#የቤተልሔሙ_ብሥራት
@Mgetem
ሔሮድስ አሳውጆ የሕዝብ ቆጠራ
ወደ ቤተልሔም ሁሉም ሰው ሲያመራ፣
ዮሴፍና ማርያም ለመሄድ አስበው
የድንግል መጽነስ ዮሴፍ ቢያስጨንቀው
ነገረው መልአኩ ተገልፆ በራዕይ
የድንግል መጸነስ መሆኑን ከሰማይ፡፡
ዮሴፍም ተደንቆ በመልአኩ ነገር
ወሰነ ለመሄድ ከድንግሊቱ ጋር፡፡
ቤተልሔም ደርሰው ከሕዝቡ በኋላ
ማደርያውም ቢያዝ በሰዉ ቢሞላ
እነሱም ተገኙ ከከብቶቹ በረት
ማረፍያ ስላጡ ለእነሱ የሚሆን ቤት፡፡
በበረት ውስጥ ሳሉ ከእንስሳቱ መሃል
የዓለም መድሐኒት ተገኘ ከድንግል፡፡
የነገስታት ንጉስ የኃያላን ኃያል
ሆኖ ሳለ እርሱ በሰማይ በምድር
እርሱ ለመወለድ መረጠ ግርግምን
እንደ ደካማ ሰው በጨርቅ መጠቅለልን፡፡
ላሞችና አህዮች ተደንቀው በጌታ
አሞቁት በትንፋሽ ሁሉም በየተርታ፡፡
ሁሌ የሚያወድሱት በሰማይ መንበሩ
ያን ጊዜም መላእክት በምድር ዘመሩ፡፡
በረቱም ተሞላ በደማቅ ብርሃን
በውስጡ ስላለ የዓለም መድኅን፡፡
እረኞችም ሰምተው የመልአኩን ብስራት
ሄዱ ገሰገሱ አምላክ ወዳለበት
ውስጣቸው ተሞልቶ በደስታ በሀሴት፡፡
ተለያይተው የኖሩ ሰውና መላእክት
አሁን ተገናኙ በጌታችን ልደት
አብሮ ለመዘመር በፍቅር በአንድነት፡፡
የሩቅ ምስራቅ ሰዎች ሠለሥቱ ነገስታት
በኮከብ ተመርተው ጌታ ወዳለበት
በእምነት አቀኑ ወደ ቤተልሔም ወደ አምላካቸው
ወርቅ እጣን ከርቤውን እጅ መንሻ ይዘው፡፡
የጌታችን ልደት ከዳር ዳር ተሰምቶ
ፍጥረቱ በሙሉ በሃሴት ተሞልቶ
ሁሉም አቀረበ ለአምላክ ምስጋና
የእርሱ ድንቅ ስራ ሁሉን ማርኳልና፡፡
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_group
@Solasc12
@Mgetem
ሔሮድስ አሳውጆ የሕዝብ ቆጠራ
ወደ ቤተልሔም ሁሉም ሰው ሲያመራ፣
ዮሴፍና ማርያም ለመሄድ አስበው
የድንግል መጽነስ ዮሴፍ ቢያስጨንቀው
ነገረው መልአኩ ተገልፆ በራዕይ
የድንግል መጸነስ መሆኑን ከሰማይ፡፡
ዮሴፍም ተደንቆ በመልአኩ ነገር
ወሰነ ለመሄድ ከድንግሊቱ ጋር፡፡
ቤተልሔም ደርሰው ከሕዝቡ በኋላ
ማደርያውም ቢያዝ በሰዉ ቢሞላ
እነሱም ተገኙ ከከብቶቹ በረት
ማረፍያ ስላጡ ለእነሱ የሚሆን ቤት፡፡
በበረት ውስጥ ሳሉ ከእንስሳቱ መሃል
የዓለም መድሐኒት ተገኘ ከድንግል፡፡
የነገስታት ንጉስ የኃያላን ኃያል
ሆኖ ሳለ እርሱ በሰማይ በምድር
እርሱ ለመወለድ መረጠ ግርግምን
እንደ ደካማ ሰው በጨርቅ መጠቅለልን፡፡
ላሞችና አህዮች ተደንቀው በጌታ
አሞቁት በትንፋሽ ሁሉም በየተርታ፡፡
ሁሌ የሚያወድሱት በሰማይ መንበሩ
ያን ጊዜም መላእክት በምድር ዘመሩ፡፡
በረቱም ተሞላ በደማቅ ብርሃን
በውስጡ ስላለ የዓለም መድኅን፡፡
እረኞችም ሰምተው የመልአኩን ብስራት
ሄዱ ገሰገሱ አምላክ ወዳለበት
ውስጣቸው ተሞልቶ በደስታ በሀሴት፡፡
ተለያይተው የኖሩ ሰውና መላእክት
አሁን ተገናኙ በጌታችን ልደት
አብሮ ለመዘመር በፍቅር በአንድነት፡፡
የሩቅ ምስራቅ ሰዎች ሠለሥቱ ነገስታት
በኮከብ ተመርተው ጌታ ወዳለበት
በእምነት አቀኑ ወደ ቤተልሔም ወደ አምላካቸው
ወርቅ እጣን ከርቤውን እጅ መንሻ ይዘው፡፡
የጌታችን ልደት ከዳር ዳር ተሰምቶ
ፍጥረቱ በሙሉ በሃሴት ተሞልቶ
ሁሉም አቀረበ ለአምላክ ምስጋና
የእርሱ ድንቅ ስራ ሁሉን ማርኳልና፡፡
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_group
@Solasc12
# ስንት_ቀን_ፈጀብህ?
/መንፈሳዊ መነባንብ /
@Mgetem
ለአዳም ኪዳን ሰጠህ
እንደምትወለድ ወደ ምድር ወርደህ
እንዴት ነበር ያኔ..?
ወደ እኛ ስትመጣ መላእክትን ትተህ?
………
የሔዋን እርግማን
የባሏም የውርስ ኃጢአት መዘገን
እንዲያ አሳሰበህና
መጣህልን ሁሉን አደረግህ በፅሙና
.........
እንዴት ነበር ያኔ..?
ያችን ንጹሕ ለመፈለግ የወሰደብህ ጊዜ
አድርገህ የሰጠኸንን ፈውስ በበድልን ጊዜ
ግን ምን ያህል ነው ልፋትህ?
ድንግልን ስትፈልግ የፈጀብህ?
.........
ከሰማያት ስትወርድ አጀቡህ መላእክት?
ዓለሙስ ተናወፀ በይባቤ በስብሐት?
ያ ምቀኛ ዲያቢሎስ ግን ምን አለ?
ወደ እኛ ስትመጣ አለ አይደል ኮበለለ?
ነው ሥጋ ለብሶ ጉድ ሠራኝ አለ?
........
እንዴት ነው እርቀቱ
የሰማይ ምጥቀቱ
የምድርስ ሥፋት
ከሷ እስክታርፍባት?
ግን ጌታ...?ሰማያት ምን አሉ
ትትሀቸው መጠህ ባንተ አጉረመረሙ?
ፍጥረታትስ ቢሆን ማሕሌት አቆሙ?
.......
ምሥጢረኛው ጌታ
መንገድህ በየት ነው ወደ እኛ ስትመጣ?
ቤተ ልሔም ስትደርስ
ማን አገለገልህ?ምን አለች ምድሪቱስ
እያቄም ወሐናን እንዴት መረጥሃቸው
አንተ እንድትወለድ ምክንያትህ ናቸው
.......
ሰማዩ ሰፊ ነው
ምድርንም ታውቃለህ
እንዴት እንድትሰፋ ሆና መረገጫህ
ግን እና ጌታ ሆይ ምኑ ነው የቻለህ?
የድንግል ማሕጸን እሳት መሸከሙ
ምድርም መልኮት በእሷ ላይ መቆሙ
..........
እንዴት ነበር ያኔ
በቤተ ልሔም ውስጥ
አንተን የሚያሞቅ ከእንስሶች ስትሰጥ?
........
ዮሴፍ ምን አለ
አንተን በማየቱ እርጅናው ታጎለ?
አንተን የጠበቀህ አዳምስ በግርማህ ምን አለ?
........
እንዴት ነው ስጦታው
የሰብአ ሰገሉ ወርቅ እጣን አምኃው
የእረኞቹ ደስታ
የመላእክት ብሥራት የልደትህማታ
.........
እንዴት ነበር ያኔ
የልደትህ ማታ
የዝማሬው ለታ
የእናትህ ደስታ
የፍጥረት እልልታ
ሚዳቋ ስትዘል ከኢትዮጵያ አይታ
ግን ጌታ እረቂቁ አምላክ
በየትስ መጠህ ነው ከኛ የተወለድክ
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_group
/መንፈሳዊ መነባንብ /
@Mgetem
ለአዳም ኪዳን ሰጠህ
እንደምትወለድ ወደ ምድር ወርደህ
እንዴት ነበር ያኔ..?
ወደ እኛ ስትመጣ መላእክትን ትተህ?
………
የሔዋን እርግማን
የባሏም የውርስ ኃጢአት መዘገን
እንዲያ አሳሰበህና
መጣህልን ሁሉን አደረግህ በፅሙና
.........
እንዴት ነበር ያኔ..?
ያችን ንጹሕ ለመፈለግ የወሰደብህ ጊዜ
አድርገህ የሰጠኸንን ፈውስ በበድልን ጊዜ
ግን ምን ያህል ነው ልፋትህ?
ድንግልን ስትፈልግ የፈጀብህ?
.........
ከሰማያት ስትወርድ አጀቡህ መላእክት?
ዓለሙስ ተናወፀ በይባቤ በስብሐት?
ያ ምቀኛ ዲያቢሎስ ግን ምን አለ?
ወደ እኛ ስትመጣ አለ አይደል ኮበለለ?
ነው ሥጋ ለብሶ ጉድ ሠራኝ አለ?
........
እንዴት ነው እርቀቱ
የሰማይ ምጥቀቱ
የምድርስ ሥፋት
ከሷ እስክታርፍባት?
ግን ጌታ...?ሰማያት ምን አሉ
ትትሀቸው መጠህ ባንተ አጉረመረሙ?
ፍጥረታትስ ቢሆን ማሕሌት አቆሙ?
.......
ምሥጢረኛው ጌታ
መንገድህ በየት ነው ወደ እኛ ስትመጣ?
ቤተ ልሔም ስትደርስ
ማን አገለገልህ?ምን አለች ምድሪቱስ
እያቄም ወሐናን እንዴት መረጥሃቸው
አንተ እንድትወለድ ምክንያትህ ናቸው
.......
ሰማዩ ሰፊ ነው
ምድርንም ታውቃለህ
እንዴት እንድትሰፋ ሆና መረገጫህ
ግን እና ጌታ ሆይ ምኑ ነው የቻለህ?
የድንግል ማሕጸን እሳት መሸከሙ
ምድርም መልኮት በእሷ ላይ መቆሙ
..........
እንዴት ነበር ያኔ
በቤተ ልሔም ውስጥ
አንተን የሚያሞቅ ከእንስሶች ስትሰጥ?
........
ዮሴፍ ምን አለ
አንተን በማየቱ እርጅናው ታጎለ?
አንተን የጠበቀህ አዳምስ በግርማህ ምን አለ?
........
እንዴት ነው ስጦታው
የሰብአ ሰገሉ ወርቅ እጣን አምኃው
የእረኞቹ ደስታ
የመላእክት ብሥራት የልደትህማታ
.........
እንዴት ነበር ያኔ
የልደትህ ማታ
የዝማሬው ለታ
የእናትህ ደስታ
የፍጥረት እልልታ
ሚዳቋ ስትዘል ከኢትዮጵያ አይታ
ግን ጌታ እረቂቁ አምላክ
በየትስ መጠህ ነው ከኛ የተወለድክ
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_group
መንፈሳዊ ግጥም ብቻ
የጥምቀት ግጥሞች እንልቀቅ??? @Ortho_quotes @Ortho_quotes
የመጀመሪያው የጥምቀት ግጥም ተለቋል! በዚያውም አዲሱ ቻናላችንን ይቀላቀሉ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/Ortho_Quotes/7
https://www.tg-me.com/Ortho_Quotes/7
https://www.tg-me.com/Ortho_Quotes/7
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/Ortho_Quotes/7
https://www.tg-me.com/Ortho_Quotes/7
https://www.tg-me.com/Ortho_Quotes/7
Telegram
ኦርቶዶክሳዊ ጥቅሶች ብቻ
#እናምናለን_በምስጢረ_ጥምቀቱ
@Mgetem
በመጋቤ ምስጢርነቱ
በመንግሥተ ሰማይ በርነቱ
ሰው ካልተወለደ ከውኃና ከመንፈስ
ሕይወት እንደሌለው ርስት እንደማይወርስ
ያመነ የተጠመቀ ይድናል
በጥምቀቱ ልጅነት ያገኛል
ባያምን ባይጠመቅ ከልጅነቱ ይወጣል
ኢጥዮጵያዊው ባኮስ በሐዋርያው በፊሊጶስ
ከነቤተሰቦቹ እስጢፋኖስ
ቅዱስ ጳውሎስ ከደማስቆ መልስ
በጥምቀት ተወልደዋል ከመንፈስ ቅዱስ
ሔዋን በሰማንያ አዳም በአርባ…
@Mgetem
በመጋቤ ምስጢርነቱ
በመንግሥተ ሰማይ በርነቱ
ሰው ካልተወለደ ከውኃና ከመንፈስ
ሕይወት እንደሌለው ርስት እንደማይወርስ
ያመነ የተጠመቀ ይድናል
በጥምቀቱ ልጅነት ያገኛል
ባያምን ባይጠመቅ ከልጅነቱ ይወጣል
ኢጥዮጵያዊው ባኮስ በሐዋርያው በፊሊጶስ
ከነቤተሰቦቹ እስጢፋኖስ
ቅዱስ ጳውሎስ ከደማስቆ መልስ
በጥምቀት ተወልደዋል ከመንፈስ ቅዱስ
ሔዋን በሰማንያ አዳም በአርባ…
"ዮርዳኖስ"
/መነባንብ/
@Mgetem
አንቺ ሰፊ ባህር ዮርዳኖስ መስክሪ
የተጠመቀብሽ የአለም ፈጣሪ
ትንቢት መነገሩ በዳዊት ነብይ
ድምፅ በውኖች ነው ብሎ መመስከሩ
በውኖች ይታያል ብሎ መዘከሩ
በዩርዳኖስ መሸሽ ትልቁ ሚስጥር
የዩርዳኖስ ባህር አምላኩን ማክበሩ
በጥልቅ ውሃዎች ላይ ስልጣን አለው ሲሉ
አምላክን ማክበሩ ፈርቶ መንቀጥቀጡ
ሰዎች ሳይረዱ ወንዙ መረዳቱ
የዳዊት ትንቢት ትውልድ መዘንጋቱ
ምን ይባላል አሁን እውነትን መሣቱ
ሰው መዳኑን ንቆ እንዲህ መቅበዝበዙ
ዳዊት ለምን ሸሸ ብሎ የጠየቀሽ
ባህረ ዮርዳኖስ ፈጣሪሽን አወቅሽ
ኧረ አንቺ ዮርዳኖስ ኢያሱየከፈለሽ
ሕዝበ እስራኤን በአንቺ ያሻገረብሽ
ከዕለቱ ክርስቶስ ውሃ ያጠጣብሽ
ኤልሳና ኤልያስ ደግሞ የቆሙብሽ
ለመጎናፀፍያ ከፍለው ያለፉብሽ
ንዕማር ሲጠመቅ ከለምጹየነፃብሽ
ሰው የሆነ ንጉስ ባንቺ ሲታይብሽ
ይህ ሁሉ ሲደረግ ትግሉ ሲሰምርብሽ
ዩሐንስ ሲያጠምቅ መድህን ሲመጣብሽ
እራሱን አዋርዶ ባንቺ ሲታይብሽ
ወልድ አምላክ በክብር ሲጠመቅ በውስጥሽ
እርጥበትሽ ሳይደርቅ እሳቱ ሳይፈጅሽ
ዮርዳኖስ ድንቅ ነው ጸንተሽ መገኘትሽ
ይመሰክር ጀመር ዩሐንስ ተረድቶ
የእግዚአብሔር በግ መጣ ይኽው ብሎ
እኔ አላውቀውም ጥንትም ነበር ደግም
አለ መስከር እውነት ተናገር
በእሳት የሚያጠምቅ ይመጣል እያለ
ታዲያ እንዲህ ሰዎች ሲጠመቁ
መድሐኒት ብቅ አለ ከወደ ጥምቀቱ
በዮሐንስ እጆች ሊጠመቅ ፈልጎ
ዩሐንስ አዘነ እጅግ ተፀፀተ
አምላከ ሰማይን እንዴት ላጥምቅ ብሎ
ፅድቅን ለመፈፀም ወዲህ መጣሁኝ
ብሎ ሲያስተምረው መድሐኒዓለም
ያጠምቀው ጀመረ በእሽታ መንፈስ
እየሱስ ሲጠመቅ በዮሐንስ እጅ
ሰማያት ተከፍተው ቃል ሲመጣለት
መንፈስ ቅዱስ መጥቶ በራሱ ላይ ሲያርፍ
የምወደው ልጄ ይህ ነው ስሙት
ተብሎ ሲነገር ከእግዚአብሔር አብ
የስላሴ ምስጢር በዮርዳኖስ ባህር
ተገልጾ ነበር የአንድነት ምስጢር
አንድነት ሶስትነት ያለመከፋፈል
ሰዎች ሲጠመቁ በስላሴ ስም
የእግዚአብሔር ልጅነት ያገኙ ነበር
ታዲያ ምን ይባላል የአሁኑ ትዕቢት
ስላሴ ምንድ ነው ብሎ መደንፋት
ኢየሱስ አንድ አካል ፍጡር ነው ማለት
ልበ ቆሻሻዎች የክርስቶስ ጠር
ጆረአቸው ተደፎኖ ልባቸው ቢዝል
በዮርዳኖስ ታይቷል የአንድነት ምስጢር
የወደደ ይምጣ የጠላ ይመለስ
አይከለስ እንደው የዮርዳኖስ እውነት
ከባህሮች ተመርጠሽ ዮርዳኖስ የታደልሽ
ምስጢር ስላሴ የተገለፀብሽ
አንቺ ሰፊ ምድር ዮርዳኖስ መስክሪ
የተጠመቀብሽ የዓለም ፈጣሪ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_group
/መነባንብ/
@Mgetem
አንቺ ሰፊ ባህር ዮርዳኖስ መስክሪ
የተጠመቀብሽ የአለም ፈጣሪ
ትንቢት መነገሩ በዳዊት ነብይ
ድምፅ በውኖች ነው ብሎ መመስከሩ
በውኖች ይታያል ብሎ መዘከሩ
በዩርዳኖስ መሸሽ ትልቁ ሚስጥር
የዩርዳኖስ ባህር አምላኩን ማክበሩ
በጥልቅ ውሃዎች ላይ ስልጣን አለው ሲሉ
አምላክን ማክበሩ ፈርቶ መንቀጥቀጡ
ሰዎች ሳይረዱ ወንዙ መረዳቱ
የዳዊት ትንቢት ትውልድ መዘንጋቱ
ምን ይባላል አሁን እውነትን መሣቱ
ሰው መዳኑን ንቆ እንዲህ መቅበዝበዙ
ዳዊት ለምን ሸሸ ብሎ የጠየቀሽ
ባህረ ዮርዳኖስ ፈጣሪሽን አወቅሽ
ኧረ አንቺ ዮርዳኖስ ኢያሱየከፈለሽ
ሕዝበ እስራኤን በአንቺ ያሻገረብሽ
ከዕለቱ ክርስቶስ ውሃ ያጠጣብሽ
ኤልሳና ኤልያስ ደግሞ የቆሙብሽ
ለመጎናፀፍያ ከፍለው ያለፉብሽ
ንዕማር ሲጠመቅ ከለምጹየነፃብሽ
ሰው የሆነ ንጉስ ባንቺ ሲታይብሽ
ይህ ሁሉ ሲደረግ ትግሉ ሲሰምርብሽ
ዩሐንስ ሲያጠምቅ መድህን ሲመጣብሽ
እራሱን አዋርዶ ባንቺ ሲታይብሽ
ወልድ አምላክ በክብር ሲጠመቅ በውስጥሽ
እርጥበትሽ ሳይደርቅ እሳቱ ሳይፈጅሽ
ዮርዳኖስ ድንቅ ነው ጸንተሽ መገኘትሽ
ይመሰክር ጀመር ዩሐንስ ተረድቶ
የእግዚአብሔር በግ መጣ ይኽው ብሎ
እኔ አላውቀውም ጥንትም ነበር ደግም
አለ መስከር እውነት ተናገር
በእሳት የሚያጠምቅ ይመጣል እያለ
ታዲያ እንዲህ ሰዎች ሲጠመቁ
መድሐኒት ብቅ አለ ከወደ ጥምቀቱ
በዮሐንስ እጆች ሊጠመቅ ፈልጎ
ዩሐንስ አዘነ እጅግ ተፀፀተ
አምላከ ሰማይን እንዴት ላጥምቅ ብሎ
ፅድቅን ለመፈፀም ወዲህ መጣሁኝ
ብሎ ሲያስተምረው መድሐኒዓለም
ያጠምቀው ጀመረ በእሽታ መንፈስ
እየሱስ ሲጠመቅ በዮሐንስ እጅ
ሰማያት ተከፍተው ቃል ሲመጣለት
መንፈስ ቅዱስ መጥቶ በራሱ ላይ ሲያርፍ
የምወደው ልጄ ይህ ነው ስሙት
ተብሎ ሲነገር ከእግዚአብሔር አብ
የስላሴ ምስጢር በዮርዳኖስ ባህር
ተገልጾ ነበር የአንድነት ምስጢር
አንድነት ሶስትነት ያለመከፋፈል
ሰዎች ሲጠመቁ በስላሴ ስም
የእግዚአብሔር ልጅነት ያገኙ ነበር
ታዲያ ምን ይባላል የአሁኑ ትዕቢት
ስላሴ ምንድ ነው ብሎ መደንፋት
ኢየሱስ አንድ አካል ፍጡር ነው ማለት
ልበ ቆሻሻዎች የክርስቶስ ጠር
ጆረአቸው ተደፎኖ ልባቸው ቢዝል
በዮርዳኖስ ታይቷል የአንድነት ምስጢር
የወደደ ይምጣ የጠላ ይመለስ
አይከለስ እንደው የዮርዳኖስ እውነት
ከባህሮች ተመርጠሽ ዮርዳኖስ የታደልሽ
ምስጢር ስላሴ የተገለፀብሽ
አንቺ ሰፊ ምድር ዮርዳኖስ መስክሪ
የተጠመቀብሽ የዓለም ፈጣሪ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_group
ስለ ቃና ዘገሊላ ግጥም ተለቋል
👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/Ortho_Quotes/8
https://www.tg-me.com/Ortho_Quotes/8
https://www.tg-me.com/Ortho_Quotes/8
👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/Ortho_Quotes/8
https://www.tg-me.com/Ortho_Quotes/8
https://www.tg-me.com/Ortho_Quotes/8
Telegram
ኦርቶዶክሳዊ ጥቅሶች ብቻ
#የቃናዋ_እመቤት
@Mgetem
ወይን ጠጁ ሲያልቅባቸው፤
የሚያደርጉት ሲጠፋቸው፤
መች ዝም አለች እናታቸው፤
እመብርሃን መውጫቸው።
የዶኪማስ ባለውለታ፤
የአገልጋያቹ ትዝታ፤
የእድምተኞቹ እርካታ፤
የሓዋርያት አለኝታ።
የምልክቶች መጀመርያ፤
ሲያደርጋት ልጇ አክብሮ፤
ለእኛ እንድትሆን አዘክሮ፤
ሲለመነን በእሷ ላይ አድሮ፤
ፈጥኖ ሰማት በአንክሮ።
የቃናዋ እመቤት አማላጅዋ፤
የማይቋረጠው እርዳታዋ፤
የማይቆጠረው…
@Mgetem
ወይን ጠጁ ሲያልቅባቸው፤
የሚያደርጉት ሲጠፋቸው፤
መች ዝም አለች እናታቸው፤
እመብርሃን መውጫቸው።
የዶኪማስ ባለውለታ፤
የአገልጋያቹ ትዝታ፤
የእድምተኞቹ እርካታ፤
የሓዋርያት አለኝታ።
የምልክቶች መጀመርያ፤
ሲያደርጋት ልጇ አክብሮ፤
ለእኛ እንድትሆን አዘክሮ፤
ሲለመነን በእሷ ላይ አድሮ፤
ፈጥኖ ሰማት በአንክሮ።
የቃናዋ እመቤት አማላጅዋ፤
የማይቋረጠው እርዳታዋ፤
የማይቆጠረው…
Forwarded from ኦርቶዶክሳዊ ጥቅሶች ብቻ
ከዳመናው መሀል ይፈልቃል ኃያል ጢስ
ድል ለሀገሬ ሊሰጥ
በፈረሱ ይነጉዳል የአራዳው ጊዮርጊስ
ይዘምታል በሰማይ አማኝ ህዝቡን ከልሎ
የአምላክ ውብ ምድር
ቅድስት ኢትዮጵያ አትደፈር ብሎ
ይጎርፋል ሰው
ጦር ጋሻውን በእጁ አንጠልጥሎ
ምንሽር አልቤኑን በጀርባው ላይ አዝሎ
በባዶ እግሩ ጋሬጣውን ረቶ
እንዴትስ ይቀራል
ከንጉሱ ከንፈር የማርያም ስም ወጥቶ
ልክ እንደ ጦር እቃ ታቦት ተሸክሞ
ልክ እንደ አዘቦት ቀን በጾም ተሸልሞ
ቅንጣት እህል ሳይጎርስ በእምነቱ ቁሞ
ቅዳሴውን ሳይሽር በሰዓቱ ተገኝቶ
‹‹አሀዱ›› ሲል በህብረት አንድነት ገንብቶ
የዋለ ገበሬ የዋለ ሰራዊት
ድል አፍሶ ቢመለስ ይደንቃል ወይ ጥቂት?
(አይደንቅም)
አቡነ ማቲዎስ እምነትን አግዝፈው
ለሰራዊት ሲባል
‹‹ጾም ይሻር›› የሚል ትእዛዝ ተላልፈው
ከንጉስ ተሟግተው
በመስቀል አሳልመው
ባርከው ተዋጊውን ቢልኩ ወደ ውጊያ
ሰው በእህል ሳይሆን
በእምነት እንደሚረታ
ምስክር ትሆን ዘንድ አሸነፈች ጦቢያ
እኔ ግን
የድል ታሪክ ይዤ
ቆሚያለሁ ፈዝዤ
ተኝቻለሁ ደንዝዤ
አልስራ ጀብድ አልፈጽም ገድል
እንዴት ያቅተኛል
መዘከር እንኳን የአባቶቼን ድል?
ቢገባኝ ኖሮ የነጻነት ክብር
የካቲት ጊዮርጊስ
ስዕለት ባስገባሁ ለመቆሜ ተአምር
በባዶ እግር ሄዶ ጫማ ያለበሰኝ
ከአራቱም አቅጣጫ
ለአንድ አላማ ዘምቶ ሀገር ያወረሰኝ
በዘር ጎጠኝነት
ተከፋፍዬ ቢያይ በእንባው በወቀሰኝ
‹‹ ከአንድነት እርካብ ቁልቁል ተፈጥፍጠህ
በቁንጽል ማንነት ራስክን ለውጠህ
የምትኖር ሁላ አድዋን አስታውሰህ
ሁን እንደ ጥንቱ ፍቅርን ተንተርሰህ
አሻፈረኝ ካልክ ግን
‹‹ማርያምን!›› እፋረድኃለው በሰማይ
በሀገሬ ጀርባ ላይ ፈልተኃል እንደ ተባይ ››
ብሎ ባወጀብኝ
ሽልብታዬን አይቶ
እብደቴን ታዝቦ ከሞቴ ባነቃኝ
ጾም ጸሎትን ትቼ
አርብ ሮብን ረስቼ
ቅዳሴ ሰዓታት
ማህሌት ኪዳንን እኒህን ዘንግቼ
ለሆዴ አድሬ ስኖር እንደ አሳማ
ይደንቃል ወይ እውነት
ተረግጬ ብቀር ልክ እንደ ቄጤማ?
ተንኜ ብቀር ልክ እንደ ጤዛ?
ተሸንፌ ብታይ ወድቄ እንደ ዋዛ?
(አይደንቅም)
ዋ ለእኔ!
ዋ እኔ!
ርግብ ጋር ዘምቼ
ለቀረሁኝ ሞቼ
#ኤልዳን
@eldan29
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
ድል ለሀገሬ ሊሰጥ
በፈረሱ ይነጉዳል የአራዳው ጊዮርጊስ
ይዘምታል በሰማይ አማኝ ህዝቡን ከልሎ
የአምላክ ውብ ምድር
ቅድስት ኢትዮጵያ አትደፈር ብሎ
ይጎርፋል ሰው
ጦር ጋሻውን በእጁ አንጠልጥሎ
ምንሽር አልቤኑን በጀርባው ላይ አዝሎ
በባዶ እግሩ ጋሬጣውን ረቶ
እንዴትስ ይቀራል
ከንጉሱ ከንፈር የማርያም ስም ወጥቶ
ልክ እንደ ጦር እቃ ታቦት ተሸክሞ
ልክ እንደ አዘቦት ቀን በጾም ተሸልሞ
ቅንጣት እህል ሳይጎርስ በእምነቱ ቁሞ
ቅዳሴውን ሳይሽር በሰዓቱ ተገኝቶ
‹‹አሀዱ›› ሲል በህብረት አንድነት ገንብቶ
የዋለ ገበሬ የዋለ ሰራዊት
ድል አፍሶ ቢመለስ ይደንቃል ወይ ጥቂት?
(አይደንቅም)
አቡነ ማቲዎስ እምነትን አግዝፈው
ለሰራዊት ሲባል
‹‹ጾም ይሻር›› የሚል ትእዛዝ ተላልፈው
ከንጉስ ተሟግተው
በመስቀል አሳልመው
ባርከው ተዋጊውን ቢልኩ ወደ ውጊያ
ሰው በእህል ሳይሆን
በእምነት እንደሚረታ
ምስክር ትሆን ዘንድ አሸነፈች ጦቢያ
እኔ ግን
የድል ታሪክ ይዤ
ቆሚያለሁ ፈዝዤ
ተኝቻለሁ ደንዝዤ
አልስራ ጀብድ አልፈጽም ገድል
እንዴት ያቅተኛል
መዘከር እንኳን የአባቶቼን ድል?
ቢገባኝ ኖሮ የነጻነት ክብር
የካቲት ጊዮርጊስ
ስዕለት ባስገባሁ ለመቆሜ ተአምር
በባዶ እግር ሄዶ ጫማ ያለበሰኝ
ከአራቱም አቅጣጫ
ለአንድ አላማ ዘምቶ ሀገር ያወረሰኝ
በዘር ጎጠኝነት
ተከፋፍዬ ቢያይ በእንባው በወቀሰኝ
‹‹ ከአንድነት እርካብ ቁልቁል ተፈጥፍጠህ
በቁንጽል ማንነት ራስክን ለውጠህ
የምትኖር ሁላ አድዋን አስታውሰህ
ሁን እንደ ጥንቱ ፍቅርን ተንተርሰህ
አሻፈረኝ ካልክ ግን
‹‹ማርያምን!›› እፋረድኃለው በሰማይ
በሀገሬ ጀርባ ላይ ፈልተኃል እንደ ተባይ ››
ብሎ ባወጀብኝ
ሽልብታዬን አይቶ
እብደቴን ታዝቦ ከሞቴ ባነቃኝ
ጾም ጸሎትን ትቼ
አርብ ሮብን ረስቼ
ቅዳሴ ሰዓታት
ማህሌት ኪዳንን እኒህን ዘንግቼ
ለሆዴ አድሬ ስኖር እንደ አሳማ
ይደንቃል ወይ እውነት
ተረግጬ ብቀር ልክ እንደ ቄጤማ?
ተንኜ ብቀር ልክ እንደ ጤዛ?
ተሸንፌ ብታይ ወድቄ እንደ ዋዛ?
(አይደንቅም)
ዋ ለእኔ!
ዋ እኔ!
ርግብ ጋር ዘምቼ
ለቀረሁኝ ሞቼ
#ኤልዳን
@eldan29
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
Forwarded from አንድ ቀለም ከከሡ ጋር
የምኩራቡ
የምኩራቡ ቸር መም'ር፥
ቃል ሆኖ ቃል ሚናገር፥
ወንጌል ሆኖ ወንጌል ሚሰብክ፥
በሰው ልሣን በፍጡር መልክ።
ለሙሴ ሕግን የሰጠ፥
ቀርቦ ክርታሱን ገለጠ፥
ያናገረውን በነቢይ፥
አስተማረው በቃል ዐቢይ።
"የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ላይ፥
ወንጌል እንድሰብክ ለነዳይ፥
ምሥራች ሚነገርባት፥
ዓመተ ምሕረት ይቺ ናት።"
ሁሉን ሠርተህ "ምሰሉኝ" ያልህ፥
ትኁት መምህር በልብ የዋህ፥
የሰገደልህም ረቢ፥
ኒቆዲሞስ ያ'ይሁድ መጋቢ።
እንበሌከ ሠራዔ ሕግ፥
ሚሽር ሚያጸና ሚደነግግ፥
"አነ እብለክሙ" ሚል ማነው፥
ሁሉ 'ሚደግም ያንተን ነው።
ምኩራብ ሸመነች ሕግ ሸማን፥
ለበሰችው ቤተ ክርስቲያን።
ምዕመን ፅጌረዳ አቀፈ፥
እሾሁ ለአይሁድ ተረፈ።
ምኩራብ አመጣች ሰደፍን፥
በዕንቁ ባሕርዩ አተረፍን፥
ምኩራብ ምግበ ሕይወት ሰቀለች፥
ምዕመን ቁርባን ተቀበለች።
✍️ከሣቴ ብርሃን
🎼ኤርምያስ በገና
የምኩራቡ ቸር መም'ር፥
ቃል ሆኖ ቃል ሚናገር፥
ወንጌል ሆኖ ወንጌል ሚሰብክ፥
በሰው ልሣን በፍጡር መልክ።
ለሙሴ ሕግን የሰጠ፥
ቀርቦ ክርታሱን ገለጠ፥
ያናገረውን በነቢይ፥
አስተማረው በቃል ዐቢይ።
"የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ላይ፥
ወንጌል እንድሰብክ ለነዳይ፥
ምሥራች ሚነገርባት፥
ዓመተ ምሕረት ይቺ ናት።"
ሁሉን ሠርተህ "ምሰሉኝ" ያልህ፥
ትኁት መምህር በልብ የዋህ፥
የሰገደልህም ረቢ፥
ኒቆዲሞስ ያ'ይሁድ መጋቢ።
እንበሌከ ሠራዔ ሕግ፥
ሚሽር ሚያጸና ሚደነግግ፥
"አነ እብለክሙ" ሚል ማነው፥
ሁሉ 'ሚደግም ያንተን ነው።
ምኩራብ ሸመነች ሕግ ሸማን፥
ለበሰችው ቤተ ክርስቲያን።
ምዕመን ፅጌረዳ አቀፈ፥
እሾሁ ለአይሁድ ተረፈ።
ምኩራብ አመጣች ሰደፍን፥
በዕንቁ ባሕርዩ አተረፍን፥
ምኩራብ ምግበ ሕይወት ሰቀለች፥
ምዕመን ቁርባን ተቀበለች።
✍️ከሣቴ ብርሃን
🎼ኤርምያስ በገና
እመ አምላክ አደራ
@Mgetem
ከቤተመቅደስሽ ፣ከፊትሽ ስጠጋ
ምኞቴ እንዲሰምር፣ ሃሳቤ እንዲረጋ
በደሌም እንዲፋቅ ፣ነፍሴም እንዳትሰጋ ።
ይቅር በይኝ ድንግል ፣ሁሉንም ረስተሽ
የበደልኩሽንም፣ ኃጢያተንም ትተሽ
ነይ በይኝ እማምላክ ፣እጅሽን ዘርግተሽ ።
ከካቡ ስር ቁሜ፣ ከመቅደሱ ታዛ
በልጅሽ ፈጣሪ፣ በሕጉ ስገዛ ።
እማምላክ አደራ፣ ፀሎቴን አትርሽኝ
ጉድፈን አንሽልኝ፣ እምባየን አብሽልኝ
እራቁት ገላዬን፣ በረከት አልብሽኝ
ከቤት ውጥቻለሁ ፣ወደቤት መልሽኝ ።
እማምላክ አደራ
ሀጥያት ያረከሳት፣ ነፍሴ እንዳትፈራ
መጫወቻ እንዳትሆን፣ በዲያብሎስ ጭፍራ
እባክሽ መልሽኝ፣ ወደ አባቴ ስፍራ
ድንግል ሆይ አስታርቂኝ፣ ከፈጣሪ ጋራ ።
ስቆም ከመቅደሱ፣ ስጠጋ ከደጅሽ
እማምላክ ዳባብሽኝ ፣የፈጣሪን ገላ፣ በዳበሱት እጅሽ
ምሕረትን አሰጭኝ ፣ከልጅ ከወዳጅሽ።
ብላችሁ ለምኗት
ሁሉን ታሰጣለች፣ ሁላችሁ እመኗት
ፈጣሪም እናቱን፣ እምቢ እይላትም ቅንጣት
መቸም የማይሻር ፣ቃሉን ነው የሰጣት
እስቲ ማን ነበረ፣ ለምኖ ያፈረ
አድርግልኝ ብሎ ፣ስለቱ ያልሰመረ ።
ስለ እማምላክ በሉ፣ ምኑ ያሳፍራል ?
እንክዋን እኛ ቀርቶ፣ ሙሉ ገላ ያለን ፣ስለ ድንግል ብሎ፣ ድሃው ጠግቦ ያድራል ።
ስለ ልጅሽ ድንግል ፣አሁንም አትርሽኝ
እንደቃናው ድግስ ፣ጓዳዬን ጎብኝልኝ፣
እንደ አባ ጊዮርጊስ፣ ሰማያዊ ፅዋ፣ እውቀትን ለግሽኝ
ቤቴ ወና እንዳይሆን፣ በረከት አትንሽኝ ።
በፊት በኋላዬ ፣እናቴ አንቺ ምሪ
ኑሮዬንም አቅኚ ፣ሕይወቴን አስምሪ
መደገፊያ ምርኩዝ፣ ደግ አማላጃችን
በረከትን ስጭን፣ ባዶ ነው እጃችን
ድንግል አትራቂን ፣ኑሪ በደጃችን
ሰላም አድርጊልን ፣ህዝበ ክርስቲያኑን ፣ኢትዮጵያ ሀገራችን ።
ክፋትና በደል፣ ኃጢያትም ላለብን
እንደ በላዔሰብ ፣ጥላ ትጣልብን።
አሜን፫
____
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
@Mgetem
ከቤተመቅደስሽ ፣ከፊትሽ ስጠጋ
ምኞቴ እንዲሰምር፣ ሃሳቤ እንዲረጋ
በደሌም እንዲፋቅ ፣ነፍሴም እንዳትሰጋ ።
ይቅር በይኝ ድንግል ፣ሁሉንም ረስተሽ
የበደልኩሽንም፣ ኃጢያተንም ትተሽ
ነይ በይኝ እማምላክ ፣እጅሽን ዘርግተሽ ።
ከካቡ ስር ቁሜ፣ ከመቅደሱ ታዛ
በልጅሽ ፈጣሪ፣ በሕጉ ስገዛ ።
እማምላክ አደራ፣ ፀሎቴን አትርሽኝ
ጉድፈን አንሽልኝ፣ እምባየን አብሽልኝ
እራቁት ገላዬን፣ በረከት አልብሽኝ
ከቤት ውጥቻለሁ ፣ወደቤት መልሽኝ ።
እማምላክ አደራ
ሀጥያት ያረከሳት፣ ነፍሴ እንዳትፈራ
መጫወቻ እንዳትሆን፣ በዲያብሎስ ጭፍራ
እባክሽ መልሽኝ፣ ወደ አባቴ ስፍራ
ድንግል ሆይ አስታርቂኝ፣ ከፈጣሪ ጋራ ።
ስቆም ከመቅደሱ፣ ስጠጋ ከደጅሽ
እማምላክ ዳባብሽኝ ፣የፈጣሪን ገላ፣ በዳበሱት እጅሽ
ምሕረትን አሰጭኝ ፣ከልጅ ከወዳጅሽ።
ብላችሁ ለምኗት
ሁሉን ታሰጣለች፣ ሁላችሁ እመኗት
ፈጣሪም እናቱን፣ እምቢ እይላትም ቅንጣት
መቸም የማይሻር ፣ቃሉን ነው የሰጣት
እስቲ ማን ነበረ፣ ለምኖ ያፈረ
አድርግልኝ ብሎ ፣ስለቱ ያልሰመረ ።
ስለ እማምላክ በሉ፣ ምኑ ያሳፍራል ?
እንክዋን እኛ ቀርቶ፣ ሙሉ ገላ ያለን ፣ስለ ድንግል ብሎ፣ ድሃው ጠግቦ ያድራል ።
ስለ ልጅሽ ድንግል ፣አሁንም አትርሽኝ
እንደቃናው ድግስ ፣ጓዳዬን ጎብኝልኝ፣
እንደ አባ ጊዮርጊስ፣ ሰማያዊ ፅዋ፣ እውቀትን ለግሽኝ
ቤቴ ወና እንዳይሆን፣ በረከት አትንሽኝ ።
በፊት በኋላዬ ፣እናቴ አንቺ ምሪ
ኑሮዬንም አቅኚ ፣ሕይወቴን አስምሪ
መደገፊያ ምርኩዝ፣ ደግ አማላጃችን
በረከትን ስጭን፣ ባዶ ነው እጃችን
ድንግል አትራቂን ፣ኑሪ በደጃችን
ሰላም አድርጊልን ፣ህዝበ ክርስቲያኑን ፣ኢትዮጵያ ሀገራችን ።
ክፋትና በደል፣ ኃጢያትም ላለብን
እንደ በላዔሰብ ፣ጥላ ትጣልብን።
አሜን፫
____
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
እኔ ማነኝ ?
@Mgetem
በእረኝነት ሳለሁ ጠርተህ ያከበርከኝ
መቃብሬን ፈንቅለህ ከሞት ያስነሳኸኝ
የተሸከመኝን አልጋ ያሸከምከኝ
ዝሙተኛ ሳለሁ በፍቅርህ ያቀፍከኝ
የኤርትራን ባህር ከፍለህ ያሻገርከኝ
ከአንበሶች መንጋጋ ከሞት አፍ ያዳንከኝ
አንገትህን ደፍተህ ቀና ያደረከኝ
አንተ እየተዋረድክ እኔን ከፍ ያከበርከኝ
ውለታህ በዛብኝ ጌታ ሆይ እኔ ማነኝ
ተናገረኝ ልስማህ ድምጽህ ያጽናናኛል
ያ ሁሉ መከራ ባንተ አልፎልኛል
ጠላቴ በፊቴ ተንበርክኮልኛል
ውስጤ አንተን ሲያስብ በሀሴት ይሞላል
የዓለም ጣጣዋ እጅግ ቢከብደኝም
ፈተና ከፊቴ ቢያደናግረኝም
በድፍረት እላለሁ ክፉውን አልፈራም
ሁሌም ከእኔ ጋር ነው ጌታ መድሃኔአለም
እሱን ተጠግቶ ያፈረ ሰው ማነው
የእጁ በረከት ልቡን ያላራሰው
እውነቱን ይናገር እኮ ይህ ሰው ማነው
ሁሉን አሳልፎ ለዚህ ቀን ያበቃን
ከነ በደላችን በፊቱ ያቆመን
የልመናችንን ድምጽ ሰምቶ ያላለፈን
እንዲህ የወደደን ከቶ እኛ ማነን
ህይወቴን ልቃኘው ወደኋላ አየሁኝ
ስለኔ የሆነውን ሁሉን ተረዳሁኝ
በበደሌ ብዛት ፈጽሞ ያልተውከኝ
ኧረ ለመሆኑ ከቶ እኔ ማነኝ
ተጨማሪ ለማግኘት ቻናሉን ይቀላቀሉ!
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
@Mgetem
በእረኝነት ሳለሁ ጠርተህ ያከበርከኝ
መቃብሬን ፈንቅለህ ከሞት ያስነሳኸኝ
የተሸከመኝን አልጋ ያሸከምከኝ
ዝሙተኛ ሳለሁ በፍቅርህ ያቀፍከኝ
የኤርትራን ባህር ከፍለህ ያሻገርከኝ
ከአንበሶች መንጋጋ ከሞት አፍ ያዳንከኝ
አንገትህን ደፍተህ ቀና ያደረከኝ
አንተ እየተዋረድክ እኔን ከፍ ያከበርከኝ
ውለታህ በዛብኝ ጌታ ሆይ እኔ ማነኝ
ተናገረኝ ልስማህ ድምጽህ ያጽናናኛል
ያ ሁሉ መከራ ባንተ አልፎልኛል
ጠላቴ በፊቴ ተንበርክኮልኛል
ውስጤ አንተን ሲያስብ በሀሴት ይሞላል
የዓለም ጣጣዋ እጅግ ቢከብደኝም
ፈተና ከፊቴ ቢያደናግረኝም
በድፍረት እላለሁ ክፉውን አልፈራም
ሁሌም ከእኔ ጋር ነው ጌታ መድሃኔአለም
እሱን ተጠግቶ ያፈረ ሰው ማነው
የእጁ በረከት ልቡን ያላራሰው
እውነቱን ይናገር እኮ ይህ ሰው ማነው
ሁሉን አሳልፎ ለዚህ ቀን ያበቃን
ከነ በደላችን በፊቱ ያቆመን
የልመናችንን ድምጽ ሰምቶ ያላለፈን
እንዲህ የወደደን ከቶ እኛ ማነን
ህይወቴን ልቃኘው ወደኋላ አየሁኝ
ስለኔ የሆነውን ሁሉን ተረዳሁኝ
በበደሌ ብዛት ፈጽሞ ያልተውከኝ
ኧረ ለመሆኑ ከቶ እኔ ማነኝ
ተጨማሪ ለማግኘት ቻናሉን ይቀላቀሉ!
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
Telegram
መንፈሳዊ ግጥም ብቻ
በዚህ ቻናል ላይ በየቀኑ ኦርቶዶክሳዊ ግጥሞችን ያገኛሉ
ለአስተያየትና ግጥም እንዲፖሰትላችሁ የምትፈልጉ ለመላክ
@Solasc12
@Solasc13
@Mgetem_group
ኦርቶዶክሳዊ ጥቅሶች ብቻ
@Ortho_quotes
ለአስተያየትና ግጥም እንዲፖሰትላችሁ የምትፈልጉ ለመላክ
@Solasc12
@Solasc13
@Mgetem_group
ኦርቶዶክሳዊ ጥቅሶች ብቻ
@Ortho_quotes
Forwarded from አንድ ቀለም ከከሡ ጋር
ገብረ ሕይወት
አቡነ ንብሎ ለገብረ ሕይወት፥
እስመ አምጽአ ለነ ትንባሌሁ ሥርየት።
ወንወድሶ በቃለ ማኅሌት፥
እንዘ ንብል ሃሌ ሉያ፥
ሰብአ ግብፅ ወኢትዮጵያ።
ስምዖን ፣ አቅሌስያ በእግዚአብሔር ፊት ፃድቃን፥
ወለዱልን ፀሐይ ብሩህ እም ብሩሃን፥
ግብፅ ብቻ አልበራ ፣ ባሕቢት አል ሐጋራ፥
ናኘ በኢትዮጵያ የትሩፋቱ ጮራ።
ዝቋላ በገድሉ ፣ ምድረ ከብድ በዐፅሙ፥
በተአምራቱም ኃይል ዝጊቲ ገዳሙ፥
በነፍስ ፣ በሥጋ ዳኑ የታመሙ፥
ወውስተ ኩሉ ምድር ወጽአ ነገሮሙ።
እንደ መቶ ሃያው አናብስት አናምርት፥
ከእግረ መቅደስህ አደግሁ ባንተ ትምህርት፥
ዛሬም እልሃለሁ "አቡየ ፣ አቡየ"
"ነዓ አድኅንነኒ ፣ ርድአኒ" ብየ።
ርእሰ ባሕታዊ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፥
በትጉኃን ክቡር ፣ በመላእክት ውዱስ፥
በማለድከው ምልጃ ተዘቅዝቀህ ባሕር፥
በኪዳንህ ያመንሁ እኔን አምላክ ይማር።
✍️ከሣቴ ብርሃን
🎼ዘማሪት ሕይወት ወልዴ
_____
http://www.tg-me.com/Andkelem
http://www.tg-me.com/Andkelem
አቡነ ንብሎ ለገብረ ሕይወት፥
እስመ አምጽአ ለነ ትንባሌሁ ሥርየት።
ወንወድሶ በቃለ ማኅሌት፥
እንዘ ንብል ሃሌ ሉያ፥
ሰብአ ግብፅ ወኢትዮጵያ።
ስምዖን ፣ አቅሌስያ በእግዚአብሔር ፊት ፃድቃን፥
ወለዱልን ፀሐይ ብሩህ እም ብሩሃን፥
ግብፅ ብቻ አልበራ ፣ ባሕቢት አል ሐጋራ፥
ናኘ በኢትዮጵያ የትሩፋቱ ጮራ።
ዝቋላ በገድሉ ፣ ምድረ ከብድ በዐፅሙ፥
በተአምራቱም ኃይል ዝጊቲ ገዳሙ፥
በነፍስ ፣ በሥጋ ዳኑ የታመሙ፥
ወውስተ ኩሉ ምድር ወጽአ ነገሮሙ።
እንደ መቶ ሃያው አናብስት አናምርት፥
ከእግረ መቅደስህ አደግሁ ባንተ ትምህርት፥
ዛሬም እልሃለሁ "አቡየ ፣ አቡየ"
"ነዓ አድኅንነኒ ፣ ርድአኒ" ብየ።
ርእሰ ባሕታዊ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፥
በትጉኃን ክቡር ፣ በመላእክት ውዱስ፥
በማለድከው ምልጃ ተዘቅዝቀህ ባሕር፥
በኪዳንህ ያመንሁ እኔን አምላክ ይማር።
✍️ከሣቴ ብርሃን
🎼ዘማሪት ሕይወት ወልዴ
_____
http://www.tg-me.com/Andkelem
http://www.tg-me.com/Andkelem
ዳግም ምን አሏቸው?
/መነባንብ/
✞**
እናታለም ተዋህዶ
ባንችነትሽ የሚኮራ
በስምሽ ስም የሚጠራ
ዛሬ ጠፋ የሚያበራ
ስለፍቅርሽ ቀልጠው ነደው
ስለ አምላካቸው ተማግደው
በሃይማኖት ፍቅር እጅጉን ተነክተው
ካንቺ ጉያ በኖሩ
እግሮችሽ ስር በተማሩ
ለምን/2/ ተዋህዶ ጠላቸው መንደሩ
ምን አሏቸው ደግሞ ቅዱሳን አበውን
አንቺን እናት እምነት ከዚህ ያበቁትን
ምን አሏቸው ደግሞ አበው ሊቃውንትን
አንድምታውን ፈተው ባመሰጠሩልን
ሚስጢርን መሰጥርው ለኛ ባኖሩልን
ብራና ወጥረው አምድ በፃፉልን
ውለታቸው ታዲያ ይህ ነው?
ስላደረጉልን የምንከፍለው
ጭራሽማ አምላክ ባከበራቸው
አክሊሉን በደፋላቸው
በሀሴት በተቀበላቸው
ልባችን ለምን አመፀ ለምንድን ማይቀበል
ተፈትኖ ያለውን የተፃፈላቸውን የህይወት ገድል
ለምንድን! የማናምን በምልጃቸው
እሱ እግዚአብሔር በሰጣቸው
ደግሞስ ምን አሏቸው?
እሄ......./በለቅሶ/
ሁሌም እውነት ነው
መልከ መልካም ሙሽራዋ
የፀናች በድንግልናዋ
ማን አለ እንደዝች እንደ ቅድስት እናት
ያልተረታ በነገስታት
አንገቷን ለሰይፍ የሠጠች
ክርስቶስን ብላ የኖረች
እኮስ ምን አሏት ይህችን እናት
የስጋ ፋላጎት ያልሠበራት።
ተዋህዶ እናት አለም
እንደድሮ ፀንቶ የሚኖር ልጆችሽ ፈርተዋል የሉም
የምልጃ ታላቅ ስራ
ለህዝቦቿ እያበራ
እየለመኑ ምህረት
ሲያስተዳድሩ አናብርቱ አናብስቱን
ከባህር ውስጥ የፀለዩ
በስራቸው የተለዩ
ገብረ መንፈስ ቅዱስ ታላቅ አባት
ምን አሏቸው ይሆን አንቺ ምስኪን እምነት
አይደል እንዴ ተዋሕዶ
ስጋቸውን የገበሩ
በእርኩሳን መናፍስት የተፈሩ
በእግዜር ጥበብ የከበሩ
ምን አሏቸው ቅዱሳንን ሰማዕታት ፃድቃናትን
የክርስቶስ ደቀመዝሙር ሃዋርያት
ትንቢት ፀሀፊ ነቢያት
ተዋህዶ ውዷ እናቴ ምን አሏቸው?
በዕቶን ውስጥ ማግደዋቸው
እንደ እንስሳ አረደዋቸው
በቁም ቆመው ቆዳቸውንገፈዋቸው
ላንቺ ቋሚ ልጆችሽን ምን አሏቸው
አይ ተዋህዶ....
በአንድ እግራቸው ሰባት ዓመት የፀለዩ
ባንቺ የፍቅር መግቦትሽ ከዓለም ላይ የተለዩ
የተክለሃይማኖት እናት አንቺ ቅድስት እምነት
አያማልዱም ሲላቸው ልጆችሽን
ዛሬ ምን ተሰማሽ ንገሪኝ በእውነት
የልጆችሽን ምልጃ ሊያስታርቅ ሊቃትት
መቻል ደጉ....
ስንቱን ቻልሽው እናታለም....
እሄ......
የእመብርሃን አስራት ኢትዮጵያ
የቅዱሳን የፃድቃን መፍለቂያ
አንቺስ ጋር ምን አሏቸው
መሠረቶችሽን ሲገፏቸው
ምን አልሻቸው ይሆን እንደው ዝም አልሻቸው
የመኖሬ ምስጢር
የመኖሬ ዘመን እምነቴ እሷናት ብለሽ ሳትነግሪያቸው
የቅዱሳንን ምልጃ የፃድቃንን ምልጃ ሳታሰተምሪያቸው
ለዚህ ይሆን አማላጅ አይደሉም ብለው የናቋቸው
ለነገሩ አይደለም
ስንቴ አስተማርሻቸው
በግልጽ አሳይተሽ አስቀምጠሽላቸው
ሰብከሻቸው ነበር ጊዜ ነጎደና በመናፍቅ እስር
የማማላዳቸው ያን ሁሉ ምስክር
ቀበሩት ከአፈር
እና ተዋህዶ ያንቺን ጓዳ የሚያውቁ
በፍቅርሽ ማነቆ የታነቁ
ቀስ በቀስ ወጡ እያለቁ
አሁንማ እናቴ
ባንቺ ጉያ እየኖሩ
አንቺንም እያሳፈሩ
ፈሉብሽ እንደ አሸን ቅዱሳንሽን እየካዱ
አያማልዱም ብለው ረግጠው እየሄዱ
ታዲያ ምን አሏቸው
ያንቺን ልጆች በቤታቸው
ዛሬስ ምን አሏቸው???
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
/መነባንብ/
✞**
እናታለም ተዋህዶ
ባንችነትሽ የሚኮራ
በስምሽ ስም የሚጠራ
ዛሬ ጠፋ የሚያበራ
ስለፍቅርሽ ቀልጠው ነደው
ስለ አምላካቸው ተማግደው
በሃይማኖት ፍቅር እጅጉን ተነክተው
ካንቺ ጉያ በኖሩ
እግሮችሽ ስር በተማሩ
ለምን/2/ ተዋህዶ ጠላቸው መንደሩ
ምን አሏቸው ደግሞ ቅዱሳን አበውን
አንቺን እናት እምነት ከዚህ ያበቁትን
ምን አሏቸው ደግሞ አበው ሊቃውንትን
አንድምታውን ፈተው ባመሰጠሩልን
ሚስጢርን መሰጥርው ለኛ ባኖሩልን
ብራና ወጥረው አምድ በፃፉልን
ውለታቸው ታዲያ ይህ ነው?
ስላደረጉልን የምንከፍለው
ጭራሽማ አምላክ ባከበራቸው
አክሊሉን በደፋላቸው
በሀሴት በተቀበላቸው
ልባችን ለምን አመፀ ለምንድን ማይቀበል
ተፈትኖ ያለውን የተፃፈላቸውን የህይወት ገድል
ለምንድን! የማናምን በምልጃቸው
እሱ እግዚአብሔር በሰጣቸው
ደግሞስ ምን አሏቸው?
እሄ......./በለቅሶ/
ሁሌም እውነት ነው
መልከ መልካም ሙሽራዋ
የፀናች በድንግልናዋ
ማን አለ እንደዝች እንደ ቅድስት እናት
ያልተረታ በነገስታት
አንገቷን ለሰይፍ የሠጠች
ክርስቶስን ብላ የኖረች
እኮስ ምን አሏት ይህችን እናት
የስጋ ፋላጎት ያልሠበራት።
ተዋህዶ እናት አለም
እንደድሮ ፀንቶ የሚኖር ልጆችሽ ፈርተዋል የሉም
የምልጃ ታላቅ ስራ
ለህዝቦቿ እያበራ
እየለመኑ ምህረት
ሲያስተዳድሩ አናብርቱ አናብስቱን
ከባህር ውስጥ የፀለዩ
በስራቸው የተለዩ
ገብረ መንፈስ ቅዱስ ታላቅ አባት
ምን አሏቸው ይሆን አንቺ ምስኪን እምነት
አይደል እንዴ ተዋሕዶ
ስጋቸውን የገበሩ
በእርኩሳን መናፍስት የተፈሩ
በእግዜር ጥበብ የከበሩ
ምን አሏቸው ቅዱሳንን ሰማዕታት ፃድቃናትን
የክርስቶስ ደቀመዝሙር ሃዋርያት
ትንቢት ፀሀፊ ነቢያት
ተዋህዶ ውዷ እናቴ ምን አሏቸው?
በዕቶን ውስጥ ማግደዋቸው
እንደ እንስሳ አረደዋቸው
በቁም ቆመው ቆዳቸውንገፈዋቸው
ላንቺ ቋሚ ልጆችሽን ምን አሏቸው
አይ ተዋህዶ....
በአንድ እግራቸው ሰባት ዓመት የፀለዩ
ባንቺ የፍቅር መግቦትሽ ከዓለም ላይ የተለዩ
የተክለሃይማኖት እናት አንቺ ቅድስት እምነት
አያማልዱም ሲላቸው ልጆችሽን
ዛሬ ምን ተሰማሽ ንገሪኝ በእውነት
የልጆችሽን ምልጃ ሊያስታርቅ ሊቃትት
መቻል ደጉ....
ስንቱን ቻልሽው እናታለም....
እሄ......
የእመብርሃን አስራት ኢትዮጵያ
የቅዱሳን የፃድቃን መፍለቂያ
አንቺስ ጋር ምን አሏቸው
መሠረቶችሽን ሲገፏቸው
ምን አልሻቸው ይሆን እንደው ዝም አልሻቸው
የመኖሬ ምስጢር
የመኖሬ ዘመን እምነቴ እሷናት ብለሽ ሳትነግሪያቸው
የቅዱሳንን ምልጃ የፃድቃንን ምልጃ ሳታሰተምሪያቸው
ለዚህ ይሆን አማላጅ አይደሉም ብለው የናቋቸው
ለነገሩ አይደለም
ስንቴ አስተማርሻቸው
በግልጽ አሳይተሽ አስቀምጠሽላቸው
ሰብከሻቸው ነበር ጊዜ ነጎደና በመናፍቅ እስር
የማማላዳቸው ያን ሁሉ ምስክር
ቀበሩት ከአፈር
እና ተዋህዶ ያንቺን ጓዳ የሚያውቁ
በፍቅርሽ ማነቆ የታነቁ
ቀስ በቀስ ወጡ እያለቁ
አሁንማ እናቴ
ባንቺ ጉያ እየኖሩ
አንቺንም እያሳፈሩ
ፈሉብሽ እንደ አሸን ቅዱሳንሽን እየካዱ
አያማልዱም ብለው ረግጠው እየሄዱ
ታዲያ ምን አሏቸው
ያንቺን ልጆች በቤታቸው
ዛሬስ ምን አሏቸው???
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
Forwarded from አንድ ቀለም ከከሡ ጋር
ለፃድቃን ከጻፍኳቸው የመዝሙር ግጥሞች በብዙ ቁጥር በመመዝገብ የአቡዬ ሥራዎች ግንባር ቀደሙ ነው። ወደ 10 አይጠጉም ብላችሁ ነው? ስላሳደጉኝ ነው መሰል ለአቡየ አደላለሁ። እሳቸው እሳቸውንም የጠየቅኋቸውን ሲሰሙ አይጣል ነው። በተለይ እሄዳለሁ ብዬ ባላሰብኩበት ሁኔታ መካነ መቃብራቸው ምድረ ከብድ ዕለተ እረፍታቸውን እዚያ እንዳከብር በአንዳች ተአምራዊ መንጀድ እንድሄድ ባደረጉበት 2015 እና 2016 የሚታይና የሚዳሰስ ተአምራትና ድንቅ በሕይወቴ ሲያደርጉ ነበር ብዬ እመሰክራለሁ። የፃድቁንም ሆነ ለሌሎች ቅዱሳን የተጻፉ ሙሉ ሥራዎቼን የ"እዩት" የመዝሙር ግጥም መድብል ቅጽ ሁለት የሆነው "ጉባኤያችን ማርያም" መጽሐፍ የፍልሰታ ሰሞን ሲወጣ አስነብባችኋለሁ። ለዕለተ ቀኑ ፣ ለበረከት ከዘማሪት ሕይወት ወልዴ ጋር አምና የሠራነውን ቆንጆ ሥራ ጋበዝኳችሁ።
ዝክረ ፃድቅ ለዓለም ይሄሉ!
https://youtu.be/YXEbsNVBKN0?si=w9is8WAEhdDH32eQ
ዝክረ ፃድቅ ለዓለም ይሄሉ!
https://youtu.be/YXEbsNVBKN0?si=w9is8WAEhdDH32eQ
YouTube
❤️ አዲስ ዝማሬ “ አቡነ ንብሎ “ ዘማሪት ሕይወት ወልዴ @-mahtot
❤️ አዲስ ዝማሬ “ አቡነ ንብሎ “ ዘማሪት ሕይወት ወልዴ @-mahtot
🔔#ዝማሬ_ተዋሕዶ
💠" ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር ስብሐተ ሐዲሰ ፣
እግዚአብሔርን በአዲስ ምስጋና አመስግኑት "
🗓 ግንቦት ፲፮ ቀን፣ ቀዳሚት
May 24, Saturday
⛪️ ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ፣ ሊቃውንተ ቤ/ክ፣ ካህናት፣ የአጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች መዘምራን እና መላው ምእመናን በሚገኙበት
📍Eissporthalle Frankfurt
Am Bornheimer Hang 4
60386 Frankfurt am Main
የጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባኤ
📌https://www.facebook.com/share/1FRmn3x9RW/
✅
https://vm.tiktok.com/ZNdJuM8V9/
🖌ዲዛይን፦ በሀገረ ስብከቱ ሚድያ
💠" ሰብሕዎ ለእግዚአብሔር ስብሐተ ሐዲሰ ፣
እግዚአብሔርን በአዲስ ምስጋና አመስግኑት "
🗓 ግንቦት ፲፮ ቀን፣ ቀዳሚት
May 24, Saturday
⛪️ ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ፣ ሊቃውንተ ቤ/ክ፣ ካህናት፣ የአጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች መዘምራን እና መላው ምእመናን በሚገኙበት
📍Eissporthalle Frankfurt
Am Bornheimer Hang 4
60386 Frankfurt am Main
የጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት
የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባኤ
📌https://www.facebook.com/share/1FRmn3x9RW/
✅
https://vm.tiktok.com/ZNdJuM8V9/
🖌ዲዛይን፦ በሀገረ ስብከቱ ሚድያ
መጻጕዕ
@Mgetem
(የዐቢይ ጾም አራተኛው ሳምንት ‹መጻጒዕ› ይባላል)
ልክ እንደ መጻጕዕ
እያየው ከሆንኩኝ ፥ የአለምን ነውር፤
በሥጋ ተመልካች ፥ በነፍስ ግን እውር፤
በአካል ከደጅህ ፥ ቆሜ ከሰው እኩል፤
እግረ ልቡናዌ ፥ ከሆነብኝ ስንኩል፤
በመውደቄ ብዛት ፥ ሀይሌ ከደከመ፤
ዘመናት ብቆጥርም ፥ ነፍሴ ከታመመ፤
ገዝተኸኛልና ፥ ከፍለህ የደም ዋጋ፤
መጥተህ እክታስነሳኝ ፥ ከኃጢአቴ አልጋ፤
ልክ እንደ መጻጕዕ ፥ ከፀበሉ ገንዳ፤
አፅናኝ እንዳሎጣ ፥ ከቤተ ሳይዳ ።
✍ አቤል ታደለ
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
@Mgetem
(የዐቢይ ጾም አራተኛው ሳምንት ‹መጻጒዕ› ይባላል)
ልክ እንደ መጻጕዕ
እያየው ከሆንኩኝ ፥ የአለምን ነውር፤
በሥጋ ተመልካች ፥ በነፍስ ግን እውር፤
በአካል ከደጅህ ፥ ቆሜ ከሰው እኩል፤
እግረ ልቡናዌ ፥ ከሆነብኝ ስንኩል፤
በመውደቄ ብዛት ፥ ሀይሌ ከደከመ፤
ዘመናት ብቆጥርም ፥ ነፍሴ ከታመመ፤
ገዝተኸኛልና ፥ ከፍለህ የደም ዋጋ፤
መጥተህ እክታስነሳኝ ፥ ከኃጢአቴ አልጋ፤
ልክ እንደ መጻጕዕ ፥ ከፀበሉ ገንዳ፤
አፅናኝ እንዳሎጣ ፥ ከቤተ ሳይዳ ።
✍ አቤል ታደለ
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem