Telegram Web Link
፨ያኔ ጥንት ነበረ፨
በዱር በገደሉ በዓለም ዙርያ ሁሉ
አምላክ ይወለዳል ብለው ተናገሩ
የነቢያት ተስፋ የነበለአም
አምላክ ተወለደ መድሃኒዓለም
ያኔ ጥንት ነበር...
ይወለዳል ሲሉ በመንፈስ ሲመሩ
አምላክ አዶናይን ለማየት ሲጥሩ
እንደው ኩርምት ብለው በተስፋ ሲኖሩ
ድንግል ትፀንሳለች ብለው ሲናገሩ
ቀናትን ሲቆጥሩ ሳምንታት ሲሠምሩ
ሳምንታት በግንድ ላይ ወራትን ሲሠሩ
ወራት ተቀናጅተው ዓመትን ሲሰጡ
ዓመታት ተቆጥረው ዘመናት ሲመጡ
እናያለን ሲሉ ለማየት ሳይበቁ
በመንፈስ ሲሰክሩ እንዲውል ሲሳለቁ
ያኔ ጥንት ነበር....
ያኔ ጥንት ነበር በመንፈስ መሰከሩ
አምላክ ይወለዳል ብሎ መዘከሩ
በርቀት ተሳልሞ ለዓለም ማብሰሩ
ያኔ ጥንት ነበር የመውደቅ ሚስጥሩ
ሃጢአትን መፀነሱ የመውደቅ ሚስጥሩ
ሃጢያትን መፀነሱ ሞትንም መውለዱ
ከገነት ተባሮ እንዲያው መዋረዱ
ፀጋውን ተገፎ በለስ ማገልደሙ
ያኔ ጥንት ነበር...
አዳምን ሊጎበኝ አምላክ መጣራቱ
አዳም አዳም አዳም ብሎ መፈለጉ
አትብሉ ያልኩህን በላህው ማለቱ
አዳምን በመፍጠር እንዲያው መፀፀቱ
አዳምም አዘነ በሔዋን ፈረደ
ሔዋንም አዘነች እባቡ ነው አለች
እባብ ተረገመች አፈራ ባይሆናት
አዳም ተባረረ ሄዋን አለቀሰች
ምድር ተረገመች እሾህ አበቀለች
አቤት ያኔ ነበር ያኔ ጥንት ነበረ
አዳም መበደሉ ሰዎችን ለውድቀት ለሞት መደረጉ
ያኔ ነበር ፅንሱ ሰዎችን ለሽንፈት ለሞት መፈለጉ
ዛሬ ግን ዛሬ ያ የጥንቱ ቀረና
እራሱን አዋርዶ አዳም ከበረና
ሲወለድ በቤተልሔም በነብዩ ተፅፎአልና
አምላክ ተወለደ በከብቶች መና
ታሪኩ ሲተርክ የሰማህ ወንድሜ
ራስክን መርምረው ና ይልሃል ዛሬ
አቤት ያኔ ጥንት ነበር....
ያኔ ጥንት ነበር የአዳም ውድቀቱ
ዛሬ በክርስቶስ ሕይወትን ማግኘቱ
ዛሬስ እኛ ወገን
የያኔ የጥንቱ ትተን ለንስሐ ቀርበን
ስጋውንም በልተን ደሙንም ጠጥተን
በድያለሁ ብለን ከፊቱ ላይ ወድቀን
መመለስ ይሻላል ክርስቶስን ብለን
መመለስ ያሻል ኪዳነ ምህረትን ብለን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳቹ አደረሰን!
መልካም ጥምቅት
መልካም በዓል

@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍7😢1
           #አያምርበት


#ፍቅርህ_የቀመሰ ከማእድህ በልቶ
#ምህረት_የጠገበ ይቅርታን ጠጥቶ
#ምንስ ያምርበታል ደምህን ረግጦ ?
      በምክርህ ተቃኝቶ ተሰርቶ ያደገ
      በመንፈስህ ህይወትን ስቦ እየማገ
      መከራ ቢያይል ተስፋ አለው ለነገ
#በእጅህ_ተዳሶ በረከት ያገኘ
#በፍቅርህ_ጥልቅ ባህር በደስታ የዋኘ
#ምኑ_ማርኮት ይሆን ምድርን የተመኘ ?
      በትእግስትህ በር ወጥቶ እየገባ
     ዳዴን ከአንተ ተምሮ ከአንተው የጠባ
      ግና ዛሬ አድጎ ከወጥመድ ሊገባ
#በሰላምህ ምርኩዝ በደስታህ ዘይት
#ነፍሱ_የመገብሃት ቃልህ ያጠገብሀት
#ከአንተ_ሌላማ ጌጥም አያምርባት
      ድቅድቁን ጨለማ ረግጦ የመጣ
      ይቅርታን ተምሮ ለቂም ቦታ ያጣ
      እንዴት ያምርበታል ከቤትህ ቢወጣ ?
#ጠረንህን_ለምዶ ግሩሙን መዓዛ
#ምንጩ_ቀራኒዮ የህይወቱ ለዛ
#የነበረው_ፍሬ ስለምን ይጠንዛ ?
   መኖሪያ አጥሩ መሸሸግያ ቅጥሩ
   ለሆንህለት ጥላ እንዲፀና ስሩ
 #አያምርበት_ቢርቅ ቢስት ከመስመሩ 🙏
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍4🥰3
           #ወይ_ማወቅ_ደጉ !


#በባህር_በጥልቁ በሰማይ ተማክሮ
#ሊወጋው_ምስኪኑን ሃይል አስተባብሮ
#ሄደ ከምስኪኑ ሰፈር
ሊያጠፋው መታሰቢያው ሳይቀር
ዉጣ ይለይልህ ኪዳን አለኝ ማለት
ፀሎቱ መዝሙሩ አይደለም ከማጀት
ይህን ሁሉ ፉከራ የሰማው ምስኪን ሰው
ወዬው ጠፋሁ ብሎ ፍርሃት ብርክ ያዘው
የሞት ሞቱን ጨክኖ ብቅ ቢልባቸው
#የያዙት_መሳሪያ ወደቀ ከጃቸው
#እግሬ_አውጭኝ እግሬ አውጭኝ
እያሉ በሽቅድምድም
ሄዱ ከመጡበት አለም
#ይህ ሁሉ የሆነው..ምክንያቱ ምንድነው?
#ጋሻ ጦር አልያዝኩኝ....ይሄው ባዶየን ነኝ
#ምን አይተው ሮጡ......ሊገሉኝ የመጡ
እያለ ምስኪኑ ግራ እየተጋባ
ግድግዳው ላይ ካለው መስታወት ተጠጋ
ድንገት ቀና ብሎ ፊቱን ቢመለከት
#ለካስ_የኢየሱስ ደም በግንባሩ አለበት
#አሃ ! ደሙን አይተው ነው የተመለሱት
ወይ ማወቅ ደጉ!
#ለካስ_መፍትሄው ግንባርን ማሳየት
#ያኔ_ይመለሳል ሰይጣን ከመጣበት ። 🙏
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍41🤬1
፨እናምናለን በምስጢረ ጥምቀቱ፨
በመጋቤ ምስጢርነቱ
በመንግሥተ ሰማይ በርነቱ
ሰው ካልተወለደ ከውኃና ከመንፈስ
ሕይወት እንደሌለው ርስት እንደማይወርስ
ያመነ የተጠመቀ ይድናል
በጥምቀቱ ልጅነት ያገኛል
ባያምን ባይጠመቅ ከልጅነቱ ይወጣል
ኢጥዮጵያዊው ባኮስ በሐዋርያው በፊሊጶስ
ከነቤተሰቦቹ እስጢፋኖስ
ቅዱስ ጳውሎስ ከደማስቆ መልስ
በጥምቀት ተወልደዋል ከመንፈስ ቅዱስ
ሔዋን በሰማንያ አዳም በአርባ ቀኑ
ገነት እንደገቡ ልጅነት እንዳገኙ
ሴቶች በሰማንያ ወንዶች ደግሞ በአርባ
ልጅነት እንዲያገኝ ተጠምቆ እንዲገባ
እናምናለን በእውነት
ያለጥርጥር በእምነት፡፡

@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
2👍2🤬1


ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ...!!!
በዓሉ የሰላም የጤና የንስሐ እንዲሆንላችሁ ምኞታችን ነው....!
*:ጊዜ ምን በደለ;*
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
እውነትን ደብቀን ሀሰትን አንግሰን
አባቶች እያሉ ልጆች እያስተማርን
አርብ እሮቡን ሳናውቅ ሁልጊዜ አየበላን
ቤቱ መመላለስ ጭራሹን አቁመን
*
*
የእግዛብሔርን መቅደስ በሀጢያት ስንሞላ
እንደሰዶም ሆነን ህግን ስንጠላ
አህዛቦች ሲቀድሙን እኛ ቁመን ሇላ
ፀጋችን እያለ እሱን ሳናውቅበት ስንፈልግ ሌላ
*
*
የምንጓዝበት መንገዱ ረዝሞብን ቤቱ መሄድ ሲቀር
ሀይማኖት በገንዘብ እንደስም ሲቀየር
መፅሀፍትን ሳናነብ አባቶች እግር ስር ቁጭ ብለን ሳንማር
ቅዱስ ሁኑ ተብለን ምርጫችን ሲቀየር
*
*
ውበት ከአምላክ በላይ እኛ ስንሰራ
ቀለም እያማረጥን አለምን ስንመርጥ አምላክን ሳንፈራ
ማህሌት አዳር ትተን ስንመርጥ ጭፈራ
ሀብታችን ሀጢያት ገዝቶ ሲያስመስል ተራራ
*
*
ልብሳችንን ጥለን እርቃንን ስንመርጥ
በማናውቀው አለም ከላይ ሁነን ሳለ ወደ ታች ሰንዘቅጥ
አማርጠን ስንበላ ከደረቅ እስከ ቁርጥ
በደካማው ስጋ ለነፍሳችን ስንቅ ጭራሽ ሳናስቀምጥ
*
*
አወቀን ብለን ሳናውቅ በትቢት እየተጓዝን
ምርጫችን ከኛ በልጦ እኛኑ ሲመክረን
አልመለስ ስንል አምላክ እላይ ሁኖ በትዝብት ሲያዩን
ፍርጃ እላይ ቆመን ጌታ ሊመዝነን
እኛ ከሱ በልጠን ጭራሽ ፈራጅ ሁነን
*
*
ክፋትን አንግሰን ጠፋቶብን በጎነት
የውጩን አድንቀን ስንጓዝ በስህተት
ምርጫችን ተምታትቶ ስናማርጥ ውሸት
ሚስጥሩን ሳናውቀው ለመፋረድ ስንዋትት
*
*
በል በትርርህን አፅና የሚባል ሲጠፋ
መገንዘብ ሲያቅተን ምንድነን እንደሆነ የወደፊት ተስፋ
በማይጠቅም ህይወት ስንማስን ስንለፋ
ማወቁ ሲጠፋን ሁሉም ሟች መሆኑን ጠብቆ ወረፋ
*
መቶ ለማይሞላው ለዚህ አጭር እድሜችን
ምን ለማይጠቅመው እንጨነቃለን ለአፈሩ ስጋችን
አድሜአችን ሲቀንስ ከግባራችን ሲለቅ ፀጉራችን
መመለስ ሲያቅተን ዛሬ ነገ እያልን ሲመርሽ ቀናችን
*
አባቶችን ሰምተን ታሪክ ካልጠበቅን
ዘመናዊነት ሚስጥሩ ካልገባን
በአምና ተምረን ዘንድሮ ካልነቃን
ጊዜ ምን በደለ በሱ የፈረድን
*
ጊዜማ ሂደት ነው ድሮም የነበረ
እራሱን ሳይለውጥ ይሆን ሁሉ ዘመን በክብር የኖረ
ታዲያ ምን አጠፋ በሰው ተደፈረ
ንገረኝ ወንድሜ(ቴ) ጊዜ ምን በደለ":;"""''!?
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍7🥰31👏1
የሚያጠፋት የለም።


ማዕበሉ ቢነሳ ቢነፍስ ነፋሱ
እሳት ቢንቀለቀል ቢጥጎለጎል ጢሱ
ሰይፎች ቢመዘዙ አበው ቢታረዱ
ወጣት አዛውንቱ እስር ቤት ቢወርዱ
ሰባኪው ዘማሪው ከመድረክ ቢባረር
መነኩሴው ካህኑ ወሕኒ ቢወረወር
ያንሰራራል እንጅ የስም አጠራሯ
ገኖ ያድራል እንጅ ተጽፎ ተአምሯ
የሴረኞች ሴራ እየተነገረ
መዝሙር በስማቼው እየተዘመረ
የሚያፈርሷት ፈርሰው
የሚያጠፏት ጠፈተው
የሚያነዷት ነደው
ጎስቁለው ተዋርደው
እናያለን እንጅ ኑራ ለዘለዓለም
ቤተክርስቲያንን የሚያጠፋት የለም።
አብ እሳት ወልድ እሳት ተብሎ ተቀድሶ
መንፈስ ቅዱስ እሳት ተብሎ ተወድሶ
ጠላት ቢያቃጥላት በእሳት ለኩሶ
እሳት ነው አምላኳ ያቃጥላል መልሶ
አወ እሳት ነው መንፈስ ቅዱስ
እሳት ነው ጰራቅሊጦስ
አሳት በላዒ ለአማፂያን
ወአቃጣይ ለከሀዲያን
ስሙን ለሚክዱ
መቅደሱን ለሚያዋርዱ
እንደቆሬ ካሕናት
የሚያቃጥል ሕያው እሳት
እንደ አዛርያስ ለቀነጣ
ግምባርን በለምጽ የሚቀጣ
በምድሩ እሳት በደካማው
ጥፋት ጥፋት በሚሰማው
የማይጠፋ እሳት ላያጠፉ
አሕዛብ በከንቱ ቢለፉ
ከንቱ ልፋት ከንቱ ድካም
ፍላጎትን አያሳካም
ዱለት ቢደወለት ቢፈጭ ቢቦካ
በግፈኞች ሚዛን ግፋችን ቢለካ
ጠላት ሰይፍ አንግቦ ቢሸልል ቢያሽካካ
ቤተክርስቲያን ክብሯ ሳይነካ
ትኖራለች እንጅ ጸንታ ለዘለዓለም
የክርስቶስን ቤት የሚያፈርሳት የለም።
አሕዛብ መናፍቃን በርሷ ላይ ቢነሱ
ሰይፍ ተሸክመው እሳት ቢለኩሱ
በሔሮድስ ቁጣ በክብሯ ቢዝቱ
አዋጅ አስነግረው በጋራ ቢዘምቱ
ከክርስቶስ ጋር ነው ፍልሚያው ጦርነቱ።
ያኔ ሰይፍ ያነሱ በሰይፍ ይጠፋሉ
ጉድጓድ የቆፈሩም በጉድጓድ ያልቃሉ
አሕዛብ መናፍቃን ይህነን አውቃችሁ
የሰይፍ የመሣሪያ ወጩን ቀንሳችሁ
ልብ እንድትገዙበት ልቦና ይስጣችሁ
ትኖራለች እንጅ ፀንታ ለዘለዓለም
ቤተክርስቲያን የሚያጠፋት የለም።
አንተ ግን አደራ
አንተ ግን አደራ በአፄ ካሌብ ገድል
በአብርሃና አጽብሃ በሰላማ መስቀል
በአቡነ አረጋዊ በክርስቶስ ሰምራ
በተክለሃይማኖት በነላሊበላ
በብርብር ማርያም በአክሱም በዝቋላ
በኤሊ ገብርኤል በደብረ ሊባኖስ
በደብር ማርያም በመስቀለ ኢየሱስ
በመስቀሉ ግማድ በግሸን ማርያም
በአቡነ ዐሮን በአሰቦት ገዳም
ምሥራቁ ምእራቡ ሰሜኑ ደቡቡ
ሁሉም በእምነቱ ሁሉም በማተቡ
ባንጃበበው ስቃይ መከራ ሰቁቃ
በቼልታ እንዳታልፍ ክርስቲያን ሲጠቃ
የተኛህ ተነሳ ያንቀላፋህ ንቃ
አንተ ለዘር ለጎጥ ስትገነጣጠል
ለወንዝ ለተራራ ልብህ ሲንጠለጠል
የወለጋን መቅደስ ለፓስተር እንትና
አርባምንጭ ጎፋን ለመንፈስ ትወና
የዝቋላን ገዳም ለኢሉማንቱ
ቅዱስ ላሊበላን ለ666ቱ
ጎንደርን ለጅዳ አክሱምን ለመካ
አማጭ እንደላኩ አልሰማህም ለካ
አንተ ግን አደራ ክርስቲያን ወገኔ
የደም እዳ አለብህ ከፈሰሰው ያኔ
በዮዲት ጭፍጨፋ በግራኝ ወረራ
ያጥንትና የደም አለብህ አደራ
ማነምን ሳታፍር ማነምን ሳትፈራ
መቅደስህን ጠብቅ ካባቶችህ ጋራ
አንተ ግን አደራ
አገልጋይ ካሕኑ
አማኙ ምእመኑ
የአቋቋም ምሁሩ
በላዜማ ባለመዝሙሩ
የቅኔው ዘራፊ
የድጓው ፀሐፊ
የዝማሬው የቅዳሴው
የትርጓሜው የውዳሴው
፬ ዓይናው ልበ ሰፊው
አስተዳደሩ ሀላፊው
መነኮሱ ቆሞሱ
ኤጲስ ቆጶሱ ጳጳሱ
የቴውሎጅው ተመራቂ
የምሥጢራቱ አርቃቂ
ሰንበት ተማሪው ማሕበራቱ
ማሕበረ ቅዱሳን ባለሕጉ
ደጆችሽ አይዘጉ
ኦረቶዶክሳዊ በሙሉ
ተማማለህ በመስቀሉ
ጠብቅ ያንተን አደራ
እንዳትሽሽ አንዳትፈራ
እንደበግ ጨው እያላሱ
እያሳሳቁ እያወደሱ
እያጠጋጉን ወደነሱ
ደሮን በጥሬ እንዲጥሉ
ሊበሉን እያታለሉ
ማዕዳቼውን ሊያቀርቡ
በደማችን ከታጠቡ
ይበቃል ከዚህ በላይ
ማን አታላይ ማን ተታላይ
ማንስ አግላይ ማን ተገላይ
ማን ሆነና ባለርስቱ
የሀገር መሠረቱ
የሀገር ፍቅርን እየመገብነ
እኛው አቅፈን ባሳደግነ
ከአውሮፖውያን ተልኮ
ከዓረብ ልጅ ልጁን ልኮ
እኛን እኛን ከገፋ
ድብቅ ሴራውን ካስፋፋ
አንተ ግን አደራ
እንዳትወሰልት እንዳትፈራ
ክርስቶስ የወለደህ
እስከሞት የወደደህ
በፍቅሩ ያሳደገህ
አንተንማ ምን አስፈራህ
ያምላክህ ስራ የተጻፈ
ሞትን በሞት ያሸነፈ
ሰይፍ አትሻ የገዘፈ
ሰይፍ አለህ የረቀቀ
ጎልያድን ያወደቀ
ሰይፍ አለን ባንገታችን
ማተባችን መስቀላችን
ሰይፍ አለን በእጃችን
ዳዊታችን ድርሳናችን
እንጠብቅ አደራችችን።
ጸልዩ በእንቲያነ ስለኛ ጸልዩ ።
አቡነ ናትናኤል አቡነ ፊሊጶስ
አቡነ አረጋዊ አባ መርሓ ክርስቶስ
አባ መልከ ጼዴቅ ወአባ ሰላማ
አቡነ አረጋዊ አቡነ ገሪማ
በአንድነት ሁናችሁ በገነት ከተማ
ስለኛ ጸልዩ ድምፃችሁ ይሰማ፡
ኦርቶዶክሳውያን እንደበግ ታርደዋል
አብያተ ክርስቲያን በእሳት ተቃጥለዋል
ቅዱሳት ንዋያት እንደጧፍ ነደዋል
ክርስቲያኖች ሁሉ ለመኖር ሰግተዋል
በግፈኞች ሰይፍ ተከበው ቁመዋል
ሱማሌ ጅግጅጋ ጅማና ሲዳማ
መለውና ጎፋ ያገሬ ከተማ
ኦርቶዶክሳውያን እየተሰደዱ
ካህናት ሊቃውንት እየተዋረዱ
ቅዱሳን ቦታዎች እየተነጠቁ
ምእመናን ካህናት እየተጨነቁ
እጅግ ስለበዛ ግፉና ስቃዩ
አሳስቡን ከጌታ ስለኛ ጸልዩ
➴ ከመምህር ኤፍሬም ተስፋ

@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍216🥰2
፨ጊዜዬን ባርክልኝ፨
በዝናብ አብቅለህ በፀሐይ አብስለህ
የምትመግብ ጌታ ሁሉን አዘጋጅተህ
ነጻነቱን ሰጥተህ ጥበቡን አድለህ
እዚህ ላደረስከኝ ምስጋና ይድረስህ
ሁሌም ጠብቀኸኝ በምሕረት ጥላ
ጊዜን ባርክልኝ ሰርቼ እንድበላ
ከፍጥረታት ሁሉ አልቀህ ፈጥረኸኝ
የጸጋን ገዢነት በፍቅርህ አድለኸኝ
ከቤትህ እንድኖር ርስትአውረሰኸኝ
ለዚህ ያበቃህኝ ከቶ እኔ ማነኝ
ያለኝ ምስጋና ነው አምላክ ክበርልኝ
እኔ ስበድልህ አንተ ስትምረኝ
በምሕረት ታግለህ ፈጥነህ ሳታጠፋኝ
ንስሐ እንድገባ ጊዜን ባርክልኝ።
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍51
የፈጣሪ ችሎት
፨፨፨፨፨፨፨፨፨

አባ ተቀምጠው ከሾላ
ለሊት አድርሰው ምህላ
ሲጠባበቁ ፅድቂቱን
ሲኖሩ ሲኖሩ አንድ ቀን
ያባን ዛፍ ላይ መኖር
ሽፍቶቹ ተረድተው
ጠጋ አሉ ከሥፍራቸው
አባም በጥርጥር
ዓይናቸው ሲማትር
አባ አባታችን
አንድ ገዜ ይስሙን
የቃየል መንፈስ እየተከተለን
አንዳች ሳንበደል
ብዙ ነፋስ አጠፋን
ግብራችንን ትተን
ንስሐ ሰጥተውን
ከራሶት እንድንሆን
ፍቃዶት ይሁነን!
አባም በተራቸው
የፈጣሪ ጥሪ እየገረማቸው
እንደዚህ አሏቸው
እኔ ካለሁበት
መራሩ ምግቤ ነው
የአራዊቱ ዜማ
ጣዕመ ዜማዬ ነው
እንደኔ ለመሆን
ፍፁም ከሻታችሁ
የጠራችሁ አምላክ
ፅናቱን ይስጣችሁ።
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍6
#ምንም_አይምሰልህ
የምትሰራው ሥራ ሰውን ካልበደለ፤
ክፋትና ተንኮል በልብህ ከሌለ፤
ጠንቅቀህ ከፈጸምክ ማድረግ ያለብህን፤
ለማንም ሳታድር ካመንክ አምላክህን፤
ላንተ ጥቅም ብለህ ካልጎዳህ ሌላውን ፤
ይቅርታ ከጠየቅህ አምነህ ጥፋትህን፤
የምታውቀው ታሪክ የምታውቀው ነገር፤
እንዳልሆነ ሁሉ ሲወራ ሲነገር ፤
የለብህም እና ዝም ብሎ መስማት፤
ቀስ ብለህ ብትሞክር እርማት ለመስጠት፤
ከኛ ሌላ አዋቂ ፍጹም የለም ባዮች፤
የወሬ አንበሳ የተግባር አንካሶች ፤
የነገር ሱሰኛ የወሬ ጥመኞች፤
ምንም እንደማታውቅ አድርገው ቢቆጥሩህ ፤
ዕውቀቱ ከአንተ ጋር እና ምን ቸገረህ፤
አምላክ ካንተ ጋር ነው ምንም አይምሰልህ።
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_bot
3👍3
#ነበርኩ_መች_ያድናል
@Mgetem

ሀጢያትን ስትሰራ አምላክን እረስተህ
ቅዱሱን ሰውነት በሀጢያት አርክሰህ
ትእዛዝን ሳትፈጽም መልካምን ሳትሰራ
ዘይት ሳታዘጋጅ መብራትህ ሳይበራ
በተጠራህ ጊዜ መላከሞት ሲመጣ
ለማያልፈው አለም ሲወጣልህ እጣ
ለሚዛን ስትቀርብ አገልጋይ ነበርኩኝ እያልክ መናገሩ
መዝሙር ዘምሬያለው ሄጃለው ከበሩ
ብሎ መከራከር ያኔ መች ይጠቅማል
ይዞ መገኘት ነው ነበርኩ መች ያድናል!!!

@Mgetem
@Mgrtem
@Mgetem_bot
👍1
የፈጣሪ ችሎት
፨፨፨፨፨፨፨፨፨

አባ ተቀምጠው ከሾላ
ለሊት አድርሰው ምህላ
ሲጠባበቁ ፅድቂቱን
ሲኖሩ ሲኖሩ አንድ ቀን
ያባን ዛፍ ላይ መኖር
ሽፍቶቹ ተረድተው
ጠጋ አሉ ከሥፍራቸው
አባም በጥርጥር
ዓይናቸው ሲማትር
አባ አባታችን
አንድ ገዜ ይስሙን
የቃየል መንፈስ እየተከተለን
አንዳች ሳንበደል
ብዙ ነፋስ አጠፋን
ግብራችንን ትተን
ንስሐ ሰጥተውን
ከራሶት እንድንሆን
ፍቃዶት ይሁነን!
አባም በተራቸው
የፈጣሪ ጥሪ እየገረማቸው
እንደዚህ አሏቸው
እኔ ካለሁበት
መራሩ ምግቤ ነው
የአራዊቱ ዜማ
ጣዕመ ዜማዬ ነው
እንደኔ ለመሆን
ፍፁም ከሻታችሁ
የጠራችሁ አምላክ
ፅናቱን ይስጣችሁ።
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_bot
👍6
በቃሉ ታክሜ
፨፨፨፨፨፨፨

ልጄ ሆይ ወዴትነሽ የት አለሽ እያለ
የወደቅኩበትን እየተከተለ
ሊያነሳኝ ሲመጣ ድምፁን ከፍ አድርጎ
ሀጢያቴን ረስቶ ከጥልቁ ሸሽጎ
ኮቴውን ሰማሁት ሲመጣ ወደኔ
ከእንግዲህ ሊበቃኝ የሐጥያት ኩነኔ
ጣቢታ በማለት ልጁን ይጠራኛል
ከያዘኝ የቁም ሞት ይቀሰቅሰኛል፡፡
ከዛም እነቃለሁ አልተኛም ደግሜ
ተነሽ ብሎ ሲለኝ በቃሉ ታክሜ።

@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍122
https://youtu.be/WlfhrFA1K2w

እህታችን ስብስክራይብ ሼር እርጉላት በፍቅር ስም

ፍቅር ሁሉም አሽናፍ ነውና
👍1
፨ትንቢተ ዮናስ፨
ክፍል ፩
፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በሕዝቡ መካከል አመጽ ስለ ጸና
በጣም ተቆጥቼ አዝኛለሁ እና
ይህንን ለነነዌ ንገራት በአዋጅ
አለና ለዮናስ ለአሚታይ ልጅ
እግዚአብሔር አዘዘው እንዲሄድ በቶሎ
ዮናስ እቢተኛው አሰበ ኮብልሎ
ከአምላኩ ተደብቆ አምልሎ ሊጠፋ
ወደ ተረሲስ ሲጓዝ የሄደ ወደ ያፋ።
ዋጋ ክፍልና ከመርከብ ተሳፍሮ
እያጉረመረመ ባሕሩን ተሻግሮ
ዮናስ ተደብቆ ሲሄድ በግስገሳ
ከእግዚአብሔር ተልዕኮ ማዕበል ተነሳ
ታላቅ ሞገድ ሆነ ባሕሩ ተቆጣ
መርከበኞች ፈሩ ታላቅ ሽብር መጣ
መርከቡ እንዲቃለል እናድርግ እያሉ
አንስተው ብዙ ዕቃ ወደ ባሕር ጣሉ
ባህሩም ባሰበት በጣም ተናወጠ
መረከቡ መሰለ የተገለበጠ
ሰው ሁሉ ተነሳ ጸሎት ለማድረስ
ይኽ ሁሉ ሲሆን ተኝቷል ዮናስ
ወደ ዮናስ ሄዶ የመርከቡ አለቃ
ቀሰቀሰው እና ከእንቅልፉ ሲነቃ
እግዜር እንዲያድነን ከዚህ ክፉ ጥፋት
ተነስ ጸልይ አለው ይብቃህ ማንቀላፋት
በመርከቡ ውስጥ ያሉ ሰዎች ተሰብስበው
ተመካከሩ እና ቢናገሩ አስበው
አለው ኃጢአት ሰርቶ ከእኛ ጋር የመጣ
ለይተን ለማወቅ እንጣጣል ዕጣ
አለዚያ አንድንም ስለተባባሉ
ተሰባሰቡና ዕጣ ቢጣጣሉ
እውነትም እንዳሉት አጥፊው ሰው ታወቀ
በእንቢተኛው ነብይ በዮናስ ወደቀ
በዮናስ ተረዳና እጁ እንደ ተያዘ
ያጠፋውን ጥፋት ገልጦ ተናዘዘ
ምነው ባትመጣ ተጣልተክ ከጌታ
እየው መርከባችን እንደሚንገላታ
ቁጣውን እንዲታገስ ለማግኘት ጸጥታ
በል አንተው ፍረደን ምን ይበጃል ቢሉ
ዮናስ መለሰና እዚህ ያለ ሁሉ
ስለምን ይጠፋል በእኔ የተነሳ
ወደ ባሕር ጣሉኝ አለብኝ አበሳ
ተመልከቱ እንሆ ስራውን ዐወቀ
ጥፋቱን ገለጠ ይኽው መች ደበቀ
እሱ ከፈረደ መልሶ በራሱ
ምን እናድርግ ብለው ሊጥሉት ተነሱ
ከደሙ አንጻን ሲሉ ለእግዜር አመልክተው
ወደ ባሕር ጣሉት ዮናስን አውጥተው
በዮናስ ላይ ኖር የመጣው ይህ ጥፋት
ባሕሩ ጸጥ አለ ልክ በዛው ሰዓት


ይቀጥላል.....

@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍6
ትንቢተ ዮናስ
ክፍል ፪
ዮናስም ተውጦ በእግዚአብሔር ፍቃድ
ሶስት ቀን ሶስት ለሊት ሊያድር በዓሣ ሆድ
ተቀይመህ ኖረህ ከላይ ብትቆጣ
እንዲህ ያለ መአት በራሴ ላይ መጣ
የባሕሩ ሞገድ እኔን አዋከበኝ
ውኃና ጨለማ ሲኦልም ከበበኝ
እያለ በአሳ ሆድ ዮናስ ሲቀመጥ
አምላኩን ለመነው በመለማመጥ
የታዛዥነትም ጠባይ እያሳየ
አዝኖ ተጸጽቶ ከልቡ ጸለየ
ምንጊዜም ቢቆጣ ነውና መሓሪ
ፊቱን መልሶለት ታረቀው ፈጣሪ
ዓሣውም ዮናስን ውጦ ሳያስቀረው
ከባሕር ተፋና መሬት ወረወረው

ይቀጥላል.....

@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍5👎1
ትንቢተ ዮናስ
ምዕራፍ፫
ይህንን የኔን ቃል ስማና በቶሎ
ሄደህ ለነነዌ እንድትነግራት ብሎ
ደገመና እግዚአብሔር ዮናስን አዘዘ
ነነዌ ሊገባ ዮናስም ተጓዘ
ድምጹን ከፍ አድርጎ ነቢዩ ዮናስም
ከዛሬ ጀምሮ አርባ ቀን ድረስ
ነነዌ ጠፊነች ከስር ተገልብጣ
አለና ለፈፈ የእግዚአብሔርን ቁጣ
ሳያንገራግሩ ሁሉም ቢለምኑ
የነነዌ ሰዎች ተጨንቀው አዘኑ
ከትልቅ ጀምሮ ሕፃኑ ድረስ
ሕይወቱ የቆመች በሥጋ በነፍስ
ሰውም ሆነ እንስሳ ይቀበል ንስሐ
ፍጡር ሁሉ ይጸልይ ይጹም ከእህል ውሃ
ሁሉም ከልብ አዝኖ ማቅ እየለበሰ
ከክፉ ወደ ደግ እየተመለሰ
መቼም ወሰን የለው የእግዚአብሔር ምሕረቱ
ይጸልይ አለና ይለምን በብርቱ
ንጉሡ አሳወጀ ከነ መኳንንቱ
የነነዌ ሰዎች በእውነት ከልቦና
መፀፀታቸውን እግዚአብሔር አየና
ፍጡር ቢለምነው እምባ እያፈሰሰ
ምሕረቱን አውርዶ መአቱን መለሰ።
ይቀጥላል...

@Mgetem

@Mgetem
👍11
#_የፍቅር_ቀን#

እኔ የማከብረው ሁሌ ምዘክረው
አለኝ የፍቅር ቀን አለኝ የማረሳው
ልቤን አሸንፎት በእንባ የማወሳው
የኔ ውድ አፍቃሪ በቀጠሮው ሰአት በቀጠሮው ቦታ
ሳያረፍድ ተገኝቶ በዛች በከፍታ
በደሙ ቀለበት ገብቶልኝ ቃልኪዳን
በእውነተኛ ፍቅር ለእውነተኛ መዳን
ልሙትልሽ ብሎ በፅኑ መሀላ
መውደዱን ገልጦልኝ እንድኖር በተድላ
በዛች በለተ አርብ በፍቅር ቀናችን
ፍቅሩን ገልጦልኛል
ቀይ አበባ ሳይሆን ቀይ ደም ሰቶኛል
ስለዚህ ያቺ ናት እርሷ ናት
የኛ ቀን የኔና የውዴ
ለአለም የታየበት በርሱ መወደዴ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!


፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ክብርና ምስጋና ይግባው በእለተ አርብ ለተሰቀለው

@Mgetem
👍9
አንተ ሰው! ወንበዴ፣ ሌባ፣ ዘማዊም ፡ ብታይ ፡ አትፍረድበት! እንደ ፡ ፈያታዊ ፡ ዘየማን ፡ እኔን ፡ ቀድሞ ፡ መንግሥተ ፡ ሰማያት ፡ ይገባ ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡ ምን ፡ አውቃለሁ ፡ ብለህ ፡ እለፍ ፡ እንጂ። “ትዳር አለኝ፤ ልጆችን አሳድጋለሁ፤ የቤት አባወራ ስለኾንኩኝ ይኽንን ማድረግ አልችልም” አትበሉኝ፡፡ ከእናንተ የሚፈለገው ፈቃዳችኁ ብቻ ነውና፡፡ ዕድሜም ቢኾን፣ ባለጸግነትም ቢኾን፣ ማጣትም ቢኾን ሌላም ቢኾን ይኽን ኹሉ ከማድረግ አይከለክላችሁምና፡፡ ምክንያቱም ሽማግሌዎችም፣ ወጣቶችም፣ ሚስቶችም፣ ሕፃናት አሳዳጊዎችም፣ ዕደ ጥበቦኞችም፣ ወታደሮችም ይኽን ኹሉ ፈጽመውታልና፡፡ ዳንኤል ወጣት ነበር፤ ሠለስቱ ደቂቅ ሕፃናት ነበሩ፤ ዮሴፍ ባርያ ነበር፤ ሉቃስ ሐኪም ነበር፤ ሊድያም ሐር ሻጭ ነጋዴ ነበረች፤ ጳውሎስንና ሲላስን በወኅኒ ሲጠብቅ የነበረውም ፖሊስ ነበር፤ ቆርነሌዎስ ደግሞ ዐሥራ አለቃ ነበር፤ ጢሞቴዎስ በሽተኛ ነበር… ነገር ግን ይኽን ከማድረግ የከለከላቸው አንዳችም ምክንያት የለም፡፡ እነዚኽ ኹሉ እንደ እኛ ሴቶች፣ እንደ እኛ ወጣቶች፣ እንደ እኛ ሽማግሎች፣ እንደ እኛ ነጋዴዎች፣ እንደ እኛ አሠሪዎች፣ እንደ እኛ ሠራተኞች፣ እንደ እኛ ወታደሮችና ሲቪል ነበሩ፡፡”
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍4
ኦፍጡነ ረድኤት/2/
የእግዚአብሔር አገልጋይ ቅዱስ ሰማዕት
አዝ…………………………………………………………….
ሰላም ላንተ ይሁን ፍጡነ ረድኤት
የልዳው ፀሐይ ‘’ ‘’
በጨካ ንጉስ ፊት ቆምክ አደባባይ
ታማኝ አገልጋይ ነህ ፍጡነ ረድኤት
ስቃይ ያልበገረህ ‘’ ‘’
አክሊል አገኘህ መከራን ታግሰህ
አዝ…………………………………………………………….
የፈጣሪውን ስም ፍጡነ ረድኤት
ስለመሰከረ ‘’ ‘’
ጊዮርጊስ ሰማዕት በሰይፍ ተመተረ
የስቃይ መሳሪያ ፍጡነ ረድኤት
ያላዘናጋህ ‘’ ‘’
መንፈሳዊ አርበኛ ጊዮርጊስ አንተነህ
አዝ…………………………………………………………….
የጌታ ተጋዳይ ፍጡነ ረድኤት
ታማኝ ወታደር ‘’ ‘’
ቢነገር አያልቅም የተሰጠህ ክብር
ስቃይ ሲደርስብህ ፍጡነ ረድኤት
በመታገስህ ‘’ ‘’
ሲወሳ ይኖራል ዘላለም ስምህ
አዝ…………………………………………………………….
ለሰማው ይደንቃል ፍጡነ ረድኤት
ያንተ ሰማዕትነት ‘’ ‘’
ምሳሌ ይሆናል በሁሉ ፍጥረት
ገድሉ ይናገራል ፍጡነ ረድኤት
ክብር እንደተሰጠው ‘’ ‘’
ጊዜ የማይሽረው ምግባር ሃማኖት

💚 @yeorthodoxmezmur 💚
💛 @yeorthodoxmezmur 💛
❤️ @yeorthodoxmezmur ❤️
👍6
2025/07/14 04:36:24
Back to Top
HTML Embed Code: