ለእቅድ ዝግጅት እና ክትትል ተገቢዉን ትኩረት በመስጠት ዉጤታማ መሆን ይገባል ተባለ
=============================================================
(ጳጉሜ 3/2013 ዓም) ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ከትናንት ጀምሮ ለሁለት ቀናት ለሚኒስቴር መስሪያቤቱ ዳይሬክተር ጀኔራሎች፣ዳይሬክተሮች እና ቡድን መሪዎች ሲሰጥ የነበረዉ የአመራር አቅም ግንባታ ስልጠና በበየነ መረብ ባደረጉት ማጠቃለያ የህዝብ አመኔታን ለማግኘት ለእቅድ ዝግጅት እና ክትትል ተገቢዉን ትኩረት በመስጠት እና የተገልጋይ እርካታን በየጊዜዉ መለካት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በአገልግሎት አሰጣጥ፣በእቅድ፣ግዢ እና ፋይናንስ እና አስተዳደር ነክ ጉዳዮች ላይ ያተኮረዉ ስልጠና በ2013 ዓም የተሰሩ ስራዎችን መነሻ ያደረገ በመሆኑ አመራሩ ለ2014 ዓ.ም ምን ላይ መድረስ አለብን፣ግባችንን ለማሳካት ምን ምን ተግባራት እንፈጽማለን የሚሉ ወሳኝ ጥያቄዎችን በመረጃ ላይ ተመስርቶ እንዲመልስ የሚያግዙ ናቸዉ ብለዋል፡፡
ስልጠናዉ ከበጀት እና ፋይናንስ አመራራችን ጋር በተገናኘ የሚገጥሙንን መነቆዎች ለመፍታት የሚያግዝ በመሆኑ በጀትን በዉጤታማት መምራት እንዲሁም በሀብት እና ቴክኒክ የሚደግፉንን የልማት አጋሮች መረዳትና በተገቢዉ ለማሰማራት በአዲሱ ዓመት በትኩረት መስራት እንደሚገባም አክለዋል፡፡
ስልጠናዉ በዛሬ ዉሎ የሳይንስ ፣ አስተዳደርና መሰረተ ልማት፣ቴክኒክና ሙያ፣አለምአቀፍ ትብብር እና ትስስር እና ስትራቴጂክ እቅድ ዘርፎች ዉጤት አመላካቾች በየዳይሬክተር ጀነራሎች በዶ/ር ሰለሞን ቢኖር፣ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ፣አቶ መለሰ…፣አቶ ደሳለኝ ሳሙኤል እና አቶ ከበደ ግዘዉ ቀርበዉ ዉይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
ለሁለት ቀናት ለሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዳይሬክተር ጀኔራሎች፣ዳይሬክተሮች እና ቡድን መሪዎች ሲሰጥ የነበረዉ የአመራር አቅም ግንባታ ስልጠና በአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ የ2013 ዓም አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ማጠቃለያ ችግኝ በመትከል ተጠናቋል፡
=============================================================
(ጳጉሜ 3/2013 ዓም) ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ከትናንት ጀምሮ ለሁለት ቀናት ለሚኒስቴር መስሪያቤቱ ዳይሬክተር ጀኔራሎች፣ዳይሬክተሮች እና ቡድን መሪዎች ሲሰጥ የነበረዉ የአመራር አቅም ግንባታ ስልጠና በበየነ መረብ ባደረጉት ማጠቃለያ የህዝብ አመኔታን ለማግኘት ለእቅድ ዝግጅት እና ክትትል ተገቢዉን ትኩረት በመስጠት እና የተገልጋይ እርካታን በየጊዜዉ መለካት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በአገልግሎት አሰጣጥ፣በእቅድ፣ግዢ እና ፋይናንስ እና አስተዳደር ነክ ጉዳዮች ላይ ያተኮረዉ ስልጠና በ2013 ዓም የተሰሩ ስራዎችን መነሻ ያደረገ በመሆኑ አመራሩ ለ2014 ዓ.ም ምን ላይ መድረስ አለብን፣ግባችንን ለማሳካት ምን ምን ተግባራት እንፈጽማለን የሚሉ ወሳኝ ጥያቄዎችን በመረጃ ላይ ተመስርቶ እንዲመልስ የሚያግዙ ናቸዉ ብለዋል፡፡
ስልጠናዉ ከበጀት እና ፋይናንስ አመራራችን ጋር በተገናኘ የሚገጥሙንን መነቆዎች ለመፍታት የሚያግዝ በመሆኑ በጀትን በዉጤታማት መምራት እንዲሁም በሀብት እና ቴክኒክ የሚደግፉንን የልማት አጋሮች መረዳትና በተገቢዉ ለማሰማራት በአዲሱ ዓመት በትኩረት መስራት እንደሚገባም አክለዋል፡፡
ስልጠናዉ በዛሬ ዉሎ የሳይንስ ፣ አስተዳደርና መሰረተ ልማት፣ቴክኒክና ሙያ፣አለምአቀፍ ትብብር እና ትስስር እና ስትራቴጂክ እቅድ ዘርፎች ዉጤት አመላካቾች በየዳይሬክተር ጀነራሎች በዶ/ር ሰለሞን ቢኖር፣ዶ/ር ሰለሞን አብርሃ፣አቶ መለሰ…፣አቶ ደሳለኝ ሳሙኤል እና አቶ ከበደ ግዘዉ ቀርበዉ ዉይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
ለሁለት ቀናት ለሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዳይሬክተር ጀኔራሎች፣ዳይሬክተሮች እና ቡድን መሪዎች ሲሰጥ የነበረዉ የአመራር አቅም ግንባታ ስልጠና በአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ የ2013 ዓም አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ማጠቃለያ ችግኝ በመትከል ተጠናቋል፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትርና ተጠሪ ተቋማት በክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር ያሳደሷቸዉን አቅመ ደካማ ቤቶችን አስረከቡ
ግሜ 5/2014 ዓ.ም) የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ካዛንቺስ በክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር ያሳደሷቸዉን የሁለት አቅመ ደካማ ቤቶችን ግንባታዉን በማጠናቀቅና ቁሳቁስ በማሟላት ያስረከበ ሲሆን የበአል መዋያ በግ በስጠታ አበርክቷል፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶ/ር ሳሙኤል ኡርቃቶ በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት የክረምት በጎ ፈቃድ በጠቅላይ ሚኒስቴር አቢይ አህመድ ተጀምረዉ ወደ ስራ ከተቀየሩ ትልልቅ ሃሳቦችን አንዱ ነዉ፡፡ “ሀሳቡን ወደ መሬት አዉርደን በዚህ መንገድ ማገዛችን ከተባበርን ምን መስራት እንደምንችል ትምህርት ያገኘንበትና ሌሎች ትልልቅ ሃገራዊ የሆኑ ጉዳዮችን በትብብር መስራት እንደሚቻል ያሳየንበት ተግባር ነዉ” ብለዋል ሚኒስትሩ፡፡
ለሚኒስቴር መ/ቤቱ 45 የመንግስት ዩኒቨርስቲዎችም በተመሳሳይ መልኩ የክረምት በጎ ፈቃድ ስራ እያከናወኑ ነዉ ያሉት ሚኒስትሩ በቀጣይም ሌሎችን ተግባራትም አጠናክረን እንቀጥላለን በማለት ለሰሩ፣ ለመሩና ለተባበሩ ሰዎችም በተቋሙ ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በበኩላቸዉ “ከተባባርንና ጥቂት ነገር ካዋጣን የተሻለ ሃገር መፍጠር እንደምንችል ማሳያ ነዉ፡፡ ካለን ትንሽ ነገር ላይ ቀንሰን ለተወሰኑት መድረስ እንችላለን፡፡ ይህንንም በየአመቱ እየሰራን ከሄድን ዜጎችን የተሻለ ኑሮ ደረጃ እንዲደርሱና የተሻለ ኑሮ መምራት እንዲችሉ ማድረግ እንችላለን” ብለዋል፡፡
እኛ ኢትዮጵያዊያን በፍቅር ከተጋገዝን አሁን ያለብንን ችግር አይደለም ሌሎችን መጋፈጥና መሻገር እንደምንችል ያሳየ ነዉ ብለዋል ሚኒስትር ዴኤታዉ፡፡
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ስራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል ረዲ በበኩላቸዉ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የሰራዉ ስራ የአቅመ ደካሞችን ቤት አፍርሶ ከብርድና ዝናብ መከላከል ከእገዛዉ ሁሉ ትልቅ እገዛ ነዉ ፡፡ይህም በአዲስ አመት መልካምነትን ያሳየንበት በጋራ የተባበርንበት ነዉ ብለዋል፡፡
የቤት እድሳት የተደረገላቸዉ ወ/ሮ እየሩሳሌም ወንድሙና ወ/ሮ አባይነሽ አለሙ ከዛሬ ነገ ፈረሰብን እያልን እንፈራና እንጨነቅ ነበር ፡፡ ፈጣሪ ይመስገን ይህን የመሰለ ቤት ስለተሰራልንና ሙሉ የቤት ቁሳቁስና እንዲሁም የበአል መዋያ ስለተሰጠን ደስ ብሎናል እናመሰግናለን ብለዋል፡፡
በርክክብ ስነ ስርአቱ ላይ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትሮች፣ የተጠሪ ተቋማት ሃላፊዎች፣ የክፍለ ከተማዉና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም የአካባቢዉ ነዋሪዎች ተገኝተዋል፡፡
ግሜ 5/2014 ዓ.ም) የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ካዛንቺስ በክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር ያሳደሷቸዉን የሁለት አቅመ ደካማ ቤቶችን ግንባታዉን በማጠናቀቅና ቁሳቁስ በማሟላት ያስረከበ ሲሆን የበአል መዋያ በግ በስጠታ አበርክቷል፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶ/ር ሳሙኤል ኡርቃቶ በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት የክረምት በጎ ፈቃድ በጠቅላይ ሚኒስቴር አቢይ አህመድ ተጀምረዉ ወደ ስራ ከተቀየሩ ትልልቅ ሃሳቦችን አንዱ ነዉ፡፡ “ሀሳቡን ወደ መሬት አዉርደን በዚህ መንገድ ማገዛችን ከተባበርን ምን መስራት እንደምንችል ትምህርት ያገኘንበትና ሌሎች ትልልቅ ሃገራዊ የሆኑ ጉዳዮችን በትብብር መስራት እንደሚቻል ያሳየንበት ተግባር ነዉ” ብለዋል ሚኒስትሩ፡፡
ለሚኒስቴር መ/ቤቱ 45 የመንግስት ዩኒቨርስቲዎችም በተመሳሳይ መልኩ የክረምት በጎ ፈቃድ ስራ እያከናወኑ ነዉ ያሉት ሚኒስትሩ በቀጣይም ሌሎችን ተግባራትም አጠናክረን እንቀጥላለን በማለት ለሰሩ፣ ለመሩና ለተባበሩ ሰዎችም በተቋሙ ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በበኩላቸዉ “ከተባባርንና ጥቂት ነገር ካዋጣን የተሻለ ሃገር መፍጠር እንደምንችል ማሳያ ነዉ፡፡ ካለን ትንሽ ነገር ላይ ቀንሰን ለተወሰኑት መድረስ እንችላለን፡፡ ይህንንም በየአመቱ እየሰራን ከሄድን ዜጎችን የተሻለ ኑሮ ደረጃ እንዲደርሱና የተሻለ ኑሮ መምራት እንዲችሉ ማድረግ እንችላለን” ብለዋል፡፡
እኛ ኢትዮጵያዊያን በፍቅር ከተጋገዝን አሁን ያለብንን ችግር አይደለም ሌሎችን መጋፈጥና መሻገር እንደምንችል ያሳየ ነዉ ብለዋል ሚኒስትር ዴኤታዉ፡፡
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ስራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል ረዲ በበኩላቸዉ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የሰራዉ ስራ የአቅመ ደካሞችን ቤት አፍርሶ ከብርድና ዝናብ መከላከል ከእገዛዉ ሁሉ ትልቅ እገዛ ነዉ ፡፡ይህም በአዲስ አመት መልካምነትን ያሳየንበት በጋራ የተባበርንበት ነዉ ብለዋል፡፡
የቤት እድሳት የተደረገላቸዉ ወ/ሮ እየሩሳሌም ወንድሙና ወ/ሮ አባይነሽ አለሙ ከዛሬ ነገ ፈረሰብን እያልን እንፈራና እንጨነቅ ነበር ፡፡ ፈጣሪ ይመስገን ይህን የመሰለ ቤት ስለተሰራልንና ሙሉ የቤት ቁሳቁስና እንዲሁም የበአል መዋያ ስለተሰጠን ደስ ብሎናል እናመሰግናለን ብለዋል፡፡
በርክክብ ስነ ስርአቱ ላይ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትሮች፣ የተጠሪ ተቋማት ሃላፊዎች፣ የክፍለ ከተማዉና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም የአካባቢዉ ነዋሪዎች ተገኝተዋል፡፡