እንኳን ለዚህ ቀን አበቃቹ
@Mgetem
እንኳን ለዚህ ቀን አበቃቹ/3/
በእግዚአብሔር ቤት መረቅናቹ።
👨🎓👩🎓👨🎓👩🎓👨🎓👩🎓👨🎓👩🎓👨🎓
አዝ
የድካም ውጤት ነው የመስቀሉ ፍቅር
እጅግ የሚያተጋ ለተሻለው ነገር
እሾህ ደፍቶ ጌታ ዘውዱን ጭኖብናል
የንጉስ ልጆች ነን ማን ይቃወመናል።
አዝ
ለፍተን ካሳረፍከን ሰርተን ከባረከን
እኛም ለአምላካችን የምንለው አለን
ቀልጧል እንደ ቅባት ፍቅርክ በውስጣችን
የማይታጠብ ነው አንተነህ ወዛችን
አዝ
መዳፍህ ሲያርፍብን እንለወጣለን
ለውርደት ሲያስቡን ለክብር እንሆናለን
ገና ነው ፍፃሜው ገና ነው አጽናፉ
እንነበባለን ሲገለጥ መፅሐፉ
አዝ
በለቅሶ የሚዘሩ በደስታ ያጭዳሉ
ትንሽ ሆነው ወጥተው እጅግ ይበዛሉ
የተከፈተ በር ስለተሰጣቹ
በማይሞተው አምላክ ኩሩ በአምላካቹ።
👨🎓☀️👩🎓☀👨🎓☀👩🎓☀👨🎓
ለ2016 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ እንኳን ደስ አላቹ እንኳን እግዚአብሔር አምላክ ለዚህ ቀን አበቃቹ እንላለን!!!
👨🎓☀️👩🎓☀👨🎓☀👩🎓☀👨🎓
__
@Mgetem
@Mgetem_group
@Mgetem_bot
@Mgetem
እንኳን ለዚህ ቀን አበቃቹ/3/
በእግዚአብሔር ቤት መረቅናቹ።
👨🎓👩🎓👨🎓👩🎓👨🎓👩🎓👨🎓👩🎓👨🎓
አዝ
የድካም ውጤት ነው የመስቀሉ ፍቅር
እጅግ የሚያተጋ ለተሻለው ነገር
እሾህ ደፍቶ ጌታ ዘውዱን ጭኖብናል
የንጉስ ልጆች ነን ማን ይቃወመናል።
አዝ
ለፍተን ካሳረፍከን ሰርተን ከባረከን
እኛም ለአምላካችን የምንለው አለን
ቀልጧል እንደ ቅባት ፍቅርክ በውስጣችን
የማይታጠብ ነው አንተነህ ወዛችን
አዝ
መዳፍህ ሲያርፍብን እንለወጣለን
ለውርደት ሲያስቡን ለክብር እንሆናለን
ገና ነው ፍፃሜው ገና ነው አጽናፉ
እንነበባለን ሲገለጥ መፅሐፉ
አዝ
በለቅሶ የሚዘሩ በደስታ ያጭዳሉ
ትንሽ ሆነው ወጥተው እጅግ ይበዛሉ
የተከፈተ በር ስለተሰጣቹ
በማይሞተው አምላክ ኩሩ በአምላካቹ።
👨🎓☀️👩🎓☀👨🎓☀👩🎓☀👨🎓
ለ2016 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ እንኳን ደስ አላቹ እንኳን እግዚአብሔር አምላክ ለዚህ ቀን አበቃቹ እንላለን!!!
👨🎓☀️👩🎓☀👨🎓☀👩🎓☀👨🎓
__
@Mgetem
@Mgetem_group
@Mgetem_bot
ገብርኤል
@Mgetem
የንጉስ ጭካኔ ፥ ክንዱ ቢበረታ፤
ለጣዖት ሳንሰግድ፥ እኛ ሳንረታ፡፡
የምናምነው አምላክ፥ ሊያድነን ወደደ፤
ገብርኤል መጣና፥ እሳቱ በረደ፡፡
፤
ፍላፃና ሠይፉን፥ አጠፈው መላኩ፤
ሰላም ይዞ መጣ፥ ባለም ለታወኩ፡፡
አትጠራጠሩ፥ ምልጃው ያስምረናል፤
የሚነደው እሳት፥ ሳይነካን ወተናል፡፡
፤
የሰልስቱ ደቂቅ፥ የእጠሉጣ ብርታት፤
የድንግል አብሳሪ፥ የቂርቆስ ረዳት፡፡
በሚመጣው አለም፥ እንዳይበላኝ እሳት፤
አማልደኝ ከጌታ፥ ነፍሴን እንዲምራት፡፡
፤
የነገርኩህ ሁሉ፥ በቀኑ ደረሰ ፤
በዘብር ገብርኤል፥ እንባዬ ታበሰ፡፡
ና ልጄ ስትለኝ፥ አልልህም እንቢ፤
ስለቴን ተቀበል፥ አባቴ ቁልቢ፡፡
፤
የልቤን ነግሬህ፥ የቁልቢው ገብርኤል፤
ሳትረሳ ፈፀምከው፥ ስለቴን ተቀበል፡፡
ለንግስ እንመጣለን፥ አንተ አትረሳምና፤
ደሞ የዛሬ አመት፥ አድርሰን በደህና፡፡
+++++++
እንኳን ለሃያሉ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ የንግስ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!!!
________________________
@Mgetem
@Mgetem_group
@Mgetem_bot
@Mgetem
የንጉስ ጭካኔ ፥ ክንዱ ቢበረታ፤
ለጣዖት ሳንሰግድ፥ እኛ ሳንረታ፡፡
የምናምነው አምላክ፥ ሊያድነን ወደደ፤
ገብርኤል መጣና፥ እሳቱ በረደ፡፡
፤
ፍላፃና ሠይፉን፥ አጠፈው መላኩ፤
ሰላም ይዞ መጣ፥ ባለም ለታወኩ፡፡
አትጠራጠሩ፥ ምልጃው ያስምረናል፤
የሚነደው እሳት፥ ሳይነካን ወተናል፡፡
፤
የሰልስቱ ደቂቅ፥ የእጠሉጣ ብርታት፤
የድንግል አብሳሪ፥ የቂርቆስ ረዳት፡፡
በሚመጣው አለም፥ እንዳይበላኝ እሳት፤
አማልደኝ ከጌታ፥ ነፍሴን እንዲምራት፡፡
፤
የነገርኩህ ሁሉ፥ በቀኑ ደረሰ ፤
በዘብር ገብርኤል፥ እንባዬ ታበሰ፡፡
ና ልጄ ስትለኝ፥ አልልህም እንቢ፤
ስለቴን ተቀበል፥ አባቴ ቁልቢ፡፡
፤
የልቤን ነግሬህ፥ የቁልቢው ገብርኤል፤
ሳትረሳ ፈፀምከው፥ ስለቴን ተቀበል፡፡
ለንግስ እንመጣለን፥ አንተ አትረሳምና፤
ደሞ የዛሬ አመት፥ አድርሰን በደህና፡፡
+++++++
እንኳን ለሃያሉ ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ የንግስ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!!!
________________________
@Mgetem
@Mgetem_group
@Mgetem_bot
ቅኔና ውዳሴሽ 21❤
@Mgetem
ቅኔና ውዳሴሽ ምግብ መጠጣችን
ማር የሆነው ስምሽ የመንገድ ስንቃችን
ፍቅርሽ እንደ ዕሳት__ ይነዳል ውስጣችን
ንኢ ንኢ ስንል ባርኪን እናታችን።
ልቡ ያዘነውን አዳምን ሊያፅናና
ትካዜውን ሊቀብር__የሞቱን ጎዳና
ማደሪያው አድርጎሽ__የሰማዩ መና
አዳነው ክርስቶስ__ ይድረሰው ምስጋና
ከወጣበት ገነት___ ተመልሷልና።
ካንቺ ተወለደ__ ያለ ወንድ ዘር
የሔዋን እርግማን__ወድቆ ሊሰበር
ያሳታት ዲያቢሎስ__ሲዖል ሊታሰር
ሥጋ ለብሶ ታየ__ ወልደ እግዚአብሔር።
ሰው የሆነና በኛ ያደረ ቃል
ኢየሱስ ክርስቶስቅዱስ አማኑኤል
መሆኑን ነገረን__ነበዩ ኢሳይያስ
አየነው ተጽፎ__ በመጽሐፍ ቅዱስ።
ሰው ሆይ ደስ ይበልህ__ተነስ ለምስጋና
እግዚአብሔር ዓለሙን__እንዲሁ ወዷልና
በአንድ ልጁ እንድናምን
ልዑል ክንዱን ሰደደልን።
የነበረው የሚኖረው__የማያልፈው ለዘለአለም
ከላይ ወርዶ ሰጠን ሰላም
በሥራው ሁሉ አልተለየም
ወልደ እግዚአብሔር__ ወልደ ማርያም።
ቅድስት ሆይ ለምኝልን
በበደልነው እንዳይቀጣን
ለንሰሀ ዕድሜን ይስጠን
በኪዳንሽ ተማፀንን።
የእግዚአብሔር ቃል መለኮት
የለበትም ሦስትነት
አንድ ብቻ__ነው እውነት
የሥላሴ__ቸርነት።
እንደ አበው__ ባንበቃ
ስምሽ ሆኖን__ ዋስ ጠበቃ
ደስታችን ሆኖ__ሲቃ
ልመናችን ሰምሮ ባንቺ
አማለደሽን ሳትሰለቺ።
ተሰበሰብን ልንጠራሸ
ማርየም ሆይ ቆምን ደጅሽ
የዘለአለም ዓንባችን ነሽ
ዕርስታችን የወረስንሽ።
እመቤታችን ሆይ የቅዱስ ኤፍሬምን በረከት አሳድሪብን
ሀገራችንን ቅድስት ኢትዮጵያን ሰላም አድርጊልን
ልመናችንን አሳርጊልን።
✒️ ከእህተ ማርያም
_____
@Mgetem
@Mgetem_group
@Mgetem_bot
@Mgetem
ቅኔና ውዳሴሽ ምግብ መጠጣችን
ማር የሆነው ስምሽ የመንገድ ስንቃችን
ፍቅርሽ እንደ ዕሳት__ ይነዳል ውስጣችን
ንኢ ንኢ ስንል ባርኪን እናታችን።
ልቡ ያዘነውን አዳምን ሊያፅናና
ትካዜውን ሊቀብር__የሞቱን ጎዳና
ማደሪያው አድርጎሽ__የሰማዩ መና
አዳነው ክርስቶስ__ ይድረሰው ምስጋና
ከወጣበት ገነት___ ተመልሷልና።
ካንቺ ተወለደ__ ያለ ወንድ ዘር
የሔዋን እርግማን__ወድቆ ሊሰበር
ያሳታት ዲያቢሎስ__ሲዖል ሊታሰር
ሥጋ ለብሶ ታየ__ ወልደ እግዚአብሔር።
ሰው የሆነና በኛ ያደረ ቃል
ኢየሱስ ክርስቶስቅዱስ አማኑኤል
መሆኑን ነገረን__ነበዩ ኢሳይያስ
አየነው ተጽፎ__ በመጽሐፍ ቅዱስ።
ሰው ሆይ ደስ ይበልህ__ተነስ ለምስጋና
እግዚአብሔር ዓለሙን__እንዲሁ ወዷልና
በአንድ ልጁ እንድናምን
ልዑል ክንዱን ሰደደልን።
የነበረው የሚኖረው__የማያልፈው ለዘለአለም
ከላይ ወርዶ ሰጠን ሰላም
በሥራው ሁሉ አልተለየም
ወልደ እግዚአብሔር__ ወልደ ማርያም።
ቅድስት ሆይ ለምኝልን
በበደልነው እንዳይቀጣን
ለንሰሀ ዕድሜን ይስጠን
በኪዳንሽ ተማፀንን።
የእግዚአብሔር ቃል መለኮት
የለበትም ሦስትነት
አንድ ብቻ__ነው እውነት
የሥላሴ__ቸርነት።
እንደ አበው__ ባንበቃ
ስምሽ ሆኖን__ ዋስ ጠበቃ
ደስታችን ሆኖ__ሲቃ
ልመናችን ሰምሮ ባንቺ
አማለደሽን ሳትሰለቺ።
ተሰበሰብን ልንጠራሸ
ማርየም ሆይ ቆምን ደጅሽ
የዘለአለም ዓንባችን ነሽ
ዕርስታችን የወረስንሽ።
እመቤታችን ሆይ የቅዱስ ኤፍሬምን በረከት አሳድሪብን
ሀገራችንን ቅድስት ኢትዮጵያን ሰላም አድርጊልን
ልመናችንን አሳርጊልን።
✒️ ከእህተ ማርያም
_____
@Mgetem
@Mgetem_group
@Mgetem_bot
ቅኔና ውዳሴሽ 21❤
@Mgetem
ቅኔና ውዳሴሽ ምግብ መጠጣችን
ማር የሆነው ስምሽ የመንገድ ስንቃችን
ፍቅርሽ እንደ ዕሳት__ ይነዳል ውስጣችን
ንኢ ንኢ ስንል ባርኪን እናታችን።
ልቡ ያዘነውን አዳምን ሊያፅናና
ትካዜውን ሊቀብር__የሞቱን ጎዳና
ማደሪያው አድርጎሽ__የሰማዩ መና
አዳነው ክርስቶስ__ ይድረሰው ምስጋና
ከወጣበት ገነት___ ተመልሷልና።
ካንቺ ተወለደ__ ያለ ወንድ ዘር
የሔዋን እርግማን__ወድቆ ሊሰበር
ያሳታት ዲያቢሎስ__ሲዖል ሊታሰር
ሥጋ ለብሶ ታየ__ ወልደ እግዚአብሔር።
ሰው የሆነና በኛ ያደረ ቃል
ኢየሱስ ክርስቶስቅዱስ አማኑኤል
መሆኑን ነገረን__ነበዩ ኢሳይያስ
አየነው ተጽፎ__ በመጽሐፍ ቅዱስ።
ሰው ሆይ ደስ ይበልህ__ተነስ ለምስጋና
እግዚአብሔር ዓለሙን__እንዲሁ ወዷልና
በአንድ ልጁ እንድናምን
ልዑል ክንዱን ሰደደልን።
የነበረው የሚኖረው__የማያልፈው ለዘለአለም
ከላይ ወርዶ ሰጠን ሰላም
በሥራው ሁሉ አልተለየም
ወልደ እግዚአብሔር__ ወልደ ማርያም።
ቅድስት ሆይ ለምኝልን
በበደልነው እንዳይቀጣን
ለንሰሀ ዕድሜን ይስጠን
በኪዳንሽ ተማፀንን።
የእግዚአብሔር ቃል መለኮት
የለበትም ሦስትነት
አንድ ብቻ__ነው እውነት
የሥላሴ__ቸርነት።
እንደ አበው__ ባንበቃ
ስምሽ ሆኖን__ ዋስ ጠበቃ
ደስታችን ሆኖ__ሲቃ
ልመናችን ሰምሮ ባንቺ
አማለደሽን ሳትሰለቺ።
ተሰበሰብን ልንጠራሸ
ማርየም ሆይ ቆምን ደጅሽ
የዘለአለም ዓንባችን ነሽ
ዕርስታችን የወረስንሽ።
እመቤታችን ሆይ የቅዱስ ኤፍሬምን በረከት አሳድሪብን
ሀገራችንን ቅድስት ኢትዮጵያን ሰላም አድርጊልን
ልመናችንን አሳርጊልን።
✒️ ከእህተ ማርያም
_____
@Mgetem
@Mgetem_group
@Mgetem_bot
@Mgetem
ቅኔና ውዳሴሽ ምግብ መጠጣችን
ማር የሆነው ስምሽ የመንገድ ስንቃችን
ፍቅርሽ እንደ ዕሳት__ ይነዳል ውስጣችን
ንኢ ንኢ ስንል ባርኪን እናታችን።
ልቡ ያዘነውን አዳምን ሊያፅናና
ትካዜውን ሊቀብር__የሞቱን ጎዳና
ማደሪያው አድርጎሽ__የሰማዩ መና
አዳነው ክርስቶስ__ ይድረሰው ምስጋና
ከወጣበት ገነት___ ተመልሷልና።
ካንቺ ተወለደ__ ያለ ወንድ ዘር
የሔዋን እርግማን__ወድቆ ሊሰበር
ያሳታት ዲያቢሎስ__ሲዖል ሊታሰር
ሥጋ ለብሶ ታየ__ ወልደ እግዚአብሔር።
ሰው የሆነና በኛ ያደረ ቃል
ኢየሱስ ክርስቶስቅዱስ አማኑኤል
መሆኑን ነገረን__ነበዩ ኢሳይያስ
አየነው ተጽፎ__ በመጽሐፍ ቅዱስ።
ሰው ሆይ ደስ ይበልህ__ተነስ ለምስጋና
እግዚአብሔር ዓለሙን__እንዲሁ ወዷልና
በአንድ ልጁ እንድናምን
ልዑል ክንዱን ሰደደልን።
የነበረው የሚኖረው__የማያልፈው ለዘለአለም
ከላይ ወርዶ ሰጠን ሰላም
በሥራው ሁሉ አልተለየም
ወልደ እግዚአብሔር__ ወልደ ማርያም።
ቅድስት ሆይ ለምኝልን
በበደልነው እንዳይቀጣን
ለንሰሀ ዕድሜን ይስጠን
በኪዳንሽ ተማፀንን።
የእግዚአብሔር ቃል መለኮት
የለበትም ሦስትነት
አንድ ብቻ__ነው እውነት
የሥላሴ__ቸርነት።
እንደ አበው__ ባንበቃ
ስምሽ ሆኖን__ ዋስ ጠበቃ
ደስታችን ሆኖ__ሲቃ
ልመናችን ሰምሮ ባንቺ
አማለደሽን ሳትሰለቺ።
ተሰበሰብን ልንጠራሸ
ማርየም ሆይ ቆምን ደጅሽ
የዘለአለም ዓንባችን ነሽ
ዕርስታችን የወረስንሽ።
እመቤታችን ሆይ የቅዱስ ኤፍሬምን በረከት አሳድሪብን
ሀገራችንን ቅድስት ኢትዮጵያን ሰላም አድርጊልን
ልመናችንን አሳርጊልን።
✒️ ከእህተ ማርያም
_____
@Mgetem
@Mgetem_group
@Mgetem_bot
የፈጣሪ_ልሳን
እጆቼን ዘርግቼ........
ልጸልይ ልማልድ ከደጅኽ ተገኘኹ
አንጋጥጬ ሽቅብ በሐሳቤ ዋኘኹ
ተንበርክኬ ለምሕላ በግንባሬ ተደፍቼ
ቀና ማለት ተዘነጋኝ የቃል ጸሎት ረስቼ
ያ'ንደበትኸ ልሳን ከየት ተሠወረ?
ቃል ከምላሴ ላይ እንደምን ታወረ?
ዝም....
ዝም ዝም....... !
እንደው ዝም! ዝምታዬ ቀረ
ሰምተኸኛል አንተ
በዝምታ ልሳን ጸሎቴ ሰመረ።
ገጣሚ #ተስፋሁን_ከበደ
@Mgetem
@Mgetem_group
@Mgetem
እጆቼን ዘርግቼ........
ልጸልይ ልማልድ ከደጅኽ ተገኘኹ
አንጋጥጬ ሽቅብ በሐሳቤ ዋኘኹ
ተንበርክኬ ለምሕላ በግንባሬ ተደፍቼ
ቀና ማለት ተዘነጋኝ የቃል ጸሎት ረስቼ
ያ'ንደበትኸ ልሳን ከየት ተሠወረ?
ቃል ከምላሴ ላይ እንደምን ታወረ?
ዝም....
ዝም ዝም....... !
እንደው ዝም! ዝምታዬ ቀረ
ሰምተኸኛል አንተ
በዝምታ ልሳን ጸሎቴ ሰመረ።
ገጣሚ #ተስፋሁን_ከበደ
@Mgetem
@Mgetem_group
@Mgetem
ግልብ ነው ነገሬ
ድልብ ነው ነውሬ
ፍቅርሽ ድርብ በፍታ
ሸፈነልኝ ሁሉን
እስርስሩን ፈታ
በለመንኹሽ አፍታ
አበረደው ጥሉን
አወረደው ጠሉን
ልቤ ተራራ ላይ
አጮልቄ እንዳይ
አሸብርቄ እንድታይ
ደፋብኝ ጸበሉን
ዝቅ አርጎት ጠለሉን።
***
የብርሃን እናት ደጅ ኩራዝ ይዤ መጣሁ
ከምስራቋ በራ'ፍ
ያ'ለም ጸሐይ ናፍቆኝ ትንሽ ኮከብ ወጣሁ፤
በጸሎቷ አቅም
በምሕረቱ ብዛት
በረከት ስለቅም
ላምባዬን ሲያበዛት፥
አማረበት በጣም፣ ደመቀ ሰማዩ
ልጥግብ ከመዓዛሽ፣ ልሙቅ ከጸሐዩ።
/ዮሐንስ ሞላ/
@Mgetem
@Mgetem_group
@Mgetem
ድልብ ነው ነውሬ
ፍቅርሽ ድርብ በፍታ
ሸፈነልኝ ሁሉን
እስርስሩን ፈታ
በለመንኹሽ አፍታ
አበረደው ጥሉን
አወረደው ጠሉን
ልቤ ተራራ ላይ
አጮልቄ እንዳይ
አሸብርቄ እንድታይ
ደፋብኝ ጸበሉን
ዝቅ አርጎት ጠለሉን።
***
የብርሃን እናት ደጅ ኩራዝ ይዤ መጣሁ
ከምስራቋ በራ'ፍ
ያ'ለም ጸሐይ ናፍቆኝ ትንሽ ኮከብ ወጣሁ፤
በጸሎቷ አቅም
በምሕረቱ ብዛት
በረከት ስለቅም
ላምባዬን ሲያበዛት፥
አማረበት በጣም፣ ደመቀ ሰማዩ
ልጥግብ ከመዓዛሽ፣ ልሙቅ ከጸሐዩ።
/ዮሐንስ ሞላ/
@Mgetem
@Mgetem_group
@Mgetem
ጠፍቼ ሳለው...
(ሳሙኤል አለሙ)
@Mgetem
°
°
በለመለመው መስክ ላይ
እኛ በጎቹ ፥ ነበርን አንድ-ላይ
ስንግጥ ባንድ ላይ
ስንጠጣ ባንድ ላይ
የማይነጥፈው ሳለ ፥ ሳለ ተንዠርግጎ
ለወዲያ ማዶ ፥ አንገቴ አስግጎ
አረሙ ናፍቆኝ ፥ ካንተ አመለጥኩኝ።
°
°
አረሙ ናፍቆኝ
መግደሉ ናፍቆኝ
ዝሙቱ ናፍቆኝ
ስርቆቱ ናፍቆኝ
ይኸው ጠገብኩኝ ፥ ካይነት ካይነቱ
ጣዕሙ አልሆነኝ ፥ እንደ ትላንቱ።
°
°
ጣዕሙ አልሆነኝ
አንገዳገደኝ
እንዴት ልመለስ...
አስሬ እያነሳ ፥ አስሬ እየጣለኝ
ወደ በጎችህ...
የማት[ቀላቅለኝ] ፥ እየመሰለኝ
ከደጅህ እመለሳለሁ።
በኩነኔ አፍሬያለሁ።
°
°
ከደጅህ እመለሳለሁ።
በምን አይኔ አይሃለሁ።
ውቅያኖስ ያህል ፥ ሀጥያት ነበረኝ
ባንዲት ዕንባዬ ፥ ሞገዱ ሲጠራኝ
ወደ ኩሬ ስትቀይረኝ...
አቤት ማለት ፥ አፌ አስፈራኝ።
°
°
ወደ ኩሬ ስትቀይረኝ
መጣኽና አጠለልከኝ።
አንተ ጠባቂዬ
አንተ ከለላዬ
አንተ እረኛዬ
አቅፈኸ ነው ፥ የሳምከኝ
ከበጎችህ ፥ የ--ቀላቀል--ከኝ።
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_group
(ሳሙኤል አለሙ)
@Mgetem
°
°
በለመለመው መስክ ላይ
እኛ በጎቹ ፥ ነበርን አንድ-ላይ
ስንግጥ ባንድ ላይ
ስንጠጣ ባንድ ላይ
የማይነጥፈው ሳለ ፥ ሳለ ተንዠርግጎ
ለወዲያ ማዶ ፥ አንገቴ አስግጎ
አረሙ ናፍቆኝ ፥ ካንተ አመለጥኩኝ።
°
°
አረሙ ናፍቆኝ
መግደሉ ናፍቆኝ
ዝሙቱ ናፍቆኝ
ስርቆቱ ናፍቆኝ
ይኸው ጠገብኩኝ ፥ ካይነት ካይነቱ
ጣዕሙ አልሆነኝ ፥ እንደ ትላንቱ።
°
°
ጣዕሙ አልሆነኝ
አንገዳገደኝ
እንዴት ልመለስ...
አስሬ እያነሳ ፥ አስሬ እየጣለኝ
ወደ በጎችህ...
የማት[ቀላቅለኝ] ፥ እየመሰለኝ
ከደጅህ እመለሳለሁ።
በኩነኔ አፍሬያለሁ።
°
°
ከደጅህ እመለሳለሁ።
በምን አይኔ አይሃለሁ።
ውቅያኖስ ያህል ፥ ሀጥያት ነበረኝ
ባንዲት ዕንባዬ ፥ ሞገዱ ሲጠራኝ
ወደ ኩሬ ስትቀይረኝ...
አቤት ማለት ፥ አፌ አስፈራኝ።
°
°
ወደ ኩሬ ስትቀይረኝ
መጣኽና አጠለልከኝ።
አንተ ጠባቂዬ
አንተ ከለላዬ
አንተ እረኛዬ
አቅፈኸ ነው ፥ የሳምከኝ
ከበጎችህ ፥ የ--ቀላቀል--ከኝ።
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_group
🌼የሩፋኤል ጠበል ከልጅነት እስከ ጅልነት🌼
ዲ/ን ከሣቴብርሃን ገብረኢየሱስ (ዶ/ር)
@Mgetem
በመዋዕለ ንጽሕ ..
ልጅ ሳለሁ ፤ እንደ ልጅ፤
ጤና ሆኜ ሳለ..
በንዕማን ልማድ፤በውሃ ተጠምቄ፤ ጤንነቴን ሳውጅ፤
በርኅወተ ሰማይ፤
ሲዘንም የምሕረት ማይ፤
በሩፋኤል ጠበል በ“አሳድገኝ” ጬኸት፤
በጋን እንድባጀው እንደ ከረምኩ ክረምት፤
ከልቤ ለምኜ፤
ስብራት ሳይኖረኝ በወግ ተጠግኜ፤
ፀአዳ ብራና ሳልዳመጥ ዳግም፤
በጥምቀት ሳልሸኘው ዘመን አልፎ አያውቅም::
እነሆ ልጅነት እንደ ጥላ አለፈ፤
በዚያ ብራና ገጽ እልፍ ኃጢአት ተጻፈ፤
ሰውነት ይሁዳ ከድቶ ሽፍታ ኖሮ፤
ባበቀለው ጫካ ጠብ መንጃ ሰውሮ፤
ጠብ ክብሪት ሲላኮስ፤
ከጽድቅ ሲታኮስ፤
እኔ ሕመምተኛ፤ የጦር ቁስለኛ፤ መፈወሻ ጠበል የምፈልግ ሳለሁ፤
ጥግ ይዤ ቆሜያለሁ::
ያ ጠለ በረከት፤
የንስሐ እጥበት ዓመቱን ጠብቆ ይኸው ዛሬ መጣ፤
የከተማው ደቂቅ ልብሱን አወላልቆ በነቂስ ሲወጣ፤
እኔ ግን ከቤቴ በለበስኩት ቁምጣ፤
በለበስኩት ሱሬ ፤
በሥራዬ ሳይሆን በመሥሪያዬ አፍሬ ፤
ራቁት ከኃጢአት ልጅነቴን ሽሬ።
@Mgetem
@Mgetem_group
@Solasc12
ዲ/ን ከሣቴብርሃን ገብረኢየሱስ (ዶ/ር)
@Mgetem
በመዋዕለ ንጽሕ ..
ልጅ ሳለሁ ፤ እንደ ልጅ፤
ጤና ሆኜ ሳለ..
በንዕማን ልማድ፤በውሃ ተጠምቄ፤ ጤንነቴን ሳውጅ፤
በርኅወተ ሰማይ፤
ሲዘንም የምሕረት ማይ፤
በሩፋኤል ጠበል በ“አሳድገኝ” ጬኸት፤
በጋን እንድባጀው እንደ ከረምኩ ክረምት፤
ከልቤ ለምኜ፤
ስብራት ሳይኖረኝ በወግ ተጠግኜ፤
ፀአዳ ብራና ሳልዳመጥ ዳግም፤
በጥምቀት ሳልሸኘው ዘመን አልፎ አያውቅም::
እነሆ ልጅነት እንደ ጥላ አለፈ፤
በዚያ ብራና ገጽ እልፍ ኃጢአት ተጻፈ፤
ሰውነት ይሁዳ ከድቶ ሽፍታ ኖሮ፤
ባበቀለው ጫካ ጠብ መንጃ ሰውሮ፤
ጠብ ክብሪት ሲላኮስ፤
ከጽድቅ ሲታኮስ፤
እኔ ሕመምተኛ፤ የጦር ቁስለኛ፤ መፈወሻ ጠበል የምፈልግ ሳለሁ፤
ጥግ ይዤ ቆሜያለሁ::
ያ ጠለ በረከት፤
የንስሐ እጥበት ዓመቱን ጠብቆ ይኸው ዛሬ መጣ፤
የከተማው ደቂቅ ልብሱን አወላልቆ በነቂስ ሲወጣ፤
እኔ ግን ከቤቴ በለበስኩት ቁምጣ፤
በለበስኩት ሱሬ ፤
በሥራዬ ሳይሆን በመሥሪያዬ አፍሬ ፤
ራቁት ከኃጢአት ልጅነቴን ሽሬ።
@Mgetem
@Mgetem_group
@Solasc12
ስንቄን ይዣለሁኝ
@Mgetem
በእንተ ስለማርያም ኮሮጆዬን ይዤ
ልለምን አይደለም ልማር ልወቅ ብዬ
ጌታዬን ማመስገን ሰዓታት ዜማውን
ውዳሴ ቅዳሴ ቅኔ ማኅሌቱን
ምን እበላ ብዬ መች አስባለሁኝ
በእንተ ማርያም ስንቄን ይዣለሁኝ
ለአባ ሕርያቆስ ጸጋው ቅዳሴሽ
የአባ ጊዮርጊስ ሰዓታት ዜማሽ
ደግሞ ለአባ ኤፍሬም ምግቡ ውዳሴሽ
ይህንን ስሰማ መሰጠኝ ፍቅርሽ
ከመምር መምር ለመማር ምስጢር
በቅሎ ፈረስ አልል አልመኝ ባቡር
ለምለም ሣር ፍራሼ ድንጋይ ነው ትራሴ
አንቺን ሳመሰግን ትረካለች ነፍሴ
ከአንዱ ሀገር ሌላ ሀገር መምር ፍለጋ
ልማር ልመራመር ድጓ ጾመ ድጓ
++++++++++++++++++++++++++
@Mgetem
@Mgetem_group
@Solasc12
@Mgetem
በእንተ ስለማርያም ኮሮጆዬን ይዤ
ልለምን አይደለም ልማር ልወቅ ብዬ
ጌታዬን ማመስገን ሰዓታት ዜማውን
ውዳሴ ቅዳሴ ቅኔ ማኅሌቱን
ምን እበላ ብዬ መች አስባለሁኝ
በእንተ ማርያም ስንቄን ይዣለሁኝ
ለአባ ሕርያቆስ ጸጋው ቅዳሴሽ
የአባ ጊዮርጊስ ሰዓታት ዜማሽ
ደግሞ ለአባ ኤፍሬም ምግቡ ውዳሴሽ
ይህንን ስሰማ መሰጠኝ ፍቅርሽ
ከመምር መምር ለመማር ምስጢር
በቅሎ ፈረስ አልል አልመኝ ባቡር
ለምለም ሣር ፍራሼ ድንጋይ ነው ትራሴ
አንቺን ሳመሰግን ትረካለች ነፍሴ
ከአንዱ ሀገር ሌላ ሀገር መምር ፍለጋ
ልማር ልመራመር ድጓ ጾመ ድጓ
++++++++++++++++++++++++++
@Mgetem
@Mgetem_group
@Solasc12
Forwarded from ኦርቶዶክሳዊ ጥቅሶች ብቻ
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#የቤተልሔሙ_ብሥራት
@Mgetem
ሔሮድስ አሳውጆ የሕዝብ ቆጠራ
ወደ ቤተልሔም ሁሉም ሰው ሲያመራ፣
ዮሴፍና ማርያም ለመሄድ አስበው
የድንግል መጽነስ ዮሴፍ ቢያስጨንቀው
ነገረው መልአኩ ተገልፆ በራዕይ
የድንግል መጸነስ መሆኑን ከሰማይ፡፡
ዮሴፍም ተደንቆ በመልአኩ ነገር
ወሰነ ለመሄድ ከድንግሊቱ ጋር፡፡
ቤተልሔም ደርሰው ከሕዝቡ በኋላ
ማደርያውም ቢያዝ በሰዉ ቢሞላ
እነሱም ተገኙ ከከብቶቹ በረት
ማረፍያ ስላጡ ለእነሱ የሚሆን ቤት፡፡
በበረት ውስጥ ሳሉ ከእንስሳቱ መሃል
የዓለም መድሐኒት ተገኘ ከድንግል፡፡
የነገስታት ንጉስ የኃያላን ኃያል
ሆኖ ሳለ እርሱ በሰማይ በምድር
እርሱ ለመወለድ መረጠ ግርግምን
እንደ ደካማ ሰው በጨርቅ መጠቅለልን፡፡
ላሞችና አህዮች ተደንቀው በጌታ
አሞቁት በትንፋሽ ሁሉም በየተርታ፡፡
ሁሌ የሚያወድሱት በሰማይ መንበሩ
ያን ጊዜም መላእክት በምድር ዘመሩ፡፡
በረቱም ተሞላ በደማቅ ብርሃን
በውስጡ ስላለ የዓለም መድኅን፡፡
እረኞችም ሰምተው የመልአኩን ብስራት
ሄዱ ገሰገሱ አምላክ ወዳለበት
ውስጣቸው ተሞልቶ በደስታ በሀሴት፡፡
ተለያይተው የኖሩ ሰውና መላእክት
አሁን ተገናኙ በጌታችን ልደት
አብሮ ለመዘመር በፍቅር በአንድነት፡፡
የሩቅ ምስራቅ ሰዎች ሠለሥቱ ነገስታት
በኮከብ ተመርተው ጌታ ወዳለበት
በእምነት አቀኑ ወደ ቤተልሔም ወደ አምላካቸው
ወርቅ እጣን ከርቤውን እጅ መንሻ ይዘው፡፡
የጌታችን ልደት ከዳር ዳር ተሰምቶ
ፍጥረቱ በሙሉ በሃሴት ተሞልቶ
ሁሉም አቀረበ ለአምላክ ምስጋና
የእርሱ ድንቅ ስራ ሁሉን ማርኳልና፡፡
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_group
@Solasc12
@Mgetem
ሔሮድስ አሳውጆ የሕዝብ ቆጠራ
ወደ ቤተልሔም ሁሉም ሰው ሲያመራ፣
ዮሴፍና ማርያም ለመሄድ አስበው
የድንግል መጽነስ ዮሴፍ ቢያስጨንቀው
ነገረው መልአኩ ተገልፆ በራዕይ
የድንግል መጸነስ መሆኑን ከሰማይ፡፡
ዮሴፍም ተደንቆ በመልአኩ ነገር
ወሰነ ለመሄድ ከድንግሊቱ ጋር፡፡
ቤተልሔም ደርሰው ከሕዝቡ በኋላ
ማደርያውም ቢያዝ በሰዉ ቢሞላ
እነሱም ተገኙ ከከብቶቹ በረት
ማረፍያ ስላጡ ለእነሱ የሚሆን ቤት፡፡
በበረት ውስጥ ሳሉ ከእንስሳቱ መሃል
የዓለም መድሐኒት ተገኘ ከድንግል፡፡
የነገስታት ንጉስ የኃያላን ኃያል
ሆኖ ሳለ እርሱ በሰማይ በምድር
እርሱ ለመወለድ መረጠ ግርግምን
እንደ ደካማ ሰው በጨርቅ መጠቅለልን፡፡
ላሞችና አህዮች ተደንቀው በጌታ
አሞቁት በትንፋሽ ሁሉም በየተርታ፡፡
ሁሌ የሚያወድሱት በሰማይ መንበሩ
ያን ጊዜም መላእክት በምድር ዘመሩ፡፡
በረቱም ተሞላ በደማቅ ብርሃን
በውስጡ ስላለ የዓለም መድኅን፡፡
እረኞችም ሰምተው የመልአኩን ብስራት
ሄዱ ገሰገሱ አምላክ ወዳለበት
ውስጣቸው ተሞልቶ በደስታ በሀሴት፡፡
ተለያይተው የኖሩ ሰውና መላእክት
አሁን ተገናኙ በጌታችን ልደት
አብሮ ለመዘመር በፍቅር በአንድነት፡፡
የሩቅ ምስራቅ ሰዎች ሠለሥቱ ነገስታት
በኮከብ ተመርተው ጌታ ወዳለበት
በእምነት አቀኑ ወደ ቤተልሔም ወደ አምላካቸው
ወርቅ እጣን ከርቤውን እጅ መንሻ ይዘው፡፡
የጌታችን ልደት ከዳር ዳር ተሰምቶ
ፍጥረቱ በሙሉ በሃሴት ተሞልቶ
ሁሉም አቀረበ ለአምላክ ምስጋና
የእርሱ ድንቅ ስራ ሁሉን ማርኳልና፡፡
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_group
@Solasc12
# ስንት_ቀን_ፈጀብህ?
/መንፈሳዊ መነባንብ /
@Mgetem
ለአዳም ኪዳን ሰጠህ
እንደምትወለድ ወደ ምድር ወርደህ
እንዴት ነበር ያኔ..?
ወደ እኛ ስትመጣ መላእክትን ትተህ?
………
የሔዋን እርግማን
የባሏም የውርስ ኃጢአት መዘገን
እንዲያ አሳሰበህና
መጣህልን ሁሉን አደረግህ በፅሙና
.........
እንዴት ነበር ያኔ..?
ያችን ንጹሕ ለመፈለግ የወሰደብህ ጊዜ
አድርገህ የሰጠኸንን ፈውስ በበድልን ጊዜ
ግን ምን ያህል ነው ልፋትህ?
ድንግልን ስትፈልግ የፈጀብህ?
.........
ከሰማያት ስትወርድ አጀቡህ መላእክት?
ዓለሙስ ተናወፀ በይባቤ በስብሐት?
ያ ምቀኛ ዲያቢሎስ ግን ምን አለ?
ወደ እኛ ስትመጣ አለ አይደል ኮበለለ?
ነው ሥጋ ለብሶ ጉድ ሠራኝ አለ?
........
እንዴት ነው እርቀቱ
የሰማይ ምጥቀቱ
የምድርስ ሥፋት
ከሷ እስክታርፍባት?
ግን ጌታ...?ሰማያት ምን አሉ
ትትሀቸው መጠህ ባንተ አጉረመረሙ?
ፍጥረታትስ ቢሆን ማሕሌት አቆሙ?
.......
ምሥጢረኛው ጌታ
መንገድህ በየት ነው ወደ እኛ ስትመጣ?
ቤተ ልሔም ስትደርስ
ማን አገለገልህ?ምን አለች ምድሪቱስ
እያቄም ወሐናን እንዴት መረጥሃቸው
አንተ እንድትወለድ ምክንያትህ ናቸው
.......
ሰማዩ ሰፊ ነው
ምድርንም ታውቃለህ
እንዴት እንድትሰፋ ሆና መረገጫህ
ግን እና ጌታ ሆይ ምኑ ነው የቻለህ?
የድንግል ማሕጸን እሳት መሸከሙ
ምድርም መልኮት በእሷ ላይ መቆሙ
..........
እንዴት ነበር ያኔ
በቤተ ልሔም ውስጥ
አንተን የሚያሞቅ ከእንስሶች ስትሰጥ?
........
ዮሴፍ ምን አለ
አንተን በማየቱ እርጅናው ታጎለ?
አንተን የጠበቀህ አዳምስ በግርማህ ምን አለ?
........
እንዴት ነው ስጦታው
የሰብአ ሰገሉ ወርቅ እጣን አምኃው
የእረኞቹ ደስታ
የመላእክት ብሥራት የልደትህማታ
.........
እንዴት ነበር ያኔ
የልደትህ ማታ
የዝማሬው ለታ
የእናትህ ደስታ
የፍጥረት እልልታ
ሚዳቋ ስትዘል ከኢትዮጵያ አይታ
ግን ጌታ እረቂቁ አምላክ
በየትስ መጠህ ነው ከኛ የተወለድክ
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_group
/መንፈሳዊ መነባንብ /
@Mgetem
ለአዳም ኪዳን ሰጠህ
እንደምትወለድ ወደ ምድር ወርደህ
እንዴት ነበር ያኔ..?
ወደ እኛ ስትመጣ መላእክትን ትተህ?
………
የሔዋን እርግማን
የባሏም የውርስ ኃጢአት መዘገን
እንዲያ አሳሰበህና
መጣህልን ሁሉን አደረግህ በፅሙና
.........
እንዴት ነበር ያኔ..?
ያችን ንጹሕ ለመፈለግ የወሰደብህ ጊዜ
አድርገህ የሰጠኸንን ፈውስ በበድልን ጊዜ
ግን ምን ያህል ነው ልፋትህ?
ድንግልን ስትፈልግ የፈጀብህ?
.........
ከሰማያት ስትወርድ አጀቡህ መላእክት?
ዓለሙስ ተናወፀ በይባቤ በስብሐት?
ያ ምቀኛ ዲያቢሎስ ግን ምን አለ?
ወደ እኛ ስትመጣ አለ አይደል ኮበለለ?
ነው ሥጋ ለብሶ ጉድ ሠራኝ አለ?
........
እንዴት ነው እርቀቱ
የሰማይ ምጥቀቱ
የምድርስ ሥፋት
ከሷ እስክታርፍባት?
ግን ጌታ...?ሰማያት ምን አሉ
ትትሀቸው መጠህ ባንተ አጉረመረሙ?
ፍጥረታትስ ቢሆን ማሕሌት አቆሙ?
.......
ምሥጢረኛው ጌታ
መንገድህ በየት ነው ወደ እኛ ስትመጣ?
ቤተ ልሔም ስትደርስ
ማን አገለገልህ?ምን አለች ምድሪቱስ
እያቄም ወሐናን እንዴት መረጥሃቸው
አንተ እንድትወለድ ምክንያትህ ናቸው
.......
ሰማዩ ሰፊ ነው
ምድርንም ታውቃለህ
እንዴት እንድትሰፋ ሆና መረገጫህ
ግን እና ጌታ ሆይ ምኑ ነው የቻለህ?
የድንግል ማሕጸን እሳት መሸከሙ
ምድርም መልኮት በእሷ ላይ መቆሙ
..........
እንዴት ነበር ያኔ
በቤተ ልሔም ውስጥ
አንተን የሚያሞቅ ከእንስሶች ስትሰጥ?
........
ዮሴፍ ምን አለ
አንተን በማየቱ እርጅናው ታጎለ?
አንተን የጠበቀህ አዳምስ በግርማህ ምን አለ?
........
እንዴት ነው ስጦታው
የሰብአ ሰገሉ ወርቅ እጣን አምኃው
የእረኞቹ ደስታ
የመላእክት ብሥራት የልደትህማታ
.........
እንዴት ነበር ያኔ
የልደትህ ማታ
የዝማሬው ለታ
የእናትህ ደስታ
የፍጥረት እልልታ
ሚዳቋ ስትዘል ከኢትዮጵያ አይታ
ግን ጌታ እረቂቁ አምላክ
በየትስ መጠህ ነው ከኛ የተወለድክ
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_group