Telegram Web Link
Live stream finished (4 hours)
♦️♦️♦️መርከዝ አቢ አዩብ የቁርዐን ሂፍዝ እና መሰረታዊ የሸሪአ ዱሩሶች ማዕከል

  ወንድም እና  እህቶች መርከዝ አቡ አዩብ የቁርአን እና መሰረታዊ የሸሪዓ ዱሩሶች ማዕከል በ ONLINE ተማሪወችን  በተለያዩ የትምህርት አይነቶች ተቀብሎ ማስተማር ከጀመረ አመታቶች  ተቆጥረዋል

ከዚህም በተጨማሪ በአካል መማር ለሚፈልጉ

⇨በአዳሪ መርሃ ግብር ለወንዶች
⇨ በተመላላሽ መርሃ ግብር ለወንዶች (ለአዋቂ ና ለህፃናቶች)
⇨በተመላላሽ መርሃ ግብር ለሴቶች (ለአዋቂ ና ለህፃናቶች)

🌐አድራሻ: ወሎ ኮንቦልቻ በርበሬ ወንዝ ዶናት 100ሜ ገባ ብሎ 

“የትምህርት አሰጣጣችንን እና ጥራት  በተመለከተ ተማሪዎቻችን ምስክር ናቸው”


ይህ ማዕከል ቱክረት የሚሰጥባቸው ትምህርቶች

♦️ከቃኢደቱ አን ኑራኒያቁርአን ሂፍዝ ድረስ
♦️የአቂዳህ ትምህርቶች በደረጃ
♦️የተጅዊድ ኪታብ
♦️  አረበኛ የሰዋሰው እውቀቶች


    ♻️ትምህርቱ የሚሰጠው በቴሌግራም በላይቭ ላይ  ነው 

የቂርአት ክፍለ ጊዜ ለ ONLINE ተማሪዎች

↪️ከሱበሂ ሶላት— 1:00
↪️ጧት 5:00⇨ ዙሁር ሶላት ድረስ
↪️ከ 8:00⇨አስር ሶላት
↪️ከኢሻ ሶላት  በኃላ ⇨5:00 ሰአት

በነዚህ ሰአቶች በፈለጋችሁበት ገብታችሁ ማሰማት ትችላላችሁ

ለመመዝገብ እነዚህን  ዩዘሮችን ይጠቀሙ 

  ♦️@Attewhid11


በስልክ

📲 +251925887118
📲 +251935564734
📲 +251912899894

አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከተግባር ጋር ይወፍቀን

አሚን

  ወደጉሩባችን ለመቀላቀል
     ⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️
https://www.tg-me.com/Merkez_Abi_Ayub
https://www.tg-me.com/Merkez_Abi_Ayub

  ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል
https://www.tg-me.com/abutoiba
https://www.tg-me.com/abutoiba
Forwarded from Abul Abas || معلم القرآن
🔴አስደሳች   ዜና ለሴቶች
🙁🙁🙁🙁🙁🙁☹️🥳

🗂 ለሴቶች አዳሪ መርከዝ ተከፈተ

🆕መርከዝ አቡ ሙሳ አል አሽ-ዐሪ ለሴቶች በአዳሪ መርኀግብር ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቆ ምዝገባ ላይ ይገኛል። የምንቀበለው የተማሪ ብዛት ውስን ስለሆነ ቦታ ሳይሞላበዎት ፈጥነው ይመዝገቡ

🔴መሟላት ያለባቸው መስፈርቶ
🔸እድሜ ከ10 - 25 ዓመት ባለው
🔸ክፍያ በአግባቡ መክፈል የምትችል
🔸ከተላላፊ በሽታ ነፃ የሆነች
🔸 ያለ ቤተሰብ ግፊት አምናበት የምትመጣ ተማሪ ።
🔸ለመርከዙ ህግና ደንቦች ተገዢ መሆን የምትችል
🔸ከመርከዙ የሚቀርቡ ምግቦችን የለ መረጣ መመገብ የምትችል 

🗂አድራሻ: አንፎ ድልድይ ፀሀይ ግሮሰሪ አከባቢ

🗂ለምዝገባ እና ለበለጠ መረጃ፡
+251928844757 +251930547776
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
በጀነት የተመሰከረላቸው ሶሐቦች
~
በስም ተጠቅሰው የጀነት እንደሆኑ የተመሰከረላቸው ሶሐቦች ቁጥራቸው ከ30 በላይ ነው። ዝርዝራቸውን ለመጠቆም ያህል፦

1- 0ብዱላህ ብኑ ዑሥማን (አቡበክር ሲዲቅ)
2- ዑመር ብኑል ኸጧብ
3- ዑሥማን ብኑ ዐፋን
4- ዐሊይ ብኑ አቢ ጧሊብ
5- ጦልሐቱ ብኑ ዑበይዲላህ
6- ዙበይር ብኑል ዐዋም
7- 0ብዱረሕማን ብኑ ዐውፍ
8- ሰዕድ ብኑ አቢ ወቃስ
9- ሰዒድ ብኑ ዘይድ
10- ዓሚር ብኑጀራሕ (አቡ ዑበይደህ)

እነዚህ በአንድ ሐዲሥ የተዘረዘሩ ናቸው። [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 50]

11. ዘይድ ብኑ ሓሪሠህ
12. ጀዕፈር ብኑ አቢ ጧሊብ
13. 0ብዱላህ ብኑ ረዋሐህ
እነዚህ ሶስቱም የሙዕታህ ዘመቻ ላይ ሲሞቱ ሸሂድ እንደሆኑ ነብያችን ﷺ ገልፀዋል። [ሙስነድ አሕመድ፡ 22551]
በተጨማሪም "ጀዕፈርን ከመላእክት ጋር ጀነት ውስጥ ሲበር አይቼዋለሁ'' ብለዋል። [አሶሒሐህ፡ 1226]

14. ያሲር ብኑ ዓሚር (የዐማር አባት)
15. ሱመያ ቢንቲ ኸያጥ (የዐማር እናት)
16. ዐማር ብኑ ያሲር
በአጋሪዎች ሲሰቃዩ ጊዜ ነብያችን ﷺ "የያሲር ቤተሰብ ታገሱ። ቃል የተገባላችሁ ቦታ ጀነት ነው" ብለዋቸዋል። [ፊቅሁ ሲረህ፣ አልባኒይ፡ 103]

17. አልሐሰን ብኑ ዐሊይ እና
18. አልሑሰይን ብኑ ዐሊይ
ነብያችን ﷺ "የጀነት ወጣቶች" ብለው ገልፀዋቸዋል። [ቲርሚዚይ፡ 3768]

19. ኸዲጀህ ቢንቲ ኹወይሊድ [አልቡኻሪይ: 1699] [ሙስሊም: 2433]
20. ፋጢመህ ቢንቲ ሙሐመድ [አልቡኻሪይ: 3623] [ሙስሊም: 2450]
21. ዓኢሻህ ቢንቲ ሲዲቅ [አልቡኻሪይ: 6687]
22. ሰዕድ ብኑ ሙዓዝ [አልቡኻሪይ፡ 3592፣ 5498] [ሙስሊም፡ 2461]
23. ሑዘይፈቱ ብኑል የማን [ሙስሊም፡ 1788]

24. ሓሪሠህ ብኑ ሱራቀህ
ነብዩ ﷺ ለእናቱ "ጀነት'ኮ ብዙ ደረጃዎች ነው ያሏት። ልጅሽ ላይኛዋን ፊርደውስ ነው ያገኘው" ብለዋል። [አልቡኻሪይ፡ 2809]

25. ቢላል ብኑ ረባሕ
ነብዩ ﷺ "በጀነት ውስጥ የጫማዎችህን ኮቴ ከፊቴ ሰማሁ" ብለዋቸዋል። [አልቡኻሪይ፡ 1098] [ሙስሊም፡ 2458]

26. ዑካሸህ ብኑ ሚሕሶን
ያለ ሂሳብ፣ ያለ ቅጣት ጀነት ከሚገቡ ልዩ ሰባ ሺ ሰዎች ውስጥ አንዱ ናቸው። [አልቡኻሪይ፡ 5378] [ሙስሊም፡ 549]

27. ኡሙ ሱለይም ሩመይሷህ ቢንቲ መልሐን (የአነስ ብኑ ማሊክ እናት) [አልቡኻሪይ፡ 3476] [ሙስሊም፡ 2456]
28. ዐብዱላህ ብኑ ሰላም [አልቡኻሪይ: 3601] [ሙስሊም: 2483]
29. ሣቢት ብኑ ቀይስ ብኒ ሸማስ [አልቡኻሪይ ፡ 4565] [ሙስሊም፡ 119]
30. ዐምር ብኑ ቀይስ (ኡሶይሪም) [ሙስነድ አሕመድ፡ 23634]
31. ዐብዱላህ ብኑ ዐምር (የጃቢር አባት) [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 7905]
32. ዐምር ብኑል ጀሙሕ [ፊቅሁ ሲረህ፣ አልባኒይ፡ 262]
33. አቡ ደሕዳሕ አልአንሷሪይ [ሙስሊም፡ 965]
34.ሐፍሷህ ቢንቲ ዑመር [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 4351]
35. ኡሙ ዙፈር አልሐበሺየህ [አልቡኻሪይ: 3528] [ሙስሊም: 2576]

ከዚህ የስም ዝርዝር ባለፈ በቡድን ደረጃ የበድር ዘመቻ ዘማቾች እና የበይ0ተ ሪድዋን ተካፋዮችም የጀነት ናቸው። [አልቡኻሪይ: 4890] [ሙስሊም: 2494] [ሶሒሕ አቢ ዳውድ፡ 4653]
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
ስልጣን አገልጋይነት ነው
~
አንድ ሰው አጠቃላይ የሃገር መሪም ይሁን ከዚያ ባነሰ ታች ላይ የሚገኝ የስልጣን እርከንም ላይ ይሁን ስልጣኑ ያሻውን ለማድረግ ነፃ የሚያደርገው ሳይሆን ህዝብን ለማገልገል የተቀመጠ የቅጥር ሰራተኛ እንደሆነ ሊያውቅ ይገባል። ስለዚህ በየትኛውም የኃላፊነት ወንበር ላይ የተቀመጣችሁ ወገኖች ባጠቃላይ በተግባር የህዝብ አገልጋይ ተቀጣሪ ሁኑ። እንጂ ስልጣናችሁን ህዝብን ለማጉላላትና ለማንገለታታት፣ ራስን በተለየ ለመጥቀም አትጠቀሙበት። ይህንን እውነታ አጉልቶ የሚያሳይ አንድ ታሪክ ልጥቀስ።

አቡ ሙስሊም አልኸውላኒይ ረሒመሁላህ ከኸሊፋው ሙዓዊያ ቢን አቢ ሱፍያን ረዲየላሁ ዐንሁ ዘንድ ገቡና

* "አሰላሙ ዐለይከ! አንተ የቅጥር ሰራተኛ!" አሉ።
- በዙሪያው የነበሩት ሰዎች "አሰላሙ ዐለይከ! አንተ አሚር (አዛዥ) በል!" አሉ።
* እርሳቸው ግን "አሰላሙ ዐለይከ! አንተ የቅጥር ሰራተኛ!" አሉ።
- ሰዎቹ እንደገና "አሰላሙ ዐለይከ! አንተ አሚር (አዛዥ) በል!" አሉ።
* እርሳቸው ግን አሁንም "አሰላሙ ዐለይከ! አንተ የቅጥር ሰራተኛ!" አሉ።
- ሰዎቹ ለሶስተኛ ጊዜ "አሰላሙ ዐለይከ! አንተ አሚር (አዛዥ) በል!" አሉ።

ሙዓዊያ በዚህን ጊዜ ፡ "አቡ ሙስሊምን ተውት፤ እርሱ የሚለውን ጠንቅቆ የሚያውቅ ነው" አሉ።

ከዚያም አቡ ሙስሊም ለሙዓዊያ እንዲህ አሉ፡- "አንተ የነዚህ በጎች ጌታ ለጥበቃቸው የቀጠረህ ቅጥር ሰራተኛ ነህ። የተጎዱትን ብትንከባከብ፣ የታመሙትን ብታክም እና ጉልበተኞቹን ከደካሞቹ ብታቅብ ጌታህ ደሞዝህን ይሞላልሃል። ነገር ግን የተጎዱትን ባትንከባከብ፣ የታመሙትን ባታክም እና ጉልበተኞቹን ከደካሞቹ ባታቅብ ጌታህ ይቀጣሃል!" [ሒልየቱል አውሊያእ፡ 2/125] [ታሪኹ ዲመሸቅ፡ 27/223፣ 67/218]

አዎ ስልጣን፣ ሹመት፣ አለቅነት ተጠያቂት ነው። ሸክም ነው። ስለዚህ ትንሽም ይሁን ትልቅ ኃላፊነት ላይ የተቀመጠ ሁሉ ልቡ እንዳያብጥ፣ ጥጋብ እንዳይሰማው አላህን ያስብ። ነፍሲያውን ይርገጥ። ትእቢቱን ያስተንፍስ። አገልጋይነትን፣ ትህትናን ይላበስ። ይህ ሲሆን የአላህ እገዛ ከሱ ጋር ይሆናል። ከአላህም ዘንድ ከሰውም ዘንድ የተወደደ ይሆናል።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
የደዕዋ ጥሪ ለሁሉም ሙስሊሞች
~
የፊታችን ጁሙዐ ምሸት 3፡00 ላይ ታላቅ የደዕዋ ፕሮግራም ይኖራል ኢንሻአላህ።

ተጋባዥ : - የተከበሩ ሸይኽ 0ሊይ ብኑ አሕመድ አራዚሒይ
فضيلة الشيخ علي بن أحمد الرازحي

* ሸይኹ በርካታ ኪታቦችን ያዘጋጁ እና ብዙ ዱሩሶች ያሏቸው ታዋቂ የየመን ዓሊም ናቸው።

* ዐረብኛ ለማይችሉ ከትርጉም ጋር አብሮ ይቀርባል።
* የሚተላለፍበት የቴሌግራም ቻናል ይሄ ነው፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor

* ማስታወቂያውን በማሰራጨት የኸይሩ ተካፋይ ይሁኑ።
إنا لله وإنا إليه راجعون
رحم الله الشيخ ربيع بن هادي رحمة واسعة
وغفر له
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የሰለፎች ኪታቦች ይዳኙን!
~
ሱብሓነላህ! ምንኛ ወኔ የሚቀሰቅስ ንግግር ነው! ጀግና ነበሩ ረቢዕ፣ የቃልም የተግባርም ሙጃሂድ። በሐቅ ላይ የወቃሽ ወቀሳ የማያስጨንቃቸው፣ የይሉኝታ ትብታብ፣ የመንጋ ግርግር የማያስደነግጣቸው። ይሄው ማንም ወደማይቀርበት ሃገር ሄደዋል። አላህ በፊርደውሱ ያሞናድላቸው!

ስሙ አልፎ የናኘው - ከወዳጅ ከጠላት
አባ ቅጣው ረቢዕ - የኢኽዋን መድሃኒት!!
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
📖 قال الله تعالى:
﴿ وَاعْتَصِمُواْ بِحَبْلِ اللّهِ جَمِيعًا وَلاَ تَفَرَّقُواْ ﴾.

🎙 الشيخ الوالد/ ربيع بن هادي المدخلي - رحمه الله -.
==

የቴሌግራም ቻናል :-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
የደዕዋ ጥሪ ለሁሉም ሙስሊሞች
~
የፊታችን ጁሙዐ ምሸት 3፡00 ላይ ታላቅ የደዕዋ ፕሮግራም ይኖራል ኢንሻአላህ።

ተጋባዥ : - የተከበሩ ሸይኽ 0ሊይ ብኑ አሕመድ አራዚሒይ
فضيلة الشيخ علي بن أحمد الرازحي

* ሸይኹ በርካታ ኪታቦችን ያዘጋጁ እና ብዙ ዱሩሶች ያሏቸው ታዋቂ የየመን ዓሊም ናቸው።

* ዐረብኛ ለማይችሉ ከትርጉም ጋር አብሮ ይቀርባል።
* የሚተላለፍበት የቴሌግራም ቻናል ይሄ ነው፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor

* ማስታወቂያውን በማሰራጨት የኸይሩ ተካፋይ ይሁኑ።


دعوة لحضور محاضرة للشيخ علي بن أحمد الرازحي - حفظه الله تعالى- من علماء اليمن السلفيين
يوم الجمعة تاريخ 11-7-2025 م  الساعة التاسعة مساء بتوقيت مكة المكرمة 🇸🇦  الثالثة مساء بتوقيت إثيوبيا 🇪🇹
يلقيها إلى إخوانه في بلاد الحبشة عبر الإنترنت والدعوة عامة لطلاب العلم والمسلمين أجمعين ويوجد ترجمة لمن لا يفهم اللغة العربية وذلك على قناة ابن منور بالتليجرام من خلال الرابط التالي:

https://www.tg-me.com/IbnuMunewor

أسأل الله أن ينفع بهذه المحاضرة ويجزي الشيخ و الإخوة المشرفين والمترجمين خير الجزاء إنه ولي ذلك والقادر عليه.
~ሁላችንም በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው፣ ከታላቁ ዓሊም ሸይኽ ዓሊይ ብኑ አሕመድ አራዚሒይ የሚተላለፈው የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም ሊጀመር ጥቂት ደቂቃዎች ቀርተውታል።

https://www.tg-me.com/IbnuMunewor?livestream=9b5f6234af43db499a
Live stream finished (1 hour)
Forwarded from Fuad Mohammed (فؤاد محمد)
ስለ ትናንቱ የኦንላይን ደዕዋ
~
በቅድሚያ አላህ ስላገራውም ስላደለንም አልሐምዱ ሊላህ። በመቀጠል ጊዜያቸውን ሰጥተው ውድ ምክሮችን ያካፈሉንን ሸይኽ ዐሊይ አራዚሒይን ከልብ እናመሰግናለን። እንዲሁም ለሃሳቡ መነሻ የሆኑ ወንድሞችን ዐብዱልፈታሕ ሙሐመድዘይን (የመን በዒልም ፍለጋ ላይ ያለ ወንድማችን ነው)፣ አሕመድኑር ኸዲር ከወሎ ወረባቦ፣ ደዕዋውን በመተርጎም ላይ ያገዙ አቡል 0ባስ ናሲር፣ ዐብዱረዛቅ ባጂ፣ አቡ ሱፍያን እና የመን ከሸይኽ ዐሊይ ጋር ያለ ሌላ የሃገራችን ልጅ (ኻሊድ?) ሁላችሁንም ጀዛኩሙላሁ ኸይረን።

ለታዳሚዎች ባጠቃላይ ለተፈጠረው የኔትዎርክ ችግር - ከኛ ቁጥጥር ውጭ ቢሆንም - ይቅርታ እየጠየቅን ፕሮግራሙን ስለታደማችሁ በጣም ደስ ብሎናል። አላህ በሰማችሁት የምትጠቀሙ ያድርጋችሁ። ለወደፊቱም በአላህ ፈቃድ ከሌሎች መሻይኾች ጋርም በመነጋገር ተመሳሳይ ፕሮግራም ለማዘጋጀት ሃሳቡ አለን። እንደዚሁም በሃገር ውስጥ መሻይኾች እና ኡስታዞችም ለማስተላለፍ የምናስብበት ይሆናል ኢንሻአላህ።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
ለህፃን ሙሐመድ እንድረስለት። ጉዳቱ የከፋ ነው። ለውጭ ህክምና የተደረገው የድጋፍ መጠን ስላልምላለ በምንችለው ብናግዘው መልካም ነው። ዱዓም እናድርግለትለት።


✔️የባንክ አካውንቶች፦
Account Name: Ziyad Nuredin

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦1000525385373
ዳሽን ባንክ: 2933592396721
አዋሽ ባንክ: 01425898257700
አቢሲንያ ባንክ:  29173998 
ኦሮሚያ ባንክ:  1756167200001
ቴሌብር: 0912844116


(ለበለጠ መረጃ):
+251912844116 (ዚያድ )   አባት
2025/07/14 12:16:22
Back to Top
HTML Embed Code: