ዓመት ከብሪታንያ 208 ሚሊዮን ዶላር የተቀበለች ሲኾን፣ ይህም ብሪታንያ ለዩክሬን ከሰጠችው እርዳታ ቀጥሎ በዓለም በከፍተኛነቱ ኹለተኛው ነበር። ከአፍሪካ የብሪታንያ ከፍተኛ የውጭ እርዳታ ተቀባዮች መካከል፣ ኬንያ፣ ሱማሊያ፣ ደቡብ ሱዳንና ሱዳን ጭምር ይገኙበታል።
ዘሌንስኪ “በዋይት ኃውስ ቆይታ ይቅርታ የሚያስጠይቅ ምንም ስህተት አልሰራንም” አሉ

የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮለድሚር ዘለንስኪ ከዶናልድ ትምፕ ጋርሀይለ ቃል የተቀላቀለበት ክርክር ከተለዋወጡ በኋላ ውይይቱ ተቋርጡ ከዋይት ኃውስ ሲወጡ ታይተዋል።

ከውይየቱ በኋላ ከፎክስ ኒውስ ጋር ቆይታ ያደረጉት ዘሌንስኪ ትምፕን ይቅርታ ይጠይቃሉ በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ “ትራምፕን የምጠይቀው ይቅርታ የለም” ብለዋል።

“ለአሜሪካ ፕሬዝዳንት እና ለአሜሪካ ህዝብ ክብር አለኝ” ያሉት ዘሌንስኪ፤ ከይቅርታ ጋር በተያያዘ ግን በጣም እዚህ ጋር በጣም ግልጽ እና ሐቀኛ መሆን ያለብን ይመስለኛል፣  ይቅርታ ሊያስጠይቅ የሚደረስ ምንም መጥፎ ነገር ያደረግን አይመስለኝም” ብለዋል።
የአውሮፓ ኢኮኖሚ ውድቀት፡ በራስ ላይ የተጫነ አደጋ

አሜሪካ፣ እንግሊዝ፣ ጣሊያን እና ፈረንሳይ የበጀት ጉድለት፣ የኢኮኖሚ መቀዛቀዝ እና የኢንዱስትሪ ውድቀት በመጋፈጥ የኪሳራ አዘቅት ላይ ይገኛሉ። ይህ በአብዛኛው የተከሰተው በሩሲያ ላይ በተጣሉ ማዕቀቦችን ጨምሮ በአጭር እይታ ፖሊሲዎች ምክንያት ነው።
አሃዞች እራሳቸውን ይናገራሉ።
አሜሪካ
🟠 የብሔራዊ ዕዳ፡ 36.22 ትሪሊዮን ዶላር አካባቢ
🟠 የፌዴራል በጀት ጉድለት፡ 1.9 ትሪሊዮን ዶላር (የኮንግረሱ የበጀት ቢሮ)
🟠 የኢኮኖሚ ዕድገት፡ በ2024 አራተኛ ሩብ ዓመት 2.3%
🟠 የኢኮኖሚ ውድቀት አደጋ፡ እስከ ህዳር 2025 ድረስ 29.4% ዕድል (የኒውዮርክ ፌዴራል ሪዘርቭ)
እንግሊዝ
🟠 የብሔራዊ ዕዳ፡ 2.91 ትሪሊዮን ዶላር አካባቢ
🟠 የዕዳ እና የሀገር ውስጥ ምርት ጥምርታ፡ በ2025 ወደ 104% ከፍ ሊል ይችላል
🟠 የኢኮኖሚ ዕድገት፡ በ2024 ዜሮ ዕድገት፣ በ2025 0.75% ዕድገት (የእንግሊዝ ባንክ)
ጀርመን
🟠 የመንግስት ዕዳ፡ 2.59 ትሪሊዮን ዶላር አካባቢ
🟠 የኢኮኖሚ አዝማሚያ፡ በ2024 የኢኮኖሚ ውድቀት፣ በ2025 መቀዛቀዝ (የኪኤል ተቋም)
🟠 የኢንዱስትሪ ምርት፡ በ2024 4.5% ቅናሽ
🟠 የማገገሚያ ትንበያዎች፡ ለ2025 ዜሮ ዕድገት (የጀርመን ኢንዱስትሪዎች ፌዴሬሽን)
ፈረንሳይ
🟠 የመንግስት ዕዳ፡ 3.43 ትሪሊዮን ዶላር (2024 ሶስተኛ ሩብ ዓመት)፣ ከሀገር ውስጥ ምርት 113.7%
🟠 የዕዳ ትንበያዎች፡ እስከ 2026 ድረስ ከሀገር ውስጥ ምርት 117% ሊደርስ ይችላል
🟠 የኢኮኖሚ መቀነስ፡ በ2024 አራተኛ ሩብ ዓመት -0.1%
ጣሊያን
🟠 የመንግስት ዕዳ፡ እስከ ህዳር 2024 ድረስ 3.12 ትሪሊዮን ዶላር
🟠 የኢኮኖሚ ዕድገት፡ በ2024 አራተኛ ሩብ ዓመት ዜሮ ዕድገት፣ በ2025 0.8% ዕድገት
🟠 የኢንዱስትሪ ምርት፡ በታህሳስ 2024 3.1% ቀንሷል

Sputnik
የአስመራው ጥምረት ከፈረሰ በኋላ ግብፅ እና ኤርትራ ወሳኙን ውይይት አካሄዱ!

የግብፁ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ባድር አብደላቲ ከኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በአስመራ ተገናኝተው በሶማሊያ፣ በሱዳን፣ በሊቢያ እና በቀይ ባህር ያለውን ሁኔታ ጨምሮ በክልሉ ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ ተወያይተዋል።

ስብሰባው ቀደም ሲል የአስመራው ጥምረት አካል የነበረችው ሶማሊያ ሳትገኝ የተካሄደ ሲሆን፣ ሶማሊያ ከአሁን በኋላ አቋሟን በመቀየር ከኢትዮጵያ ጋር መቀራረብን መርጣለች።

የሶማሊያ አዲስ አሰላለፍ በክልሉ ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ላይ ከፍተኛ ለውጥ ያመጣ ሲሆን፣ ግብፅ እና ኤርትራ ስትራቴጂካዊ ቅንጅታቸውን እንደገና እንዲያጤኑ አስገድዷቸዋል።
👍1
Due to Ilhan Omar's malign influence on the weak Biden-Harris administration, Somalian regime has been receiving $1.2 billion annually from U.S. taxpayers.

Trump should investigate this funding and demand that Somalian regime reimburse the money it fraudulently obtained through Omar's sway over the Biden administration.
Source : inside Africa
ደም መፍሰስ የሚያስከትለው አዲሱ ወረርሽኝ አሁንም መነሻው አልተለየም
****
በኮንጎ ኪንሻሣ ምንነቱ በውል ያልተለየው ሰውነት ደም መፍሰስ አስከታይ ወረርሽኝ አሁንም ድረስ መነሻ ምክንያት አልተለየም ተባለ፡፡

ወረርሽኙ በአገሪቱ ሰሜናዊ ምዕራብ ክፍል 5 መንደሮች ከ60 ያላነሱ ሰዎችን እንደገደለ አሶሼትድ ፕሬስን ዋቢ አርጎ ሸገር ኤፍኤም ዘግቧል፡፡

የአለም የጤና ድርጅት የአፍሪካ ቅርንጫፍ ወረርሽኙ በውሃ መበከል ምክንያት የመጣ ሳይሆን አይቀርም ማለቱ ተሰምቷል ያለው ዘገባው ይሄም ገና ከመላ ምት ያልዘለለ ነው መባሉን ጠቁሟል፡፡

ከ1 ሺህ በላይ ሰዎች በበሽታው ተይዘው እንደሚገኙ የተገለጸወው ይሄው ያልታወቀ ወረርሽኝ ከሰውነት ደም መፍሰስ አስከታይነቱ በተጨማሪ ከፍተኛ ትኩሳት ፣ የራስ ምታት የጡንቻ መዛል እና የመሳሰሉ ምልክቶችን ያሳያል ተብሏል፡፡

ከኢቦላ እና ማርበርግ ጋር ተመሳሳይ ምልክቶችን ያሳያል ይሁንና ኢቦላም ማርበርግም እንዳልሆነ እየተነገረም ነው ተብሏል፡፡
ግብፅ ኢትዮጵያ የባህር ሃይል እንድታቋቁም አልፈቅድም አለች

ወደብ አልባ የሆነችው ኢትዮጵያ በቀይ ባህር የራሷን ወደብ ለማግኘት እና የባህር ሀይል ለመቋቋም እንቅስቃሴ ላይ እንደምትገኝ ይታወቃል።

ግብጽ የቀይ ባህር አካል ያልሆነ ማንኛውም ሀገር በባህሩ ዙሪያ የሚያደርገውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ እና የባህር ሀይል ለማቋቋም የሚደረግ ጥረት እንደማትቀበል አስታወቀች፡፡

ይህ የተባለው በግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብዳላቲ የተመራ ልዑክ በኤርትራ ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ውይይት ማድረጉን ተከትሎ ነው፡፡

በውይይቱ ሁለቱ ሀገራት የቀይ ባህርን ጨምሮ የጋራ በሚያደርጓቸው ቀጠናዊ እና በተለያዩ መስኮች የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን ለማጠናከር ተስማተዋል፡፡

የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር “የቀይ ባህር ደህንነት በተዋሳኝ ሀገራቱ ፍላጎት ላይ ብቻ የተመሰረተ ነው ፤ምንም አይነት ወታደራዊም ሆነ የባህር ሃይል በአካባቢው መገኘትን አንፈቅድም” ብለዋል።

አክለውም “ወደብ አልባ ሀገራት በቀይ ባህር ዙሪያ የባህር ሀይል ማቋቋም የቀጠናውን እና የባህሩን ደህንነት ለመጠበቅ የተደረሰውን ስምምነት ክፉኛ የሚጎዳ ነው” ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መግለጫ እንዳስታወቀው አብዳላቲ ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጋር ባደረጉት ውይይት፤ በአህጉራዊ የጋራ ጉዳዮች በተለይም በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ሰላምና ደህንነትን መደገፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ፣ በሶማሊያ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት እና ሉዓላዊነቷን በሁሉም ግዛቶቿ ላይ ለማስረፅ የሚያስችል የሃሳብ ልውውጥ ተካሂዷል።
ስብሰባው በሊቢያ እና በአፍሪካ ሳህል አካባቢ ስላለው ሁኔታ እንዲሁም በቀይ ባህር ውስጥ ያሉ ለውጦች እና ማንኛውም ቀይ ባህር አካል ያልሆነ መንግስት በፀጥታ እና በአስተዳደር ውስጥ ተሳትፎን ውድቅ በማድረግ ላይ ትኩረቱን አድርጓል ።

በተጨማሪም በጥቅምት 2024 በኤርትራ ከተካሄደው የመጀመሪያው የመሪዎች ጉባኤ በኋላ ተመሳሳይ የሚኒስትሮች ስብሰባዎችን በሞቃዲሾ እና በአስመራ ለማካሄድ እና በቅርቡ ለሁለተኛው የፕሬዝዳንት ጉባኤ ለመዘጋጀት መምከራቸውን አብዳላቲ ጠቁመዋል።

የኤርትራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ በበኩሉ ትላንት ምሽት ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብዳላቲ ከተመራ ልዑካን ጋር በቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይቶች ማድረጋቸውን አስታውቋል፡፡

በሱዳን ሶማሊያ እና በአጠቃላይ በአፍሪካ ቀንድ እንዲሁም በቀይ ባህር አካባቢዎች የሰላም እና የደህንነት ፈተናዎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ውይይት መካሄዱንም መግለጫው አክሏል፡፡
👍31
ከአዲግራት ከተማ አቅራቢያ በሬክተር ስኬል 5.2 የተለካ ርዕደ መሬት ተከሰተ

ዛሬ እሁድ ከአዲግራት ከተማ 46 ኪሎ ሜትር በስተምስራቅ ርቀት ላይ በሚገኝ አካባቢ ላይ በሬክተር ስኬል 5.2 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ መስሪያ ቤት ገለጸ። ርዕደ መሬቱ የተከሰተው ከቀኑ 5 ሰዓት ከ14 ደቂቃ ላይ መሆኑንም መስሪያ ቤቱ አስታውቋል።

በኢትዮጵያ በአፋር ክልል ባሉ አካባቢዎች ካለፈው መስከረም ወር ጀምሮ ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ቢከሰትም፤ በትግራይ ክልል ከተሞች አቅራቢያ ርዕደ መሬት ሲመዘገብ ግን በዚህ ዓመት የመጀመሪያው ነው። የዛሬው የመሬት መንቀጥቀጥ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ድንበር ቀጠና የተከሰተ መሆኑን የጠቆመው የአውሮፓ ሜዲትራንያን ሴይስሞሎጂ ማዕከል (EMSC)፤ መጠኑም በሬክተር ስኬል 5.3 የተለካ እንደሆነ አስታውቋል።

በኤርትራ ከአንድ ሳምንት በፊት የደረሰ ርዕደ መሬት በሬክተር ስኬል 4.6 ሆኖ ተመዝግቧል። የመሬት መንቀጥቀጡ የተከሰተው በቀይ ባህር ሰሜናዊ አቅጣጫ ከአስመራ 24 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ባለ አካባቢ ነበር። በሀገሪቱ ባለፈው ታህሳስ ወር አጋማሽም እንዲሁ ተመሳሳይ ርዕደ መሬት ተመዝግቧል።

በሐምሌ 2015 ዓ.ም. በኤርትራ ባህር ዳርቻ ዳህላክ ደሴት አካባቢ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ፤ በትግራይ ክልል የተለያዩ ከተሞች ተደጋጋሚ ንዝረቶች አስከትሎ እንደነበር ይታወሳል። ንዝረቱን በሽሬ፣ አዲግራት፣ አድዋ፣ አክሱም እና መቐለ ከተማ ያሉ ነዋሪዎች መስማታቸውን በወቅቱ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ገልጸው ነበር። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
2👍1
2025/07/13 18:47:52
Back to Top
HTML Embed Code: