Telegram Web Link
እመልክዐ መድኃኔ ዓለም

ሰላም ለቆምከ ዘዐቀምዎ በዐውድ፥
ተጋቢኦሙ ደርገ በቀራንዮ አይሁድ፥
መድኃኔ ዓለምክርስቶስ ኢተሃበኒ ለባዕድ፥
እንዘ እስእለከ አነ በልሣነ ሥጋ ክቡድ፥
እስመ አልቦ ዘከማከ በቋዒ ዘመድ።

ውርስ ትርጉም

ሰላም ለእግሮችህ ለቆሙ አደባባይ፥
በቀራንዮ ደብር በአይሁድ ለሥቃይ፥
መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ አትስጠኝ ለባዕድ፥
እያልኩኝ ለመንኩህ በአፌ ትሰማኝ ዘንድ፥
እንዳንተ የለምና የሚጠቅም ዘመድ።
___
www.tg-me.com/andkelem
www.tg-me.com/andkelem
አንቺ ካለሺኝ
@Mgetem

ማርያም ብዬ ፤ ማንን እፈራለሁ
አባ ጊዮርጊስ ፤ ሲቀኝ እንዳለው ።
እኔን ለመፍጨት፤
ምድርም ወፍጮ ፤ ሰማይ መጅ ቢሆን
አንቺ ካለሺኝ ፤ ከቶ ምን ልሆን።
የጥፋት ውሃን ፤ ዛሬም ለማውረድ
እንደ ኖኅ ዘመን ፤ ሰማይ ቢቀደድ
በቅድስናሽ መርከብ ተርፌ
እሻገራለሁ ሞትን አልፌ።
በሰዶምና በገሞራ ላይ
እንደ ዘነበው ፤ እሳት ከሰማይ
ቢዘንብብኝስ ፤ ምን እሆናለሁ
ባንቺ ልመና ፤ አምኜ ሳለሁ።

✍️ አቤል ታደለ


https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
https://www.tg-me.com/Mgetem
ለአስተያየት : @abeltadele
2025/07/05 06:30:57
Back to Top
HTML Embed Code: