Telegram Web Link
አንድ ቀን እረፍት ሰአት ላይ ቁጭ ብየ ብቻየን እያሰብኩ ናርዶስ የምትባል የክፍላችን ልጅ ...ወደ እኔ መጥታ ከጎኔ ቁጭ አለች.......
.....ናርዶስም ነዋል በሰላም ነዉ ብቻሽን ቁጭ ያልሽዉ ?? አለችኝ
.......እኔም አዎ በሰላም ነዉ ከይቅርታ ጋር ብቻየን መሆን ፈልጌ ነዉ ናርዶስ ብቻየን እንደሆን ፍቀጅልኝ ......የምፈልጊኝ ከሆነ ክፍል ስንገባ እንገናኛለን አልኳት
......እሺ ነዋል አንድ ነገር ብቻ እንድናገር ፍቀጅልኝ ብቸኝነት አታብዢ አትጨናነቂ የሰዉ ወሬ እንደሆነ መቼም አያልቅም የዘንድሮ ሰዉ እንዳያወራ አፉን ቢዘጉት በቂጡ ማዉራቱ አይቀርም.....ከአንቺ የባሰ ሒወት የሚኖሩ አሉ እኮ የኔ ተመስገን የተሻለ ነዉ ያስብላል አንቺም ልትይ ትችያለሽ......ስለሆነም አንቺ ስታለቅሺ ስትተክዢ ማየት አልፈልግም ...ለምን ብትይ አንቺ ለኔ ጥንካሬ ብርታት እንድትሆኚኝ እፈልጋለሁ ነዋል አለችኝ
........እኔም ግራ ገባኝ ከአሁን በፊት ናርዶስ ጋር ብዙም አንግባባም ከክፍል ጓደኝነት ዉጭ.....ሚስጥር አዉርታኝም አዉርቻትም አታቅም አላዉቅም ......ናርዶስ የክርስቲያን ሀይማኖት ተከታይ ናት """ምን ለማለት ፈልገሽ ነዉ?? አልገባኝም"""አልኳት
.......ናርዶስም፡- ቅዳሜ ከሰአት ብንገናኝ በሰፊዉ ላወራሽ እችላለሁ ይመችሻል ??? አለችኝ
........እኔም አዎ ይመቸኛል አልኳት......
ናርዶስም እሺ ቅዳሜ 10 ሰአት ላይ ዶሎሎ ሆቴል መናሀሪያ አካባቢ እንገናኝ አለችኝ
.....እኔም እሺ እንገናኛለን አልኳት፡፡ ከዛም እረፍት ሰአት አልቆ  ተደዉሎ ወደ ክላስ ገባን....

ናርዶስ ያለችኝ ነገር በጣም ግራ ገባኝ በአእምሮየ እየደጋገምኩ ማብሰልሰል ጀመርኩ""" ከአንቺ የባሰ ሒወት የሚኖሩ አሉ እኮ የኔ ተመስገን የተሻለ ነዉ ያስብላል አንቺም ልትይ ትችያለሽ......ስለሆነም አንቺ ስታለቅሺ ስትከዢ ማየት አልፈልግም ...""" እንዴት እንዲህ ልትለኝ ቻለች???? እያልኩ ብቻየን ማሰብ ይዣለሁ.........

የተቀጣጠርንበት ቀን ቅዳሜ ደረሰ በተባባልነዉ በ10 ሰአት ስሄድ ናርዶስ ጋር ጅማ የሚገኘዉ ዳሎል ሆቴል ተገናኘን ...ከዛም ሰላምታ ከተለዋወጥን ቡሀላ ወንበር ይዘን ተቀምጠን
የሚጠጣ አዘን አንዳንድ ወሬ ካወረን ቡሀላ ....>>>>>ምንድን ነበር የምነግሪኝ ናርዶስ??? አልኳት
.....ናርዶስም አደራ የምነግርሽ ቤተሰቦች ወንድሜም እህቴም እናት እና አባቴ የማያቁት ሚስጥር ነዉ......የምናቀዉ  ፈጣሪ  እኔ እና ከዛሬ ጀምሮ ደግሞ አንቺ ነሽ...ስለሆነም ሚስጥራችን እዚሁ ይቅር አለችኝ
..........ከዛም እሺ ናርዶስ ለማንም አላወራም ብየ ቃል ገባሁ
>>>>>>>>_ናርዶስም ወደ መሬት አጎንብሳ የምታወጣቸዉን ቃላቶች ከየት ልጀምር እያለች እንደ ምጥ ከብዷታል.......ምን መሰለሽ ነዋል እኔ በልጅነቴ ....................___


#ክፍል 6⃣
ይ...........ቀ........
.........ጥ.........ላ.............ል


Join👇👇

https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAEOFXIlKIXVySUTDcA
👍1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ ስድስት 6⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ


...ምን መሰለሽ ነዋል እኔ በልጅነቴ ... ገና የስድስት አመት ልጅ እያለሁ አጎቴ ጋር ከአባቴ በላይ በጣም እንቀራረብ ነበር ....ከመቀራረባችን የተነሳ አጎቴ ቤት እየሄድኩ አድር ነበር ..አንድ ቀን እንደተኛሁኝ አጎቴ ገና በስድስት አመቴ የልጅነት ህልሜን አበላሸዉ ...ጠዋት ከእንቅልፌ ስነሳ የተኛሁበት አልጋ ደም በደም ሁኖ አገኘሁት... በህፃንነቴ በምወደዉ አጎቴ ተደፈርኩኝ....ከዚች ቀን ቡሀላ
አፈርኩኝ ደነገጥኩ አጎቴን ተዉ የምልበት ድፍረት እና ቃላት አጠረኝ... ወደ ቤቴ ከተመለስኩ ቡሀላ ይህንን ወሬ ለእናት እና አባቴ ሳልናገር ዝም አልኩኝ..........
.....አጎቴ በሰራዉ ስራ አፍሯል ከደፈረኝ ቀን ጀምሮ እሱ ቤት መሔድ አቆምኩኝ እሱም ወደ እኛ ቤት መምጣት አቆመ ....
እናት እና አባቴ ምን ሁነህ ጠፋህ??? ሲሉት የተለያየ ዉሸት እየደረደረ እኛ ቤት መምጣቱን አቆመ .....በልጅነቴ ይህን ጉድ ተሸክሜ ብቻየን ሳለቅስ ኖርኩኝ ፡፡
     ይሄዉ በደሌ ይሄዉ ግፍ ፈጣሪ አይበቃሽም ብሎኝ ደግሞ አጎቴ በደፈረኝ ከአንድ አመት ቡሀላ የአባቴ ጓደኛ እቤት መጥቶ አባቴም እናቴም የሉም ነበር ከዛም አባትሽ እስከሚመጣ እዚሁ ልጠብቀዉ አለኝ
...እኔም እሺ ብየ እቤት አሰገባሁት
ሳላወቀዉ ቁጭ ባልኩበት መጥቶ በጉልበት አስፈራርቶ የሚፈልገዉን በለጋ ሰዉነቴ የሚሰቀጥጥ ተግባር  ፈፀመብኝ ....በአባቴ ጓደኛ በእድሜዉ በገፋ ሰዉ ሁለተኛ በልጅነት የመደፈር ሰለባ ሆንኩኝ ......እግዚአብሔርን እስከ አሁን እናት እና አባቴ ይሄንን ሚስጥር አያቁም ...የምነግረዉ የለኝ የሚረዳኝ የለም ፡፡ ለአንቺ ስነግርሽ ትንሽ ቀለለኝ ብላ ...እምባዋን ቁልቁል ዘረገፈችዉ፡፡

ናርዶስ ስነግረኝ ጀምራ እምባየን መቋቋም አልቻልኩም ነበር ህመምህን መንገር ያለብህ ታሞ ለሚያቅ ሰዉ ነዉ ይባል የለ...እኔ ስነግረኝ እኔም በልጅነቴ የደረሰብኝ ትዝ እያለኝ አለቅስ ይዣለሁ፡፡ ሁለታችንም እያለቀስን ሁለታችንም ባለብሰተኞች ነን፡፡ በሆዳችን የፉም እሳት ነበልባል ተሸክመን ነዉ የምንሄደዉ ..ይሄ ነበልባል ሆድ ዉስጥ ይቀጣጠልና ቢተነፍሱት ለሰዉ ለመድረስ የሚከብድ ቀጥታ ወደ አይን ሂዶ አይንን ለብልቦ በእምባ የሚወጣ የማያባራ ጊዜ ቦታ የማይመርጥ እንደ ወራጅ ወንዝ መቆሚያ የሌለዉ ስቃይ ነዉ፡፡

ካፌዉ ዉስጥ ያሉ ሰዎች ትኩረታቸዉ ወደ እኛ ነዉ እኔ እንደምንም እምባየን ተቋቁሜ ናርዶስን እምባዋን እየጠረኩ አባበልኩኝ
   የዘንድሮ ሴቶች የሚያለቅሱት ወንጀል ሰርቻለሁ ሀራም ሰርቻለሁ ሳይሆን ጓደኛየ እወድሻለሁ ብሎኝ ተወኝ ሌላ አገባብኝ ሁኗል፡፡ እኛ ግን በህፃንነታችን በመደፈራችን ነዉ የእድል ነገር ሁኖብን ፈጣሪ ግፉን አሸከመን...

.......ናርዶስም እንደዚህ አለችኝ ነዋል የአንቺ የአደባባይ ሚስጥር ሁኖ ነዉ እንጂ ብዙ ሴቶች እኮ በጎረቤት በዘመድ በአባት ሳይቀር የልጅነት ህልማቸዉ የተበላሸባቸዉ ቤት ይቁጠረዉ ስለሆነም ከአሁን ቡሀላ ማንም ቢናገርሽ እንዳታለቅሺ ቆራጥ ጀግና ሁኚ...የበታችነት ሳይሰማን ተምረን ጥሩ ደረጃ ላይ ደርሰን እንደዚህ ያሉ እህቶቻችንን መርዳት አለብን አለችኝ፡፡
...እኔም እሺ ቃል ገብቻለሁ ለሰዉ ወሬ ትኩረት ላልሰጥ በትምህሬቴም ጠንክሬ ተምሬ በሴት ልጅ የሚደርስን በደል ግፍ ከእህቶቼ ጎን ለመቆም ወሰንኩኝ
....ከዛም ከካፌ ወጥተን ከአሁን ቡሀላ ሀይማኖታችን ላያግደን ጓደኛ ልንሆን ቃል ተገባብተን አንቺም ከጎኔ ሁኚ እኔም ከጎንሽ አለሁ ተባብለን ተለያየን፡፡

የኡስሚ ጓደኛነት እንዳለ ሁኖ ናርዶስ ጋር ምርጥ ጓደኞች ሁነናል ...ናርዶስ ጋር ስለ ድንግልና ስናወራ ለወደፊት ለሚያገባን ባላችን ስንጠየቅ ምንድን ነዉ ግን የምንለዉ ???ብየ ጠየኳት
>>>>>>>>> ነዋል እኛ እኮ ፈልገነዉ ስሜታችን አስቸግሮን ድንግልናችንን አጥተናል እንዴ ???አላጣንም እኮ...ሳንወድ በግዳችን ነፍስ ሳናቅ በልጅነታችን የድንግልና ትርጉሙን ሳናቅ  ነዉ  በማያስቡ ሰዉነት በማይሰማቸዉ በስሜታቸዉ ያደሩ ወንዶች የተነጠቅነዉ ስለሆነም እኛ ሁሌም ቢሆን ድንግል ነን ....>>>>እኔ ሁሌ እራሴን የማሳምነዉ ድንግል ነኝ ብየ ነዉ አለችኝ፡፡ እኔም ናርዶስ እንደዚህ ካለች ቡሀላ እኔ ድንግል ነኝ ብየ እራሴን አሳመንኩ ለምን ምንም የድንግል ጥቅም ሳላቅ በልጅነቴ ስላጣሁት እራሴ ድንግል ነኝ ብየ አሳመንኩኝ....
ከዛ ቡሀላ በልጅነትሽ ተደፍረሻል ቢሉኝም ወሬ ቢያወሩ ምንም አይመስለኝም ነበር ግን ጠባሳዉ ባይለቀኝም......እራሴን አሳመንኩኝ ለዘንድሮ ሰዉ ጆሮ ላልሰጥ ብየ ...... ሰዉ ቢያወራ ቢጠቋቆሙብኝ ምንም አይመስለኝም........

ለሁሉም ነገር የሰዉንም ትችት ለመቋቋም ትዕግስት ማድረግ እንዳለብኝ እራሴን አሳመንኩኝ ...
ግን የኛ ትዕግስት እስከ የት ነዉ??? ተወዳጁ ነብያችን ሀቢቡና ሙሀመድ ሰ.ዐ.ወ
ስድስት ልጆቻዉን በተለያየ ጊዚያት በራሳቸዉ እጅ ከመቃብራቸዉ ዉስጥ ካስገቡ ቡሀላ የህሊና ሚዛናቸዉ ሳይዛባ ሁሉንም ዋጥ አርገዉ በትዕግስት የሚኖር በዚህ አለም ግን እንደ ነብዩ ሙሀመድ
ሰ ዐ.ወ ይገኛልን ??ከልጅነት እስከ እዉቀት በዚህ ሁሉ መካራ እንደ አላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ)የተፈተነ ይገኛልን??በዚህ አለም ይህ ሁሉ የመከራ መደራረብ የተፈራረቀበት ይህም ሁኖ ጌታዉን የሚያመሰግን ከነብዩ ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) ዉጭ ሌላ ሰዉ ፈፅሞ አይገኝም ...
አላህ ሆይ ለኔም ለዚህ ለተፈፀመብኝ ነገር ትዕግስቱን ስጠኝ እያልኩ የዘወትር ዱአየ ነዉ...እናንተም በዱአ እገዙኝ

   እኛ ክፍል አንድ ሙባረክ የሚባል ልጅ አለ ...ሁሌ ቀን በቀን ለኔ የፍቅር ደብዳቤ እየፃፈ እንደሚወደኝ ለጓደኞቼ ይልክልኛል .....ወደ ሆላ ታሪኬ ሙባረክ ጋር ያለዉን ስንመለስ ሙባረክ ደብዳቤ መላክ የጀረዉ አምስተኛ ክፍል ጀምሮ ነዉ ........እኔ ግን ለሙባረክ ምንም ጥሩ አመለካከት የለኝም ከነመፈጠሩም ትዝ አይለኝ....የኡስሚ ያለኝ አመለካከት ግን እኔም ግራ ይገባኛል፡፡ አልርቀዉ አልቀርበዉ ነገር ....

ወንድ ሲባል እንደ ቶፊቅ ተጠቅሞ የሚጥለኝ ነዉ የሚመስለኝ ....ሙባረክን ከአሁን ቡሀላ ደብዳቤ ብትልክ ብትረብሸኝ ለአባቴ ነዉ የምነግረዉ ተወኝ ብያለሁ ብየ በደብዳቤ ላኩለት ከዛ ቡሀላ ........ሙባረክ ደብዳቤ መላኩን አቆመልኝ፡፡

      የሚገርማችሁ ከአንድ እስከ ስድስት በምማርበት ጊዜ ከአንድ እስከ አምስት ነበር የምወጣዉ ....ሰባተኛ ክፍል ግን ለቤተሰብ ለመንገር የሚያሳፍር ደረጃ ወጣሁኝ...ከሀምሳ ተማሪ ሰላሳ አምስተኛ ነበር የወጣሁት.......በትምህርት ደረጃየ እኔ በጣም አዘንኩኝ ሰባተኛ ክፍል መቀለዴ ዋጋ አስከፈለኝ......ለአባቴ ካርዴን ሳሳየዉ ቢከፋዉም እኔን መጥፎ ቃል መናገር አልፈፍግም ..፡፡ ነዋል አብሽሪ ለሚመጣዉ አመት ዋና ፈተናዉ ሚኒስትሪ ላይ ታሻሽይዋለሽ አለኝ፡፡
....አባቴ አብሽሪ ቢለኝም እኔ ግን ዉጤቴ በመዉረዱ በጣም ተናደድኩኝ፡፡👇👇👇
ክረምት አልፎ ስምንተኛ ክፍል ተመዘገብኩ ..ስምንተኛ ክፍል እያለሁ እኛ ክፍል የሚገኙ ሴት ልጆች ኡስማንን ...ነዋልን እወድታለሁ ብልሀል ወይ ?? እሷ እኮ ሁሌ ኡስማን የፍቅር ደብዳቤ ሰጠኝ እወድሻለሁ እለኝ እያለች ትነግረናለች እዉነቷን ነዉ እንዴ ?? ብለዉ ይጠይቁታል
.....እሱ ግን መልሱ ዝምታ ብቻ ነበር
የኛ ክላስ ልጆች በዉሸት እኔ እና ኡስማንን በተለያየ በዉሸቱም በእዉነቱም ወሬ ለማጣላት የማይፈነቅሉት ዲንጋይ የላቸዉ ነበር ..

እነሱም ከእሷ ምን አለህ አንተ እኮ ብዙ ላይፍ ይጠብቅሀል ካልወደድካት ተዋት እያሉ ብዙ ነገር ካሳመኑት ቡሀላ በማላቀዉ ምክንያት በተለያዩ ወሬዎች ኡስማን እኔን ዘጋኝ......ኡስሚ በእኛ ክላስ የተቀነባበረ ወሬ ጆሮዉን ሞልቶ እኔን ጀርባዉን ሰጠኝ...



ኡስሚም በፊት ቁርአን ቤት እንገናኝ ነበር ከቁርአን ቤት ወጥቶ እቤቱ ሸህ ይዞ ኪታብ መቅራት ጀመረ....ትምህርት ቤት ስንሄድ አብረን ነበር የምንመለሰዉ ..አሁን ለብቻዉ በባጃጅ ሁኗል የሚመላለሰዉ ... በሁሉም አጋጣሚዎች እኔን እራቀኝ አንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ኡስማን ጋር ተጣላን...

እኔም ምን አጥፍቼ ነዉ የዘገሀኝ ምን አጥፍቼ ነዉ የተዉከኝ ??? ብየ አልጠየኩትም ዝም ሲለኝ ዝም አልኩት ሲዘጋኝ ዘጋሁት ........ልቤ ፍቅር እንደማይገዛዉ .. ማንንም ወንድ ወደ ልቤ እንደማይገባ አየሁት ..ለምን አንዴ ቶፊቅ ጉድ ሰርቶኛል ..ወንድ እንዳላምን አርጎኛል..........ኡስማን ጋር አብረን በሆንበት ጊዜ ለኔ ባለዉለታየ ብቸኝነት አይሰማኝም ነበር.... እወደዉ ነበር አልክድም ከመዉደዴ የተነሳ አልቅሼም ዱአ አድርጌያለሁ ኡስሚን ለኔ አርግልኝ ብየ ......ግን የኔ ልብ የፍቅር ልብ ማንንም መዉደድ እንደማይችል ተረዳሁኝ......አሁን አንድ ጓደኛ አለችኝ እንደ እኔዉ በልጅነቷ ክብሯን ያጣችዉ ናርዶስ ብቻ ናት.......

   የሰባተኛ ክፍል ዉጤቴ መዉረዱ በጣሞ ስላናደደኝ አሁን ሀሳቤ እና አላማየ አንድ እና አንድ፡ብቻ ነዉ ይሄዉም ለሚኒስትሪ ጥሩ ዉጤት ይዞ ማለፍ እና አባቴን ማስደሰት ነዉ የምፈልገዉ.....


  ሰምንተኛ ክፍል ላይ ትምህርቴ ላይ ብቻ ፎከስ ማድረግ ብቻ ሁኗል ትኩረቴ .....ከትምህርት ቤት ጓደኞቼም እንደበፊቱ የማይጠቀም የማይጎዳ የጊዜ ማሳለፊያ ወሬ ማዉራት ..አፍ መካፈት ዘመናይ ነኝ ከሚባሉት ከሁሉም ነገሮች እራኩኝ........ አልሀምዱሊላህ ሶላቴን ተከታትዪ ሰጋጅ ሁኛለሁ
ቁርአንም ምላሽ እየቀራሁ ነዉ፡፡
   
   በተጨማሪም ትምህርት ቤታችን ያሉት ጎበዝ ሴት ተማሪዎች ጋር ላይብረሪ እየገባሁ ማጥናት ጀምሪያለሁ፡፡ እራሴን ለመቀየር ወገቤን ጠበቅ አርጌ ተነስቻለሁ... ግራ የገባኝ ነገር ቢኖር እኔ ሳጠና ናርዶስ በጭራሽ አላጠናም አለችኝ ...ናርዶስን ቀን በቀን ተስፋ ሳልቆርጥ ላይብረሪ እንግባ እናጥና ብላት ሁሌም ከአፏ የሚወጣዉ መልስ እምቢታ ብቻ ነዉ፡፡


ናርዶስ የሀብታም ልጅ ናት ቤተሰቦቿ ጅማ ከተማ ላይ ህንፃ እና ታዋቂ ሆቴል አላቸዉ ፡፡

ትጋብዘኛለች ...ናርዶስ ብር በጣም ታባክናለች አባቷ የወጭ እያለ ይሰጣታል ብዙም አያካብድም፡፡ ብር እንደፈለገች ስለሚሰጣት አዳዲስ ልብስ መልበስና የፈለገችዉን ምግብ መብላት መጠጣት የዘወትር ተግባሯ ነዉ ...
ከትምህርት ስንለቀቅ ብዙ ጊዜ ካፌ ትጋብዘኛለች

ናርድስ ስለምታባክነዉ ብር ግራ እየገባኝ ..ተይ ብር መበተኑ ማባከኑን ቀንሽ እያልኩ ሁሌ ብመክራትም፡ የእሷ መልስ ግን እኔ በዚህ ጊዜ የምፈልገዉ እራሴን ዘና አድርጌ መኖር ነዉ የምፈልገዉ በስንቱ ልጨናናነቅ?? መጨናነቅ ይበቃኛል.....በትምህርት ጥናትም መጨናነቅ አልፈልግም ከመጣ ዉጤት ይምጣ ካልመጣም የራሱ ጉዳይ.....ትለኛለች፡፡

አንድ ቀን ናርዶስን ብቻዋን ቁጭ ብላ ጭልጥ ያለ አለም የሄደች ትመስላለች ከአጠገቧ ሂጄ ናርዶስ ናርዶስ እያልኩ ብጠራት ልትሰማኝ አልቻለችም ..ከጎኗ ሁኜ ናርዶስ ብየ ፊቷን ነካ ሳረጋት ከእንቅልፍ እንደባነነ ሰዉ ብንን ብላ ነቃች
...እኔም፡- ግን ለምን እንደዚህ በሀሳብ እርቅሽ እስከምትሄጅ ታስቢያለሽ?? ብቻሽን ተቀምጠሽ በሀሳብ ከምትበታተኝ አብረን ላይብረሪ ገብተን እናጥና ለወደፊት እኔ እና አንቺ በልጅነታችን ህልማችን ቢወሰድም ...ለወደፊት ህልም ያለን ህልማችንን መመለስ የምንችል ልጆች ነን ....ባለፈዉ ስንመካከር እኮ እኛ አርአያ መሆን አለብን ብለን ሁለታችን ቃል ገብተናል ለምን እንደዚህ ተስፋ ትቆርጫለሽ ??? ብዙ ጊዜ ብር በመበተን በመዝናናት በመልበስ መደሰት ምን ይሰራልሻል ??? አልኳት

ናርዶስም :- >>>>>>>እኔ በልጅነቴ በአጎቴ እና በአባቴ ጓደኛ የደረሰብኝ በደል አሁን ድረስ ከአእምሮየ አልጠፋም .,ቀን ቀን ስንገናኝ ደስተኛ እመስልሻለሁ ሰዉ ጋር ተጨዋች እመስላለሁ ግን ማታ መኝታየ ላይ ተኝቼ የተኛ ሰዉ ብመስልም ንፁህ እንቅልፍ ከወሰደኝ ብዙ አመታት አለፈኝ... ሁሌ ለሊት ለሊት ሳለቅስ ነዉ የማድረዉ ምንም መረጋጋት አልቻልኩም፡፡ እቤቴ ምንም አልጎደለብኝም ቤታችንም ዉስጥ የምንኖረዉ በደስታ ነዉ ምንም የማስብበት የምጨነቅበት ነገር የለኝም፡፡ ግን ይሄ የልጅነቴ በደል ምንም ሊረሳኝ ሊለቀኝ ከአእምሮየ ልሰርዘዉ አልቻልኩም፡፡
ማታ ስተኛ እያለቀስኩ እየኖርኩኝ በቀኑ ደስተኛ ልምሰል ብየ ነዉ ...ትምህርት ለማጥናት ሞከርኩኝ ግን አእምሮየ ምንም ሊቀበልልኝ አልቻለም ...መፅሀፉን ስገልጠዉ ካላነበብኩት እምባየ የምማርበት መፅሀፍ ላይ ቢያርፍ ምን ጥቅም አለዉ ??ብላ ጥያቄየን በጥያቄ መለሰችልኝ ...,
    በናርዶስ አነጋገር በጣም ተሰማኝ ምን ማረግ እችላለሁ ...እኔም የእሷ አይነት አደጋ በልጅነቴ ደርሶብኛል፡፡ አብሽሪ አላህ አለን ከማለት ዉጭ

    የማይደርስ የለም ሚኒስትሪ ፈተና ደረሰ ተፈተንኩኝ ...........ከተፈተንኩ ቡሀላ ናርዶስ ጋር በእናቴ ስልክ እንደዋወላለን በሳምንት አልፎ አልፎ አንገናኛለን ......

የሚኒስትሪ ዉጤት ሲመጣ አባቴ ዉጤቴን ለማየት ቸኩሎ መጀመሪያ እኔ ነኝ ማየት ያለብኝ ብሎኝ ወደ ትምህርት ቤት ካርዴን ሊያመጣ ሄደ

የሚኒስትሪ ዉጤቴ አባቴ ይዞት መጣ .....በሩን ሲከፍተዉ አባቴ ጋር ፊት ለፊት ተያየን ....ምን ይለኝ ይሆን??? ጥሩ ዉጤት ነዉ ወይስ አይደለም ??"እያልኩ በቆምኩበት ጨንቀት ያዘኝ.......






#ክፍል 7⃣
ይ........ቀ......
......ጥ.......ላ.......ል


JOIN
´´´´´´´ :¨·.·¨: ❀ share
           `·. www.tg-me.com/Islam_and_Science
www.tg-me.com/Islam_and_Science
•════•••🍃🌺🍃•••════•
👍2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ ሰባት 7⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ




    የስምንተኛ ክፍል ዉጤቴ ሲመጣ በጣም አሪፍ እኔንም አባቴንም ያስደሰተ ዉጤት ነዉ ..ከትምህርት ቤት ሰቃይ ተማሪዎች ተርታ ሁኜ 97 አመጣሁ፡፡ አባቴ በጣም ተደሰተ ልጄ አኮራሽኝ አስደሰትሽኝ እያለ ደስታዉን መቋቋምና በቃላት መግለፅ እንደተቸገረ ከአነጋገሩ ያስታዉቃል

አባቴም:- በዚህ በሚያስደስት ዉጤት የተወሰነ ቀን ላዝናናሽ ተዘጋጂ አለኝ
..እኔም በደስታ እሺ አልኩኝ

የማይነጋ የለም ጨለማ ለጀንበር ሲያስረክብ ከጅማ ተነስተን 117 km ተጉዘን ወደ ወልቂጤ ከተማ ሄድን ..ወልቂጤ ከተማ እንደ ደረስን ማራኪ
ካፌ እና ሰላም ካፌ ገብተን የሚያምሩ ጊዚያትን አሳለፍን ..ከዛም..ከወልቂጤ ከተማ አለፍ ብሎ የሚገኙ ገስት ሀዉስ መዝናኛ እና ዋቤ መዝናኛ የሚያምሩ የማይረሱ ሁለት ቀናቶችን አባቴ ጋር አሳለፍን.....
ከሁለት ቀን ቡሀላ ወደ ጅማ ተመለስን፡፡

ከዛም አባቴ ሌላ ሽልማት አለሽ አብረን ሂደን የምፈልጊዉን ልብስ ግዢ አለኝ....ጅማ የሚገኘዉ ህብር ህንፃ መርካቶ አካባቢ አባቴ ጋር ሂጄ አዳዲስ ልብሶችና ጫማዎች በራሴ ምርጫ ገዛሁኝ፡፡ እኔም ደስ አለኝ የኛ ጎበዝ መሆን መጠንከር ከእኛ አልፎ ለቤተሰብ ደስታ ፍቅር መሆኑን ተረዳሁኝ፡፡ ክረምትን በመዝናናት እና አባቴ ጋር ሁኜ ወደ ተለያዩ ሀገሮች ወደ ድሬ ወደ አዋሽ እየወሰደ እያዝናናኝ አሳለፍኩኝ

  መስከረም ሲደርስ ዘጠነኛ ክፍልን ለመማር እኔና ናርዶስ ከኮምዩኒቲ ትምህርት ቤት መሸኛችንን ተቀብለን ከግል ትምህርት ቤት ወደ ጅሬን(አጂፕ) አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ የመንግስት ትምህርት ቤት ተመዘገብን፡፡

ከኮምዩኒቲ ት/ቤት ለመልቀቅ ዋነኛዉ ምክንያቴ ተማሪዎቹ በእኔ ስለሚጠቋቆሙ እና በልጅነቷ ተደፍራለች የሚባለዉ ወሬ መስማት ሲሰለቸኝ ነዉ ናርዶስን አማክሪያት አብረን ተስማምተን ከኮምዩኒቲ ትምህርት ቤት መሸኛ ተቀብለን ወጣን ፡፡

ትምህርት ጀምረናል ..መቼም ደህና ዋሉ ተብሎ ከቤት ከወጡ ሰዉ ጋር መደባለቁ አይቀርም...ጅሬን ትቤት ከናርዶስ ዉጭ ሌሎች አዳዲስ ጓደኞች ጨምሪያለሁ..........

ዘጠነኛ ክፍል በጓደኛ ግፊት ልበላሽ የነበረበት ኢስላም ሁኜ እነሱ ጋር ስሄድ ሀይማኔቱን የሚያዘኝን ለመተግበር እፍረት የሆነብኝ ጊዜ ነበር......

ነገሩ ምን መሰላችሁ....በምንማርበት ጊዜ ከናርዶስ ዉጭ ሶስት ክርስቲያን ጓደኞች ያዝኩኝ ..ሶስቱም የወንድ ጓደኛ አላቸዉ...መኖር ብቻ ሳይሆን አንዱ ጋር ላይፍ ቀጭተዉ አብረዉ ከአደሩ ቡሀላ የመቀየር የሌላ ወንድ ሰዉነት የሚመኙ ወንድ ልጅ ለእነሱ የሒወት እስትንፋሳቸዉ አርገዉ የሚያስቡ ናቸዉ...እነዚህ አዲስ ጓደኞቼ መጠጥ መጠጣት ቤርጎ ወንድ ጋር ማደር ክለብ ሒደዉ መጨፈር ለእነሱ ሒወታቸዉ ኑሯቸዉ ነዉ...ገና በዘጠነኛ ክፍል እነሱ አላማቸዉን የሳቱ በወጣትነት የእሳት ነበልባል ይጓዛሉ፡፡
     እናም ይሄን ሁሉ ሲያደርጉ መጥተዉ ለኔ ይነግሩኛል ፡ የት እንዳደሩ ምን እንደሰሩ ምንም የሚቀራቸዉ ነገር የለም ስለአዳራቸዉ ልጁ ጋር የነበራቸዉን የሀራም አዳር ሳይቀር ይነግሩኛል...
እኔም ምነዉ እንደ እነሱ ብሆን ብየ እመኛለሁ
መጥፎ ሀሳብ ሳስብ መልሼ አኡዙቢላህ እላለሁ

....ግን እነሱ በወንድ በመጠጥ ሲደሰቱ እኔ የሚያወሩኝ ወሬ ካለሁበት እድሜ አንፃር ለኔ ፈታኝ ከባድ ጊዜ ነዉ ..እንደ ጓደኞቼ ለመሆን ወጣትነት ቢፈታተነኝም ለዱንያ ለጊዜያዉ ደስታ ብየ አኼራየን ማጥፋት አልከለኩም ..በመቀጠል ደግሞ ቃል አለኝ አባቴን በትምህርቴ ጥሩ ደረጃ ደርሼ ለማስደሰትና እንደኔ በልጅነታቸዉ ለተደፈሩ ህፃናት ጎን ለመሆን  ..... ከትምህርት ቤት ስለቀቅ ሶስቱ ጓደኞቼ ሱሪ ለብሰዉ ሲሔዱ እኔ ደግሞ ሒጃብ ለብሼ ስሔድ መንገድ ላይ ላየኝ ሰዉ በጣም አፍራለሁ፡፡ ጓደኞቼ ምሽት ቤት ሲጨፍሩ እንደሚያመሹ የተወሰኑ የትምህርት ቤት ተማሪዎች ያቃሉ...እነሱ ጋር ስሄድ እኔም አብሬ ጭፈራ ቤት የማመሽ ታድራለች ብለዉ የሚጠረጥሩም ነበሩ፡፡
     አያችሁ ሰዉ መጥፎ ጓደኛ ጋር ስትሆን አንተ ጥሩ ብትሆንም  እንደ እነሱ መጥፎ ስራ ባሰራም የሰዉ አመለካከት እንደ መጥፎ ጓደኞች አብረዉ ነዉ የሚስሉት፡፡
መጥፎ ጓደኛ በህይወት ላይ የራሱ የሆነ መጥፎ ጫና አለዉ ...

ጓደኝነት በኢስላም ልዩ ትኩረት ከተሰጣቸዉ ግንኙነቶች አንዱ ነዉ፡ሰዉ ዉሎዉን ይመስላል ይባላል ከመጥፎ ሰዎች የዋለ እንደዛዉ መጥፎ የመሆን እድል ይገጥመዋል ፡ ከጥሩ ሰዎች የዋለ እንደ እነሱ ጥሩ ሰዉ የመሆን እድሉ ሰፊ ነዉ፡፡

መጥፎ ጓደኞች ጫናቸዉ ስለሚበረታ ከማህበራዊ ግንኙነት ላይ ከባድ ችግር ይፈጥራሉ ፡፡ ብዙ አመት ደህና ነዉ የተባለዉ ሰዉ መጥፎ ጓደኛ ከገጠመዉ በአንድ ቀን ወደ መጥፎነት ይቀየራል ..ሁሌም በመጥፎ ጓደኛ የተጎዱ እና ችግር ዉስጥ የገቡ ሰዎች መጨረሻ ሰአት ላይ ይነቃሉ...ግን የሚነቁት ብዙ ነገር ከተበላሸ ቡሀላ ባለቀ ሰአት ላይ ይባንናሉ ..ኢስላም ግን ቀድመህ አስብበት በማለት ግልፅ መመሪያ አስቀምጧል ..፡፡ መጀመሪያ ነበር አስቦ መደቆስ አሁን ምን ያደርጋል ድስት ጥዶ ማልቀስ እንደተባለዉ ማለት ነዉ፡፡

 የያዝኳቸዉ አዲሶቹ ጓደኞቼ እየመጡ ማንኛዉንም ይነግሩኛል ...ብዙዉ ጥፋት የጓደኞቼ ቢሆኑም......እኔም ግን በመቆጨት መቼ ድረስ ነዉ ወንድ ልጅ በሴት ልጅ ሰዉነት የሚጫወተዉ ??? ግን ለምን አንዴ ተጠቅሞ ሴትነት ወዟን ተጠቅሞ እንደ አሮጌ ጫማ የሚጥላት ???እያልኩኝ እናደድ እቆጭ ነበር....የእኔ ለወሬ አይመችም ገና በልጅነቴ ነዉ ክብሬን ያጣሁት.....በትምህርቴ ጠንከራ ሁኜ ፕሪፓራቶሪ ስገባ ወንድን ልጅ በፍቅር እያጠመድኩ እንደ ቁንጫ ፍትልትል እያረኩ በፍቅር እየጎዳሁ እነሱ ሲያለቅሱ ማየት የወደፊቱ እቅዴ አድርጌ ያዝኩኝ......
  
ዘጠነኛ ክፍል ጨርስኩኝ ጥሩ ዉጤት አምጥቼ ከክላስ 2ኛ ደረጃ ወጥቼ ወደ 10 ክፍል አለፍኩኝ.....ግን እነዛ ክርስቲያን ጓደኞቼ ሁለቱ ከዘጠነኛ ክፍል ማለፍ አልቻሉም ፡፡


ዘጠነኛ ክፍል ጨርሼ ክረምት ላይ ዘመድ ጋር  ለማሳለፍ ከጅማ 360km ርቀት ተጉዤ ወደ አዲስ አበባ ሄድኩኝ፡፡
እኔንም ያሳለፍኳቸዉን የሚያስጠሉ የሒወት መስናክሎች ጠባሳዎች ትዝም ሳይሉኝ ጥሩ ጊዜ ሸገር አሳለፍኩኝ....ትምህርት ሲጀመር ወደ ጅማ ተመለስኩ
....የ10 ክፍል ትምህርት መማር ጀምረናል..ግን 10ክፍል ላይ በነበርኩበት ጊዜ የሚያስጠላ ሒወት ያሳለፍኩበት በጓደኛ ግፊት አላማየን የሳትኩበት አመት ነበር...ዘጠነኛ ክፍል የነበሩኝ ክርስቲያን ጓደኞቼ ሌላ የወንድ ጓደኞች ነበሯቸዉ ...እኔ እና እና ናርዶስን ወደ ስድስት የሚሆኑ ክርስቲያን ወንዶች ጋር እንድንግባባ አስተዋወቁን....እኔም ከ6 ወንድ የትምህርት ቤተ ተማሪዎች ጋር ሲስተርሊ ብራዘርሊ መቀራረብ ጀመርን
    እነዚህ ክርስቲያን የወንድ ጓደኞች ጋር ከተዋወኩኝ ቡሀላ ብዙ አላማየን የሳትኩበት የተበላሸሁበት ጊዜያቶች ናቸዉ ....
  አምስት አዉቃት ሶላት መስገድ ..ቁርአን መቅራት በጓደኞቼ ግፊት ምክንያት
አቆምኩኝ👇👇👇
ደግሞ በተጨማሪም በመንገድ ሒጃብ ለብሼ የሴት ጓደኞቼ ጋር ስሄድ ምንድን ነዉ በልጅነትሽ ባልቴት መስለሽ የምትሄጂዉ??? እያሉ ቀን በቀን እኔን አሸማቀቁኝ...ሒጃብ ስለብስ ፋራ እያሉ ሲያስቸግሩኝ ሒጃብ መልበስም ሙሉ በሙሉ አቆምኩኝ.....የሌላ ሀይማኖት ተከታይ ጓደኛ መያዝ በዲን ላይ ተፅእኖ አመጣብኝ፡፡ በጓደኛ ግፊት ሂጃብ መልበስ ተዉኩኝ...ግን አሁን ላይ ሳስበዉ ከኔ ዉጭ ተጠያቂ የማድረገዉ ቤተሰቦቼን ነዉ፡፡ ሂጃብ ትቼ ሌላ ፋሽን ልብስ ስለብስ አባቴም እናቴም ለምን ሂጃብ መልበስ አቆምሽ ???ብሎ የተናገረኝ የጠየቀኝ የለም...በዚህ እድሜየ የወላጅ ክትትትል ግዴታ ነዉ ብየ አምናሁ..

እነዛ የተዋወኳቸዉ የወንድ ጓደኞች የትምህርት ቤት ልጆች ሁሌ ትምህርት ቤት ስልካቸዉን ይዘዉ ይመጣሉ..በስልካቸዉ ላይ ብዙ የተለያዩ የባለጌ video ፊልሞች አሏቸዉ ....ናርዶስም እስኪ ድንግልና ሲሄድ ስሜቱን አሳዩኝ ትላቸዋለች..
እነሱም ስልካቸዉን እየሰጧት ትመለከታች...እኔ መመልከት ባልፈልግም ሳልወድ በግዴ እኛ በልጅነታችን ያጣነዉ ድንግልና እንዲዚህ ነዉ የሄደዉ ተመልከች እያለች እኔም በናርዶስ አስገዳጂነት ተመለከትኩኝ ...ናርዶስ የዚህ የባለጌ ፊልም video ሱሰኛ ሆነች ቀን በቀን ማየት ያስደስታታል...ተይ ብላት በዚህ የፊልም ሱስ ሰለባ ሆነች....

ነብዩ ሰ.ዐ.ወ መጥፎና ፀያፍ ነገር በህዝቦች ዉስጥ በምንም መልኩ ግልፅ አትሆንም ፡ በዉስጣቸዉ ቀደምት አባቶቻቸዉ የማያዉቅት ወረርሽኝ እና የተለያዩ በሽታዎች ቢከሰቱ እንጂ በማለት ይገልፃሉ

ፓርኖግራፊ(ልቅ ወሲባዊ ፊልሞች እና ምስሎች)መመልከት ያልተገደበ ወሲባዊ ጡዘትን እና የአእምሮ መረብሽን ያስከትላል፡ልቦናን መረጋጋት እንዳይኖረዉ በማድረግ ላልተፈለገ የወሲብ ሩጫ እና መልከስከስ ይጋብዛል፡፡ አንድ ቀን የሚታይ የወሲብ ፊልም ወይም ምስል ሁለት ወይ ሶስት ቀን ሙሉ አእምሮ ይረብሻል በተደጋጋሚ በአይነ-ህሊና እየመጣ የዉስጣችንን ሰላም የሚያናጋ ክስተት ነዉ፡፡

ኢስላም የተራቆቱ ገላዎች መመልከት ግልፅ በሆነ ቁርአናዊ አንቀፅ የተከለከለ እና በተለያየ ነብያዊ ሀዲሶች አፅንኦተ ተሰጥቶት የተወገዘ ተግባር ነዉ ፡፡ ይህን አስመልክቶ አሏህ በተከበረ ቁርአኑ እንዲህ ይላል ፡-
""ለምእመናን ንገራቸዉ ዓይኖቻቸዉን(ያልተፈቀደን ከማየት) ይከልከሉ ፡ብልቶቻቸዉንም ይጠብቁ፡ይህ ለነርሱ የተሻለ ነዉ ፡ አላህ እነርሱ በሚሰሩት ሁሉ ዉስጥ አዋቂ ነዉ፡፡""(ሱረቱ ኑር 30)

ይህ የፊልም ሱስ አመጣጣጡ ዲነል ኢስላምን እና ወጣቱን ለማዳከም ነዉ .በዚህ የተነሳ በርካታ ወጣቶች ለሞት ዳርጓል;በርካቶች ለተለያዩ ህመምና ስቃይ ዉስጥ እያቃሰቱ እንዲኖሩ አድርጓል፡ በርካቶች በዚሁ ተለክፈዉ የቀን ዉሏቸዉ የለሊት አዳራቸዉ እርሱ ሁኗል...በዚህ ምክንያት ዉድ የሆነ ሒወታቸዉ ጊዜያቸዉን የገንዘብ ብኩንነት ..ሰላማቸዉ ተናግቶ ደስታ የራቀዉ ሒወት እየተገደዱ ነዉ፡፡

እንደ ተርብ እስታስቲክስ መረጃ ከሆነ ለፓርኖግራፊክስ(ለልቅ የወሲብ ፊልሞችና ምስሎች)ድህረ ገፆች የሚወጣዉ ገንዘብ በአመት 57.8ቢሊዮን ዶላር ሲሆን በአሜሪካ ብቻ 12 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ይደረጋል..የፓርናግራፊ ድህረ ገፆች ብቻ 4.2ሚሊየን እና 420.ሚሊየን ገፆች ይጠጋሉ፡ በአጠቃላይ ድህረ ገፅ 12በመቶ ለዚሁ ርካሽ ተግባር ማስፋፊያነት ተመድቧል ፡፡በሳምንት 70ሚሊየን የሚጠጉ ሰዎች የብልግና ምስሎችን በኢንተርኔት ይመለከታሉ ከእነዚህ ሰዎች መካከል 20ሚሊየኑ የሚገኙት በአሜሪካ እና በካናዳ ሲሆን በአዉሮፓ ደግሞ ጀርመን እንግሊዝ ስፔን ቀጣዮችን ቦታዎች ይይዛሉ..ምዕራባዊያን እራሳቸዉን ሆነ የዓለምን ህዝብ ወደ አልሆነ መጥፎ አቅጣጫ እየመሩት እንደሆነ መመልከት ይቻላል፡፡

እንደ እስታስቲካዊ መረጃዎች ከሆነ ሙስሊም በሆኑ ሀገሮች ላይ ያሉ ወጣቶች ቁጥር ሙስሊም ባልሆኑ ሀገር ላይ ካሉት ወጣቶች ቁጥር በጣም በልጦ ይገኛል ..በአጠቃላይ የሙስሊም ዓለም ወጣት ብዛት 70 በመቶ ሲጠጋ በምዕራቡ ዓለም ያለዉ ወጣት ቁጥር 25 በመቶ መሆኑን ያሳያል ፡፡ስለዚህ ለወደፊቱ አለምን የሚረከበዉ ጠንካራ ትዉልድ ያለዉ በሙስሊሙ ዓለም መሆኑ ምዕራቡን አለም ክፉኛ ስላሳሰባቸዉ ሙስሊሙን ወጣት በዚህ የፊልም ሱስ ተለክፎ ከአላህ ጋር ከቁርአን ከሀዲስ ከመስጊድ ያለዉን ግንኙነት ቀንሶ ከዲነል ኢስላም ርቆ ለኢስላም የማይጠቅም የማይጎዳ ትዉልድ ለማድረግ የመጣ ነዉ፡፡ ምእራባዉያን ለወደፊት ለሚመጣዉ ሙስሊም ትዉልድ እንዲበላሽ ከበፊት ጀምሮ ዛሬም ጭምር ቀን ለሊት እየሰሩ ነዉ ፡፡ እኛስ ለሚመጣዉ ትዉልድ ዲነል ኢስላምን ለማስረከብ ምነ እየሰራን ነዉ???

በጣም የሚያሳዝነዉ ይህን ፊልም መመልከት ለተለያዩ የወሲብ ችግሮች መፍትሄ ይሆናል በሚል እምነት የሚናገሩና የሚተገብሩ መኖራቸዉ ነዉ፡፡ ወጤቱ ግን በለቃራኒዉ መሆኑን ዘንግተዉታል

አላህ ከብልግና ፀያፍ ነገር..ከማንኛዉም መጥፎ ተግባር እንዲሁም ወሰንን ከማለፍ ይከለክላል
በሱረቱል ነህል 90 ላይ ..በዚህ አንቀፅ ፋህሽ ሙንከርና አል-በግይ የሚሉ ቃላቶች ሰፍረዋል ፡፡ ፋህሽ ማለት ብልግና .እፍረተቢስና ቆሻሻ ማለት ሲሆን ወሲባዊ ፊልሞችና ምስሎችን ያካትታል፡፡ሙንከር የሚለዉ ደግሞ ማንኛዉም በአለም ዙሪያ ያሉ ኢሞራላዊ መጥፎ ስነ-ምግባሮች መገለጫ የሆኑ ባህሪያትን ያካትታል ፡፡ አልበግይ የሚለዉ ኢፍትሀዊ የሆኑ ተግባሮችን ድንበር ያለፈ ጋጠወጥነትን ያካትታል፡፡ከዚህ የተነሳ ልቅ የወሲብ ፊልሞችና ምስሎች በዚህ የቁርአን አንቀፅ ዉስጥ የተገለፀ ስለሆነ ህዝቡን የሚጎዱ ለክፉ ዉድቀት የሚዳርጉ ስለሆነ ህዝበ ሙስሊሞ ሊርቃቸዉና ሊያወግዛቸዉ ሀራም መሆኑን አዉቆ ሊጠነቀቅ ይገባል፡፡

ልቅ የወሲብ ፊልሞችና ምስሎችን የመመልከት ሱስን ለማስወገድ የሚደረገዉ ህክምና በጣም ከባድ ሁኗል..ምክንያቱም ሱሱ በአንጎል ዉስጥ በቀላሉ ለመፋቅ በማይቻል መልኩ ትዉስታዉን ጥሎ ስለሚያልፍ ይላሉ የተመራመሩ ባለሙያዎች ..ይሄ ሱስ በማንኛዉም ሁኔታ ትዝ እያለ ህይወትን ሊረብሽ የሚችል የትዝታ ዕፅ ነዉ፡፡ ነገር ግን እንደ ኢስላም አላህ ሁሉን ቻይ ከመሆኑ አኳያ እና ኢማን ከዚህም በላይ ተአምር ይሰራል ..የሰዉ ልጅ ከዚህም በላይ በከፋ በጣም መጥፎ ልምዶች ዉስጥ ተነክሮ መዉጣት በመቻሉ ከዚህ ሱስ መላቀቅና መዉጣት ይቸላል..መጀመሪያ በአላህ ተስፋ ማድረግ ከዛም ጠንካራ ዉሳኔ ወስኖ ከችግሩ ለመራቅ ቆራጥ አቋም ለመያዝ ሞክሮ መላቀቅ ይቻላል ..የመጀመሪያ መፍትሄዉ ከእነዚህ ልቅ የወሲብ ቻናሎች መዉጣት እና ከተለያዩ እነዚህ ካሉባቸዉ ሚዲያዎችና ደህረ ገፆች ማግለል የመጀመሪያዉ መፍትሄ ነዉ፡፡ ከዛም ቁርአን መቅራት እና ሙሉ በሙሉ ቶብቶ ወደ አላህ መመለስ ነዉ ይሄ ካልሆነ ለወደፊት ትዳር ቤተሰብ መምራት እንደማይቻል ሊታሰብበት ይገባል
(ስለ ልቅ የወሲብ ፊልም በእዉነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ በኔ አሚር ሰይድ የተፃፈ የሕይወት መሰናክል የሚለዉን ታሪክ ቢያነቡ ጉዳቱ ምን እንደሆነ መገንዘብ ይችላሉ ያንብቡት ተጋብዛችሆል)
  
እነዛ የያዝኳቸዉ ጓደኞቼ ሁሌ Fb ላይ ሲጀናጀኑ ስልክ ሲያወሩ ቀናሁኝ .....እኔም እንደነሱ እንደመሆን ..አባቴን ስልክ ማስገዛት አለብኝ ብየ ወሰንኩኝ

#ክፍል 8⃣

ይ.........ቀ...
......ጥ.......ላ.........ል


Join👇👇👇
https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAEOFXIlKIXVySUTDcA
👍1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ ስምንት 8⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ



እነዛ የያዝኳቸዉ ጓደኞቼ ሁሌ Fb ላይ ሲጀናጀኑ ስልክ ሲያወሩ ቀናሁኝ .....እኔም እንደነሱ እንደመሆን ..አባቴን ስልክ ማስገዛት አለብኝ ብየ ወሰንኩኝ

አባቴ ኮንትራክተር ስለሆነ ድሬድዋ የተወሰኑ ቀናት ስራ ነበረዉ ሰርቶ ሲመለስ ... ስልክ አስገዛሁኝ...

ስልክ ከአስገዛሁኝ ቡሀላ ትምህርት ማጥናት የለ ቁርአን መቅራት የለ ሶላት መስገድ የለ በትምህርት ሰአት ሳይቀር facebook ላይ ቸክየ መዋል ስራየ ሁኗል... በfb ፎቶየን እፓስታለሁ በcomment ነዋል አምሮብሻል ሲሉኝ አቤት ያለኝ ደስታ ከኔ ዉጭ ቆንጆ ያለ አይመስለኝም ነበር ፡፡ በFb ብዙ ጓደኞች አፈራሁኝ በመጀናጀን ቢዚ አደረጉኝ....አላማየን እረሳሁኝ በfb እወድሻለሁ ያለአንቺ መኖር አልችልም የሚባሉ የወንዶች ከአንጀት ያልሆነች ከአፍ ብቻ ቃላቶች ማንበብ ለኔ የሚላኩ የፍቅር ገጠመኞች በfb message ተጨናንቆብኛል

የኔ ሴት ጓደኞችም ከኔ በላይ በfb ይጀናጀናሉ እነሱ ግን እንደፈለጉ ወንድ ጋር ማደር መጠጣት ካፌ መቀጣጠር ሲገናኙ መሳሳም ሴክስ ማድረግ ምንም አይመስላቸዉ የእነሱ አስተሳሰብ በዚህ እድሜያችን ላይፍ እንቅጭ ነዉ

እነዛ የተዋወኳቸዉ የወንድ የትምህርት ቤት ጓደኞቼም ስራቸዉ በfb አዉርተዉ ሴቶች ጋር መቀጣጠር ከዛም ማደር ዚና መስራት የተለመደ ተግባራቸዉ ነዉ ፡፡
ጠዋት ትምህርት ቤት ስንገናኝ አዳራቸዉን ይነግሩኛል ....በሚያስጠሉ ፈጣሪን የማይፈሩ ጓደኞች መሀል ሁኜ አላማየን እረሳሁኝ
አንድ ቀን ተሰባስበን ቁጭ ብለን የምታምር ልጅ በጎናችን አለፈች......አንዱ ተነስቶ ይቺን ልጅ በአንድ ሳምንት ዉስጥ ጀንጅኜ አብሪያት አድራለሁ ይላል
.....ጓደኞቹም አረ በጭራሽ አይሳካልህም ይቺ ሀርድ የቦጨቀች ናት እሺ አትልህም ይሉታል
.......እሱም በእጄ አርጌ አብረን ስናድር Video ቀርጬ አሳያችሇለሁ ብሎን ከጎናችን ተነስቶ ልጅቱ በሄደችበት አቅጣጫ ተከትሏት ሄደ.....
 
ከአራት ቀን ቡሀላ ይሄዉ ልጅ ምሳ ሰአት ላይ እኛ የተቀመጥንበት መጣ .....አንድ ሳምንት እንኳ ሳይፈጅበት ልጅቱ ተበላች ትናንት አብረን አደርን እኮ አለን
......እኛም አረ በጭራሽ ልናምንህ አንችልም ዉሸትህን ነዉ አልነዉ
.....እሱም ይሄዉ ማመን ከፈለጋችሁ ብሎ 30ደቂቃ ቆይታ ያለዉ video ማስረጃ አብሮ ያደረበትን ይዞ መጣ ፡፡ ሁላችንም Video አየነዉ ልጁ እዉነቱን ነበር ልጅቱ ጋር አብሮ አድሯል፡፡

እነዚህ ስድስቱም ጓደኛሞች ስራቸዉ ሴትን ልጅ በዛ በዚህ በማያምር የፍቅር ቃላት ለመናገር ከመተንፈስ የቀለለች እወድሻለሁ በሚሉት ስድስት ፊደል ቃላት ሴቶችን በቁጥጥራቸዉ አድርገዉ የፈለጉትን ከአገኙ ቡሀላ እንደተፉት ማስቲካ ዘወር ብለዉ እንኳ አያዮቸዉም ፡፡ ደግሞ ገርሞ የሚገርመኝ ማደራቸዉ ሳያንስ አብረዋቸዉ ሲያድሩ በስልካቸዉ ቀርፀዉ ለሁላችንም ያሳዩናል

እህቴ ሆይ እንደነዚህ አይነት ወንድ ልጆች አንዴ የሚፈልጉትን ከአንቺ ከአገኙ ቡሀላ ማስቲካ ሲገዛ ወረቀቱ ይጣላል ማስቲካዉ ይታኘካል፡፡ አንቺም ማስቲካዉ ወረቀቱን ልጦ ሲበላ አንቺን የፈለገዉን አገኘ ማለት ነዉ...ማስቲካዉ ጠአሙ ሲለቅ እሱ ጋር ከነበርሽ ሰለቸሽ ማለት ነዉ...መቼም ማስቲካዉን አይዉጠዉም ቢዉጠዉ ትርፍ አንጀት ይሆንብኛል ብሎ ያስባል...አንቺንም ተፍቶ ቆሻሻ ቦታ ይጥልሻል ለምን ለእሱ እንዳትሆኝ የማስቲካዉ ጠአም ስላበቃ አንቺም ከአንቺ የሚገኘዉ ጠአም ከኒካህ በፊት አልቋል ማለት ነዉ፡፡ ማስቲካ የሰዉ ልብስ ከነካ እኮ በቀላሉ አይለቅም አይደል..አንቺም አንተን አለቅም ያለአንተ መኖር አልችልም ብለሽ ሙጥኝ ብትይ ብታለቅሽ ምን ብትይ..ማስቲካዉ በእጅ ተፈግፎጎ እንደሚለቅ ወይም በነጭ ጋዝ እንደሚለቅ ..አንቺንም በእጁ ወይ ደርግሞ ወይ በተለያየ ዘዴ ያስወግድሻል ተግባባን መጀመሪያ ላይ ክብርን መጠበቅ ጥቅም ለራስ ነዉ፡፡ አንቺ ሂወትሽ የማስቲካ ሂወት እንዲሆን አትፍቀጅለት...ስንቶቻችንን ነን በዚህ የተተፋ ማስቲካ ሂወት እያሳለፍን ያለነዉ???አሁንስ ሳንተፋ እየታኘክን ያለነዉ ስንቶቻችን ነን?? ገና ማስቲካዉ ተገዝቶ ተፈቶ ለመታኘክ የተዘጋጀነዉስ ስንቶቻችን እንሆን??ከዚህ ሁሉ ግን የሚሻለዉ ገና ፓክድ እንደሆነ የተቀመጠዉ ማስቲካ አይሻልም ወይ እህቴ??


የሚገርማችሁ በትምህርት ቤታችን ጎበዝ ናት አላህን ትፈራለች ፀባይተኛ ናቸዉ ብለን የምናስባቸዉ ከእስላምም ከክርስቲያንም የነዚህ ልጆች ሰለባ በጣጣጣጣም ብዙ ናቸዉ፡፡ ሴት ልጅ ተላላ መሆኗ በዉብ ቃላትና ስራ በፈታ አፍ እንደምታምንና ላተቅረቡ ዚና ብሎ አላህ የከለከለንን ፀያፍ ወንጀል ለእነዚህ ዱርየ በሆኑ ልጆች በቀላሉ ክብራቸዉን በቀላሉ የሚያስረክቡ መሆናቸዉን ታዘብኩ፡፡

ለ30 ደቂቃ ለማይሞላ ስሜት ለምን የ30 አመት ፕላናችንን እናበላሻለን??የሴት ልጅ ፕላን አንዴ ከተበላሸ ለመመለስ ከዲፕሬሽን ለመዉጣት ብዙ አመታት እንደሚፈጅ ለምን እንዘነጋለን??
 
  ደግሞም የሚገርመኝ እነዚህ ልጆች መጀመሪያ አካባቢ እነሱ ፍቅር ይጀምሩ እና ሴቶቹ በእጃቸዉ መሆናቸዉን ሲያቁ ይተዋቸዋል....ከዛ ቡሀላ እራሳቸዉ ሴቶቹ እየደወሉ እወድሀለሁ ምን ሁነህ ጠፋህ ??ድምፅህን ሳልሰማ ማደር አልችልም እያሉ ሲያለቅሱ ስልኩን ላዉድ እያረጉ ያሰሙኛል.....

ሴትነት እንደዚህ ነዉ ወይ ??? እላለሁኝ......
እራሳቸዉ ደዉለዉ ዛሬ አንተ ጋር ማደር እፈልጋለሁ እያሉ የሚደዉሉም አሉ ....ልጆቹም ዛሬ አይመቸንም ይሏቸዋል....እባክህ እንደር ብለዉ የሚለምኑም ነበሩ ይሄን ሁላ ለኔ ይነግሩኛል በስልክም ያሰሙኛል፡፡
  
የልጆቹ ስልካቸዉ ዉስጥ የተለያዩ ሴቶች ፎቶ እና አብረዉ የሚያድሯቸዉ ሴቶች video ነዉ የሞላዉ....... ደግሞ የሚገርመኝ ፎቶሽን ላኪልኝ ልብስሽን አዉልቀሽ እያሉ ልብስ እያስወለቁ ሴቶችን ፎቶ ያስልኳቸዉና ፎቶዉን ለጓደኞቻቸዉ ለማሳየት ያስቀምጡታል

ይገርማል ሴቶች እንማራለን እያሉ ትምህርት ይሄዳሉ ግን ትምህርቱ ባለጌነት ስድነት ሁኗል..አሁን ዘመን ተማሪዉ ትምህርት ቤት የሚሄደዉ ላይፍ ለመቅጨት ነዉ እንጂ ተምሬ ያልፍልኛል ቤተሰቤን አሳልፍላቸዋለሁ...ለነገር ለሀገር ለወገን እጠቅማለሁ ብሎ የሚማር ከመቶ አንድ ቢገኝ ነዉ፡፡ ለምን ትምህርት ተምሮም ስራ የለም ...ግን የትምህርት ቤት ላይፍ እየተባለ ብዙ ሴቶች ስንት ሒወታቸዉን የወደፊት ፕላናቸዉን ያበላሻሉ???...., ስንት ሴቶች ራሳቸዉን እንደርካሽ ቆጥረዉ ከሚያረክሱ ወንዶች ጋር በዚህ ርካሽ አለም የረከሰ ተግባር በርካሽ ቦታ በርካሽ የስሜት ነበልባል የወደፊት ሰፊ ህልማቸዉን ዛሬ ላይ ያረክሳሉ፡፡
ጥፋት የወንዶችም ቢሆን ሴቶች መጀመሪያ ፊት ባይሰጡ ባይስቁ ..ወንድ ልጅ ጋር ቅርርብ ባይፈጥሩ...
የሴት ልጅ ሁሉም ገላዋ እፍረተ ገላ ስለሆነ ኢስላማዊ አለባበስ ቢለብሱ ፈጣሪ ያለዉን ትእዛዝ ቢተገብሩ ይሄ ሁሉ ባልመጣ እላለሁ👇👇👇
1👍1
የሚገርመዉ እነዛ ልጆች የቀመሷቸዉን ሴቶች እያነሱ ያወራሉ ስንት ድንግል እንዳገኙም ይነጋገራሉ ....ድንግልና በወንድ ልጅ የዉሸት የፍቅር ቃል የሚወሰድበት ..ሴት ልጅ ለባሏ ማስረከብ ያቃታት አሳዛኝ የትምህርት ቤት ጊዚያት ...የምንሰማዉ የምናየዉ የዘንድሮም የትዳር ፍች ድንግል አይደለሽም በሚል ሁኗል፡፡ ታዳ ሴት ልጅ በወንድ ልጅ በአፍ ብቻ እያመነች እሷዉ ደዉላ ድንግልናየን ዉሰድ ካለች ምን ዋጋ አለዉ ??? የሴት ልጅ መገለጨዋ ቁጥበነቷ አይናፋርነቷ ሀያእ ማድረጓ ነዉ ታዳ ዲነል ኢስላም ለሴት ልጅ ትልቅ ክብር ሰጥቶሽ ለምን ለፍጡር ተታለሽ አላህ ያከበረሽን በራስሽ ታከስሪያለሽ ???

ሴት ልጅ የምትከበረዉ አይናፋርነቷ ሀያእ ሲኖራት ነዉ..ሴትነት ቁጥብነት ከአይነአፋርነት ጋር የተያያዘ ነዉ...
ነብዩ ሰ.ዐ.ወ እንዲህ ብለዋል፡- ሀያእ አይናፋርነት ከእምነት ሲሆን እሱን የታደለ ሰዉ ደግሞ መኖሪያዉ ጀነት ነዉ ፡፡
ሀያእ ማጣት (ዓይን አዉጣነት)
ከደረቀ ቀልብ(ልብ)ሲሆን የደረቀ ልብ ያለዉ ሰዉ መኖሪያዉ ጀሀነም ነዉ፡፡ ብለዋል
ታዳ አይናፋርነት ከሌለ ሴት ልጅ ከወንድ በምን ተለየች???በተለይ የሴት ልጅ ማንነት እና ሂወት አይናፋርነት ጋር የተያያዘ ነዉ

አሁን አንድ ወንድ የፈለገዉን ሴት መርጦ አገላብጦ አይኑን አፍጥጦ በሚያገባበት ዘመን ....ልታገቢ ስትይ ድንግል ነሽ ወይ??? ሲልሽ ድንግልና እና ዳይነሰር ከጠፋ ቆይቷል ወይም አንዳንድ ደፋሮች ደም ከፈለክ ቄራ ሂደህ ደም ማየት ትችላለሁ ወይም አንዳንድ በንፍጥ ጭንቅላት የሚያስቡ ሴቶች ..ድንግልና ከፈለክ አንድ ንፍጣም በግ ገዝተህ አርደህ እንደነብር መጠጣት ትችላለህ እያሉ ከሆድ ያልወጣ ከአፍ ያመለጠ ሙድ መያዝ መፍትሄ ነዉ ወይ ?? ጥያቄዉ ጋር የማይመሳሰል መልስ ከመመለስ ለወደፊት ጥያቄዉን ለመመለስ ከዛሬዉኑ መዘጋጀት አይሻልም ወይ ???



ከትምህርት ቤታችን ከኦል አንደኛ የምትወጣዉን ልጅ በፍቅር ለማጥመድ እነዛ ልጆቾ እልክ ተያያዙ ፡፡ ከዛም እኔ ላጥምዳት እኔ እየተባባሉ ሊስማሙ ስላልቻሉ ወረቀት ጠቅልለዉ በእጣ አደረጉት፡፡ ከዛም ስሙ የወጣለትን በፍቅር አክንፈህ እወድሀለሁ ስትልህ የፍቅር ወሬ ስታወራህ በስልክ ሪከርድ አርገህ አሰማን  አሉት
....... ልጁም ተስማማ ታያላችሁ በቅርብ ቀን የተሰጠኝን ተልዕኮ አሳካለሁ ብሎ ከትምህርት ቤታችን አንደኛ የምትወጣዉን ልጅ በፍቅር ለማጥመድ ስራዉን ጀመረ....


ይቺኑ ጎበዝ ተማሪ ተብየ አስራ አምስት ባልሞሉ ቀናት ዉስጥ በፍቅር አጥምዷት እራሷዉ ደዉላ እያለቀሰች እወድሀለሁ ያለ አንተ መኖር አልችልም ስትል ላዉድ አድርጎ አሰማን ፡፡ በጣም ገረመን እንደዚህ መሆኑ ይገርማል...ሴት ልጅ እንደዚህ ተላላ ልፍስፍስ ናት ወይ ???አልኩኝ ፡፡ እነዚህ ልጆች ብዙ ነገር አሳዩኝ
ይህ ሁሉ ሙስሊም ክርስቲያኑም ከሀይማኖት መዘናጋታችንን እና የሁሉም ሀይማኖት ተከታይ መሪዎች ፓለቲካ ላይ ስለገቡ .. ይሄን ህዝብ መታደግ ከዚህ መጥፎ ባህሪ በተለያዩ መድረኮች አዘጋጅተዉ የማስተማር አቅማቸዉ አናሳ መሆኑን ያሳያል

የሚገርመኝ እነዚህ ልጆች ሁሉም ሴት እህቶች አሏቸዉ ግን ለሴት ልጅ የሚያዝን ሩህሩህ ልብ የላቸዉም ፡፡ግን በሰፈሩት ቁና መሰፈር አይቀርም አይደል የሚባለዉ የነሱም እህቶች ሌላ ወንድ ልጆች ጋር የተለያዩ ቦታዎች አያቸዋለሁ .ለሌላ ሴት ልጅ የማያዝን በእህቱ ላይ ወጥመድ እያጠመደ እንደሆነ መዘንጋት የለበትም..ለምን አንተ ለሌላ ሴት ልብህ ካላዘነ ካልራራ የአንተን እህት የሚያጀዝበዉም ልብህን አይቶታል ማለት ነዉ በሌላ ሴት ቢዚ ስለመትሆን ለእህትህ ከለላ መሆን አችልም..ነገር ግን አንተ ፈጣሪህን የምፈራ ከሆነ ለሴት ልጅ ክብር ካለህ..እህትህ ለራሱ ሌላ ወንድ ጋር ምንም የፍቅር ግንኙነት አጀምርም፡፡ ሌሎች ተኩላ ወንዶች አንተን አልፈዉ እህትን መቼም እንደማያጠቁ እርግጠኛ ሁን፡፡

    እኔን ደግሞ የሚወዱኝ የሚያፈቅሩኝ የትምህርት ቤት ልጆች ነበሩ... እነሱ እኔን ማዉራት ሲፈሩኝ አጣብሱን ብለዉ ሲጠይቋቸዉ ..እሺ ብር ክፈሉ ለጉዳዩ ማስጨረሻ እያሉ ብር እያስከፈሉ ብሩን እንደሚያጠፉት ሁሌ ይነግሩኛል፡፡

እኔን ማንም ወንድ ጋር መቀራረብ እንደማልፈልግ ያቃሉ በጭራሽ አሳልፈዉ ለወንድ አይሰጡኝም...እኔን አንድ ወንድ መጥቶ አጣብሱኝ  አብሪያት እንዳድር ብሎ ከጠየቃቸዉ እስከ መጣላት እስከ መደባደብ ድረስ ብዙ ጊዜ ደርሰዋል፡፡

  አንድ ቀን የሆነ ልጅ ግድ ካላወራሽኝ እያለ ሲያስቸግረኝ ሶስቱ እሱን ደብድበዉት ለተወሰኑ ቀናት ፓሊስ ጣቢያ ታስረዋል.....ምን ጥቅም አለዉ የስንቱን ሒወት እያበላሹ እኔን ቢከላከሉልኝ ምንም ፋይዳ የለዉም....ብዙ ሴት ልጆች የነዚህ ልጆች ሰለባ ሁነዋል


አይ ትምህርት ቤት አሁን ዘመን ላይ እንዲህ ሁኗል...መፍትሄዉ መቼ ይሆን እኛ ሙስሊሞች የራሳችን የሆነ ትምህርት ቤት አቋቁመን ወንድ ለብቻ ሴት ለብቻ በተለያየ ቦታ ተከፍቶ ማስተማር እና መማር ስንችል ብቻ ነዉ፡፡
ለወደፊት ይጠቅሙናል ዲነል ኢስላምን ይረከባሉ ለጥሩ ደረጃ ይደርሳሉ ብለን ተስፋ ያደረግናቸዉ ልጆቻችን በትምህርት ቤት መዘዝ ረክሰዉ እንዳይቀሩ እላለሁ፡፡

በሁለም ከተሞች የሙስሊም ትምህርት ቤት ተብየ አለ...ግን የሚያስተምሩት ሴትና ወንድ በአንድ ላይ እንደዉም የሙስሊም ትምህርት ቤት ተብሎ ስንት ወንጀል ስንት ግፍ እየተሰራበት አይደል??
ለትዉልድ የጠቀመዉ የለም ብቻ የሙስሊም ትምህርት ቤት ተብሎ ስሙ ብቻ ተረፈን ...

በነብዩ ( ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም) ዘመን የነበሩ ሴቶች በመስጅድም ይሆን በገቢያ ቦታ ከወንድ ጋር በጭራሽ አይቀላቀሉም ነበር"

አላህ የነቢዩን ﷺ ባለቤቶች ያዘዘው በቤታቸው የረጉ ቁጥቦች ይሆኑ ዘንድ እንጅ ከማንኛውም ወንድ ጋር እንዲቀላቀሉ አይደለም።
አላህ በተከበረ ቁርአኑ እንዲህ ይላል፦

«የነቢዩ ሴቶች ሆይ ከሴቶች እንደማናቸው አይደላችሁም፤ አላህን ብትፈሩ (ትበልጣላችሁ)፤ ያ በልቡ ውስጥ በሽታ ያለበት እንዳይከጅል በንግግር አትለስልሱም፤ መልካምንም በንግግር ተናገሩ። በቤቶቻችሁም ውስጥ እርጉ፤ እንደ ፊተኛይቱ መሃይምንነት ጊዜ መገለጥም በማጌጥ አትገለጡ፤ ሶላትንም በደንቡ ስገዱ፤ ዘካንም ስጡ፤ አላህንና መልክተኛውንም ታዘዙ፤ የነቢዩ ቤተሰቦች ሆይ! አላህ የሚሻውን ከናንተ ላይ ርክሰትን ሊያስወግድና ማጥራትንም ሊያጠራችሁ ብቻ ነው።»
[አል-አሕዛብ፡ 32-33]
አላህ የነቢዩን ﷺ ሚስቶችን ያዘዘበት ይህ ትዕዛዙ ሌሎች አማኝ ሴቶችን በሙሉ እንደሚመለከት ኢብኑ ከሢርና ሌሎችም የተፍሲር ሊቃውንት ተናግረዋል።

«ይህ አላህ የነቢዩን ﷺ ሴቶችና እነርሱን በዚህ ላይ የተከተሉ አማኝ ሴቶችን በሙሉ ያዘዘበት ስነ ስርዓት ነው።ብለዋል

«ሴት ልጅ ዐውራህ (ድብቅ) ናት። ብቻዋን ከቤቷ ከወጣች ሸይጧን ይከተላታል።»ብለዋል ሀቢቡና ሙሀመድ ሰዐወ


ማትሪክ ፈተና ደረሰ፡፡ ፈተናዉንም ያለምንም ቅድመ ዝግጅት  ተፈተንኩኝ........ትምህርት ተዘጋ በክረምት አልፎ አልፎ የክላስ ጓደኞቼ ጋር በመደዋወል በfb በማዉራት አሳለፍኩኝ



የማይደርስ የለም የማትሪከ ዉጤት በኢንተርኔት ተለቀቀ ..እኔም ዉጤቴን ለማየት ጓደኞቼ ጋር ሄድኩ...የማትሪክ ዉጤቴም...


#ክፍል 9⃣
ይ.........ቀ.........
......ጥ.........ላ...........ል


JOIN

           `·. www.tg-me.com/Islam_and_Science
www.tg-me.com/Islam_and_Science
•════•••🍃🌺🍃•••════•
👍1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ ዘጠኝ 9⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ




     የማትሪክ ዉጤት በኢንተርኔት ተለቀቀ የሚገርመዉ ነገር በኢንተርኔት ሁሉም ተመለከቱ... የኔን ኮዱን ስናሰገባዉ አልሰራ አለኝ፡፡ ቢባል ቢባል የኔን ዉጤት ለማየት በጭራሽ ሊሳካ አልቻለም ...

የትምህርት ቤት ጓደኞቼ ..ናርዶስም እነዛ ስድስቱ የትምህርት ቤት ዱርየ ልጆች ሳይቀር ሁሉም ወደ አስራ አንደኛ ክፍል የሚያሳልፋቸዉን ዉጤት አግኝተዋል፡፡ የእኔን ለመመልከት ግን የአላህ ነገር እምቢ አለኝ፡፡

ናርዶስ ቢጨንቃት ነዋል እስትሬት 4 ነጥብ አምጥተሽ ይሆናል የአንቺ እምቢ ያለዉ ትለኛለች ....ደግሞ ሌሎች ጓደኞቼ ዉጤትሽ ሁሉም F ሁኖ ትምህርት ሚኒስተር የአንቺን በonline መልቀቁ ደብሮት ነዉ እያሉ ሙድ መያዣ አረጉኝ፡፡

ባለመሰልቸት እኔም ሁሉም ጓደኞቼም ከአንድ ሳምንት በላይ ለማየት ብንታገል እምቢ አለን......
  
   አዲስ አበባ ያለዉ አጎቴ ደዉሎልኝ... ነይ ትንሽ ቀን እኛ ጋር አሳልፈሽ ትመለሻለሽ አለኝ.....
እኔም እሺ ብየ ወደ ሸገር ጉዞየን ቀጠልኩኝ፡፡
አዲስ አበባ ስመጣ የማሳልፈዉ የአጎቴ ልጆች ጋር ስዝናና ነዉ የምዉለዉ ፡፡

ሸገር ሁኜ ዉጤቴን ለማየት ያላረኩት ጥረት የለኝም ግን የኔ code ሲገባ ጭራሽ አይሰራም ነበር፡፡ ጓደኞቼ እንዳሉት ዉጤት ሀሉም F ስለሆነ ትምህርት ሚኒስተር አፍሮበት በኢንተርኔት የኔን ዉጤት ያለቀቀ አስመሰለዉ እኔንም አጠራጠረኝ...
  
   አጎቴ ጠዋት ላይ ቁርስ እየበላን ነዋል ዛሬ የተጨናነቅሽዉን ዉጤት በህልሜ አየሁት ያመጣሽዉ 3.0  ነዉ  ደግሞ የኔ ህልም የሚፈታዉ በተቃራኒ ስለሆነ ወድቀሻል አለኝ...
......እኔም ህልም አኮ ዉሸት ነዉ አጎቴ እያልን ተሳሳቅን፡፡

የማትሪክ ዉጤት ኢንተርኔት ላይ ተለቆ የኔን ለማየት አልሰራም ማለቱ ቅዠትም ህልምም ከተለለቀ ጀምሮ እየተፈራረቀብኝ ነዉ፡፡ በህልሜ አንዴ አልፌ ፕሪ ፓራቶሪ ጓደኞቼ ጋር ስማር ይታየኛል፡፡ ደግሞ አንዳንዴ ወድቄ ስናደድ ይታየኛል ፡፡ ህልሜ ጥሩ ሲሆን አልሀምዱሊላህ ..ህልሜ መጥፎ ሲሆን አኡዙቢላህ ማለት የዘወትር ተግባሬ ሁኗል ...


እስኪ ስለህልም አንዲት ቀለል ያለች ቀልድ ጀባ ልበላችሁ ጥርስም ላይ ባደርስ ለአይን ጥራት ትሆናለች😊...
አንድ ዲነል ኢስላምን ጠለቅ ብሎ የማያቅ(ጃሂል) የገጠር ሰዉ እና እዛዉ አካባቢ የሚኖሩ ሸህ ነበሩ፡፡ ሸህየዉ ሚስት የላቸዉም ግን የጃሂሉን ሚስት ሚስቴ በሆነች እያሉ ትንሽ ሆዳቸዉ ይቋምጥ ነበር...
ከዛም አንድ ቀን ጃሂሉ ህልም ያያል ፡-ህልሙም ሚስቱን ሶስቴ ሲፈታት ይመለከታል..ከዛም ከእንቅልፉ ይባንናል ፡፡ ጃሂሉ ግራ ገባዉ በህልሜ ሚስትን ሶስቴ ፈትቻታለሁ ምን ይሻለኛል ??እያለ ግራ ይገበዋል ..ከዛም ያየዉን ህልም የሚያማክረዉ የሚጠይቀዉ ሰዉ ሲፈልግ የሰፈሩ ሸህ ትዝ ይሉታል...ከዛም ወደ ሸህየዉ ሄደ፡፡
ከዛም ሰላምታ ከተለዋወጠ ቡሀላ ሸሀችን ዛሬ የመጣሁት ሚስቴን በህልሜ ሶስቴ ስፈታት አይቼ ነዉ በቁርአን በሀዲሱ ህልሙ እንዴት ይታያል??ብሎ ይጠይቃቸዋል..
ሸህየዉም:-በህልምህ ሶስቴ ከፈታህማ ሚስትህን ፈተሀታል ማለት ነዉ ይሉታል፡፡
ጃሂሉም ሰዉየ በአየዉ ህልም እየተናደደ እቤቱ ተመልሶ ሚስቱን በህልሜ ሶስቴ ስለፈታሁሽ ከአላህ ጋር መጣላት አልፈልግም ብሎ ከመኖሪያ ቤቱ ያሰናብታታል፡፡

ከተወሰኑ ቀናት ቡሀላ ሸህየዉ የጃሂሉን ሚስት አግብተዉ ወደ ራሳቸዉ ጎጆ ወስደዉ ሂወታቸዉን እየመሩ ነዉ..ጃሂሉም ሚስቱን በነሸህ መነጠቁን ሲያይ እየለደመ ዝም ማለት ብቻ ምርጫዉ ሆነ...

የጃሂሉ አንድ ምርጥ ጓደኛ ነበረዉ...ሚስቱን እነሸህ ጋር ሲያያት ወደ ጃሂሉ መጥቶ ሲጠይቀዉ...እኔማ በህልሜ ሚስቴን ሶስቴ ስፈታት አይቼ ለነሸህ ሳማክራቸዉ ግዴታ መፍታት አለብህ ሲሉኝ እኔም እዉነት መስሎኝ ፈታሁኝ ከዛም ሸህየዉ አገቧት ብሎ ለጓደኛዉ ይነግረዋል...
ጓደኛዉም ተናዶ ና አብረን እንሂድ ጥልቆ ይዘህ ተከተለኝ ብሎ ወደ ሸህየዉ ቤት ሄዱ..ከዛም በያዙት ጥልቆ የሸህየዉን ቤት ግድግዳዉን መምታት ጀመሩ..
ሸህየዉ ከቤት ወጥተዉ ...ምን እያደረጋችሁ ነዉ?? ቤቴን እናዳታፈርሱ ብለዉ ጠየቋቸዉ
..ጓደኛዉም ፡-ሸሀችን ማታ በህልሜ የአንቱን ቤት በጥልቆ ሁለታችን እየመታን ስናፈርሰዉ አይቼ ነዉ ..አላቸዉ
..ሸህየዉም:- እንዴ ህልም እኮ ዉሸት ነዉ ቤቴን እንዳታፈርሱ .ሲሉ
..ህልም ዉሸት ከሆነ .ህልም እዉነት ነዉ ብለሁ የወሰድኳትን የጓደኛየን ሚስት መልሱ 😆😆😆ብሎ እርፍ

  አጎቷም ያየዉ ህልም እኔም ያየሁት ህልም  እንደዚህ ቀልድ ግራ የሚያጋባ ህልም ሁኗል፡፡

ደግሞ አጎቴ ህልሙን ከነገረኝ ከሁለት ቀን ቡሀላ ማታ ተኝቼ እኔም የሚገርም ተአምር የሚመስል ህልም አየሁኝ....,ሁሉም የክፍል ጓደኞቼ አልፈዉ የኔ ዉጤት ግን በጥቁር ቀለም ተሰርዞ አየሁት ከዛም ጓደኛየን ምንድን ነዉ ይሄ በጥቁር ቀለም የተሰረዘዉ ??? አልኳት
.....እሷም ነዋል አንቺ እኮ ከሁላችንም ተነጥለሽ ወድቀሻል ስትለኝ ብንን ብየ ተነሳሁኝ...አኡዙቢላሂ ሚነሸይጧን ኢሮጂም ብየ መልሼ ተኛሁኝ፡፡

ይሄን ህልም ካየሁ ከሶስት ቀን ቡሀላ የማትሪክ ዉጤት ትምህርት ቤት መጣ፡፡ ናርዶስ የኔን ዉጤቴን ካርድ አይታ ለአባቴ ደዉላ ነገረችዉ......

አባቴም ደዉሎ መጀመሪያ እኔን ከአረጋጋኝ ቡሀላ አብሽሪ ማለፍ መዉደቅ ያለ ነዉ ትኩረት አትስጭዉ ...... የማትሪክ ዉጤትሽ ለpriparatoty የሚያስገባ ዉጤት አላመጣሽም፡፡ ተረጋጊ አላህ ያለዉ ነዉ የሚሆነዉ ሰዉ እርዚቁ በትምህርት ብቻ አይደለም አለኝ፡፡

እኔም መዉደቄን ሲነግረኝ ስልኩን ዘጋሁት እንባየ ቀደመኝ በጣጣም አለቀስኩኝ ከምነግራችሁ በላይ በጣም አዘንኩኝ ሁሉም ጓደኞቼ  ሲያልፉ ከጓደኞቼ እኔን ብቻ ስወድቅ በጣጣም ተሰማኝ፡፡ በሒወት ተስፋ ቆረኩኝ ወደፊት የመኖር ህልም አልታየኝ አለ ...ፈጣሪየ ምን አረኩህ በኔ ላይ ይሄን ያህል በደል ?? እያልኩ ማልቀስ ሆነ ስራየ፡፡ በጣም ተሰማኝ ዲፕሬሽን ዉስጥ ገባሁ...ፈታኝ ሀዘን በአንዴ ዉስጤን ወረረዉ ....ጭራሽ መቋቋም አልቻልኩም፡፡ በማልቀስ በመበሳጨት ከአንድ ሳምንት በላይ ሆነኝ

አጎቴ እና ሚስቱ እኔን ማፅናናት ማባበል ሁኗል ስራቸዉ መዉደቄን ከሰማ ቡሀላ አጎቴ ለኔ መጨነቅ ይዟል፡፡እጅግ የበዛ ደስታና እጅግ በጣም የሚከብድ ሀዘን ለሰዉ ልጅ ሂወት ትልቅ ወጥመዶች ናቸዉ ፡፡በጣም ከመበሳጨቴ ከመናደዴ የተነሳ ከአሁን ቡሀላ ጅማ ከተማ አልሄድም እዚሁ አዲስ አበባ ነዉ የምኖረዉ አልኩኝ
.........የአጎቴ ሚስትም አብሽሪ እዚሁ በግል አሪፍ ኮሌጅ ገብተሽ በዲፕሎማ ትማሪያለሽ ብላ አፅናናችኝ፡፡

አጎቴ ለአባቴ ደዉሎ ነዋል እዚሁ አዲስ አበባ በግል ኮሌጅ ልናስተምራት አስበን ነበር ፍቃደኝነትህን ልንጠይቅህ ነዉ የደወልኩልህ አለዉ
.....አባቴም አረ አይሆንም በጭራሽ አታስቡት እኔ ያለ ነዋል መኖር አልችልም ..እንኳን ከእኔ አመት እርቃ ትምህርት ልትማር ይቀርና እናንተ ጋር ለተወሰነ ቀናት ስታሳልፍ እንዴት እንደምናፍቀኝ እኔ እና አላህ ነን የምናቀዉ ..በጭራሽ የማይሆን ነዉ፡፡ እዚሁ ጂማ ስትመጣ ተማክረን የምፈልገዉን አደርግላታለሁ እንጂ መቼም ቢሆን ከእኔ እርቃ ትምህርት እንድትማር አልፈቅድም አለ አባቴ፡፡👇👇👇
👍1
ለነገሩ አይፈረድበትም አባቴ እዉነቱን ነዉ ከሁላችንም ልጆች እኔን በጣም ይወደኛል በፊት ጀምሮ አንቺ ባትኖሪ ይሄ ቤት እስከ አሁን ትዳሩ ይፈርስ ነበር ብዙ ቀን ብሎኛል፡፡

አባቴም ይሄንን ሀሳብ ከአጎቴ እንደሰማ ..,በሚቀጥለዉ ቀን አዲስ አበባ መጥቶ ወደ ጂማ ወሰደኝ....እኔን በዚሁ የምለየዉ ነዉ የመሰለዉ ...ነዋል ሁሌም ቢሆን ከጎኔ እንድትርቂኝ አልፈልግም አለኝ....

ሀምሌ ነሀሴ ክረምቱ ብርዱ አልፎ መስከረም ተተክቷል ትምህርት ተከፈተ ጓደኞቼ እየተማሩ ነዉ ፡፡

እኔ ግን ከቤት መዉጣት የለ እንደበፊቱ ጓደኞቼ ጋር መገናኘት የለ እቤት ታሽጌ ተሸሽጌ መዋል ጀምሪያለሁ.....በቃ ብዙ ነገር አስጠላኝ በሒወቴ አዘንኩኝ....አላህ ጋር በመጣላት ትልቅ ጦርነት ጀመርኩኝ ቀዷ እና ቀደር ነዉ ብየ መቀበል ሲገባኝ አላህን የተለያዩ ነገሮች እያነሳሁ ማማረር መዉቀስ ጀመርኩኝ...አላህን እንዴት ለምን እያልኩ ጥያቄ በጥያቄ ሁንኩኝ ይሄ ሁላ ፈተና ለኔ ለምን?? አልኩኝ....

>>>>ጓደኞቼ ማግባት ቢፈልጉ ትዳር ልመስርት ቢሉ የሚፈልጉት ነገር አላቸዉ ይሄዉም የሚፈለገዉ ድንግልና ነዉ የሚፈልጉትን ወንድ መርጠዉ ማግባት ይችላሉ ....እኔ እኮ ድንግል አይደለሁም በልጅነቴ አጥቸዋለሁ ..መልክ ቢኖረኝም እንዴት ብየ ነዉ ወንድ ሲጠይቀኝ የማገባዉ ?? በመልክ ብመረጥም ለትዳር ብቁ አይደለሁም ....ሰንት የማቃቸዉ ሴቶች ጂማ ላይ ከትዳር የሚፋቱት ቢክራ አይደለሸም እየተባለች ስትፈታ ስትባረር እያየሁ እንዴት እኔ ተስፋ ወኔ ይኑረኝ ??? ተስፋ ቆረጥኩኝ ደግሞም ወይ ትምህርቴን አልተማርኩ ከአስር ወደኩኝ ብማር እኮ ይሄን የልጅነቴን በደል የምነግረዉ የሚረዳኝ አገኝ ነበር ብየ ብቻየን መጨናነቅ ሆነ ስራየ የአእመሮ ጭንቀት ዲፕሬሸን ዉስጥ ወደኩኝ፡፡
     ነብዩ ሙሀመድ ﷺእንዲህ ብለዋል:- በአላህ ዓይን ጠንካራዉ የሆነዉ አማኝ ከደካማዉ ይልቅ የበለጠና የተወደደ ነዉ፡፡ የሚጠቅማችሁን ነገር ለማግኘት ጥረት አድርጉ፡፡አንዳች መጥፎ ነገር ካጋጠማችሁ እርር ኩምትር በማለት "እንዲህ እንዲህ አድርጌ ቢሆን ኖሮ ይህ ነገር አያጋጥመኝም ነበር""አትበሉ፡፡ ከዚህ ይልቅ አላህ የሻዉ ነገር ሆነ ተፈፀመ በሉ፡፡ ""ቢሆን ኖሮ""የምትለዉ አባባል ሰይጣንን ታስደስታለች..ብለዉናል
.....አላህ ባመጣዉ በቀዷና በቀድር እንዳምን ልቦናዉን ማስተንተኑን ይስጥሽ በሉኝ


    ከተወሰኑ ቀናት ቡሀላ አባቴ እቤት ነበር.. መኝታ ክፍሌ ሁኜ ተኝቼ ብዙ ነገር እያሰብኩኝ...አባቴ ነዋል ነዋል እያለ ሲጠራኝ ሰማሁኝ ....
...... አባቴ እተቀመጠበት ሳሎን ሄድኩኝ
.......አባቴም ነይ ከጎኔ ቁጭ በይ ዛሬ የማማክርሽ ጉዳይ አለኝ ...ዛሬ የምንማከረዉ ቀልድ አይደለም ስለወደፊት ሂወትሽ ነዉ.......የምጠይቅሽን ተረጋግተሽ ትመልሽልኛለሽ አለኝ..
....እኔም እሺ አልኩት
.......አባቴም ለወደፊት ምንድን ነዉ አላማሽ ?? ምን አስበሻል ?? በግል ኮሌጅ ገብተሽ በዲፕሎማ መማር ነዉ አላማሽ?? ወይስ አጥንተሽ ፕራይቤት ለመፈተን ነዉ ?? ወይስ ብር እና
ስራ ላመቻችልሽ እና ንግድ ዉስጥ መግባት ትፈልጊያለሽ ?? ወይስ ሌላ ያሰብሽዉ ካለ ንገሪኝ....... አለኝ
..........ይሄን ጥያቄ ሲጠይቀኝ ብቻየን ጭልጥ ያለ ሀሳብ ወሰደኝ....ወላሂ በጣም እልክ ተሰማኝ እንዴት እነዛ ሰነፍ ጓደኞቼ አልፈዉ እኔ እወድቃለሁ ?? እያልኩ አእምሮየ ጋር ማመላሰስ ጀመርኩኝ....
ግን መልሼስ ፕራይቤት ተፈትኜ ብወድቅስ ብየ ለሁለት ሀሳብ ተከፈልኩ.....
....አባቴን አሁን ላይ ምንም ማሰብ አልፈልግም መወሰንም አልችልም.... አልኩት
-----------------አባቴም፡- ነዋል ተረጋግተሽ እሰቢበት አንቺ እንድትጨናነቂ አልፈልግም...መማርም ከፈለግሽ ምን መማር እንደምፈልጊ ..ወደ ስራም መግባት ከፈለግሽ ብር ሰጥቼሽ ምን መስራት እንደምፈልጊ ..በተጨማሪም እኔ ካልኩሽ ዉጭ የራስሽ ሀሳብ እቅድ ካለሽ  የአንድ ወር ጊዜ ሰጥቸሻለሁ...በአንድ ወር ዉስጥ አስበሽ ወስነሽ ትነግሪኛለሽ  አለኝ.....
እኔም እሺ አባቴ ብየ ከአጠገቡ ተነስቼ መኝታ ክፍሌ ሂጄ ተቀመጥኩኝ.....

አባቴ እንዳለኝም አንድ ሀሳብ መጣልኝ....ጓደኞቼ የሚደርሱበት ደረጃ መድረስ አለብኝ ..ስለሆነም አጥንቼ ፕራይ ቤት ተፈትኜ ጥሩ ዉጤት አምጥቼ priparatory መግባት አለብኝ ...የኔ ችግር 10ክፍል ላይ በመጥፎ ጓደኞች ተከብቤ ተተብትቤ ስላላጠናሁ ስላልተዘጋጀሁ ነዉ እንጂ ካጠናሁ ከተዘጋጀሁ እኔ ጎበዝ ነኝ እኮ አቃለሁ...እያልኩ ያሳለፍኳቸዉ ስህተቴ ዋጋ ማስከፈሉን አወኩኝ....10ን ፕራይ ቤት ካለፍኩኝ ቡሀላ  ዩኒቨርስቲ መመረቅ አለብኝ የሚል ሀሳብ በአእምሮየ ይደጋገም ይዟል፡፡

ከሁለት ቀን ቡሀላ አባቴ ወስኛለሁ ስለዉ ..ጊዜዉ ገና ነዉ በደንብ እሰቢበት አለኝ... ከአንድ ሳምንትም ቡሀላ ወስኛለሁ ስለዉ አባቴም በጭራሽ ይሄ የፍጥነት ዉሳኔ አይሆንም አንድ ወር ሰጥቸሻለሁ አንድ ወሩ ሲያልቅ እኔዉ ምን ወሰንሽ ብየ እጠይቅሻለሁ አለኝ፡፡


የተሰጠኝ አንድ ወር የማሰብ ጊዜ አለቀ....ከአንድ ወር ቡሀላ አባቴም ጠርቶ ምን ወሰንሽ ????አለኝ
....እኔም አባቴ አጥንቼ ተዘጋጅቼ ፕራይቤት ተፈትኜ ዉጤቴን አሻሽየ 11 ክፍል ለመግባት ወስኛለሁ አልኩት፡፡
....አባቴም ግን በደንብ አስበሽበታል እርግጠኛ ነሽ?? አለኝ
........እኔም አዎ አስቤበታለሁ እርግጠኛ ነኝ አልኩት
....አባቴም እሺ በሀሳብሽ ምንም አልልም ጣልቃ አልገባም ግን ይሄ ሀሳብሽ የራስሽ ሀሳብ ነዉ ..እራስሽ መጀመሪያ አስበሽ ወስኝ ብየሽ ወስነሻል የዘንድሮዉን አመት በአንቺ ሀሳብ በአንቺ ፍላጎት ተስማምቻለሁ፡፡ ነገር ግን በሚቀጥለዉ አመት ግን አንቺ ያሰብሽዉ ባይሳካ ፕራይ ቤት ዉጤት ባይመጣልሽ አንቺ ሒወት ዉስጥ መወሰን የምችለዉ እኔ ነኝ.... የዛን ጊዜ አንቺ ሳትሆኝ እኔ አባትሽን ያልኩሽን ብቻ ነዉ መታዘዝ እና መሆን የምትችይዉ ...በዚህ በኔ ሀሳብ ትስማሚያለሽ አትስማሚም ???አለኝ
.......እኔም ትንሽ ከአሰብኩኝ ቡሀላ በአባቴ ሀሳብ.......


#ክፍል 🔟
ይ......ቀ.......
.....ጥ.........ላ.........ል


: ❀ share
           `·. www.tg-me.com/Islam_and_Science
www.tg-me.com/Islam_and_Science
•════•••🍃🌺🍃•••════•
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ አስር 🔟

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ




እኔም ትንሽ ከአሰብኩኝ ቡሀላ አባቴ አቃለሁ ለኔ አስበህ እንደሆነ ሁሌም ቢሆን በአንተ ሀሳብ እስማማለሁ ...መጀመሪያ እድሉን ስለሰጠሀኝ አመሰግናለሁ አልኩት፡፡
     አባቴም የኔ እኮ አይኔ ማረፊያ መኩሪያ የወደፊት ተስፋየ አንቺ ነሽ ነዋል ብሎ ግንባሬን ሳመኝ.....እኔም አንገቱ ላይ ጥምጥም አልኩኝ

    ፕራይቤት ለመፈተን የተሻለ ዉጤት ለማምጣት ማጥናቴን ጀመርኩኝ ፡፡ አጋዥ መፅሀፎች ገዛሁኝ ...ቀን በቀን ችከላዉን ተያይዠዋለሁ... ጠዋት ጀምሬ እስከ ማታ ድረስ ነበር የማጠናዉ ፡፡ ወላሂ ይገርመኛል ምግብ ለመብላት ለራሱ ትዝ አይለኝም ነበር፡፡

ለሒወቴ መስተካከል ከፍተኛ ሚና የወሰደዉ ከ10 ከወደኩኝ ቡሀላ ነዉ፡፡ ከትምህርት መዉደቄ በያናድደኝ ቢያበሳጨኝም ፈጣሪ አንዳንድ ፈተናዎችን የሚያሽክመዉ ለኛዉ ለዉጥ መሆኑን የተረዳሁበት እኔ ካሰብኩት አላህ የመረጠልኝ የተሻለ መሆኑን ያየሁበት ጊዜያቶች ናቸዉ፡፡ እቤት ብቻየን ስለምዉል የትምህርት ቤት መጥፎ ጓደኞችን እራኩኝ ..ሰአቱን ሳላሳልፍ ሶላት መስገድ ጀመርኩኝ ..በወጣትነቴ ሒጃብ ለብሰሽ ባልቴት መሰልሽ ብለዉ ያስወለቁኝን ሒጃቤን መልሼ አላህን ማረኝ አይለመደኝም ብየ ለበስኩኝ.....ከነመኖሩ የረሳሁትን አንስቸዉ የማላቀዉን ቁርአን መቅራት ሙራጅአ ማድረግ ጀመርኩኝ ፡፡ እስኪ ስለሂጃብና የተከበረዉ ቅዱስ ቁርአን አንዳንድ ነገር ልበላችሁ.....

✿✿✿ ሒጃብን ሸሪዓው በሚያዘው መልኩ ዘውትር ለብሶ ማክበር ነው እንጂ የሒጃብ ቀን የሚባል የተለየ ቀን የለውም!!
"ሒጃብ ማለት እስልምና በሴት ልጅ ግዴታ ያደረገባት ሙሉ አካሏን የምትሸፍንበት ሰፊ ልብስ እንጂ በአመት አንዴ አናቷ ላይ ብጣሽ ሻሽ ጠምጥማ ቀን ለይታ የምታከብረው ነገር አይደለም!!
"
ሒጃብ ማለት ሴት ልጅ እዚህች አለም ላይ ከተለያዩ ባለጌዎች ሙሉ አካሏን የምትሸፍንበትና የተለያዩ ጨዋ ወንዶች ደግሞ እርቃኗ በመሄዷ እንዳይፈተኑ የምታደርግበት ከፈጣሪዋ አላህ ዘንድ የታዘዘችው በህይወት ዘመኗ ሁሉ የማትለየው ልብስ ነው።
"
ሒጃብ ማለት ሸይጧን እና የእስልምና ጠላቶች እንደሚፈልጉት የምትለብሰው ልብስ ሳይሆን የፈጠራት ፈጣሪዋ እንዳዘዛት ዘውትር የምትለብሰው ወደ ፈጣሪዋም የምትቃረብበት የፅድቅ ልብስ ነው።
ከሸሪዓው ከሚፈልገው የሒጃብ አይነት ውጪ ከሆንሽ ራስሽን ለባለጌዎችና ለብልግና እያመቻቸሽ ነው ማለት ነው።
"
ሒጃብሽን አላህ ባዘዘሽ መልኩ ከለበሺው ነገ በአኼራ ሰውነትሽ እሳት እንዳይነካውም ይከላከልልሻል።
"
ሒጃብ ስለብሺ ትልቅ ሰዉ አስመሰለሽ አላማረብሽም እያሉ የሚያጃጅሉሽን ትተሽ ፈጣሪሽ ከሰባት ሰማይ በላይ ያዘዘሽን ትእዛዝ አክብረሽ ዘውትር አላህ በሚፈልገው መልኩ ሒጃብሽን ጠብቂ!!...የዛን ጊዜ አንቺን ማንም ቀጥ ብሎ አይቶሽ ልጋጉን ተፍቶብሽ የሚሄድ የለምና ....

✿✿✿ እስኪ ስለ ቅዱስ ቁርአን አንዳንድ ነገር ልበላችሁ ...ሊከበሩ ከሚገባ መፅሀፎች ትልቁና ዋናው ቁርዓኑል ከሪም ነው። ምክንያቱም የፈጠረን ጌታ የአላህ ቃል ነውና። ለኛ መመሪያ ነው። መተዳደሪያችን ነው። ማንዋላችን ነው። አዛዣችን ነው። ጀነት መግበያችን ነው።ከጀሀነም ማስጠንቀቂያችን ነው። እና ምንም ብለው መግለፅ አልችልም። ምክንያቱ የቁርዓን ሚስጥሩ ማንም ቢሆን ያወቀው የለም። ሁሌም ሩቅ ነው።
እሺ ለምንድ ነው ዛሬ እኛ ለቁርዓን ክብር ያልሰጠነው???
ቁርዓን እንኳን ሊቀደድ እንኳን ሊቃጠል ሲቀራ እንኳን ዝም በሉ ነው የተባልነው
አላህ በተከበሩ ቃሉ እንዲህ ይላል
ቁርኣንም በተነበበ ጊዜ እርሱን አዳምጡ፡፡ ጸጥም (ዝም) በሉ ይታዘንላችኋልና፡፡(አል-አዕራፍ 204)

ዛሬ ይቀደዳል። ዛሬ ይወረወራል። ዛሬ ይቃጠላል። አይ የኛ ነገር በቃ ችሎታችን ይህ ብቻ ነው?? ወላሂ እኛ ለቁርዓን ክብር ብንሰጥ ኖሮ እኛ ብንኖርለት ብንኖርበት ቦታ ብንሰጠው ዛሬ ይህ አይመጣም ነበር። እንኳን ሰሀቦች ያ~ብፁዕ ትውልድ ይቅርና ሰለፎች እንኳን ለቁርዓን ለነብዩ ﷺ ሀዲስ ቦታ ይሰጡ ነበር።
አቡበክር ረ.ዐ እንዲህ ይሉ ነበር፦
አንድ ሰው ቁርዓን ከቀራና ከሰራበት ምንም ያጣው ነገር የለም። ቁርዓን መቅራት ያልቻለና ያልሰራበት ድሀ ማለት እሱ ነው አሉ። እነሱማ እንኳን ለአላህ ይቅርና ለረሱል ﷺ ሀዲስ ክብር ነበራቸው።

ኢማም ማሊክ ረ,ዐ ታላቁ ታብይ የረሱል ﷺ ሀዲስ ለማስቀራት ሲጀምሩ ውዱዕ አድርገው ሁለት ረከዐ ሰግደው ሙሉ ሱናው ጠብቀው ይጀምሩ ነበር። አንድ ሰው ከጮኸ በረሱል ﷺ ላይ እንደ ጮኸ ይቆጥሩት ነበር። መስጅድ ውስጥ ጊንጥ አስራስድስት ቦታ ሲነክሳቸው እግራቸው በደም ሲላወስ የነብዩ ﷺ ሀዲስ ክብር ብሎ ሳይንቀሳቀሱ ያስቀሩን ነበር ።
አሉ አብድላህ ኢብን ሙባረክ ረዓ
እስቲ ማን ነው ከእኛ መሀል ይህን ያህል ፅናት ለቁርዓን ክብር ብሎ የሰጠ??

ከዚህ በፊት የነበሩ ሰለፎች እንኳን ቁርዓን ይዞ ሊጨፍሩ ቁርዐን ይዞ ሊጮሁ ሊያወሩ ይቅርና ቁርዓን የወረደበት ሀገር መካ ውስጥ መጮህ አይቻልም ይሉ ነበር። ኢማሙ አሽ~ሻፊዒ ረ.ዐ እንዲህ ይሉ ነበር፦
ቁርዓን ያለበት ቤት ውስጥ መተኛት አይቻልም ይላሉ፤ምክንያቱምበመኝታ ሰዓት ራስን መቆጣጠር ስለ ማይቻል የሚጮህ ከሆነ ፣ህልም ላይ መናዘዝ፣ ዉዱዕ የሚያስፈታ ነገር ስለሚፈፅም
ይህ ሁሉ ጥንቃቄ ቁርዓንን ይዞ ሳይሆን ቁርዓን ቤት ውስጥ ካለ ሌላ ቤት ማደር ነው። ይላሉ።
ውዱዕ ካላደረጋችሁ ቁርዓንን እንዳትነኩ ይላሉ።
ማሻዓላህ ቁርዓን አክትመናል፤ ስንት ቁርዓን ቀደድን???
ለቁርዓኑስ ምን ያህል ክብር ሰተነዋል??
በየቤታችን ቁርዐን የቡፌ ማስዋቢያ አርገነዋል። ምንአልባት ረመዳን ሲመጣ አዉርደነዉ በሶፍት ወይም በጨርቅ እንጠርገዉ ይሆናል።
አባታችን የሆነ ውርስ ቢያወርሰንና የአባት ውርስ ቦታ ይሰጠዋል እኮ እና አንዱ መጣና ስብርብር፣ ቅድድ፣ ቢያረገውና ምን ታመጣለህ ብሎ ቢጐርርብን ቆመን እናየው ነበርን?
ወላሂ እስክንሞት ወይም እስክንገድለው ድረስ በፍፁም አንተወውም ነበር።
እና የአላህ ቃል የረሱል ﷺ ውርስ እንዴት ይህ ሁሉ በደል ሲደርስበት ለምንድን ነው ዝም ያልነው???
ወላሂ ዛሬ ክብር የሰጠነው ቢሆን ኖሮ የማንም ክብር የሌለዉ ፍጥረት
ቁርዓንን እንዲህ ባልጨፈረበት፤ ነበር።አጃዒብ ሚሆነው ደሞ ቁርዓን ሲረገጥ እንደ ሶፍት ሲጠቀሙበት ምንም የማይመስለን ሰው ምን ሆነን ነው???
ፈጣሪ ሆይ በቁርአን ይምንሰራ በቁርአን የምንተዳደር በቁርአን መመሪያ ኑረን የምንሞት አድርገን ያረብ
  

                   አልሀምዱሊላህ ከትምህርት ቤት መጥፎ ጓደኞቼ አንድ ባንድ እራኩኝ የተወሰኑት እየደወሉ ያወሩኛል...
ናርዶስ ጋር ግን ቀን በቀን ሁሌ እንደዋወላለን ፡፡

ለዉጥ ከሆነ ሙሉ በሙሉ መቀየር አለብኝ ብየ ወሰንኩኝ...የበፊት ትምህርት ቤት ጓደኞቼ እንዳያገኙኝ ብዙ ሰዉ ወንድም ሴትም የሚያቀዉን ስልክ ቁጥሬን ለመቀየር ወሰንኩኝ👇👇👇
.....አባቴን አዲስ ሲም ካርድ አዉጣልኝ ብየዉ አወጣልኝ... ይሄን ሲም ካርድ የሚያቁት እናት እና አባቴ በተጨማሪም ለናርዶስ ደዉየ ለማንም ይሄ የኔ ቁጥር መሆኑን እንዳትነግሪ ብየ አሳወኳት.... ከማይጠቅም ከማይጎዳ በስልክ ወሬ ከመዘናጋት በዚህ ተገላገልኩ፡፡ አሁን የቀረኝ Facebbok.ላይ የሚያወሩኝ የምጀናጀንበት ወደ ሇላ እንዳይመልሰኝ መላ መዘየድ አለብኝ .... ያለኝ አማራጭ አንድ እና አንድ ብቻ ነዉ..ይሄዉም ፌስቡኬንም delete አድርጌ በአዲሱ ቁጥሬ ለመጀናጀን ሳይሆን በሳምንት አንዴ መረጃ ለማየት ያህል ከፈትኩኝ......

አካበዳችሁ እንዳትሉኝ እዉነቴን ነዉ...ምንም ቢሆን ምንም ከቤት በጭራሽ አልወጣም .... በፊት ቤት ስሆን ጓደኞችሽ ጋር ሂጂ ሂጂ ነበር የሚለኝ..ደግሞ አሁን የዛ ተዘዋዋሪ ከቤት መዉጣት በጣም ነበር የሚያስጠላኝ ..,ከቤት የምወጣዉ ለጁምአ ሶላት ብቻ ሲሆን ነዉ..ጁምአም የምሰግደዉ ኑር(አጂፕ)መስጊዱ ከኛ ቤት በጣም ቅርብ ነዉ፡፡  መስጊድ አምስት ሰአት አካባቢ እገባለሁ አወለ ሶፍ ከጥግ በኩል እሆናለሁ ኹጥባዉ እስከሚጀምር ቁርአኔን እቀራለሁ ፡፡ መስጊድ ማን ይምጣ ማን ይቅር የማቀዉ ነገር የለም ...
ከቤት ከወጣሁም በ15ቀን አንዴ ለገበያ እናቴ ጋር ነዉ የምወጣዉ ፡፡ አባቴ እንደዚህ መሆኔን ሲያየኝ ከቤት እንድወጣ እንድዝናና በማሰብ የተለያየ ቦታ መልዕክት ይልከኛል
.......እኔ ግን በጭራሽ መላክም ከቤትም መዉጣት ፍላጎቱ የለኝም
አባቴ ግድ ነዉ መዉጣት አለብሽ ብሎ ይቆጣኛል...ብር ይሰጠኝ እና በዛዉም ካፌ ገብተሽ ተዝናንተሽ ነይ ይለኛል
.......በብዙ ቀናት ልዩነት ቢያንስ በ20ቀን ልዩነት ስወጣ የሰፈር ሰዎች ..በፊት የማቃቸዉ የትምህርት ቤት ጓደኞቼ ብዙ ሰዉ እኔን እያየ እየተገረመ ...አረ ነዋል አለሽ ወይ?? የት ጠፍተሽ ነዉ ?? ወላሂ በጣም አምሮብሻል የተወለወለ ጠመንጃ መስለሻል..በተጨማሪ ትልቅ ሰዉ ሁነሻል ሳይለኝ የማያልፈኝ ሰዉ የለም.... እኔም በሰዉ እኔን አጥብቀዉ ሲጠይቁ ግራ እየገባኝ ...አንዳንዴ መጥፋት ከሰዉ አይን መራቅ እንደዚህ ያስናፍቃል ማለት ነዉ??ብየ እራሴን እጠይቀዋለሁ .. 
  
   ፀሀዩ ንፋሱ ብርዱ ቅዝቃዜዉ ሙቀቱ ስለማያገኘኝ ስላልተፈራረቀብኝ ነዉ መሰለኝ ዉበት ይጨመርኩበት ..ፊዚካሌ ከልጅነት ወደ ትልቅነት የተቀየርኩበት አመት ነዉ፡፡  ብዙ ሰዉ ነዋል አምሮብሻል ትልቅ ሰዉ ሁነሻል ..አንዳንድ ትላልቅ የሰፈራችን ሰዎች እንደ ቀልድም ለልጄ ነዉ የምድርሽ ትልቅ ሰዉ ሁነሻል ሲሉኝ... እቤት ስመለስ ወደ ክላሴ ሂጄ ..ሰዎቹ እንዳሉኝ አምሮብኛል እንዴ ?? ትልቅ ሰዉ ሁኛለሁ እንዴ??ብየ እቤታችን መኝታ ክፍሌ ያለዉ ትልቅ መስተዋቱን እኔዉ ስመለከተዉ እሱም የቀኜን በግራ የግራየን በቀኝ አርጎ እየተመለከተኝ ፊት ለፊት እንደተፋጠጥን እጠይቀዋለሁ....
እኔ አላማየ የዉበት መጨመር ሳይሆን ፕራይ ቤት ለማለፍ ስለሆነ አባቴን ለራሱ የማወራበት ጊዜ አጣሁኝ ..,ማታ አባቴ ሲመጣ እንዴት ዋልክ ብየ 30ደቂቃ አዉርቼ መልሼ መኝታ ክፍሌ ገብቼ ኢሻን ሰግጄ እተኛለሁ ከዛም  ለሊቱ 8፡00 ሰአት ለማጥናት  እነሳለሁ ከዛም ሱብሒን ሰግጄ እተኛለሁ  ትንሽ ተንቼ  የቤት ሰራተኛችን ጋር አብረን ቤት አፅድተን ሰትረን ከጨረስን ቡሀላ ቤተሰቦቼን ቁርስ አብልቼ  መልሼ ወደ ጥናት እስከ ዙሁር አጠናለሁ ፡፡ ዙሁርን ሰግጄ ምሳ በልቼ እስከ አሱር ማጥናት ፈተናዉ እስኪ ድረስ ፕሮግራሜ እንደዚህ ነበር..

ደጅ ፀሀይ እንደበፊቱ ሳያጠወልገኝ ማን ሞተ??፡ ማን አገባ ??፡ማን ታመመ?? ብየ ሳልጠይቅ ከማንም ጋር ሳልገናኝ አላማየ ለፈተና መዘጋጀት ብቻ ሆነ፡፡

    ይሄ አመት በሒወቴ ትልቅ ለዉጥ ያመጣሁበት እራሴን ማንነቴን የፈተሽኩበት ጊዜ ነዉ ፡፡ የመጀመሪያ ለዉጤ እኔ ከአሁን ቡሀላ ልጅ አይደለሁም ትልቅ ሰዉ ሁኛለሁ .. እንደትልቅ ሰዉ እንዳስብ አደረገኝ.. በተጨማሪም ብቸኛ ሁኖ መኖር የለመድኩት በዚሁ አመት ነዉ፡፡ ብቸኝነት እቤት መዋል ለምጄ ሰዉ ጋር መቀራረብ እስከሚያስጠላኝ ድረስ ነበር ከሰዉ የተለያየሁት ...እቤት ለራሱ እናቴ አትዉልም ነጋዴ ናት ጠዋት ወጥታ ማታ ነዉ የምትገባዉ፡፡ ወንድም እና እህቶቼም ጠዋት ትምህርት ቤት የሄዱ የሚመጡት ወደ 11:00 አካባቢ ነዉ፡፡አባቴም ያዉ ኮንትራክተር ስለሆነ የሚመጣዉ ማታ ላይ ነዉ፡፡ ያለነዉ እኔ እና ሰራተኛችን ነን ...የቤት ሰራተኛችንም ስራዉን ሰርታ ስትጨርስ የራሷ ክፍል አላት እዛ ነዉ የምትዉለዉ...ቤቱ እና እኔ ብቻ ነዉ የምንዉለዉ ..ቤቱ ፀጥ ሲል ብቻየን ስሆን በጣጣጣም ደስ ይለኛል፡፡ ጎረቤቶቼ እንዴት ነዉ እንደዚህ የምትኖሪዉ ??ይሉኛል...እኔ ግን ሰዉ ሲኖር ነዉ የምጠላዉ ብቻኛ መሆን ነዉ የምፈልገዉ

  ደግሞ ይሄ አመት ስለእስልምና በደንብ እንዳዉቅ አደረገኝ ....የተለያዩ ኢስላማዊ መፅሀፍ በመግዛት እያነበብኩኝ እራሴን ቀየርኩኝ፡፡ አላህን እንድወድ ተማሪ ሁኜ እነዛ መጥፎ ጓደኞች ጋር ያሳለፍኩት መጥፎ ትዝታ ሳስታዉስ እያለቀስኩ ተዉበት እያደርኩ አላህ ይቅር በለኝ እያልኩ ነዉ የምዉለዉ አልሀምዱሊላህ፡፡ እናም ለወደፊት ሒወቴ መጥፎ ጓደኛ ላልይዝ የበፊቱ ጥፋት መሆኑን አመንኩኝ፡፡
    
በተጨማሪም ለወደፊት ያሰብኩት አሁን ላለሁበት እያንዳንዱ ሒወቴ አላማ እንዲኖረኝ የወደፊት እቅድ አዉጥቼ ማሰብ ጀመርኩ ፡፡ አሁን የመጀመሪያዉ ፕራይ ቤት መፈተን አይደል አላህ ብሎ ከተሳካ ማሻ አላህ ግን ደግሞ ካልተሳካም ተስፋ ላልቅርጥ ሌላ ትምህርት በግል ለመማር ወሰንኩኝ፡፡

   ይህ አመት ለዉጥ እንዳመጣሁ ሁሉ በተዘዋዋሪም ከእስከዛሬዉ ተማሪ ልጅ በነበርኩበት ጊዜ  ያሳለፍኩት መከራ ታዉቁ የለ ከዛ በላይ ፈተና መጣብኝ፡፡ ቤት መዋል አንዳንዴ ከሰዉ የሌለንን ስም እንዲሰጠን ያደርጋል...ይህም የወንድ ልጅ የትዳር መስፈርቱ ከአፉ የማትጠፋ ሁለት ቃላት የቤት ልጅና ድንግል ናት ወይ?የምትለዉ አፋቸዉ ላይ እንደ ማስቲሽ ተጣብቆ የድርጅት ማህተም የተመታበት ነዉ የምመስለዉ...እኔም ለፕራይቤት ፈተና አጥንቶ ለመፈተን እያጠናሁ እቤቴ ብዉል .. #ነዋል_የቤት_ልጅ_ናት ተብሎ የኔ ስም አንዴ በኛ ሰፈር ለትዳር እደረሱት የዘመኑ ጎረምሳ ተብየ የሰፈር ልጆች ጋር በአንዴ ተናፈሰ ፡፡

ይሄ እቤት መዋል የቤት ልጅ መባል ...ያልጠበኩት ያላሰብኩት ሌላ መዘዝ ችግር የአእምሮ ጭንቀት ዲፕሬሽን ይዞቦኝ መጣ........የኔዉ ዉበት ቁመት ሙቀት እድገት በአንዴ በማዳበሪያ አንደተዘራ በቆሎ እሸቱ ደረሰ፡፡ በጣም ትልቅ ሰዉ ሆንኩኝ ከቤት ቢያንስ በ15ቀን አንዴ ለሆነ ሀጃ እናቴ ጋር ስወጣ ..በኔ ዉበት እራሱን የማያክ ..በሁለቱም አይኑ እስከሚነቀል ቡዝዝ ብሎ የማያየኝ ..እኔን ለማግባት የማይቋምጥ መቁጠሩ ይቀላል... የሰፈር ለትዳር የደረሱ ወጣቶች አይን ዉስጥ ተሰነቀርኩኝ..


#ክፍል 1⃣1⃣

ይ........ቀ..........
......ጥ........ላ...........ል

ቤተሰብ ሼር አይዘንጉ
´´´´´´´ :¨·.·¨: ❀ share
           `·. www.tg-me.com/Islam_and_Science
www.tg-me.com/Islam_and_Science
•════•••🍃🌺🍃•••════•
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🔺አሳዛኝ እዉነተኛ ታሪክ🔺
 
የታሪኩ ርዕስ
😔😢 #የሆድ_ዉስጥ_ፉም_እሳት🔥🔥
      #ክፍል ☞ አስራ አንድ 1⃣1⃣

ፀሀፊ ☞ #አሚር_ሰይድ




እኔን ለማግባት የማይቋምጥ መቁጠሩ ይቀላል... የሰፈር ለትዳር የደረሱ ወጣቶች አይን ዉስጥ ተሰነቀርኩኝ..
እናቴ ጋርም አንዳንዴ ስሄድ የአንቺ ልጅ ናት ??ብለዉ ይጠይቋታል...እናቴም አዎ ትላቸዋለች ..ማሻ አላህ ብለዉ የሚያስቡትን አስበዉ ይሄዳሉ ፡፡
      እኔም ይሄን አመት ትልቅ ሰዉ መሆኔን...በፊት ልጅ እንደነብርን ባልሽ ሚስትሽ ስንባል እንደማናለቅስ ግን ሲያድጉ ትዳር የማይቀር መሆኑ ለወደፊት ትዳር እንደሚጠብቀኝ ተረዳሁኝ... እናቴ ወደ ዉጭም ይዛኝ የምታወጣዉ ሳልወድ በግዴ ነይ ገበያ እንሂድ የምትለኝ ለዚህም እንደሆነ ተጠራጠርኩኝ፡፡

እኔን ያየ ለማግባት የማይቋምጥ የለም ነበር፡፡
ወላሂ እኔን የጠየቀኝ ባል ቆጥሬ አልጨርሰዉም ለኔ የነገሩኝ አባቴ እና እናቴ ያልነገሩኝም ብዙ አሉ፡፡
የትዳር ጥያቄ በጣም በዛ እንደጎርፍ ሆነ፡፡
እናቴም:- ነዋል ምንድን ነዉ አንቺን የሚፈልግሽ በዛ እኮ ለማን እንድርሽ ይሆን ?? ግራ ገባን እኮ ትለኛለች..

እናቴን የሚያቋት እናቴን ይጠይቃሉ... አባቴን የሚያቁት ደግሞ አባቴን ይጠይቁታል፡፡ አባቴ ግን እኔን ሳያማክር በተረጋጋ በሰከነ መልኩ ይመልሳቸዉ ነበር....
......የአባቴ መልስ እጥር ምጥን ያለ ነበር .. ነዋል ታገቢያለሽ ወይ ብየ ጠይቂያት ነበር ግን እሷ አሁን ማግባት አልፈልግም ፕራይቤት ተፈትኜ ትምህርቴን መማር ነዉ የምፈልገዉ ብላለች እያለ ይመልስልኛል፡፡ በተዘዋዋሪ ደግሞ እናቴ እንደ አገባ ትፈልጋለች ሲጠይቋት ኢንሻ አላህ እያለች ተስፋ ትሰጣቸዋለች ፡፡

   ግን ከባድ ጥያቄ እና መልስ የሌለዉ የሒወቴ ጥያቄ እዚህ ላይ ነዉ...እነዚህ ለትዳር የሚመጡት ሰዎች በፍቅር ሳይሆን የመጡት በዉበት እና እቤት ስለምዉል ከማንኛዉም ሰዉ ጋር ስለማልገናኝ የቤት ልጅ ናት ተብለዉ ነዉ፡፡ እነሱ ለኔ ያላቸዉ አመለካከት ከቤት ስለማልወጣ ከሁሉም ሴቶች የተለየ ነዉ.....ግን አንድ ጥያቄ አለ.... #ድንግል_ነሽ_ወይስ_አይደለሽም ??? ብለዉ ቢጠይቁኝ ምንድን ነዉ መልሴ ?? ወይስ ገና በልጅነቴ መደፈሬን ያቃሉ ወይስ አያቁም ??? እያልኩኝ ብቻየን ሀሳብ ሁኖብኛል፡፡ በልጅነቴ በጊዜዉ ብናደድም የምናደደዉ እንዴት በቶፊቅ የተደፈርሽዉ ?? ይሉኛል ነበር..ግን አሁን በመናደድ ብቻ የሚተዉ አይደለም ለሚጠይቁኝ ጥያቄ መልስ ያስፈልገኛል፡፡

    እንደዚህ ያሉ ትዳሮች በጣም ከባድ ትዳሮች ናቸዉ ፡፡ በፍቅር በመቀራረብ ቢሆን የሚወደኝ ከሆነ ግልፁን እነግረዋለሁ ከወደደኝ እና ካመነኝ አንድ ጎጆ ቀልሰን መኖር እንችላለን .. ካመነበት ያምናል ካላመነበት ይቀራል እላለሁ ፡፡ ግን ይሄ የሚመጡት ትዳር የደህና ቤተሰብ ልጅ ናት፡ ጨዋ ናት፡ እቤት ነዉ የምትዉለዉ በሚል ምክንያት ነዉ የሚመጡት ፡፡

ግን ደስ የሚለዉ አባቴ ምን ወሰንሽ ብሎ አይጠይቀኝም እራሱ ነበር፡በተለያየ ምክንያት የሚከለክላቸዉ አንዴ በትምህርተ ሌላዉን በተለያየ ዘዴ ተስፋ ያስቆርጣቸዋል፡፡

ከሁሉ ደግሞ ያስቸገረችኝ እናቴ ነች...የእኔ እና እናቴ አስተሳሰብ እህል ከዉሀዉ አልገጥም አለን .እሷን የጠየቋትን ሰዎች ብዙዎቹን ነገረችኝ እና ምረጭና አንዱን አግቢ እያለች ትነዛነዘኝ ትቸካቸከኛለች .. እናቴ በመሸ በነጋ ቁጥር አግቢ እያለች ጫና ስታበዛብኝ ...የማይሆን አስተሳሰብ ማሰብ ጀመርኩኝ
......እኔ ከትምህርት ስለወደኩኝ እቤት ስለምዉል ይሄን ያህል ሸክም ሆንኩ ማለት ነዉ ?? ገና ትዳር መጥቶ አግቢ አግቢ እያለች መቆሚያ መቀመጫ የምታሳጣኝ??? እያልኩ ሌላ ሀሳቦች አእምሮየ ላይ ተንባረቀብኝ ፡፡
......,,እናቴንም በኔ ሒወት አትግቢ እያልኩኝ ቀን በቀን መጣላት የዘወትር ተግባራችን ሆነ ...በእናቴ አንዱን አግቢ ምረጭ እያለች በምታጨናንቀኝ ጊዜ የማነባቸዉን መፅሀፎች ላይ አይኔ ቢተከልም ግን ከማገላበጥ ዉጭ ወደ አእምሮየ ዉስጥ ሊገባ አልቻለም..የእኔና እናቴ እሰጣ ገባ ቀን በቀን እየባሰ እየጨመረ መጣ.....

.እናቴ ግን እንዴት ይሆን የኔን ዉስጤን መረዳት የምትችለዉ??? ቀርባ እንደ እናት ምክንያቴን እና የሆዴን የዉስጤን የሀሳብ ማዕበል   ለመረዳት ፍቃደኛ አይደለችም ግን ለምን እናትነት ትርጉሙ ምንድን ነዉ???

እናቴንም በኔ ሒወት አትግቢ እያልኩኝ ቀን በቀን እንጥላለን....ግን ይሄንን መጣላታችንን አባቴ አያቅም.........አባቴ እቤት ባለ ሰአት አትናገረኝም ዝም ነዉ የምትለኝ ..አባቴ ከቤት ሲወጣ እግሩን ጠብቃ ጠዋት ማታ አንዱን ምረጪ እና አግቢ አግቢ እያለች በልጅነት አእምሮየ ሌላ ሀሳብ ሆነችብኝ...
 
  እኔ ደግሞ ለአባቴ እናቴ አግቢ እያለች እረብሻኛለች ብየ ብነግረዉ ..አባቴ በእሷ ሒወት ምን አገባሸ ??እንደሚላት አቃለሁኝ....እናት እና አባቴ በጣም ከባድ ፀብ እስከ ትዳር መፋታት እንደሚደርሱ ይታየኛል፡፡ ምንም አማራጭ የለኝም እናቴ ቀን በቀን ብትቸከችከኝም ለአባቴ ግን መቼም አልናገርም በኔ የተነሳ እንዲጣሉ አልፈልግም ...


ቀናቶች በተቀያየሩ ቁጥር ከዛሬ ነገ ይሻላል ብየ ተስፋ ባደርግም ባዶ ተስፋ ሆነብኝ ..የእናቴ ፀባይ ቀን በቀን እየባሰ ሄደ ....በጭራሽ አመሏን መሸከም አቃተኝ ሳንጣላ የዋልንበት ቀን መቁጠር ይቀላል
  እናቴ የትዳር ጥያቄ በሷ በኩል ሲመጣ ..ነዋል ለምን ትዳር ትመልሻለሽ?? ለምን አታገቢም??? ትለኛለች
..... እኔም አሁን ማግበባት አልፈልግም መማር ነዉ የምፈልገዉ እላታለሁ
...እናቴ ለኔ የምመልስልኝ መልስ አእምሮየን ያደማዋል አስተዉላ አገናዝባ መናገር አትችልም ሰዉ ይከፈዋል ብላ ቃላቶች መምረጥ አችልም ንግግሬ ሰዉ ይጎዳል አይጎዳም ብላ መጥና መናገር አይሆንላትም እንደ አዛባ ዱላ የምትወረዉረዉ መጥፎ የቃላት ማዕበል እኔን አእምሮየ ሊመጥነዉ ሊቀበለዉ አልቻለም...  ብዙ ቀን እንደዚህ ትለኛለች....የማታገቢዉ ለመንዘላዘል ፈልገሽ ነዉ ?? """""""""ለነገሩ አንቺም እሺ ብትይም እነሱ በተለያየ ምክንያት ላይፈልጉሽ ይችላሉ """"""""" እያለች ብዙ ቀን ትደጋግመዋለች ...ወይስ ምንድን ነዉ ትምህርቴ ትምህርቴ የምትይዉ ተምረሽ ምን ልታመጪ ነዉ ??? እያለች ሁሌ አእምሮየን ታደመዋለች፡፡ እኔ በልጅነት መደፈሬ ደግሞ ቀን በቀን ሁሌም ሳልጨነቅ አድሬ አላቅም አንዴ አእምሮየ ላይ ተቀርፇል፡፡ የእናቴ መጥፎ ንግግሮች ከዚሁ ጋር የተያያዘም ነዉ

በዚህ የትዳር ጥያቄ የተነሳ በልጅነቴ ድንግልናየን ማጣቴ  ታንቄ ወይ ኤሌክትሪክ ይዤ ብሞት እመኛለሁ ፡፡
    ግን የአባቴ ታናሽ ወንድም አለ . .አጎቴን እንደ ወንድሜም የማየዉ ብዙ ነገር አማክረዉዋለሁ፡፡ ብዙ ነገሮችን ይመክረኛል ከጎኔ እሱ ነዉ ያለኝ...በሒወቴ ለኔ ተፅእኖ ፈጣሪ ነዉ ብየ ደፍሬ የማወራዉ ከአባቴ ቀጥሎ አጎቴ ነበር፡፡

   እኛ ቤት ተቆጪ ተቆጣጣሪ ሀይለኛ አዛዥ ከልካይ ፈላጭ ቆራጭ እናቴ ስትሆን ደግሞ በተዘዋዋሪ ለልጆቹ አዛኝ ልጆቹን የሚያጫዉት የሚያዝናና ሩህሩህ አባታችን ነዉ ፡፡ እኛ ቤት የእናት አመለካከት እንደ አባቴ ሲሆን ..የእናት አመለካከት ደግሞ አባቴ ላይ ይስታወላል፡፡👇👇👇
👍1
  
   ከተወሰኑ የቀናት ቆይታ ቡሀላ  በእናቴ አማካኝነት ይሄዉ መከረኛ የትዳር ጥያቄ መጣ ...እናቴም ስታማክረኝ  .እናቴ መደጋገም አያስፈልግም አንዴ ተናግሪያለሁ እኮ መጀመሪያ ትምህርቴን መማር ነዉ  የምፈልገዉ  ብየ ብዙ ቀን ደጋግሜ ነግሬሻለሁ ስለትዳር አታንሽብኝ ብየሽ የለ እንዴ?? ስላት
.........ያለ የለለ አእምሮየን የሚነካ ንግግር እና መንገር የማልፈልገዉ የልጅነት ትዉስታዎች የሚቀሰቅስ ..በልጅነቴ መደፈሬን የሚያስታዉስ  ልብን የሚያደማ ከእናቴ የማልጠብቀዉ መርዝ ቃላቶች ተናገረችኝ፡፡የልጅነቴ ትዉስታዎችን ቀሰቀችብኝ ..ጥሩ መናገር ላያስከፍል ለምን ሰዉ መጥፎ ይናገራል??? ከሰዉም ሰዉ ይመረጣል ግን ከእናቴ ሲሆን ደግሞ ልብን ያደማል.መልካም ንግግር ሰደቃ ነዉ ተብሎ በሀዲስ ተነግሮን ምነዉ ለኛ መልካም ንግግር ከአፋችን እንዳይወጣ ምን አገደን??

...... እናቴ በተናገረችኝ ከአእምሮ መሰረዝ የማይችል የመርዝ ቃላት በጣም ከፋኝ እምባየ ቁልቁል ይወርድ ይዟል........ጭራሽ ንግግሯን መቋቋም አልቻልኩም የተናገረችኝ ንግግር መልሶ መላልሶ አእምሮየ ላይ ይደጋገም ይዟል... በቃ እኔ እዚህ ቤት መኖሬ ከበደሽ አይደል አይኔን ማየት አይደል የጠላሽዉ አልኩኝ እና ከተቀመኩበት ተነስቼ ..የቤት ሰራተኛችን የአይጥ መርዙን የምታሰቀምጥበት ቦታዉን ስለማዉቀዉ ....የአይጥ መርዙን አንስቼ መኝታ ክፍሌ ይዤ ገብቼ በሩን ከዉስጥ ቆለፍኩኝ .....


የቤት ሰራተኛችን እናቴ ጋር ስንጣላ አይታናለች ..ነዋል የሆነ ነገር እንዳትሆን እያለች እኔ ሳላያት እየተከታተለችኝ ነበር.... የአይጡንም መርዝ ይዤ ስገባ አይታኝ እየሮጠች መጥታ ለእናቴ ነዋል የአይጡን መርዝ ይዛ መኝታ ክፍሏ አሁን ገባች ብላ ነገረቻት...

እኔም ይችን የተረገመች አለም ለመገላገል አንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ወስኛለሁ መርዙን ልጠጣዉ ተዘጋጅቻለሁ....

እናቴ እና የቤት ሰራተኛችን ቤቱን ክፈች እያሉ እናቴም እያለቀሰች  ይለምኑኝ ይዘዋል...እኔ ግን የእናቴ ለቅሶን ወደ ጎን በመተዉ መርዙን ልጠጣ በፊት የሰራሁትን ወንጀል አላህ እንዲምረኝ እራሴን በማጥፋቴ አላህ እንዳይጠይቀኝ እማፀን ተዉበት አደርግ ይዣለሁ....

እናቴ ብትለምነኝ እምቢ ስላት የአጎቴ ቤት እኛ የምንኖርበት ሰፈር ነዉ ..... እናቴ ደወለችለት

አጎቴ ጊዜ ሳያባክን ወዳዉ መጥቶ እንድከፍት በሚያሳዝኑ ቃላቶች ለመነኝ...ነዋልየ ትወጅኝ እንደሆነ ሚስጥሬን አካፍየሽ አንቺም አካፍለሽኝ እኔ ለምኘሽ እንዳጨክኚ እያለ እያለቀሰ ለመነኝ....
  .....አጎቴ ሳያለቅስ ሆዴ ባባ እኔም እራሴን ማጥፋቱን መርዝ መጠጣቱን ትቼ በሩን ከፈትኩት....
አጎቴ ከከፈትኩት ቡሀላ አልሀምዱሊላህ ብሎ በደስታ እምባዎቹን ጠራርጎ ነዋልን ብቻዋን ማዉራት እፈልጋለሁ ብሎ እናቴ እና ሰራተኛችን እንዲሄዱ ነገራቸዉ
....ሁለቱም ሲሄዱልን እኔና አጎቴ ብቻ ቀረን
...,አጎቴም በጣም ተቆጣኝ እንዴት ይሄን ዉሳኔ ትወስኛለሽ ??? እራስሽን ልታጠፊ ያሰብሽበት ምክንያት ተይዉ አትንገሪኝ መስማት አልፈልግም እሰቢ እንጂ እንስፍስፍ ብሎ የሚወድሽ አባትሽ አንቺን አጥቶ ሰዉ ይሆናል ወይ ?? እያለ ብዙ ነገሮች አወራኝ

.........እኔም አባቴ ትዝ ሲለኝ ጥፋተኛ መሆኔ ተሰምቶኝ አለቀስኩኝ ምን ላርግ አጎቴ ምን ላርግ ተቸግሬ እኮ ነዉ እንጂ እራሴን ማጥፋት ፈልጌዉ ወድጀዉ አይደለም እያልኩ እምባየን አፈስ ይዣለሁ ..



#ክፍል 1⃣2⃣
ይ...........ቀ.....
.......ጥ........ላ..........ል


JOIN
´´´  www.tg-me.com/Islam_and_Science
www.tg-me.com/Islam_and_Science
•════•••🍃🌺🍃•••════
1👍1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
2025/07/11 21:32:53
Back to Top
HTML Embed Code: