በሟች ወ/ሪት ቀነኒ አዱኛ ዋቆ አሟሟት ዙሪያ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ
በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው ሰንሻይን ቤቶች ፊት ለፊት ከሚገኘው ውዳሴ ህንፃ ላይ ነዋሪ የነበረችው ሟች ወ/ሮ ቀነኒ አዱኛ ዋቆ መጋቢት 01 ቀን 2017 ዓ/ም ከሌሊቱ 10፡00 ሠዓት አካባቢ ከቤቷ የማብሰያ ክፍል በኩል ካለው በረንዳ 5ኛ ፎቅ ላይ ለጊዜው ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ወድቃ ለህክምና እርዳታ ወደ ያኔት ሆስፒታል እየተወሰደች ባለበት ወቅት ህይወቷ አልፏል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ መረጃው ከደረሰው በኋላ የምርመራ ቡድን በማዋቀርና ቦታው ድረስ በመሄድ ተገቢውን የቴክኒክና የታክቲክ መረጃዎችን ያሰባሰበ ሲሆን የሟችንም አስከሬን ወደ ዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል ለተጨማሪ ምርመራ እንዲሄድ አድርጓል፡፡
ሟች ወ/ሮ ቀነኒ አዱኛ በወቅቱ ከበረዳ ላይ በወደቀችበት ሰዓት ፖሊስ በቤቱ ውስጥ የነበረውን ባለቤቷን ድምፃዊ አንዷለም ጎሳን በቁጥጥር ስር በማዋልም ምርመራ እያጣራ ሲሆን በቀጣይ የመጨረሻውን የምርመራ ውጤትም ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ እያስታወቀ በተለያዩ ማህበራዊ ድረ ገጾች ላይ ከፖሊስ የወንጀል ምርመራ ውጤት በፊት የሚናፈሱ መረጃዎች ተገቢነት የሌላቸው ከመሆኑም ባሻገር በምርምራ ሒደቱ ላይ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተፅህኖ በመገንዘብ የተሳሳተ መረጃ የሚያስተላልፉ እና የሚያሰራጩ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳስቧል፡፡
*
ዘገባ፦ ረ/ኢንስፔክተር ዳዊት እርገጤ
በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው ሰንሻይን ቤቶች ፊት ለፊት ከሚገኘው ውዳሴ ህንፃ ላይ ነዋሪ የነበረችው ሟች ወ/ሮ ቀነኒ አዱኛ ዋቆ መጋቢት 01 ቀን 2017 ዓ/ም ከሌሊቱ 10፡00 ሠዓት አካባቢ ከቤቷ የማብሰያ ክፍል በኩል ካለው በረንዳ 5ኛ ፎቅ ላይ ለጊዜው ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ወድቃ ለህክምና እርዳታ ወደ ያኔት ሆስፒታል እየተወሰደች ባለበት ወቅት ህይወቷ አልፏል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ መረጃው ከደረሰው በኋላ የምርመራ ቡድን በማዋቀርና ቦታው ድረስ በመሄድ ተገቢውን የቴክኒክና የታክቲክ መረጃዎችን ያሰባሰበ ሲሆን የሟችንም አስከሬን ወደ ዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል ለተጨማሪ ምርመራ እንዲሄድ አድርጓል፡፡
ሟች ወ/ሮ ቀነኒ አዱኛ በወቅቱ ከበረዳ ላይ በወደቀችበት ሰዓት ፖሊስ በቤቱ ውስጥ የነበረውን ባለቤቷን ድምፃዊ አንዷለም ጎሳን በቁጥጥር ስር በማዋልም ምርመራ እያጣራ ሲሆን በቀጣይ የመጨረሻውን የምርመራ ውጤትም ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ እያስታወቀ በተለያዩ ማህበራዊ ድረ ገጾች ላይ ከፖሊስ የወንጀል ምርመራ ውጤት በፊት የሚናፈሱ መረጃዎች ተገቢነት የሌላቸው ከመሆኑም ባሻገር በምርምራ ሒደቱ ላይ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተፅህኖ በመገንዘብ የተሳሳተ መረጃ የሚያስተላልፉ እና የሚያሰራጩ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳስቧል፡፡
*
ዘገባ፦ ረ/ኢንስፔክተር ዳዊት እርገጤ
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን "ታኪሎ ኢንቨስትመንት ባንክ" ሕገ-ወጥ ነዉ ሲል አስጠነቀቀ
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን "ታኪሎ ኢንቨስትመንት ባንክ" በሚል ስም የሚንቀሳቀስ አካል ያለ ምንም ህጋዊ ፈቃድ የኢንቨስትመንት አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አሳውቋል።
ባለስልጣኑ ይህ አካል የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ባንክ ነኝ ብሎ ድረ-ገጽ ከፍቶ ማስተዋወቁን ገልጿል።
ባለስልጣኑ ባወጣው መግለጫ መሰረት ታኪሎ ኢንቨስትመንት ባንክ በካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አሰጣጥና ቁጥጥር መመሪያ ቁጥር 980/2016 መሰረት ፈቃድ ሳያገኝ አገልግሎት እየሰጠ ነው። በዚህም ምክንያት በኢትዮጵያ ውስጥ የካፒታል ገበያ አገልግሎት እንዲሰጥ ያልተፈቀደለት አካል መሆኑን አሳስቧል።
በተጨማሪም ባለስልጣኑ የካፒታል ገበያ አገልግሎት መስጠት የሚችሉት በህጋዊ መንገድ የተመዘገቡና ፈቃድ ያላቸው አካላት ብቻ መሆናቸውን አስገንዝቧል። ግለሰቦች እና ድርጅቶች ከዚህ አካል ወይም ከሌሎች ፈቃድ ከሌላቸው "የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች" ጋር ማንኛውም አይነት የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ አሳስቧል።
Capital
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን "ታኪሎ ኢንቨስትመንት ባንክ" በሚል ስም የሚንቀሳቀስ አካል ያለ ምንም ህጋዊ ፈቃድ የኢንቨስትመንት አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አሳውቋል።
ባለስልጣኑ ይህ አካል የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ባንክ ነኝ ብሎ ድረ-ገጽ ከፍቶ ማስተዋወቁን ገልጿል።
ባለስልጣኑ ባወጣው መግለጫ መሰረት ታኪሎ ኢንቨስትመንት ባንክ በካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አሰጣጥና ቁጥጥር መመሪያ ቁጥር 980/2016 መሰረት ፈቃድ ሳያገኝ አገልግሎት እየሰጠ ነው። በዚህም ምክንያት በኢትዮጵያ ውስጥ የካፒታል ገበያ አገልግሎት እንዲሰጥ ያልተፈቀደለት አካል መሆኑን አሳስቧል።
በተጨማሪም ባለስልጣኑ የካፒታል ገበያ አገልግሎት መስጠት የሚችሉት በህጋዊ መንገድ የተመዘገቡና ፈቃድ ያላቸው አካላት ብቻ መሆናቸውን አስገንዝቧል። ግለሰቦች እና ድርጅቶች ከዚህ አካል ወይም ከሌሎች ፈቃድ ከሌላቸው "የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች" ጋር ማንኛውም አይነት የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ አሳስቧል።
Capital
"የፌደራል መንግስት የትግራይ ህዝብ ዳግም ወደ እልቂት ሲገባ ዝም ብሎ ሊመለከት አይገባም" ሲል የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አስታወቀ
👉 አስተዳደሩ ፌደራል መንግስት አስፈላጊውን እርዳታ እንዲያደርግም ጠይቋል
የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር በትግራይ ክልል ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ በማስመልከት ዛሬ ረፋድ መግለጫ አውጥቷል። አስተዳደሩ የትግራይ ጦር አዛዦች ከተልኮ ወጭ የአንድ ጠባብ ቡድን የስልጣን ጥም ለማርካት በማለት ግልፅ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ እየተንቀሳቀሱ ቆይተዋል ያለ ሲሆን በዚህ ሳምንትም በተመሳሳይ በሰሜን ምስራቅና በደቡብ ግንባር አዛዦች እንቅስቃሴው በከፋ ሁኔታ ተባብሶ ቀጥሏል ማለቱን ዳጉ ጆርናል ከመግለጫው ተመልክቷል።
አስተዳደሩ በመግለጫው ይህንን አደገኛ እንቅስቃሴ እንዲያስቆም ለአጠቃላይ ጦር አዛዡ ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ ትእዛዝ ቢሰጥም የጥፋት ድርጊቱ ማስቆም እንዳልቻለ አስታውቋል።
የጥፋት ድርጊቶቹ ተባብሰው በቀጠሉበት በአሁኑ ሰዓት በስቪሎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እየተፈፀመ መሆኑንና ከላይ እስከታች ያለውን የመንግስት መዋቅር የማፍረስ እንቅስቃሴዎች ቀጥለዋል ማለቱንም ዳጉ ጆርናል ሰምቷል።
ጊዜያዊ አስተዳደሩ በመግለጫው የትግራይ ጦር የበላይ አዛዦች የኃላ ቀሩን ቡዱን ፍላጎት ለማሟላት ሲሉ መንግስት እንዲፈርስ እንዲሁም የፕሪቶርያ ስምምነት በይፋ እንዲጣስ በማድረግ የትግራይን ህዝብ ዳግም ወደ ጦርነት እያስገቡት ነውም ብሏል።
አስተዳደሩ በመጨረሻም " የፌደራል መንግስት በትግራይ የፀጥታ ሀይል ስም የሚንቀሳቀሱት አዛዦች የአንድ ኃላቀርና ወንጀለኛ ቡዱን ተላላኪዎች እንጂ የትግራይ ህዝብና ጊዝያዊ አስተዳደሩን እንደማይወክሉ በመረዳት አስፈላጊ እርዳት ማድረግ አለበት" ብሏል። ከዚህ ባሻገር የፕሪቶርያ ስምምነት እንዲ በይፋ ሲፈርስና የትግራይ ህዝብ ዳግም ወደ እልቂት ሲገባ ዝም ብሎ ሊመለከት አይገባም ሲል የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር ዛሬ ረፋድ ባወጣው መግለጫ አስታዉቋል።
#ዳጉ_ጆርናል
👉 አስተዳደሩ ፌደራል መንግስት አስፈላጊውን እርዳታ እንዲያደርግም ጠይቋል
የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር በትግራይ ክልል ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ በማስመልከት ዛሬ ረፋድ መግለጫ አውጥቷል። አስተዳደሩ የትግራይ ጦር አዛዦች ከተልኮ ወጭ የአንድ ጠባብ ቡድን የስልጣን ጥም ለማርካት በማለት ግልፅ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ እየተንቀሳቀሱ ቆይተዋል ያለ ሲሆን በዚህ ሳምንትም በተመሳሳይ በሰሜን ምስራቅና በደቡብ ግንባር አዛዦች እንቅስቃሴው በከፋ ሁኔታ ተባብሶ ቀጥሏል ማለቱን ዳጉ ጆርናል ከመግለጫው ተመልክቷል።
አስተዳደሩ በመግለጫው ይህንን አደገኛ እንቅስቃሴ እንዲያስቆም ለአጠቃላይ ጦር አዛዡ ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ ትእዛዝ ቢሰጥም የጥፋት ድርጊቱ ማስቆም እንዳልቻለ አስታውቋል።
የጥፋት ድርጊቶቹ ተባብሰው በቀጠሉበት በአሁኑ ሰዓት በስቪሎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እየተፈፀመ መሆኑንና ከላይ እስከታች ያለውን የመንግስት መዋቅር የማፍረስ እንቅስቃሴዎች ቀጥለዋል ማለቱንም ዳጉ ጆርናል ሰምቷል።
ጊዜያዊ አስተዳደሩ በመግለጫው የትግራይ ጦር የበላይ አዛዦች የኃላ ቀሩን ቡዱን ፍላጎት ለማሟላት ሲሉ መንግስት እንዲፈርስ እንዲሁም የፕሪቶርያ ስምምነት በይፋ እንዲጣስ በማድረግ የትግራይን ህዝብ ዳግም ወደ ጦርነት እያስገቡት ነውም ብሏል።
አስተዳደሩ በመጨረሻም " የፌደራል መንግስት በትግራይ የፀጥታ ሀይል ስም የሚንቀሳቀሱት አዛዦች የአንድ ኃላቀርና ወንጀለኛ ቡዱን ተላላኪዎች እንጂ የትግራይ ህዝብና ጊዝያዊ አስተዳደሩን እንደማይወክሉ በመረዳት አስፈላጊ እርዳት ማድረግ አለበት" ብሏል። ከዚህ ባሻገር የፕሪቶርያ ስምምነት እንዲ በይፋ ሲፈርስና የትግራይ ህዝብ ዳግም ወደ እልቂት ሲገባ ዝም ብሎ ሊመለከት አይገባም ሲል የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር ዛሬ ረፋድ ባወጣው መግለጫ አስታዉቋል።
#ዳጉ_ጆርናል
👍2
" ለሦስት ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነው ሁኔታ የተፈጠረው ' የፍቅር ጥያቄዬ ምላሽ አላገኘም ' በሚል ነው " - ፖሊስ
በአዲስ አበባ ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስድስት ካርል አደባባይ አካባቢ በሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ አንድ ግለሰብ ሁለት ሰዎችን ገድሎ ራሱን እንዳጠፋ የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ አማርኛ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?
" ክስተቱ ያጋጠመው ትናንት ማክሰኞ መጋቢት 02/2017 ዓ.ም. ጠዋት ከአንድ ሰዓት ተኩል እስከ ለሁለት ሰዓት ሩብ ጉዳይ ድረስ ባላው ጊዜ ውስጥ ነው።
ለሦስት ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነው ሁኔታ የተፈጠረው ' የፍቅር ጥያቄዬ ምላሽ አላገኘም ' በሚል ምክንያት ነው።
አቶ ሽፈራው ረጋሳ የተባለ የባንኩ የጥበቃ ሠራተኛ ለሥራ ባልደረባው የፍቅር ጥያቄ አቅርቦላት ምላሽ ባለማግኘቱ ግለሰቧን እና ከግለሰቧ ጋር የፍቅር ግንኙነት አለው በሚል የጠረጠረውን ሌላ ባልደረባውን በመግደል ራሱን አጥፍቷል።
ግለሰቡ የፍቅር ጥያቄ ያቀረበላት ወይዘሪት ሃና ተስፋዬ የተባለች 32 ዓመት ወጣት እና አቶ ንጉሤ ብርሃኑ የተባለ የሥራ ባልደረቦቹን ነው በጥይት ተኩሶ የገደለው።
ወንጀሉን የፈፀመው የጥበቃ ሠራተኛ ካልተራው ሌላ ሠራተኛን ተክቶ በመግባት እና ከምሽት የጥበቃ ሠራተኞች የጦር መሳሪያ በመቀበል ነው ግድያውን የፈጸመው።
ግለሰቡ ግድያውን የፈጸመው ወደ ዕለታዊ ሥራቸው እስኪገቡ ድረስ በመጠበቅ ነው።
መጀመሪያ አቶ ንጉሤ ብርሃኑ የተባለውን ግለሰብ በሁለት ጥይት መትቶ ገድሏል።
ባልደረባውን ተኩሶ ከገደለ በኋላ ሌላኛዋን የጥቃቱ ሰለባን ከመግደሉ በፊት ከድርጊቱ እንዲቆጠብ መጠየቁን ነገር ግን ፈቃደኛ አልነበረም።
ግለሰቡ መሳሪያውን እንዲያስቀምጥ እና እጁን እንዲሰጥ በተደጋጋሚ ጥያቄ ቀርቦለት የነበረ ሲሆን፣ በዚህ መካከልም ወደ ባንኩ አንደኛ ፎቅ በማምራት የፍቅር ጥያቄውን አልተቀበለችም ያላትን በተመሳሳይ ሁኔታ በጥይት መትቶ ገድሏል።
በሁለቱ ግድያዎች መካከል እስከ 15 ደቂቃ የሚሆን የጊዜ ክፍተት ነበር።
ግለሰቡ ሁለቱን ባልደረቦቹን ከገደለ በኋላ በያዘው መሳሪያ የእራሱንም ሕይወት አጥፍቷል።
በክስተቱ በአጠቃላይ የሦስት ሰዎች ሕይወት ጠፍቷል።
ሁለቱ ሟቾች ወ/ሪት ሃና ተስፋዬ እና አቶ ንጉሤ ብርሃኑ የፍቅር ግንኙነት እንደነበራቸው የሚጠቁም ፎቶግራፎች ተገኝተዋል። ፖሊስ በምርመራው ስለግንኙነታቸው ያጣራል።
ከዚሁ ክስተት ጋር በተያያዘ ፖሊስ እያካሄደ ያለውን የምርመራ ሂደት ይቀጥላል። "
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው።
#tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስድስት ካርል አደባባይ አካባቢ በሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ አንድ ግለሰብ ሁለት ሰዎችን ገድሎ ራሱን እንዳጠፋ የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ለቢቢሲ አማርኛ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?
" ክስተቱ ያጋጠመው ትናንት ማክሰኞ መጋቢት 02/2017 ዓ.ም. ጠዋት ከአንድ ሰዓት ተኩል እስከ ለሁለት ሰዓት ሩብ ጉዳይ ድረስ ባላው ጊዜ ውስጥ ነው።
ለሦስት ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነው ሁኔታ የተፈጠረው ' የፍቅር ጥያቄዬ ምላሽ አላገኘም ' በሚል ምክንያት ነው።
አቶ ሽፈራው ረጋሳ የተባለ የባንኩ የጥበቃ ሠራተኛ ለሥራ ባልደረባው የፍቅር ጥያቄ አቅርቦላት ምላሽ ባለማግኘቱ ግለሰቧን እና ከግለሰቧ ጋር የፍቅር ግንኙነት አለው በሚል የጠረጠረውን ሌላ ባልደረባውን በመግደል ራሱን አጥፍቷል።
ግለሰቡ የፍቅር ጥያቄ ያቀረበላት ወይዘሪት ሃና ተስፋዬ የተባለች 32 ዓመት ወጣት እና አቶ ንጉሤ ብርሃኑ የተባለ የሥራ ባልደረቦቹን ነው በጥይት ተኩሶ የገደለው።
ወንጀሉን የፈፀመው የጥበቃ ሠራተኛ ካልተራው ሌላ ሠራተኛን ተክቶ በመግባት እና ከምሽት የጥበቃ ሠራተኞች የጦር መሳሪያ በመቀበል ነው ግድያውን የፈጸመው።
ግለሰቡ ግድያውን የፈጸመው ወደ ዕለታዊ ሥራቸው እስኪገቡ ድረስ በመጠበቅ ነው።
መጀመሪያ አቶ ንጉሤ ብርሃኑ የተባለውን ግለሰብ በሁለት ጥይት መትቶ ገድሏል።
ባልደረባውን ተኩሶ ከገደለ በኋላ ሌላኛዋን የጥቃቱ ሰለባን ከመግደሉ በፊት ከድርጊቱ እንዲቆጠብ መጠየቁን ነገር ግን ፈቃደኛ አልነበረም።
ግለሰቡ መሳሪያውን እንዲያስቀምጥ እና እጁን እንዲሰጥ በተደጋጋሚ ጥያቄ ቀርቦለት የነበረ ሲሆን፣ በዚህ መካከልም ወደ ባንኩ አንደኛ ፎቅ በማምራት የፍቅር ጥያቄውን አልተቀበለችም ያላትን በተመሳሳይ ሁኔታ በጥይት መትቶ ገድሏል።
በሁለቱ ግድያዎች መካከል እስከ 15 ደቂቃ የሚሆን የጊዜ ክፍተት ነበር።
ግለሰቡ ሁለቱን ባልደረቦቹን ከገደለ በኋላ በያዘው መሳሪያ የእራሱንም ሕይወት አጥፍቷል።
በክስተቱ በአጠቃላይ የሦስት ሰዎች ሕይወት ጠፍቷል።
ሁለቱ ሟቾች ወ/ሪት ሃና ተስፋዬ እና አቶ ንጉሤ ብርሃኑ የፍቅር ግንኙነት እንደነበራቸው የሚጠቁም ፎቶግራፎች ተገኝተዋል። ፖሊስ በምርመራው ስለግንኙነታቸው ያጣራል።
ከዚሁ ክስተት ጋር በተያያዘ ፖሊስ እያካሄደ ያለውን የምርመራ ሂደት ይቀጥላል። "
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው።
#tikvahethiopia
👍2
የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ በክልሉ ወቅታው ሁኔታ ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ
የፌድራል መንግስት ጣልቃ እንዲገባ ያቀረብነው ህጋዊ ጥያቄ የለም፣
ጊዜዊ አስተዳደሩ በፌድራል መንግስትና በህውሃት መካከል በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት የተቋቋመ ነው፣
የፌድራል መንግስቱ በራሱ ፍቃድ የተቋቋመውን መንግስት አደጋ ላይ በሚወድቅበት ጊዜ አደጋውን የመቀልበስ ግዴታ ይኖርበታል፣
አሁን ባለው የትግራይ ሁኔታ ተስብስቦ ጥያቄ ሊያቀርብ የሚችል ምክር ቤት የለም፣
በአሁኑ ሰዓት ትግራይ ውስጥ እየተፈጠረ ያለው ቀውስ የህግ ተቀባይነትን ያጣ አንድ የህውሃት አንጃ ደጋፊ የሚላቸውን የተወሰኑ ከፍተኛ መኮንኖች በመያዝ እየሰራ ነው፣
ሂደቱን ሥርዓት ለማስያዝ በሚደረጉ እንቅስቃሴ ውስጥ ጊዜዊ አስተዳደሩ ውስጡ ያለውን አቅም ለመጠቀም የሚያስችለው እድልን እየተነፈገ መቷል፡፡
የፌድራል መንግስት አግባብነት ያለው እርምጃዎችን መውሰድ አለበት ስንል ጦር አዝምቶ ጦርነት ይቀስቅስ እያልን አይደለም፡፡
የፌድራል መንግስት ወደ ጦርነት ለማስኬት የሚያዣብብ ሂደትን ለማስቆም የሚያስችል ሁሉንም አይነት እርምጃ መውሰድ አለበት ብለን እናምናለን፡፡
እኔ እንደ ጊዜዊ አስተዳደሩ ዋናወቅ ራስ ምታቴ በአንድም በሌላም መንገድ ትግራይ ውስጥ ሌላ ጦርነት ተከፍቶ ህዝባችን ወደ መከራ የሚገባበትን ሁኔታ ማስቀረት እንጂ እንግጠም ብሎ መሟገት አይደለም፡፡
እንግጠም ያለ ያለን ኃይል አደብ ለማስገዛት ለፌድራል መንግስቱ የኔ ግብዣ ያስፈልገዋል የሚል እምነት የለኝም፡፡ምክንያቱም ጉዜዊ አስተዳደሩ የፌድራል መንግስት ውሳኔ አካል ነው፡፡
በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት አንድ ሰራዊት ነው በክልሉ መኖር ያለበት፡፡ነገር ግን እጅግ ግዙፍ የሠራዊት አቅም በትግራይ ክልል ውስጥ አለ፡፡
የሰራዊት አቅሙ በሙሉ አይደለም አሁን ወደ ጥፋት እንቅስቃሴ ውስጥ የገባው በተወሰነ ደረጃ ጉባኤ አድርጌለው ከሚለው ቡድን ጋር የጥቅም ቁርኝት አለን የሚሉ የተወሰኑ ኃይል የመረበሽ እንቅስቃሴ ውስጥ ገብቷል፡፡
ፌድራል መንግስት በቂ የሚለውን ድጋፍ መስጠት አለበት የሚል እምነት አለን፡፡
የፌድራል ምንግስት በትግራይ ክልል ያሉ የመከላከያ ካምፖችን ለመረከብ የኔ ጥሪ አያስፈልገውም ፡፡
የፌድራል መንግስት ጣልቃ እንዲገባ ያቀረብነው ህጋዊ ጥያቄ የለም፣
ጊዜዊ አስተዳደሩ በፌድራል መንግስትና በህውሃት መካከል በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት የተቋቋመ ነው፣
የፌድራል መንግስቱ በራሱ ፍቃድ የተቋቋመውን መንግስት አደጋ ላይ በሚወድቅበት ጊዜ አደጋውን የመቀልበስ ግዴታ ይኖርበታል፣
አሁን ባለው የትግራይ ሁኔታ ተስብስቦ ጥያቄ ሊያቀርብ የሚችል ምክር ቤት የለም፣
በአሁኑ ሰዓት ትግራይ ውስጥ እየተፈጠረ ያለው ቀውስ የህግ ተቀባይነትን ያጣ አንድ የህውሃት አንጃ ደጋፊ የሚላቸውን የተወሰኑ ከፍተኛ መኮንኖች በመያዝ እየሰራ ነው፣
ሂደቱን ሥርዓት ለማስያዝ በሚደረጉ እንቅስቃሴ ውስጥ ጊዜዊ አስተዳደሩ ውስጡ ያለውን አቅም ለመጠቀም የሚያስችለው እድልን እየተነፈገ መቷል፡፡
የፌድራል መንግስት አግባብነት ያለው እርምጃዎችን መውሰድ አለበት ስንል ጦር አዝምቶ ጦርነት ይቀስቅስ እያልን አይደለም፡፡
የፌድራል መንግስት ወደ ጦርነት ለማስኬት የሚያዣብብ ሂደትን ለማስቆም የሚያስችል ሁሉንም አይነት እርምጃ መውሰድ አለበት ብለን እናምናለን፡፡
እኔ እንደ ጊዜዊ አስተዳደሩ ዋናወቅ ራስ ምታቴ በአንድም በሌላም መንገድ ትግራይ ውስጥ ሌላ ጦርነት ተከፍቶ ህዝባችን ወደ መከራ የሚገባበትን ሁኔታ ማስቀረት እንጂ እንግጠም ብሎ መሟገት አይደለም፡፡
እንግጠም ያለ ያለን ኃይል አደብ ለማስገዛት ለፌድራል መንግስቱ የኔ ግብዣ ያስፈልገዋል የሚል እምነት የለኝም፡፡ምክንያቱም ጉዜዊ አስተዳደሩ የፌድራል መንግስት ውሳኔ አካል ነው፡፡
በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት አንድ ሰራዊት ነው በክልሉ መኖር ያለበት፡፡ነገር ግን እጅግ ግዙፍ የሠራዊት አቅም በትግራይ ክልል ውስጥ አለ፡፡
የሰራዊት አቅሙ በሙሉ አይደለም አሁን ወደ ጥፋት እንቅስቃሴ ውስጥ የገባው በተወሰነ ደረጃ ጉባኤ አድርጌለው ከሚለው ቡድን ጋር የጥቅም ቁርኝት አለን የሚሉ የተወሰኑ ኃይል የመረበሽ እንቅስቃሴ ውስጥ ገብቷል፡፡
ፌድራል መንግስት በቂ የሚለውን ድጋፍ መስጠት አለበት የሚል እምነት አለን፡፡
የፌድራል ምንግስት በትግራይ ክልል ያሉ የመከላከያ ካምፖችን ለመረከብ የኔ ጥሪ አያስፈልገውም ፡፡
በገበያተኞች ላይ የወደቀ ዛፍ የ 7 ሰዎች ህይወት ቀጠፈ።
በሸካ ዞን የኪ ወረዳ ፌዴ ከተማ በሀሙስ ገበያ መሐል የነበረ ትልቅ ዛፍ በገበያተኛ ላይ ወድቆ የ 7 ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን በ8 ሰዎች ላይም ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል፡፡
አደጋ የደረሰባቸው ወገኖች በቴፒ አጠቃላይ ሆስፒታል ህክምና እያገኙ ሲሆን ከፍተኛ ጉዳት ያስተናገዱ ወገኖችም ወደ ጅማ ሪፈር ተደርገዋል ሲል የዞኑ ኮሚኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል።
ፎቶ: ማኅበራዊ ሚዲያ
በሸካ ዞን የኪ ወረዳ ፌዴ ከተማ በሀሙስ ገበያ መሐል የነበረ ትልቅ ዛፍ በገበያተኛ ላይ ወድቆ የ 7 ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን በ8 ሰዎች ላይም ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል፡፡
አደጋ የደረሰባቸው ወገኖች በቴፒ አጠቃላይ ሆስፒታል ህክምና እያገኙ ሲሆን ከፍተኛ ጉዳት ያስተናገዱ ወገኖችም ወደ ጅማ ሪፈር ተደርገዋል ሲል የዞኑ ኮሚኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል።
ፎቶ: ማኅበራዊ ሚዲያ
👍1
የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ለ "ሶስት ተጨማሪ ኩባንያዎች" የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርት ፈቃድ ሰጠ
የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ለማሳደግና የሎጅስቲክስ ዘርፉን ለማጠናከር በማለም ለሶስት ተጨማሪ ኩባንያዎች የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ የስራ ፈቃድ ሰጠ።
ፈቃድ የተሰጣቸው ኩባንያዎች ኢትዮ ሬል ሎጅስቲክስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር፣ ኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ትራንስፖርት አክስዮን ማህበር እና ገልፍ ኢንጎት ኤፍ ዜድ ሲ ኢንደስትሪስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ናቸው።
የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ እንደገለጹት (ዶ/ር) ፣ ተጨማሪ ኩባንያዎች ወደ ዘርፉ መግባታቸው በገበያው ውስጥ ፉክክርን በማነቃቃትና በትብብር በመስራት የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ ለማሳደግ አስተዋጽኦ ያደርጋል።
የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር አብዱልበር ሸምሱ በበኩላቸው፣ የመልቲ ሞዳል አገልግሎት ወጪን በመቀነስ እና የገቢ ዕቃዎች ደህንነትን በመጠበቅ በፍጥነት ወደ ተፈለገው ቦታ እንዲደርሱ እንደሚያግዝ ገልጸዋል።
በአጠቃላይ፣ የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርት ዘርፉን የተቀላቀሉ ኦፕሬተሮች ቁጥር ወደ ሰባት አድጓል። በቅርቡ ዘርፉን የተቀላቀሉት ኦፕሬተሮች ፓናፍሪክ ግሎባል፣ ጥቁር አባይ ትራንስፖርት እና ኮስሞስ መልቲ ሞዳል ኦፕሬሽን የተሰኙ ኩባንያዎች መሆናቸዉ ይታወቃል።
Capital
የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ለማሳደግና የሎጅስቲክስ ዘርፉን ለማጠናከር በማለም ለሶስት ተጨማሪ ኩባንያዎች የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጡ የስራ ፈቃድ ሰጠ።
ፈቃድ የተሰጣቸው ኩባንያዎች ኢትዮ ሬል ሎጅስቲክስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር፣ ኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር ትራንስፖርት አክስዮን ማህበር እና ገልፍ ኢንጎት ኤፍ ዜድ ሲ ኢንደስትሪስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ናቸው።
የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ እንደገለጹት (ዶ/ር) ፣ ተጨማሪ ኩባንያዎች ወደ ዘርፉ መግባታቸው በገበያው ውስጥ ፉክክርን በማነቃቃትና በትብብር በመስራት የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ ለማሳደግ አስተዋጽኦ ያደርጋል።
የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር አብዱልበር ሸምሱ በበኩላቸው፣ የመልቲ ሞዳል አገልግሎት ወጪን በመቀነስ እና የገቢ ዕቃዎች ደህንነትን በመጠበቅ በፍጥነት ወደ ተፈለገው ቦታ እንዲደርሱ እንደሚያግዝ ገልጸዋል።
በአጠቃላይ፣ የመልቲ ሞዳል ትራንስፖርት ዘርፉን የተቀላቀሉ ኦፕሬተሮች ቁጥር ወደ ሰባት አድጓል። በቅርቡ ዘርፉን የተቀላቀሉት ኦፕሬተሮች ፓናፍሪክ ግሎባል፣ ጥቁር አባይ ትራንስፖርት እና ኮስሞስ መልቲ ሞዳል ኦፕሬሽን የተሰኙ ኩባንያዎች መሆናቸዉ ይታወቃል።
Capital
ሲዳማ ክልል ለውጥ ያስፈልገዋል በማለት የተቃወመች አርቲስት ኢትዮጵያ በቀለች ታሰረች።
ያለፉትን ሁለት ሳምንት ከአርቲስት #ቶኪቻው ጋር በመሆን የሲዳማ ህዝብ ለውጥ ይሻል በማለት ንቅናቄ በማድረግ የምትታወቀው አርቲስት #ኢትዮጵያ በቀለች ትላንት መጋቢት 5 በቁጥጥር ስር ውላለች።
ባለስልጣናት፣ ባለሃብቶች እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎች ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት በወንጀል የተጠረጠሩት ግለሰቧ መጋቢት 5 በህግ ቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተደረገባት መሆኑን የሲዳማ ክልል የፀጥታ ግብረሀይል ገልጿል።
ያለፉትን ሁለት ሳምንት ከአርቲስት #ቶኪቻው ጋር በመሆን የሲዳማ ህዝብ ለውጥ ይሻል በማለት ንቅናቄ በማድረግ የምትታወቀው አርቲስት #ኢትዮጵያ በቀለች ትላንት መጋቢት 5 በቁጥጥር ስር ውላለች።
ባለስልጣናት፣ ባለሃብቶች እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎች ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት በወንጀል የተጠረጠሩት ግለሰቧ መጋቢት 5 በህግ ቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተደረገባት መሆኑን የሲዳማ ክልል የፀጥታ ግብረሀይል ገልጿል።
ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ እግድ የተጣለባቸው ሀገራት እነማን ናቸው ?
የትራምፕ አስተዳደር 43 ሀገራት ላይ የቪዛ እግድ መጣሉ ተነግሯል። እግዱ ሦስት ክፍሎች ያሉት መሆኑን ጊዜያዊ እቅዱ እንደሚያሳይ ተዘግቧል።
በዚህም በመጀመሪያው ምድብ ሙሉ ለሙሉ ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ የተከለከሉት ውስጥ ሶማሊያ እና ሱዳን ይጠቀሳሉ። ሰሜን ኮሪያም በዚህ ዝርዝር ውስጥ ተካታለች።
በከፊል እግዱ ከተጣለባቸው ሀገራት መካከል ደግሞ ኤርትራ፤ ደቡብ ሱዳን እንዲሁን ማይናማር ይገኙበታል። በዚህም የእነዚህ ሀገራት ዜጎች በቱሪስት፣ በትምህርት እና መሰል ቪዛዎች ተከልክለዋል።
ሌሎች ወደ 26 የሚደርሱ ሀገራት ደግሞ የጸጥታ ሁኔታቸው ወይም ለአሜሪካ መንግስት በ60 ቀናት ውስጥ በሚሰጡት መረጃ ላይ ተንተርሶ የሚወሰን እግድ ቀርቧል።
የትራምፕ አስተዳደር 43 ሀገራት ላይ የቪዛ እግድ መጣሉ ተነግሯል። እግዱ ሦስት ክፍሎች ያሉት መሆኑን ጊዜያዊ እቅዱ እንደሚያሳይ ተዘግቧል።
በዚህም በመጀመሪያው ምድብ ሙሉ ለሙሉ ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ የተከለከሉት ውስጥ ሶማሊያ እና ሱዳን ይጠቀሳሉ። ሰሜን ኮሪያም በዚህ ዝርዝር ውስጥ ተካታለች።
በከፊል እግዱ ከተጣለባቸው ሀገራት መካከል ደግሞ ኤርትራ፤ ደቡብ ሱዳን እንዲሁን ማይናማር ይገኙበታል። በዚህም የእነዚህ ሀገራት ዜጎች በቱሪስት፣ በትምህርት እና መሰል ቪዛዎች ተከልክለዋል።
ሌሎች ወደ 26 የሚደርሱ ሀገራት ደግሞ የጸጥታ ሁኔታቸው ወይም ለአሜሪካ መንግስት በ60 ቀናት ውስጥ በሚሰጡት መረጃ ላይ ተንተርሶ የሚወሰን እግድ ቀርቧል።
👍1
የአሜሪካ ቪዛ እግድ!!
ኤርትራ ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ በከፊል ወይም በእንግሊዝኛው (Visas Sharply Restricted) የቪዛ እግድ ከተጣለባቸው ሀገራት ዝርዝር ውስጥ መካተቷ ተሰምቷል፡፡
የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር 43 ሀገራት ላይ የቪዛ እግድ መጣሉ ተነግሯል።
እግዱ ሦስት ክፍሎች ያሉት መሆኑን ጊዜያዊ እቅዱ እንደሚያሳይም ነው የሬውተርስ ዘገባ ያስነበበው፡፡
በዚህም በመጀመሪያው ምድብ ሙሉ ለሙሉ ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ተብለው የቪዛ እግድ ከተጣለባቸው ሀገራት ውስጥ ሶማሊያ እና ሱዳን ይጠቀሳሉ።
ሰሜን ኮሪያም በዚህ ዝርዝር ውስጥ ተካታለች።
በከፊል እግዱ ከተጣለባቸው ሀገራት መካከል ደግሞ ደቡብ ሱዳን እንዲሁን ማይናማር ይገኙበታል።
በዚህም መሰረት የእነዚህ ሀገራት ዜጎች የቱሪስት፣ ትምህርት እና መሰል ቪዛዎች መከልከላቸው ነው የተገረው፡፡
ሌሎች ወደ 26 የሚደርሱ ሀገራት ደግሞ የጸጥታ ሁኔታቸው ወይም ለአሜሪካ መንግስት በ60 ቀናት ውስጥ በሚሰጡት መረጃ ላይ ተንተርሶ የሚወሰን እግድ ቀርቧል።
የሀገራቱ ቁጥር ከዚህም ሊጨምር ሊቀንስ እንደሚችል እየተነገረ ነው፡፡
ኤርትራ ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ በከፊል ወይም በእንግሊዝኛው (Visas Sharply Restricted) የቪዛ እግድ ከተጣለባቸው ሀገራት ዝርዝር ውስጥ መካተቷ ተሰምቷል፡፡
የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር 43 ሀገራት ላይ የቪዛ እግድ መጣሉ ተነግሯል።
እግዱ ሦስት ክፍሎች ያሉት መሆኑን ጊዜያዊ እቅዱ እንደሚያሳይም ነው የሬውተርስ ዘገባ ያስነበበው፡፡
በዚህም በመጀመሪያው ምድብ ሙሉ ለሙሉ ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ተብለው የቪዛ እግድ ከተጣለባቸው ሀገራት ውስጥ ሶማሊያ እና ሱዳን ይጠቀሳሉ።
ሰሜን ኮሪያም በዚህ ዝርዝር ውስጥ ተካታለች።
በከፊል እግዱ ከተጣለባቸው ሀገራት መካከል ደግሞ ደቡብ ሱዳን እንዲሁን ማይናማር ይገኙበታል።
በዚህም መሰረት የእነዚህ ሀገራት ዜጎች የቱሪስት፣ ትምህርት እና መሰል ቪዛዎች መከልከላቸው ነው የተገረው፡፡
ሌሎች ወደ 26 የሚደርሱ ሀገራት ደግሞ የጸጥታ ሁኔታቸው ወይም ለአሜሪካ መንግስት በ60 ቀናት ውስጥ በሚሰጡት መረጃ ላይ ተንተርሶ የሚወሰን እግድ ቀርቧል።
የሀገራቱ ቁጥር ከዚህም ሊጨምር ሊቀንስ እንደሚችል እየተነገረ ነው፡፡
👍2
በኢትዮጵያ ዛሬ ምሽት 5.1 ሬክተር ስኬል የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቷል
ዛሬ ምሽት 3፡53 ላይ አዋሽ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተት እነደነበር በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂዮ ፊዝክስ፣ ስፔስ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተመራማሪው ኤሊያስ ሌዊ (ዶ/ር) ለኢቢሲ ዶትስትሪም ተናግረዋል።
ከዚህ በፊት ተመሳሳይ እንቅስቃሴ ይስተዋልበት በነበረው የፈንታሌ እና ዶፈን ተራራዎች መካከል ከሳቡሬ መንደር በስተምስራቅ በኩል ቀረብ ባለ ቦታ ላይ የተከሰተ ርዕደ መሬት መሆኑንም ኤሊያስ ሌዊ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ለ9 ሰከንድ በቆየው ርዕደ መሬት አዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች ላይ ንዝረቱ ስለመሰማቱም ነው የገለጹልን።
በኢትዮጵያ ከአዋሽ በስተሰሜን 50 ኪ.ሎ ሜትር ርቀት ላይ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 5.1 መሆኑን የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ መረጃ አመላክቷል።
የመሬት መንቀጥቀጡ ከመሬት በ10 ኪ.ሎ ሜትር ርቀት ውስጥ ስለመፈጠሩም ይሄው ተቋም ያወጣው መረጃ ያመላክታል።
የርዕደ መሬቱ ንዝረት አዲስ አበባን ጨምሮ በብዙ ቦታዎች ላይ ተሰምቷል።
ዛሬ ምሽት 3፡53 ላይ አዋሽ አካባቢ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተት እነደነበር በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂዮ ፊዝክስ፣ ስፔስ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተመራማሪው ኤሊያስ ሌዊ (ዶ/ር) ለኢቢሲ ዶትስትሪም ተናግረዋል።
ከዚህ በፊት ተመሳሳይ እንቅስቃሴ ይስተዋልበት በነበረው የፈንታሌ እና ዶፈን ተራራዎች መካከል ከሳቡሬ መንደር በስተምስራቅ በኩል ቀረብ ባለ ቦታ ላይ የተከሰተ ርዕደ መሬት መሆኑንም ኤሊያስ ሌዊ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ለ9 ሰከንድ በቆየው ርዕደ መሬት አዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች ላይ ንዝረቱ ስለመሰማቱም ነው የገለጹልን።
በኢትዮጵያ ከአዋሽ በስተሰሜን 50 ኪ.ሎ ሜትር ርቀት ላይ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 5.1 መሆኑን የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ መረጃ አመላክቷል።
የመሬት መንቀጥቀጡ ከመሬት በ10 ኪ.ሎ ሜትር ርቀት ውስጥ ስለመፈጠሩም ይሄው ተቋም ያወጣው መረጃ ያመላክታል።
የርዕደ መሬቱ ንዝረት አዲስ አበባን ጨምሮ በብዙ ቦታዎች ላይ ተሰምቷል።
"በዜጎቻችን ተታለን ነው የሄድነው" - ከማይናማር የተመለሱ ኢትዮጵያውያን
ከማይናማር እገታ ተርፈው ታይላንድ የነበሩ 30 ኢትዮጵያውያን ዛሬ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
ተመላሾቹ እንደገለጹት አብዛኞቹ በኢትዮጵያውያን ደላሎች ተታለው ወደዚያች አደገኛ ምድር ያመሩ ናቸው።
የማጭበርበሪያው መንገድ
* "የማሸጊያ ስራ አለ"፣ "ኦንላይን ቢዝነስ ነው"፣ "ሴልስ ስራ አለ" በሚሉ ማራኪ የውሸት ስራዎች ይታልላሉ።
* በወር እስከ 1500 ዶላር እንደሚከፈላቸው ይነገራቸዋል።
* በቴሌግራም እና በሌሎች የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች አማካኝነት ይገናኛሉ።
* በቀላሉ ትኬት ተቆርጦላቸው ይላክላቸዋል።
* አንዳንዶች እስከ 500 ሺህ ብር ለደላሎች ይከፍላሉ።
የማይናማር የገሃነም ጉዞ
* ታይላንድ ከገቡ በኋላ ወደ ማይናማር ይወሰዳሉ።
* ከባድ ስቃይና እንግልት ይደርስባቸዋል።
* ለቀናት ያለ ምግብና ውሃ ይታሰራሉ።
* በጨለማ ውስጥ ይሰቀላሉ።
* ጥፍሮቻቸው ይነቀላሉ።
* በተሳሳተ የኦንላይን ፕላትፎርም ዶላር የማጭበርበር ስራ ይሰራሉ።
የተመላሾቹ መልእክት
* ወጣቶች በምንም አይነት ሁኔታ በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ውጭ ሀገር እንዳይሄዱ።
* "የቪዛ ቪዚት"፣ "ኦንላይን ስራ" የሚሉትን ማስታወቂያዎች እንዳያምኑ።
* ማንኛውንም የውጭ ሀገር የስራ እድል ሲያገኙ በህጋዊ መንገድ ብቻ እንዲሄዱ።
* በማይናማር ያሉ ኢትዮጵያውያኖች በአስቸኳይ እንዲድኑ መንግስት እና ሚዲያዎች እንዲደርሱላቸው ጠይቀዋል
* ደላሎች እንዲያዙ እና ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ጠይቀዋል።
ይህ አሳዛኝ ሁኔታ ወጣቶች የስራ እድል ፍለጋ ሲንቀሳቀሱ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የሚያግዝ በመሆኑ ለሌሎችም ያጋሩ
ከማይናማር እገታ ተርፈው ታይላንድ የነበሩ 30 ኢትዮጵያውያን ዛሬ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።
ተመላሾቹ እንደገለጹት አብዛኞቹ በኢትዮጵያውያን ደላሎች ተታለው ወደዚያች አደገኛ ምድር ያመሩ ናቸው።
የማጭበርበሪያው መንገድ
* "የማሸጊያ ስራ አለ"፣ "ኦንላይን ቢዝነስ ነው"፣ "ሴልስ ስራ አለ" በሚሉ ማራኪ የውሸት ስራዎች ይታልላሉ።
* በወር እስከ 1500 ዶላር እንደሚከፈላቸው ይነገራቸዋል።
* በቴሌግራም እና በሌሎች የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች አማካኝነት ይገናኛሉ።
* በቀላሉ ትኬት ተቆርጦላቸው ይላክላቸዋል።
* አንዳንዶች እስከ 500 ሺህ ብር ለደላሎች ይከፍላሉ።
የማይናማር የገሃነም ጉዞ
* ታይላንድ ከገቡ በኋላ ወደ ማይናማር ይወሰዳሉ።
* ከባድ ስቃይና እንግልት ይደርስባቸዋል።
* ለቀናት ያለ ምግብና ውሃ ይታሰራሉ።
* በጨለማ ውስጥ ይሰቀላሉ።
* ጥፍሮቻቸው ይነቀላሉ።
* በተሳሳተ የኦንላይን ፕላትፎርም ዶላር የማጭበርበር ስራ ይሰራሉ።
የተመላሾቹ መልእክት
* ወጣቶች በምንም አይነት ሁኔታ በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ውጭ ሀገር እንዳይሄዱ።
* "የቪዛ ቪዚት"፣ "ኦንላይን ስራ" የሚሉትን ማስታወቂያዎች እንዳያምኑ።
* ማንኛውንም የውጭ ሀገር የስራ እድል ሲያገኙ በህጋዊ መንገድ ብቻ እንዲሄዱ።
* በማይናማር ያሉ ኢትዮጵያውያኖች በአስቸኳይ እንዲድኑ መንግስት እና ሚዲያዎች እንዲደርሱላቸው ጠይቀዋል
* ደላሎች እንዲያዙ እና ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ ጠይቀዋል።
ይህ አሳዛኝ ሁኔታ ወጣቶች የስራ እድል ፍለጋ ሲንቀሳቀሱ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የሚያግዝ በመሆኑ ለሌሎችም ያጋሩ
👍2
Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)
Photo
"ፈለገ ግዮን" አውቶብስ በታጣቂዎች ተጠልፎ ተሳፋሪዎች ታገቱ
* ዛሬ ከአዲስ አበባ ወደ ማርቆስ ተሳፋሪዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ "ፈለገ ግዮን" የተባለ አውቶብስ በኦሮሚያ ክልል ከፍቼ እና ጎሃፂዮን መሃል አሊደሮ በተባለ ቦታ ላይ በታጣቂዎች ተጠልፏል።
* አውቶብሱ 50 የሚሆኑ ተሳፋሪዎችን እና ሹፌሩን አሳፍሮ ነበር።
* የዓይን እማኝ ሹፌሮች እንደገለጹት አውቶብሱ በታጣቂዎች በጥይት ተመትቶ መስታወቱ እና የፊት ለፊት ጎማው ተጎድቷል።
* ታጣቂዎቹ ተሳፋሪዎችን እና ሹፌሩን ይዘው ወደማይታወቅ ቦታ ወስደዋል።
* አካባቢው የሸኔ ታጣቂዎች የሚንቀሳቀሱበት በመሆኑ በተደጋጋሚ ተመሳሳይ ጥቃቶች ይፈጸማሉ።
* ቅዳሜ ዕለትም ታጣቂዎች በአካባቢው ተመሳሳይ ጥቃት በመፈጸም 5 የከባድ መኪና ሹፌሮችን ይዘው ሄደዋል።
* የፈለገ ግዮን ባስ ሰራተኞች ለሹፌሩ እና ረዳቱ ደጋግመው እየደወሉ እንደሆነ እና እስካሁን ማግኘት እንዳልቻሉ ገልጸዋል።
* ታጣቂዎቹ ታጋቾችን ለመልቀቅ ከፍተኛ ገንዘብ እንደሚጠይቁ ተገልጿል።
የአካባቢው ነዋሪዎችና አሽከርካሪዎች ስጋት
* አሽከርካሪዎች እና የአካባቢው ነዋሪዎች መንግስት ችግሩን ለመፍታት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድ እየጠየቁ ነው።
* ታጣቂዎቹ ታጋቾችን ከለቀቁ በኋላም በህይወት የመመለሳቸው ዋስትና እንደሌለ ስጋታቸውን ገልጸዋል።
* አካባቢው የሸኔ ታጣቂዎች እንቅስቃሴ የሚታይበት በመሆኑ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ ጠይቀዋል።
መንግስት በአስቸኳይ ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድ እና የታጋቾችን ደህንነት እንዲያስጠብቅ ጥሪ ቀርቧል።(ቲክቫ)
* ዛሬ ከአዲስ አበባ ወደ ማርቆስ ተሳፋሪዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ "ፈለገ ግዮን" የተባለ አውቶብስ በኦሮሚያ ክልል ከፍቼ እና ጎሃፂዮን መሃል አሊደሮ በተባለ ቦታ ላይ በታጣቂዎች ተጠልፏል።
* አውቶብሱ 50 የሚሆኑ ተሳፋሪዎችን እና ሹፌሩን አሳፍሮ ነበር።
* የዓይን እማኝ ሹፌሮች እንደገለጹት አውቶብሱ በታጣቂዎች በጥይት ተመትቶ መስታወቱ እና የፊት ለፊት ጎማው ተጎድቷል።
* ታጣቂዎቹ ተሳፋሪዎችን እና ሹፌሩን ይዘው ወደማይታወቅ ቦታ ወስደዋል።
* አካባቢው የሸኔ ታጣቂዎች የሚንቀሳቀሱበት በመሆኑ በተደጋጋሚ ተመሳሳይ ጥቃቶች ይፈጸማሉ።
* ቅዳሜ ዕለትም ታጣቂዎች በአካባቢው ተመሳሳይ ጥቃት በመፈጸም 5 የከባድ መኪና ሹፌሮችን ይዘው ሄደዋል።
* የፈለገ ግዮን ባስ ሰራተኞች ለሹፌሩ እና ረዳቱ ደጋግመው እየደወሉ እንደሆነ እና እስካሁን ማግኘት እንዳልቻሉ ገልጸዋል።
* ታጣቂዎቹ ታጋቾችን ለመልቀቅ ከፍተኛ ገንዘብ እንደሚጠይቁ ተገልጿል።
የአካባቢው ነዋሪዎችና አሽከርካሪዎች ስጋት
* አሽከርካሪዎች እና የአካባቢው ነዋሪዎች መንግስት ችግሩን ለመፍታት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድ እየጠየቁ ነው።
* ታጣቂዎቹ ታጋቾችን ከለቀቁ በኋላም በህይወት የመመለሳቸው ዋስትና እንደሌለ ስጋታቸውን ገልጸዋል።
* አካባቢው የሸኔ ታጣቂዎች እንቅስቃሴ የሚታይበት በመሆኑ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ ጠይቀዋል።
መንግስት በአስቸኳይ ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድ እና የታጋቾችን ደህንነት እንዲያስጠብቅ ጥሪ ቀርቧል።(ቲክቫ)
👍3