የቻይና ሰላዮች በአሜሪካ
በአሜሪካ ውስጥ ለቻይና ሲሰልሉ የነበሩ 2 የቻይና ዜግነት ያላቸውን ሠዎች ክስ እንደተመሰረተባቸው የአሜሪካ ፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የአሜሪካን የባህር ሃይል ጣቢያን ፎቶግራፍ በማንሳት፣ አመጽ በገንዘብ በመደገፍና በማስተባበር እንዲሁም የተለያዩ የስለላ ስራዎችን በመስራት በሚል ክስ ተመስርቶባቸዋል።
የሳን ፍራንሲስኮ የፌደራል ፍርድ ቤት አቃቤ ህግ እንደገለጹት ፣ የቻይና መንግስት ስለ አሜሪካ ወታደራዊ አቅም በድብቅ መረጃ ለመሰብሰብ የቻይና መንግስት የማያቋርጥ ጥረቶች ማሣያ ነው በማለት አብራርተዋል።
አክለውም "ይህ ጉዳይ የቻይና መንግስት ወታደሮቻችንን ሰርጎ ለመግባት እና ብሄራዊ ደህንነታችንን ከውስጥ ለማዳከም የሚያደርገውን ያልተቋረጠ ጥረት አጉልቶ ያሳያል" ሲሉ ተናግረዋል።
"የውጭ ተላላኪዎችን እናጋልጣለን ፣ወኪሎቻቸውን እናያለን እና የአሜሪካን ህዝብ በብሄራዊ ደህንነታችን ላይ ከሚደርሱ ስውር አደጋዎች እንጠብቃለንም" ብለዋል።
እ.ኤ.አ በ2015 ወደ አሜሪካ የገቡት ሠላዮቹ ዩያንስ ቼን እና ሊረን ራያን በመባል ይጠራሉ። የቻይና መንግስት ደህንነት ሚኒስቴርን ወክለው ሚስጥራዊ የስለላ ስራዎችን ለመከታተል የተደረገው ጥረት አካል እንደሆኑም ገልጸዋል።
በዋሽንግተን የሚገኘው የቻይና ኤምባሲ ቃል አቀባይ ሊዩ ፔንግዩ ስለ ጉዳዩ መረጃ እንደሌላቸው ገልፀው፣ ነገር ግን በቻይና ላይ የተከሰሱ ውንጀላዎች ምንም ዓይነት ማስረጃ የላቸውም እንዲሁም አሜሪካ በቻይና ላይ የምታደርገውን የስለላ ተግባር አላቆመችም ማለታቸውን ኤፒ ዘግቧል።
በአሜሪካ ውስጥ ለቻይና ሲሰልሉ የነበሩ 2 የቻይና ዜግነት ያላቸውን ሠዎች ክስ እንደተመሰረተባቸው የአሜሪካ ፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የአሜሪካን የባህር ሃይል ጣቢያን ፎቶግራፍ በማንሳት፣ አመጽ በገንዘብ በመደገፍና በማስተባበር እንዲሁም የተለያዩ የስለላ ስራዎችን በመስራት በሚል ክስ ተመስርቶባቸዋል።
የሳን ፍራንሲስኮ የፌደራል ፍርድ ቤት አቃቤ ህግ እንደገለጹት ፣ የቻይና መንግስት ስለ አሜሪካ ወታደራዊ አቅም በድብቅ መረጃ ለመሰብሰብ የቻይና መንግስት የማያቋርጥ ጥረቶች ማሣያ ነው በማለት አብራርተዋል።
አክለውም "ይህ ጉዳይ የቻይና መንግስት ወታደሮቻችንን ሰርጎ ለመግባት እና ብሄራዊ ደህንነታችንን ከውስጥ ለማዳከም የሚያደርገውን ያልተቋረጠ ጥረት አጉልቶ ያሳያል" ሲሉ ተናግረዋል።
"የውጭ ተላላኪዎችን እናጋልጣለን ፣ወኪሎቻቸውን እናያለን እና የአሜሪካን ህዝብ በብሄራዊ ደህንነታችን ላይ ከሚደርሱ ስውር አደጋዎች እንጠብቃለንም" ብለዋል።
እ.ኤ.አ በ2015 ወደ አሜሪካ የገቡት ሠላዮቹ ዩያንስ ቼን እና ሊረን ራያን በመባል ይጠራሉ። የቻይና መንግስት ደህንነት ሚኒስቴርን ወክለው ሚስጥራዊ የስለላ ስራዎችን ለመከታተል የተደረገው ጥረት አካል እንደሆኑም ገልጸዋል።
በዋሽንግተን የሚገኘው የቻይና ኤምባሲ ቃል አቀባይ ሊዩ ፔንግዩ ስለ ጉዳዩ መረጃ እንደሌላቸው ገልፀው፣ ነገር ግን በቻይና ላይ የተከሰሱ ውንጀላዎች ምንም ዓይነት ማስረጃ የላቸውም እንዲሁም አሜሪካ በቻይና ላይ የምታደርገውን የስለላ ተግባር አላቆመችም ማለታቸውን ኤፒ ዘግቧል።
ባልታዛር ተፈረደበት
የቀድሞው የኢኳቶሪያል ጊኒ የብሄራዊ የፋይናንስ ምርመራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ባልታዛር ኢንጎንጋ ከበርካታ የቀድሞ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር የህዝብን ገንዘብ በማጭበርበር ወንጀል ተከሰው የ18 አመት እስራት ተፈረደባቸው።
ባልታዛር ባለፈው አመት መስከረም ወር ላይ ከበርካታ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር የህዝብን ገንዘብ በማጭበርበር ወንጀል ተከሰው ማረሚያ ቤት ታስረው ነበር።
የቀድሞ ብሄራዊ የፋይናንስ ምርመራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ባልታዛር ኢንጎንጋ የፋይናንስ ወንጀሎችን ፣ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር እና ሙስናን የመከላከል ትልቅ ስልጣን ነበራቸው ።
ባልታዛር ኢንጎንጋ ከባለስልጣናቱ ጋር 1ቢሊዮን ፍራንክ ከመንግስት ካዝና አጭበርብረዋል ።
ባልታሳር ኢንጎንጋ ወደ ኪሳቸው 910 ፍራንክ እንዳስገቡ ተገልጿል ።
ከባልታዛር ጋር አገር ሲዘርፉ በነበሩት በሌሎች ባለስልጣናት ላይም ፍርዱ እንደሚቀጥል ተገልጿል
የቀድሞው የኢኳቶሪያል ጊኒ የብሄራዊ የፋይናንስ ምርመራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ባልታዛር ኢንጎንጋ ከበርካታ የቀድሞ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር የህዝብን ገንዘብ በማጭበርበር ወንጀል ተከሰው የ18 አመት እስራት ተፈረደባቸው።
ባልታዛር ባለፈው አመት መስከረም ወር ላይ ከበርካታ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር የህዝብን ገንዘብ በማጭበርበር ወንጀል ተከሰው ማረሚያ ቤት ታስረው ነበር።
የቀድሞ ብሄራዊ የፋይናንስ ምርመራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ባልታዛር ኢንጎንጋ የፋይናንስ ወንጀሎችን ፣ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር እና ሙስናን የመከላከል ትልቅ ስልጣን ነበራቸው ።
ባልታዛር ኢንጎንጋ ከባለስልጣናቱ ጋር 1ቢሊዮን ፍራንክ ከመንግስት ካዝና አጭበርብረዋል ።
ባልታሳር ኢንጎንጋ ወደ ኪሳቸው 910 ፍራንክ እንዳስገቡ ተገልጿል ።
ከባልታዛር ጋር አገር ሲዘርፉ በነበሩት በሌሎች ባለስልጣናት ላይም ፍርዱ እንደሚቀጥል ተገልጿል
ኢትዮጵያ በግንቦት ወር ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የወባ በሽታ ጉዳዮችን ሪፖርት አደረገች
በአንድ ዓመት ውስጥ የተመዘገበው ከፍተኛው ቁጥርም 8.4 ሚሊዮን ደርሷል
የዓለም ጤና ድርጅት ባወጣው ሪፖርት መሰረት፣ ኢትዮጵያ በግንቦት ወር ብቻ 520,782 የወባ በሽታ ጉዳዮችን ሪፖርት አድርጋለች። ይህ ቁጥር አሳሳቢ ሲሆን፣ በ2024 በአንድ ዓመት ውስጥ የተመዘገበው የወባ በሽታ ጉዳይ ደግሞ ከ8.4 ሚሊዮን በላይ መድረሱ ተገልጿል፤ ይህም እስካሁን ከተመዘገበው ሁሉ ከፍተኛው ነው።
የዓለም ጤና ድርጅት በኢትዮጵያ የጤና ክላስተር ቡለቲን ሪፖርቱ ላይ እንዳብራራው፣ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከወባ በተጨማሪ እንደ ኮሌራ፣ ኩፍኝ እና ኤምፖክስ (mpox) የመሳሰሉ በርካታ በሽታዎችን እየተቋቋመች ትገኛለች።
በተለይም በአገሪቱ እየተካሄዱ ያሉት ግጭቶች በህዝብ ጤና ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደሩ ሲሆን፣ ብዙ ሰዎች የሰብአዊ እርዳታ እጦትና የተገደበ የጤና አገልግሎት በሚያገኙባቸው አካባቢዎች ተይዘው ይገኛሉ።
ወባ በኢትዮጵያ ከባህር ወለል በላይ በ2,000 ሜትር ከፍታ በታች ባሉ አካባቢዎች በስፋት የሚታይ በሽታ ነው። እነዚህ አካባቢዎች የአገሪቱን የመሬት ስፋት ሶስት አራተኛውን የሚሸፍኑ ሲሆን፣ በእነዚህ ስፍራዎች ከሚኖሩት የአገሪቱ ህዝብ ውስጥ 69 በመቶ የሚሆነው በበሽታው የመያዝ ስጋት ተጋርጦበታል።
የወባ በሽታ ስርጭት በተለምዶ ከዋናው የዝናብ ወቅት በኋላ ከመስከረም እስከ ታህሳስ ባሉት ወራት፣ እና ከሁለተኛው የዝናብ ወቅት በኋላ ከሚያዝያ እስከ ግንቦት ባሉት ወራት ይጨምራል።
Capital
በአንድ ዓመት ውስጥ የተመዘገበው ከፍተኛው ቁጥርም 8.4 ሚሊዮን ደርሷል
የዓለም ጤና ድርጅት ባወጣው ሪፖርት መሰረት፣ ኢትዮጵያ በግንቦት ወር ብቻ 520,782 የወባ በሽታ ጉዳዮችን ሪፖርት አድርጋለች። ይህ ቁጥር አሳሳቢ ሲሆን፣ በ2024 በአንድ ዓመት ውስጥ የተመዘገበው የወባ በሽታ ጉዳይ ደግሞ ከ8.4 ሚሊዮን በላይ መድረሱ ተገልጿል፤ ይህም እስካሁን ከተመዘገበው ሁሉ ከፍተኛው ነው።
የዓለም ጤና ድርጅት በኢትዮጵያ የጤና ክላስተር ቡለቲን ሪፖርቱ ላይ እንዳብራራው፣ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከወባ በተጨማሪ እንደ ኮሌራ፣ ኩፍኝ እና ኤምፖክስ (mpox) የመሳሰሉ በርካታ በሽታዎችን እየተቋቋመች ትገኛለች።
በተለይም በአገሪቱ እየተካሄዱ ያሉት ግጭቶች በህዝብ ጤና ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደሩ ሲሆን፣ ብዙ ሰዎች የሰብአዊ እርዳታ እጦትና የተገደበ የጤና አገልግሎት በሚያገኙባቸው አካባቢዎች ተይዘው ይገኛሉ።
ወባ በኢትዮጵያ ከባህር ወለል በላይ በ2,000 ሜትር ከፍታ በታች ባሉ አካባቢዎች በስፋት የሚታይ በሽታ ነው። እነዚህ አካባቢዎች የአገሪቱን የመሬት ስፋት ሶስት አራተኛውን የሚሸፍኑ ሲሆን፣ በእነዚህ ስፍራዎች ከሚኖሩት የአገሪቱ ህዝብ ውስጥ 69 በመቶ የሚሆነው በበሽታው የመያዝ ስጋት ተጋርጦበታል።
የወባ በሽታ ስርጭት በተለምዶ ከዋናው የዝናብ ወቅት በኋላ ከመስከረም እስከ ታህሳስ ባሉት ወራት፣ እና ከሁለተኛው የዝናብ ወቅት በኋላ ከሚያዝያ እስከ ግንቦት ባሉት ወራት ይጨምራል።
Capital
ኢትዮጵያ ከዓለም ባንክ ገቢ ምደባ ዝርዝር ዉጪ መሆኗ ተገለፀ
የ2025 የበጀት ዓመት ዝቅተኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ተብላ የተመደበችው ኢትዮጵያ፣ ለ2026 የበጀት ዓመት የዓለም ባንክ የገቢ ምደባ ዝርዝር ውስጥ አለመካተቷ ካፒታል ተመልክቷል።
የዓለም ባንክ በየዓመቱ ሐምሌ 1 ቀን በሚያወጣው የሀገራት ገቢ ምደባ፣ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት "ጊዜያዊ ምደባ አልተሰጣትም" ተብሏል። ይህ ማለት ኢትዮጵያ በዝቅተኛ ገቢ ወይም ዝቅተኛ መካከለኛ ገቢ ሀገራት ምድብ ውስጥ አልተካተተችም ማለት ነው።
ያልተመደቡ አገሮችን በተመለከተ መረጃው እንደሚያረጋግጠው :- ቬንዙዌላ እስከ 2021 ድረስ የከፍተኛ መካከለኛ ገቢ አገር የነበረች ቢሆንም፣ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ መረጃ ባለመኖሩ ምክንያት ከምደባ ውጭ ሆናለች። ኢትዮጵያም በአሁኑ ወቅት ለ 2026 በጀት በጊዜያዊነት ከምደባ ውጭ ሁኔታ ላይ ትገኛለች።
የዓለም ባንክ የ2025 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው አገሮች ዝርዝር በ2023 የአንድ ሰው አጠቃላይ አገራዊ ገቢ (GNI) 1,195 የአሜሪካ ዶላር ወይም ከዚያ በታች የሆኑ አገሮችን ይፋ ሲያደርግ ኢትዮጵያ አንደኛው ነበረች።
ምንም እንኳን የዚህ ምደባ አለመስጠት ትክክለኛ ምክንያቶች ግልጽ ባይሆኑም፣ የሀገር ገቢ ምድብ ለውጦች በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ሊከሰቱ እንደሚችሉ ይገለጻል ።
"በአትላስ" ዘዴ በሚሰላው የነፍስ ወከፍ GNI ላይ በሚከሰቱ ለውጦች (ለምሳሌ የኢኮኖሚ እድገት፣ የዋጋ ግሽበት፣ የምንዛሪ ተመን እና የህዝብ ብዛት መጨመር ወይም በምደባ ወሰኖቹ ላይ በሚደረጉ ማስተካከያዎች ሊሆኑ እንደሚችሉ ተጠቁሟል።
Capital newspaper
የ2025 የበጀት ዓመት ዝቅተኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ተብላ የተመደበችው ኢትዮጵያ፣ ለ2026 የበጀት ዓመት የዓለም ባንክ የገቢ ምደባ ዝርዝር ውስጥ አለመካተቷ ካፒታል ተመልክቷል።
የዓለም ባንክ በየዓመቱ ሐምሌ 1 ቀን በሚያወጣው የሀገራት ገቢ ምደባ፣ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት "ጊዜያዊ ምደባ አልተሰጣትም" ተብሏል። ይህ ማለት ኢትዮጵያ በዝቅተኛ ገቢ ወይም ዝቅተኛ መካከለኛ ገቢ ሀገራት ምድብ ውስጥ አልተካተተችም ማለት ነው።
ያልተመደቡ አገሮችን በተመለከተ መረጃው እንደሚያረጋግጠው :- ቬንዙዌላ እስከ 2021 ድረስ የከፍተኛ መካከለኛ ገቢ አገር የነበረች ቢሆንም፣ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ መረጃ ባለመኖሩ ምክንያት ከምደባ ውጭ ሆናለች። ኢትዮጵያም በአሁኑ ወቅት ለ 2026 በጀት በጊዜያዊነት ከምደባ ውጭ ሁኔታ ላይ ትገኛለች።
የዓለም ባንክ የ2025 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው አገሮች ዝርዝር በ2023 የአንድ ሰው አጠቃላይ አገራዊ ገቢ (GNI) 1,195 የአሜሪካ ዶላር ወይም ከዚያ በታች የሆኑ አገሮችን ይፋ ሲያደርግ ኢትዮጵያ አንደኛው ነበረች።
ምንም እንኳን የዚህ ምደባ አለመስጠት ትክክለኛ ምክንያቶች ግልጽ ባይሆኑም፣ የሀገር ገቢ ምድብ ለውጦች በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ሊከሰቱ እንደሚችሉ ይገለጻል ።
"በአትላስ" ዘዴ በሚሰላው የነፍስ ወከፍ GNI ላይ በሚከሰቱ ለውጦች (ለምሳሌ የኢኮኖሚ እድገት፣ የዋጋ ግሽበት፣ የምንዛሪ ተመን እና የህዝብ ብዛት መጨመር ወይም በምደባ ወሰኖቹ ላይ በሚደረጉ ማስተካከያዎች ሊሆኑ እንደሚችሉ ተጠቁሟል።
Capital newspaper
ኢትዮጵያ የጋዝ ምርት ለመጀመሪያ ጊዜ የፊታችን መስከረም ወር ላይ ለገበያ ታቀርባለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር
ኢትዮጵያ የጋዝ ምርት የፊታችን መስከረም ወር ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ለገበያ ታቀርባለች አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምክር ቤቱ 42ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው የመንግስትን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው፡፡
በማብራሪያቸውም በለውጡ መንግስት ጋዝ ለማምረት ፋብሪካዎች ለመትከል ስምምነት ተደርጎ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
ጋዝና አካባቢ የሚመጡ የግል ድርጅቶች እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የነበራቸው ፍላጎት ፈቃድ መውሰድና በዛ ፈቃድ ብር መፈለግ ነበር ሲሉም ተናግረዋል፡፡
ይሁን እንጂ ይህ አካሄድና መንገድ አያዋጣም ብለን የነበሩትን በመሰረዝ አዳዲስ ኩባንያዎች ወደ ዘርፉ እንዲገቡ አድርገናል ነው ያሉት፡፡
ይህን ተከትሎም ምናልባትም የምክር ቤት አባላት ከእረፍት ሲመለሱ የፊታችን መስከረም ወር ላይ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የጋዝ ምርት ለገበያ ታቀርባለች ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ የጋዝ ምርት የፊታችን መስከረም ወር ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ለገበያ ታቀርባለች አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምክር ቤቱ 42ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው የመንግስትን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው፡፡
በማብራሪያቸውም በለውጡ መንግስት ጋዝ ለማምረት ፋብሪካዎች ለመትከል ስምምነት ተደርጎ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
ጋዝና አካባቢ የሚመጡ የግል ድርጅቶች እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የነበራቸው ፍላጎት ፈቃድ መውሰድና በዛ ፈቃድ ብር መፈለግ ነበር ሲሉም ተናግረዋል፡፡
ይሁን እንጂ ይህ አካሄድና መንገድ አያዋጣም ብለን የነበሩትን በመሰረዝ አዳዲስ ኩባንያዎች ወደ ዘርፉ እንዲገቡ አድርገናል ነው ያሉት፡፡
ይህን ተከትሎም ምናልባትም የምክር ቤት አባላት ከእረፍት ሲመለሱ የፊታችን መስከረም ወር ላይ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የጋዝ ምርት ለገበያ ታቀርባለች ብለዋል፡፡
#NewsinBrief | አነጋጋሪው የኦጋዴን ነዳጅ ጉዳይ መጨረሻ | መንግስት ለከፍተኛ የዕዳ ጫና ተጋለጠ | የባከ...
https://youtube.com/watch?v=6ioI3kPkwhU&feature=shared
https://youtube.com/watch?v=6ioI3kPkwhU&feature=shared
YouTube
#NewsinBrief | አነጋጋሪው የኦጋዴን ነዳጅ ጉዳይ መጨረሻ | መንግስት ለከፍተኛ የዕዳ ጫና ተጋለጠ | የባከነው 14 ቢሊየን ብር የት ገባ
ኦፌኮ ከተመድ የውጭ መረጃ አሰባሳቢ ልዑክ ጋር በ2018 ሀገራዊ ምርጫ ዙሪያ ተወያየ፤ የምርጫ ቦርድ እንደገና ማዋቀርን ጨምሮ ቁልፍ ጥያቄዎችን አቀረበ!
የኦሮሞ ፌዴራላሲት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ጋር በ2018 ዓ.ም. በሚካሄደው 7ኛው ዙር አጠቃላይ ምርጫ ዙርያ ውይይት ማድረጉን አስታወቀ።
በኦፌኮ ዋና ጽ/ቤት በተካሄደው ስብሰባ ላይ የፓርቲው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና እና የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሱልጣን ቃሲም የተገኙ ሲሆን በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ህብረት ቢሮ (UNOAU) የምርጫ ድጋፍ ክፍል ዋና ኦፊሰር የሆኑት አኪንየሚ ኦ. አዴግባላን ጨምሮ አራት አባላትን የያዘ ልዑክ መገኘቱን ከፓርቲው ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ኦፌኮ በስብሰባው ላይ ነጻ፣ ፍትሃዊ እና ተአማኒነት ያለው የምርጫ ሂደት እንዲረጋገጥ መንግስት ሊያሟላቸው የሚገቡ "መሰረታዊ" ጥያቄዎችን ማቅረቡ ተጠቁሟል።
የፓርቲው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ኦፌኮ በ2018 ምርጫ ላይ መሳተፉ ሙሉ በሙሉ "በመሠረታዊ እና በተጨባጭ ለውጦች" ላይ የተመሰረተ መሆኑን ለልዑካን ቡድኑ አስረድተዋል።
"ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ድምፅ የመስጠት ቴክኒካዊ ሂደት ብቻ አይደለም፤ የዲሞክራሲያዊ ሂደት ውጤት ነው" ያሉት ፕሮፌሰር መረራ፣ "ይህ ሂደት ዛሬ በኢትዮጵያ የለም። በጦርነት እና በፖለቲካ ስደት ውስጥ ተአማኒነት ያለው ምርጫ ማካሄድ አይቻልም" ሲሉ አክለዋል።
ኦፌኮ በ2018 ዓ.ም አጠቃላይ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ መሠረታዊ ተቋማዊ እና ህጋዊ ማሻሻያዎች እንዲደረጉ የጠየቀ ሲሆን የምርጫ ቦርድን እንደገና ማዋቀርን ጨምሮ የምርጫ ስርዓት ማሻሸያ እንዲደረግ እና ከምርጫ በፊት በገዢው ፓርቲ እና በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል ግልጽ የሆነ ፍኖተ ካርታ ላይ ለመስማማት የሚያስችል ውይይት እንዲካሄድ ጥሪ አቅርቧል።
በተጨማሪም በኦሮሚያና በመላ ኢትዮጵያ ያለው ግጭት እንዲቆም፣ የኦፌኮ አባላት፣ አመራሮችንና ደጋፊዎችን ጨምሮ በመላ አገሪቱ የታሰሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች፣ ጋዜጠኞችና አክቲቪስቶች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ፣ በተቃዋሚዎች ላይ የሚደርሰው ማስፈራራት፣ ወከባና እስራት እንዲቆም እና የጸጥታ ሀይሎች በፖለቲካው ሂደት ውስጥ ገለልተኛ የሚሆኑበት ስምምነት እንዲፈረም ጠይቋል።
የኦሮሞ ፌዴራላሲት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ጋር በ2018 ዓ.ም. በሚካሄደው 7ኛው ዙር አጠቃላይ ምርጫ ዙርያ ውይይት ማድረጉን አስታወቀ።
በኦፌኮ ዋና ጽ/ቤት በተካሄደው ስብሰባ ላይ የፓርቲው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና እና የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሱልጣን ቃሲም የተገኙ ሲሆን በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ህብረት ቢሮ (UNOAU) የምርጫ ድጋፍ ክፍል ዋና ኦፊሰር የሆኑት አኪንየሚ ኦ. አዴግባላን ጨምሮ አራት አባላትን የያዘ ልዑክ መገኘቱን ከፓርቲው ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ኦፌኮ በስብሰባው ላይ ነጻ፣ ፍትሃዊ እና ተአማኒነት ያለው የምርጫ ሂደት እንዲረጋገጥ መንግስት ሊያሟላቸው የሚገቡ "መሰረታዊ" ጥያቄዎችን ማቅረቡ ተጠቁሟል።
የፓርቲው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ኦፌኮ በ2018 ምርጫ ላይ መሳተፉ ሙሉ በሙሉ "በመሠረታዊ እና በተጨባጭ ለውጦች" ላይ የተመሰረተ መሆኑን ለልዑካን ቡድኑ አስረድተዋል።
"ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ድምፅ የመስጠት ቴክኒካዊ ሂደት ብቻ አይደለም፤ የዲሞክራሲያዊ ሂደት ውጤት ነው" ያሉት ፕሮፌሰር መረራ፣ "ይህ ሂደት ዛሬ በኢትዮጵያ የለም። በጦርነት እና በፖለቲካ ስደት ውስጥ ተአማኒነት ያለው ምርጫ ማካሄድ አይቻልም" ሲሉ አክለዋል።
ኦፌኮ በ2018 ዓ.ም አጠቃላይ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ መሠረታዊ ተቋማዊ እና ህጋዊ ማሻሻያዎች እንዲደረጉ የጠየቀ ሲሆን የምርጫ ቦርድን እንደገና ማዋቀርን ጨምሮ የምርጫ ስርዓት ማሻሸያ እንዲደረግ እና ከምርጫ በፊት በገዢው ፓርቲ እና በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል ግልጽ የሆነ ፍኖተ ካርታ ላይ ለመስማማት የሚያስችል ውይይት እንዲካሄድ ጥሪ አቅርቧል።
በተጨማሪም በኦሮሚያና በመላ ኢትዮጵያ ያለው ግጭት እንዲቆም፣ የኦፌኮ አባላት፣ አመራሮችንና ደጋፊዎችን ጨምሮ በመላ አገሪቱ የታሰሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች፣ ጋዜጠኞችና አክቲቪስቶች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ፣ በተቃዋሚዎች ላይ የሚደርሰው ማስፈራራት፣ ወከባና እስራት እንዲቆም እና የጸጥታ ሀይሎች በፖለቲካው ሂደት ውስጥ ገለልተኛ የሚሆኑበት ስምምነት እንዲፈረም ጠይቋል።
ዜና: "የኃይሌ ኃይሎች" የተሰኘና በአንጋፋው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ የስኬት ሚስጥሮች ዙርያ የሚያጠነጥን መጽሐፍ ለምርቃት ሊበቃ ነው
"የኃይሌ ኃይሎች" ወይም 'Dissecting Haile' የተሰኘና በአንጋፋው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ የህይወት ስኬት ሚስጥሮች ዙርያ የሚያጠነጥን መጽሐፍ ለምርቃት ሊበቃ መሆኑ ተገለጸ።
የመጽሐፉን ምረቃ ቅድመ ዝግጅት አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ መርሀግብር ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 28 ቀን 2017 ዓ.ም በኃይሌ ግራንድ ሆቴል ተካሄዷል።
በመርሀግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የመጽሐፉ ደራሲ እና የአትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ልጅ ሜላት ኃይሌ መጽሐፉ ስለ አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ የህይወት ፍልስፍናዎች የሚዳስስ መሆኑን አንስተዋል።
አክለውም መከራን ወደ ተጽዕኖ ለመለወጥ ለሚፈልጉ ሰዎች ምሳሌ የሚሆን እና ከሀይሌ ገብረስላሴ የህይወት ስኬቶች ጀርባ ያሉ ሚስጥሮችን ያካተተ መጽሐፍ መሆኑን ተናግረዋል።
አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ በመርሀግብሩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉ ሲሆን "ብቻን ሆኖ ጀግና መሆን አይቻልም: እኔም ከቤተሰብ ጀምሮ የማህበረሰቤ ውጤት ነኝ" ብለዋል።
አክለውም በመጽሐፉ ላይ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሰዎች ምስጋና አቅርበዋል።
"የኃይሌ ኃይሎች" /Dissecting Haile/ በ12 ምዕራፎች ተከፋፍሎ በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች እንዲሁም በብሬል የተሰናዳ እንደሆነም ተገልጿል።
መጽሐፉ የፊታችን ነሐሴ 2017 ዓ.ም በኤሌክትሮኒክስ እና በሀርድ ኮፒ አማራጮች በይፋ ለአንባቢያን ይቀርባል ተብሏል።
"የኃይሌ ኃይሎች" ወይም 'Dissecting Haile' የተሰኘና በአንጋፋው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ የህይወት ስኬት ሚስጥሮች ዙርያ የሚያጠነጥን መጽሐፍ ለምርቃት ሊበቃ መሆኑ ተገለጸ።
የመጽሐፉን ምረቃ ቅድመ ዝግጅት አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ መርሀግብር ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 28 ቀን 2017 ዓ.ም በኃይሌ ግራንድ ሆቴል ተካሄዷል።
በመርሀግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የመጽሐፉ ደራሲ እና የአትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ልጅ ሜላት ኃይሌ መጽሐፉ ስለ አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ የህይወት ፍልስፍናዎች የሚዳስስ መሆኑን አንስተዋል።
አክለውም መከራን ወደ ተጽዕኖ ለመለወጥ ለሚፈልጉ ሰዎች ምሳሌ የሚሆን እና ከሀይሌ ገብረስላሴ የህይወት ስኬቶች ጀርባ ያሉ ሚስጥሮችን ያካተተ መጽሐፍ መሆኑን ተናግረዋል።
አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ በመርሀግብሩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉ ሲሆን "ብቻን ሆኖ ጀግና መሆን አይቻልም: እኔም ከቤተሰብ ጀምሮ የማህበረሰቤ ውጤት ነኝ" ብለዋል።
አክለውም በመጽሐፉ ላይ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሰዎች ምስጋና አቅርበዋል።
"የኃይሌ ኃይሎች" /Dissecting Haile/ በ12 ምዕራፎች ተከፋፍሎ በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች እንዲሁም በብሬል የተሰናዳ እንደሆነም ተገልጿል።
መጽሐፉ የፊታችን ነሐሴ 2017 ዓ.ም በኤሌክትሮኒክስ እና በሀርድ ኮፒ አማራጮች በይፋ ለአንባቢያን ይቀርባል ተብሏል።
ቶምቦላ እጣ ወጥቷል
ቶምቦላ ሎተሪ 2017 ዕጣ ዛሬ ሰኔ 29 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በዕድል አዳራሽ የወጣ ሲሆን የወጡት የዕጣ ቁጥሮች ከላይ ተያይዟል።
ቶምቦላ ሎተሪ 2017 ዕጣ ዛሬ ሰኔ 29 ቀን 2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት በዕድል አዳራሽ የወጣ ሲሆን የወጡት የዕጣ ቁጥሮች ከላይ ተያይዟል።
አል-ፋሽጋ ዳግም በኢትዮጵያውያን እጅ ገባ
ለዘመናት የኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች የእርሻና የኑሮ መሰረት የነበረው ለም መሬት፣ አል-ፋሽጋ፣ ዳግም ወደ ህጋዊ ባለቤቶቹ ተመልሷል።
የሱዳን ጦር የኢትዮጵያን የውስጥ ችግር እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠር፣ በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎንደር ዞን የሚገኙትን የመተማና የቋራ ወረዳ ለም መሬቶችን በኃይል ተቆጣጥሮ ነበር።
በወቅቱ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በቅርብ ርቀት ላይ ሆኖ ሁኔታውን በትዕግስት ሲከታተል የነበረ ሲሆን፣ መንግሥትም ችግሩን በዲፕሎማሲና በውይይት ለመፍታት ያለውን ፍላጎት በተደጋጋሚ መግለጹ ይታወሳል፡፡
በዚህ የሱዳን ወረራ ወቅት ኢትዮጵያውያን ገበሬዎች ከእርሻቸው ከመፈናቀላቸውም በላይ ከፍተኛ የሆነ የሰብልና የንብረት ውድመት እንደደረሰባቸው አይዘነጋም፡፡
የሱዳን ባለሥልጣናት ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ታጣቂዎች በአገሪቱ መከላከያ ሠራዊት በመታገዝ የአማራ ክልል አዋሳኝ ወደኾኑ የሱዳን ለም መሬቶች በመስፋፋት ላይ ናቸው ሲሉ መክሰሳቸው ተዘግቦ ነበር፡፡
ለዘመናት የኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች የእርሻና የኑሮ መሰረት የነበረው ለም መሬት፣ አል-ፋሽጋ፣ ዳግም ወደ ህጋዊ ባለቤቶቹ ተመልሷል።
የሱዳን ጦር የኢትዮጵያን የውስጥ ችግር እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠር፣ በአማራ ክልል፣ ምዕራብ ጎንደር ዞን የሚገኙትን የመተማና የቋራ ወረዳ ለም መሬቶችን በኃይል ተቆጣጥሮ ነበር።
በወቅቱ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በቅርብ ርቀት ላይ ሆኖ ሁኔታውን በትዕግስት ሲከታተል የነበረ ሲሆን፣ መንግሥትም ችግሩን በዲፕሎማሲና በውይይት ለመፍታት ያለውን ፍላጎት በተደጋጋሚ መግለጹ ይታወሳል፡፡
በዚህ የሱዳን ወረራ ወቅት ኢትዮጵያውያን ገበሬዎች ከእርሻቸው ከመፈናቀላቸውም በላይ ከፍተኛ የሆነ የሰብልና የንብረት ውድመት እንደደረሰባቸው አይዘነጋም፡፡
የሱዳን ባለሥልጣናት ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ታጣቂዎች በአገሪቱ መከላከያ ሠራዊት በመታገዝ የአማራ ክልል አዋሳኝ ወደኾኑ የሱዳን ለም መሬቶች በመስፋፋት ላይ ናቸው ሲሉ መክሰሳቸው ተዘግቦ ነበር፡፡
የሰነደ መዋዕለ ንዋዮች ገበያ በሚቀጥለው ሳምንት ይፋዊ ግብይት ሊጀምር ነው
ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረው የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋዮች ( ስቶክ ገበያ) በሚቀጥለው ሳምንት ሥራ ሊጀምር መሆኑ ተሰምቷል። ይህ እርምጃ ለአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ ታውቋል።
ገበያዉ በኖቬምበር 2023 በተደረገ የካፒታል ማሰባሰቢያ ዘመቻ 1.5 ቢሊዮን ብር በማሰባሰብ ከታሰበው ግብ በ631% በልጧል። ይህ ገንዘብ ከ48 የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ተቋማት የተገኘ መሆኑ ይታወቃል።
በሕዝብና በግል ሽርክና የሚሰራው አዲሱ የበይነመረብ ንግድ ልዉዉጥ መድረክን መንግሥት 25%፣ የግል ዘርፍ ደግሞ 75% ድርሻ አላቸዉ። አሁን ላይ ገዳ ባንክ አ.ማ. እና ወጋገን ካፒታል ኢንቨስትመንት ባንክ አ.ማ. በገበያው ላይ ከተመዘገቡት ኩባንያዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
የሰነደ መዋዕለ ንዋይ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ውስጥ እስከ 50 ኩባንያዎችን፣ በአሥር ዓመታት ውስጥ ደግሞ ከ90 በላይ ንግዶችን ለማካተት አቅዷል። ይህ ልውውጥ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለማዘመን፣ ግልጽነትን ለማሳደግ እና ለንግዶች ካፒታል ማሰባሰቢያ አዳዲስ አማራጮችን ለመስጠት ያለመ ሲሆን፣ የኢኮኖሚ ዕድገትን እንደሚያነቃቃም ይጠበቃል።
ዝርዝሩን ያንብቡ
ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረው የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋዮች ( ስቶክ ገበያ) በሚቀጥለው ሳምንት ሥራ ሊጀምር መሆኑ ተሰምቷል። ይህ እርምጃ ለአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ ታውቋል።
ገበያዉ በኖቬምበር 2023 በተደረገ የካፒታል ማሰባሰቢያ ዘመቻ 1.5 ቢሊዮን ብር በማሰባሰብ ከታሰበው ግብ በ631% በልጧል። ይህ ገንዘብ ከ48 የአገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ተቋማት የተገኘ መሆኑ ይታወቃል።
በሕዝብና በግል ሽርክና የሚሰራው አዲሱ የበይነመረብ ንግድ ልዉዉጥ መድረክን መንግሥት 25%፣ የግል ዘርፍ ደግሞ 75% ድርሻ አላቸዉ። አሁን ላይ ገዳ ባንክ አ.ማ. እና ወጋገን ካፒታል ኢንቨስትመንት ባንክ አ.ማ. በገበያው ላይ ከተመዘገቡት ኩባንያዎች መካከል ይጠቀሳሉ።
የሰነደ መዋዕለ ንዋይ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት ውስጥ እስከ 50 ኩባንያዎችን፣ በአሥር ዓመታት ውስጥ ደግሞ ከ90 በላይ ንግዶችን ለማካተት አቅዷል። ይህ ልውውጥ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለማዘመን፣ ግልጽነትን ለማሳደግ እና ለንግዶች ካፒታል ማሰባሰቢያ አዳዲስ አማራጮችን ለመስጠት ያለመ ሲሆን፣ የኢኮኖሚ ዕድገትን እንደሚያነቃቃም ይጠበቃል።
ዝርዝሩን ያንብቡ
በህዳሴው ግድብ ምርቃት ላይ ፕሬዝደንት ፑቲን ሊጋበዙ ነው
የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን በመጪው መስከረም ወር በሚደረገው የህዳሴ ግድብ ምርቃት ስነስርአት እንዲገኙ ግብዣ ሊላክላቸው መሆኑ ተሰማ፡፡
ስፑትኒክ የተሰኘው የሩሲያ ሚዲያ ዛሬ እንደዘገበው በግድቡ መክፈቻ ስነስርአት ላይ ፑቲን እንዲገኙ የኢትዮጵያ መንግስት ግብዣ ሊላክላቸው ይችላል፡፡ ይሁንና ግብዣው ቢላክ ፕሬዝደንቱ ለመገኘት ፈቃደኛ ስለመሆንና አለመሆናቸው ያለው ነገር የለም፡፡ የሩሲያው ፕሬዝደንት ፑቲን በአለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት በቀረበባቸው ክስ የእስር ማዘዣ የተቆረጠባቸው መሆኑ ይታወቃል፡፡
በአሁኑ ወቅት በብራዚል እየተካሄደ ባለው የብሪክስ የመሪዎች ስብሰባ ላይ በአካል ያልተገኙትም ለዚህ ነው፡፡ ስለጉዳዩ የተጠየቁት የክሬሚሊን አማካሪ ዩሪ ኡሻኮቭ ‹‹ከአይሲሲ ሁኔታዎች ጋር በተያያዘ ፕሬዝደንት ፑቲን በአካል ብራዚል ለመገኘት አይችሉም›› ሲሉ ባለፈው ሳምንት ተናግረው ነበር፡፡
በመሆኑም በስብሰባው ላይ በቪዲዮ ኮንፈረንስ እንደሚሳተፉ ማስታወቃቸው አይዘነጋም፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ኢትዮጵያ የአለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት(አይሲሲ) አባል አይደለችም፡፡ በሮም ፍርድ ቤቱን በተመለከተ የተፈረመውን ስምምነት ባለመፈረሟ የፍርድ ቤቱን ትእዛዝ የማስፈፀም ግዴታ እንደሌለባት ዘገባዎች ገልፀዋል፡፡
የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን በመጪው መስከረም ወር በሚደረገው የህዳሴ ግድብ ምርቃት ስነስርአት እንዲገኙ ግብዣ ሊላክላቸው መሆኑ ተሰማ፡፡
ስፑትኒክ የተሰኘው የሩሲያ ሚዲያ ዛሬ እንደዘገበው በግድቡ መክፈቻ ስነስርአት ላይ ፑቲን እንዲገኙ የኢትዮጵያ መንግስት ግብዣ ሊላክላቸው ይችላል፡፡ ይሁንና ግብዣው ቢላክ ፕሬዝደንቱ ለመገኘት ፈቃደኛ ስለመሆንና አለመሆናቸው ያለው ነገር የለም፡፡ የሩሲያው ፕሬዝደንት ፑቲን በአለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት በቀረበባቸው ክስ የእስር ማዘዣ የተቆረጠባቸው መሆኑ ይታወቃል፡፡
በአሁኑ ወቅት በብራዚል እየተካሄደ ባለው የብሪክስ የመሪዎች ስብሰባ ላይ በአካል ያልተገኙትም ለዚህ ነው፡፡ ስለጉዳዩ የተጠየቁት የክሬሚሊን አማካሪ ዩሪ ኡሻኮቭ ‹‹ከአይሲሲ ሁኔታዎች ጋር በተያያዘ ፕሬዝደንት ፑቲን በአካል ብራዚል ለመገኘት አይችሉም›› ሲሉ ባለፈው ሳምንት ተናግረው ነበር፡፡
በመሆኑም በስብሰባው ላይ በቪዲዮ ኮንፈረንስ እንደሚሳተፉ ማስታወቃቸው አይዘነጋም፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ኢትዮጵያ የአለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት(አይሲሲ) አባል አይደለችም፡፡ በሮም ፍርድ ቤቱን በተመለከተ የተፈረመውን ስምምነት ባለመፈረሟ የፍርድ ቤቱን ትእዛዝ የማስፈፀም ግዴታ እንደሌለባት ዘገባዎች ገልፀዋል፡፡
በመዲናዋ ለ2018 የትምህርት ዘመን የነባር እና አዲስ ተማሪዎች ምዝገባ እንዲሁም የመፀሀፍ ስርጭት የሚካሄደው ከሐምሌ 1 እስከ ነሃሴ 23/2017 ዓ/ም መሆኑ ታውቋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ/ም የትምህርት ቀናትን ዛሬ ይፋ አድርጓል ለ11ዱም ክ/ከተማ የትምህርት ፅ/ቤቶች ልኳል።
በዚሁ ካላንደር መሰረት ምዝገባ ከሃምሌ 1 እስከ ነሔሴ 23 /2017 ዓ/ም ይካሄዳል።
መምህራን በትምህርት ቤታቸው ተገኝተው ሪፖርት የሚያደርጉበት እንዲሁም አጠቃላይ የመምህራን ጉባኤ የሚደረገው ነሃሴ 28 እና ነሃሴ 29/2017 ዓ/ም እንደሆነ ተመላክቷል።
ከነሃሴ 24 እስከ ጳጉሜ 5/2017 ዓ/ም ደግሞ የ7ኛና የ9ኛ ክፍል ከአዲስ አበባ ውጭ ለሚመጡ አዲስ ተመዝጋቢዎች ተማሪዎች ምዝገባ ይከናወናል።
መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ/ም የመጀመሪያው ቀን የመጀመሪያ መደበኛ ትምህርት ክፍለ ጊዜ (day one class one) እንደሆነ ይፋ ተደርጓል።
በ2018 ዓ/ም የሚሰጠው የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና እንደሚሰጥ በትምህርት ካላንደሩ ላይ ታሳቢ ተደርጓል።
(ሙሉውን ከላይ ይመለከቱ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ/ም የትምህርት ቀናትን ዛሬ ይፋ አድርጓል ለ11ዱም ክ/ከተማ የትምህርት ፅ/ቤቶች ልኳል።
በዚሁ ካላንደር መሰረት ምዝገባ ከሃምሌ 1 እስከ ነሔሴ 23 /2017 ዓ/ም ይካሄዳል።
መምህራን በትምህርት ቤታቸው ተገኝተው ሪፖርት የሚያደርጉበት እንዲሁም አጠቃላይ የመምህራን ጉባኤ የሚደረገው ነሃሴ 28 እና ነሃሴ 29/2017 ዓ/ም እንደሆነ ተመላክቷል።
ከነሃሴ 24 እስከ ጳጉሜ 5/2017 ዓ/ም ደግሞ የ7ኛና የ9ኛ ክፍል ከአዲስ አበባ ውጭ ለሚመጡ አዲስ ተመዝጋቢዎች ተማሪዎች ምዝገባ ይከናወናል።
መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ/ም የመጀመሪያው ቀን የመጀመሪያ መደበኛ ትምህርት ክፍለ ጊዜ (day one class one) እንደሆነ ይፋ ተደርጓል።
በ2018 ዓ/ም የሚሰጠው የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና እንደሚሰጥ በትምህርት ካላንደሩ ላይ ታሳቢ ተደርጓል።
(ሙሉውን ከላይ ይመለከቱ)
ትራምፕ እስከ 40% የሚደርስ አዲስ ታሪፍ በበርካታ ሀገራት ላይ እንደሚጥሉ አስታወቁ
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በአሜሪካ የንግድ አጋሮች ላይ ጫና ለመፍጠር አዲስ እስከ 40% የሚደርስ ታሪፍ እንደሚጥሉ በበርካታ ሀገራት መሪዎች ላይ በላኳቸው ደብዳቤዎች አስታውቀዋል። ይህ እርምጃ የተወሰደው ቀደም ሲል የነበረውን የታሪፍ ቀነ ገደብ ከጁላይ 9 ወደ ኦገስት 1 ካራዘሙ በኋላ ነው።
ትራምፕ፣ ጃፓንንና ደቡብ ኮሪያን ጨምሮ ለተለያዩ ሀገራት በላኳቸው ደብዳቤዎች 25% ታሪፍ እንደሚጥሉ ሲገልጹ፣ ለማሌዥያ፣ ካዛኪስታን፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ምያንማር እና ላኦስ የተላኩ ተመሳሳይ ደብዳቤዎች ደግሞ እስከ 40% የሚደርስ ታሪፍ እንደሚያስከትሉ ተዘግቧል። ዋይት ሀውስ በድምሩ ወደ 12 የሚጠጉ ደብዳቤዎች እንደሚላኩ አስታውቋል።
ትራምፕ በእነዚህ ደብዳቤዎች ላይ እንደ ምክንያት የጠቀሱት፣ አሜሪካ ከእነዚህ ሀገራት ጋር ያላትን የንግድ ጉድለት (አሜሪካ ከምትልከው ይልቅ የምትገዛው ምርት መብዛት) እና የአሜሪካ ምርቶች ወደ ውጭ እንዳይላኩ የሚያግዱ ፖሊሲዎችን ነው። ሀገራቱ ታሪፉን ለማስቀረት ምርቶቻቸውን በአሜሪካ ውስጥ እንዲያመርቱ አበረታተዋል።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው የቀድሞው የታሪፍ ቀነ ገደብ ሊያልቅ ሲል ሲሆን፣ ዋይት ሀውስ የጊዜ ገደቡን እስከ ነሐሴ ማራዘሙ "ለአሜሪካ ህዝብ ጥቅም" እንደሆነ ገልጿል።
ትራምፕ በላኳቸው ሰባቱም ደብዳቤዎች ላይ፣ ሀገራት በአሜሪካ ላይ በቀል ታሪፍ ከጣሉ፣ ከተጠቀሰው መጠን በላይ ታሪፉን ከፍ እንደሚያደርጉ አስጠንቅቀዋል። ሆኖም፣ እነዚህ አዳዲስ ታሪፎች ቀደም ሲል በነበሩ የዘርፍ ታሪፎች ላይ እንደማይጨመሩ ተረጋግጧል።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በአሜሪካ የንግድ አጋሮች ላይ ጫና ለመፍጠር አዲስ እስከ 40% የሚደርስ ታሪፍ እንደሚጥሉ በበርካታ ሀገራት መሪዎች ላይ በላኳቸው ደብዳቤዎች አስታውቀዋል። ይህ እርምጃ የተወሰደው ቀደም ሲል የነበረውን የታሪፍ ቀነ ገደብ ከጁላይ 9 ወደ ኦገስት 1 ካራዘሙ በኋላ ነው።
ትራምፕ፣ ጃፓንንና ደቡብ ኮሪያን ጨምሮ ለተለያዩ ሀገራት በላኳቸው ደብዳቤዎች 25% ታሪፍ እንደሚጥሉ ሲገልጹ፣ ለማሌዥያ፣ ካዛኪስታን፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ምያንማር እና ላኦስ የተላኩ ተመሳሳይ ደብዳቤዎች ደግሞ እስከ 40% የሚደርስ ታሪፍ እንደሚያስከትሉ ተዘግቧል። ዋይት ሀውስ በድምሩ ወደ 12 የሚጠጉ ደብዳቤዎች እንደሚላኩ አስታውቋል።
ትራምፕ በእነዚህ ደብዳቤዎች ላይ እንደ ምክንያት የጠቀሱት፣ አሜሪካ ከእነዚህ ሀገራት ጋር ያላትን የንግድ ጉድለት (አሜሪካ ከምትልከው ይልቅ የምትገዛው ምርት መብዛት) እና የአሜሪካ ምርቶች ወደ ውጭ እንዳይላኩ የሚያግዱ ፖሊሲዎችን ነው። ሀገራቱ ታሪፉን ለማስቀረት ምርቶቻቸውን በአሜሪካ ውስጥ እንዲያመርቱ አበረታተዋል።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው የቀድሞው የታሪፍ ቀነ ገደብ ሊያልቅ ሲል ሲሆን፣ ዋይት ሀውስ የጊዜ ገደቡን እስከ ነሐሴ ማራዘሙ "ለአሜሪካ ህዝብ ጥቅም" እንደሆነ ገልጿል።
ትራምፕ በላኳቸው ሰባቱም ደብዳቤዎች ላይ፣ ሀገራት በአሜሪካ ላይ በቀል ታሪፍ ከጣሉ፣ ከተጠቀሰው መጠን በላይ ታሪፉን ከፍ እንደሚያደርጉ አስጠንቅቀዋል። ሆኖም፣ እነዚህ አዳዲስ ታሪፎች ቀደም ሲል በነበሩ የዘርፍ ታሪፎች ላይ እንደማይጨመሩ ተረጋግጧል።
የእነ ጌታቸው ረዳ ስምረት ፓርቲ መግለጫ አወጣ
በመግለጫው የትግራይ ጉዳይ ከመጥፎ ወደባሰና ውስብስብነት እየተሸጋገረ መሆኑን በመጥቀስ የጀመረው መግለጫው ለዚህም ተጠያቂ ያደረገው ‹‹ኮርና ከዚያ በላይ›› የሆኑትን ወታደራዊ አመራሮች ነው፡፡
እነዚህ ወታደራዊ አመራሮች ባለፈው ጥር ወር አጋማሽ ላይ የመንግስትን መዋቅር በሀይል ማፍረሳቸውንና በወጣቶች ላይ ተኩስ እንዲከፈት ማድረጋቸውን ያወሳው ስምረት ፓርቲ ጨምሮም ‹‹ይህ ቡድን የአገሪቱንና የትግራይን ህገ መንግስት በመጣስ ከኤርትራ መንግስት ጋር በማበር በትግራይና በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት ለማወጅ እስከመሰናዳት ደርሷል፡፡›› ብሏል፡፡
ሲቀጥልም ይህ ቡድን በአፋር ክልል በኩል ተደጋጋሚ ትንኮሳ እያደረገ መሆኑን የጠቀሰው ስምረት ደቡባዊ ትግራይን በሀይል ለመቆጣጠር መዘጋጀቱንም ጠቅሷል፡፡ የስምረት መግለጫ ሲቀጥል ‹‹ተፈናቃዮች እንዳይመለሱና የትግራይ ህገ መንግስታዊ መሬት ከጦርነቱ በፊት ወደነበረበት እንዳይመለስ እያደረገ ያለው ይህ ኋላ ቀርና አምባገነናዊ ቡድን ነው፡፡
ይህ ቡድንና በጊዜያዊ አስተዳደሩ ውስጥ ያሉ ተላላኪዎቹ ሌላ እድል ካገኙ ከሻእቢያ ጋር ጦርነት ከፍተው የህዝባችንን ችግር ወደባሰ ሁኔታ ውስጥ ይከታሉ›› በማለት አሳስቧል፡፡ በመሆኑም መላው ሰላም ፈላጊ የትግራይ ወጣቶች፣ ምሁራን፣ ፖለቲከኞች፣ ዲያስፖራዎችና የሀይማኖት አባቶች እንዲሁም ሽማግሌዎች ይህ ቡድን አፍራሽ እንቅስቃሴውን እንዲያቆም መታገል እንዳለባቸው ጥሪ አቅርቧል፡፡ ለፌዴራል መንግስቱም ተመሳሳይ ማሳሰቢያ ሰጥቷል ሲል የዘገበው ዘሃበሻ ነዉ፡፡
በመግለጫው የትግራይ ጉዳይ ከመጥፎ ወደባሰና ውስብስብነት እየተሸጋገረ መሆኑን በመጥቀስ የጀመረው መግለጫው ለዚህም ተጠያቂ ያደረገው ‹‹ኮርና ከዚያ በላይ›› የሆኑትን ወታደራዊ አመራሮች ነው፡፡
እነዚህ ወታደራዊ አመራሮች ባለፈው ጥር ወር አጋማሽ ላይ የመንግስትን መዋቅር በሀይል ማፍረሳቸውንና በወጣቶች ላይ ተኩስ እንዲከፈት ማድረጋቸውን ያወሳው ስምረት ፓርቲ ጨምሮም ‹‹ይህ ቡድን የአገሪቱንና የትግራይን ህገ መንግስት በመጣስ ከኤርትራ መንግስት ጋር በማበር በትግራይና በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት ለማወጅ እስከመሰናዳት ደርሷል፡፡›› ብሏል፡፡
ሲቀጥልም ይህ ቡድን በአፋር ክልል በኩል ተደጋጋሚ ትንኮሳ እያደረገ መሆኑን የጠቀሰው ስምረት ደቡባዊ ትግራይን በሀይል ለመቆጣጠር መዘጋጀቱንም ጠቅሷል፡፡ የስምረት መግለጫ ሲቀጥል ‹‹ተፈናቃዮች እንዳይመለሱና የትግራይ ህገ መንግስታዊ መሬት ከጦርነቱ በፊት ወደነበረበት እንዳይመለስ እያደረገ ያለው ይህ ኋላ ቀርና አምባገነናዊ ቡድን ነው፡፡
ይህ ቡድንና በጊዜያዊ አስተዳደሩ ውስጥ ያሉ ተላላኪዎቹ ሌላ እድል ካገኙ ከሻእቢያ ጋር ጦርነት ከፍተው የህዝባችንን ችግር ወደባሰ ሁኔታ ውስጥ ይከታሉ›› በማለት አሳስቧል፡፡ በመሆኑም መላው ሰላም ፈላጊ የትግራይ ወጣቶች፣ ምሁራን፣ ፖለቲከኞች፣ ዲያስፖራዎችና የሀይማኖት አባቶች እንዲሁም ሽማግሌዎች ይህ ቡድን አፍራሽ እንቅስቃሴውን እንዲያቆም መታገል እንዳለባቸው ጥሪ አቅርቧል፡፡ ለፌዴራል መንግስቱም ተመሳሳይ ማሳሰቢያ ሰጥቷል ሲል የዘገበው ዘሃበሻ ነዉ፡፡