የፋይናንስና የክዋኔ ኦዲት ግንዛቤ ለተቋም ዓላማ ስኬት መረጋገጥ ሚናው የላቀ እንደሆነ ተገለፀ።
==================
የኢኖቬሽንና ቴክኖሊጂ ሚኒስቴር ለመካከለኛ አመራሮች የፋይናንስና የክዋኔ ኦዲት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል።
በኢኖቬሽንና ቴክኖሊጂ ሚኒስቴር የኦዲት ስራ አስፈፃሚ አቶ አሻግሬ አለሙ የፋይናንስና የክዋኔ ኦዲት ላይ የጠራ ግንዛቤ መፍጠር ለተቋማዊ ውጤታማነት ያለውን ሚና አስረድተዋል።
ተቋማት ሳያውቁ ከሚሰሯቸው የኦዲት ግኝቶች ለመታደግ በዘርፉ ላይ ያሉ መመሪያና ደንቦች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠቱ ለሁለም የሚበጅ መሆኑን ገልፀዋል።
ኦዲት የሀገራዊ ኢኮኖሚ ውጤታማነትን የሚጨምር ነው ያሉት ስራ አስፈፃሚው ተቋማት በዘርፉ ላይ የግንዛቤ አቅምን በመፍጠር የሀገራዊ ብሎም የተቋሙን የአሰራር ስርዓት በማሳለጥ የሚፈለገውን ውጤት ለማስመዝገብ ምቹ ስነምህዳር ይፈጥራል ብለዋል።
የኦዲት ስራ ጫናን ለመቀነስ እየተተገበረ ያለው የዲጂታል አገልግሎት ከሚያመጣው ታምራዊ ለውጥ ባሻገር የኦዲት ህግና ደንብ ዙሪያ የተቋም የሰው ሀይል ልማት ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ገልፀዋል።
በቀጣይ የፋይናሻል ኦዲት የማይሸፍናቸውን ስራዎች በግብ ተኮር የሆነው የክዋኔ ኦዲትን ተግባራዊ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተጠቁሟል።
በመድረኩ ሁሉም ሰራተኛ የመንግስትን ያሰራር ስርዓቶችን ጠንቅቆ በማወቅ የተመደበበትን ስራ በውጤታማነት ለማከናወን የሚያግዘውን የፋይናንስና የክዋኔ ኦዲት ዕውቀት የሚያገኝበትን ዕድል በየጊዜው መፈጠር እንዳለበት ተሳታፊዎች አንስተዋል።
==================
የኢኖቬሽንና ቴክኖሊጂ ሚኒስቴር ለመካከለኛ አመራሮች የፋይናንስና የክዋኔ ኦዲት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል።
በኢኖቬሽንና ቴክኖሊጂ ሚኒስቴር የኦዲት ስራ አስፈፃሚ አቶ አሻግሬ አለሙ የፋይናንስና የክዋኔ ኦዲት ላይ የጠራ ግንዛቤ መፍጠር ለተቋማዊ ውጤታማነት ያለውን ሚና አስረድተዋል።
ተቋማት ሳያውቁ ከሚሰሯቸው የኦዲት ግኝቶች ለመታደግ በዘርፉ ላይ ያሉ መመሪያና ደንቦች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠቱ ለሁለም የሚበጅ መሆኑን ገልፀዋል።
ኦዲት የሀገራዊ ኢኮኖሚ ውጤታማነትን የሚጨምር ነው ያሉት ስራ አስፈፃሚው ተቋማት በዘርፉ ላይ የግንዛቤ አቅምን በመፍጠር የሀገራዊ ብሎም የተቋሙን የአሰራር ስርዓት በማሳለጥ የሚፈለገውን ውጤት ለማስመዝገብ ምቹ ስነምህዳር ይፈጥራል ብለዋል።
የኦዲት ስራ ጫናን ለመቀነስ እየተተገበረ ያለው የዲጂታል አገልግሎት ከሚያመጣው ታምራዊ ለውጥ ባሻገር የኦዲት ህግና ደንብ ዙሪያ የተቋም የሰው ሀይል ልማት ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ገልፀዋል።
በቀጣይ የፋይናሻል ኦዲት የማይሸፍናቸውን ስራዎች በግብ ተኮር የሆነው የክዋኔ ኦዲትን ተግባራዊ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተጠቁሟል።
በመድረኩ ሁሉም ሰራተኛ የመንግስትን ያሰራር ስርዓቶችን ጠንቅቆ በማወቅ የተመደበበትን ስራ በውጤታማነት ለማከናወን የሚያግዘውን የፋይናንስና የክዋኔ ኦዲት ዕውቀት የሚያገኝበትን ዕድል በየጊዜው መፈጠር እንዳለበት ተሳታፊዎች አንስተዋል።
👍5❤2
የብሔራዊ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን የፖሊሲ ግንዛቤ መፈጠር ለተግባራዊነቱ መረጋገጥ መሰረት መሆኑ ተገለፀ፡፡
==================
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ለአሶሳ ዩኒቨርስቲ ከፍተኛ አመራሮች፣ ዳይሬክተሮች፣ ስራ አስፈፃሚዎች፣ ቡድን መሪዎችና አስተባባሪዎች የብሔራዊ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ፖሊሲ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል፡፡
የመድረኩን መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር አብዱልሙህሰን ሀሰን ተሻሽሎ የፀደቀውን የሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን ፖሊሲ ላይ የዩኒቨርሲቲውን አመራሮች ግንዛቤ ማሳደግ እና ብቁ የሰው ሀይል መፍጠር፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ ምርምር እና ፈጠራ ስራዎችን ለማሳደግ፣ ከግል ዘርፉ ጋር በጋራ ለመስራት እና የሀገር በቀል ዕውቀቶችን ለማልማት ወሳኝ ሚና እንዳለው ገልፀዋል፡፡
ሀገራችን በቴክኖሎጂና ፈጠራ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ነው ያሉት ም/ፕሬዝዳንቱ የፖሊሲውን ተግባራዊነት ለማረጋገጥ በዩኒቨርሲቲው ምሁራን የሚሰሩ የምርምርና የፈጠራ ስራዎችን ከኢንዱስትሪው ጋር በማገናኘት የአካባቢውን ማህበረሰብ እና የሀገር ልማትን ማሳደግ የሚችሉ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የፓሊሲና ስትራቴጂ ጥናትና ምርምር ተጠባባቂ መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር በኩረፅዮን አለማየሁ በ2014 ዓ.ም የተከለሰውን የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፖሊሲ ላይ ሀገራዊ ግንዛቤን ለማስፋትና አላማውን ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
==================
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ለአሶሳ ዩኒቨርስቲ ከፍተኛ አመራሮች፣ ዳይሬክተሮች፣ ስራ አስፈፃሚዎች፣ ቡድን መሪዎችና አስተባባሪዎች የብሔራዊ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ፖሊሲ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል፡፡
የመድረኩን መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር አብዱልሙህሰን ሀሰን ተሻሽሎ የፀደቀውን የሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ ኢኖቬሽን ፖሊሲ ላይ የዩኒቨርሲቲውን አመራሮች ግንዛቤ ማሳደግ እና ብቁ የሰው ሀይል መፍጠር፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ ምርምር እና ፈጠራ ስራዎችን ለማሳደግ፣ ከግል ዘርፉ ጋር በጋራ ለመስራት እና የሀገር በቀል ዕውቀቶችን ለማልማት ወሳኝ ሚና እንዳለው ገልፀዋል፡፡
ሀገራችን በቴክኖሎጂና ፈጠራ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ ነው ያሉት ም/ፕሬዝዳንቱ የፖሊሲውን ተግባራዊነት ለማረጋገጥ በዩኒቨርሲቲው ምሁራን የሚሰሩ የምርምርና የፈጠራ ስራዎችን ከኢንዱስትሪው ጋር በማገናኘት የአካባቢውን ማህበረሰብ እና የሀገር ልማትን ማሳደግ የሚችሉ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል።
በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የፓሊሲና ስትራቴጂ ጥናትና ምርምር ተጠባባቂ መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር በኩረፅዮን አለማየሁ በ2014 ዓ.ም የተከለሰውን የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ፖሊሲ ላይ ሀገራዊ ግንዛቤን ለማስፋትና አላማውን ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የፓሊሲና ስትራቴጂ፣ ጥናትና ምርምር አናሊስት ዶ/ር አበበ ሞላ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዘርፍ ተዋናይ የሆኑ ዩኒቨርስቲዎችና ሌሎች አካላት በፖሊሲው ላይ በቂ የሆነ ግንዛቤ እንዲኖራቸው በማድረግ ትግበራውን ማሳለጥ እንደሚቻል ገልፀዋል፡፡
የብሔራዊ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ፖሊሲ ደንብና መመሪያዎችን ተገንዝቦ ወደ ውጤት ለመቀየርና የዘርፉን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ የግንዛቤ ማስጨበጫው መድረክ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተሳታፊዎች ጠይቀዋል፡፡
የብሔራዊ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ፖሊሲ ደንብና መመሪያዎችን ተገንዝቦ ወደ ውጤት ለመቀየርና የዘርፉን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ የግንዛቤ ማስጨበጫው መድረክ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተሳታፊዎች ጠይቀዋል፡፡
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና የሱጆ (Suzhou) ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ
በውሃና በጤና ዘርፍ ላይ በጋራ የምርምር ላብራቶሪ ለመገንባት ተስማሙ፡፡
====================
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና የባዮ እና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከቻይናው ሱጆ (Suzhou) ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በውሃና በጤና ዘርፍ ላይ በጋራ የምርምር ላብራቶሪ ለመገንባት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ባይሳ በዳዳ ኢትዮጵያን በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዘርፍ እየሰራች ያለችውን ዘርፈ ብዙ ስራዎችና እያስመዘገበች ያለው ውጤት ዙሪያ ገለፃ አድርገዋል።
ኢትዮጵያ ከቻይና መንግስት ጋር በትብብር የምትሰራቸው ፕሮጀክቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው በውሃና በጤና ዘርፍ ላይ በጋራ የሚገነባውን የምርምር ላብራቶሪ ግንባታ ፕሮጀክት ቀደም ብሎ የተፈረመውን የስምምነት ሰነድ ወደ ትግበራ ለመግባት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በአጭርና በረጅም ጊዜ ከ 230 በላይ ኢትዮጵውያን ላይ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ላደረገው የሰው ኃይል ልማት ምስጋና በማቅረብ በቀጣይ በምርምር መሰረት ልማትና በቴክኖሎጂ ሽግግር የነበረው ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
በውሃና በጤና ዘርፍ ላይ በጋራ የምርምር ላብራቶሪ ለመገንባት ተስማሙ፡፡
====================
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርና የባዮ እና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከቻይናው ሱጆ (Suzhou) ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በውሃና በጤና ዘርፍ ላይ በጋራ የምርምር ላብራቶሪ ለመገንባት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ባይሳ በዳዳ ኢትዮጵያን በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ዘርፍ እየሰራች ያለችውን ዘርፈ ብዙ ስራዎችና እያስመዘገበች ያለው ውጤት ዙሪያ ገለፃ አድርገዋል።
ኢትዮጵያ ከቻይና መንግስት ጋር በትብብር የምትሰራቸው ፕሮጀክቶች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው በውሃና በጤና ዘርፍ ላይ በጋራ የሚገነባውን የምርምር ላብራቶሪ ግንባታ ፕሮጀክት ቀደም ብሎ የተፈረመውን የስምምነት ሰነድ ወደ ትግበራ ለመግባት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በአጭርና በረጅም ጊዜ ከ 230 በላይ ኢትዮጵውያን ላይ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ላደረገው የሰው ኃይል ልማት ምስጋና በማቅረብ በቀጣይ በምርምር መሰረት ልማትና በቴክኖሎጂ ሽግግር የነበረው ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
