የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞች ‹‹የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተመንግስት›› ህዝባዊ ንቅናቄ ተቀላቀሉ
======================================
(መስከረም 19/2014ዓ.ም) የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞች ‹‹የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተመንግስት›› ህዝባዊ ንቅናቄ ፕሮግራም በዛሬዉ እለት አካሂደዋል።
“የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ-መንግስት” በሚል መሪ ሃሳብ የአሸባሪውን ሕወሓት ሀገር የማፍረስ እቅድ ለማጋለጥ እንደ ሃገር ከመስከረም 3 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ንቅናቄዉ እየተካሄደ ይገኛል።
የዚህ ንቅናቄ ዋና ዋና ዓላማዎች በአገራችን ኢትዮጵያ ላይ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እየደረሰ ያለውን ያልተገባ አሉታዊ ጫና ለመመከት፣ የኢትዮጵያውያን እውነታ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ፣ የአሸባሪውን ህወሓት አገር የማፍረስ ወረራ ለማጋለጥ እና በሰሜን ዕዝ የመከላከያ ሰራዊት ላይ አሸባሪው ህወሓት የፈጸመውን ግፍ ማሳየት ሲሆን ይህ ፕሮግራም እንደአገር እየተካሄደ ባለዉ የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግስት ዘመቻ አጋርነታችንን የምንገልጽበት እና በአገራዊ ጉዳይም ያለንን ድጋፍ በፊርማ የምናረጋግጥበት መሆኑ በተሳታፊ ሰራተኞች ተገልጸዋል፡፡
በዛሬው ዕለት የተካሄደውን መርሃ ግብር ጨምሮ በዘመቻው የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች፣ ዳይሬክተር ጀኔራሎች ፣ ዳይሬክተሮች እና ሌሎች ከ210 በላይ ሰራተኞች ተሳትፈዋል።
======================================
(መስከረም 19/2014ዓ.ም) የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሰራተኞች ‹‹የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተመንግስት›› ህዝባዊ ንቅናቄ ፕሮግራም በዛሬዉ እለት አካሂደዋል።
“የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ-መንግስት” በሚል መሪ ሃሳብ የአሸባሪውን ሕወሓት ሀገር የማፍረስ እቅድ ለማጋለጥ እንደ ሃገር ከመስከረም 3 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ንቅናቄዉ እየተካሄደ ይገኛል።
የዚህ ንቅናቄ ዋና ዋና ዓላማዎች በአገራችን ኢትዮጵያ ላይ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እየደረሰ ያለውን ያልተገባ አሉታዊ ጫና ለመመከት፣ የኢትዮጵያውያን እውነታ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ፣ የአሸባሪውን ህወሓት አገር የማፍረስ ወረራ ለማጋለጥ እና በሰሜን ዕዝ የመከላከያ ሰራዊት ላይ አሸባሪው ህወሓት የፈጸመውን ግፍ ማሳየት ሲሆን ይህ ፕሮግራም እንደአገር እየተካሄደ ባለዉ የነጩ ፖስታ ጎርፍ ወደ ነጩ ቤተ መንግስት ዘመቻ አጋርነታችንን የምንገልጽበት እና በአገራዊ ጉዳይም ያለንን ድጋፍ በፊርማ የምናረጋግጥበት መሆኑ በተሳታፊ ሰራተኞች ተገልጸዋል፡፡
በዛሬው ዕለት የተካሄደውን መርሃ ግብር ጨምሮ በዘመቻው የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች፣ ዳይሬክተር ጀኔራሎች ፣ ዳይሬክተሮች እና ሌሎች ከ210 በላይ ሰራተኞች ተሳትፈዋል።
የሴቶችን አቅም ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየተሰራ ነዉ
=====================================
(መስከረም 22/2014ዓ.ም) የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የሴት ሰራተኞችን አቅም፣ ክህሎትና ተሳታፊነት ለማሳደግ እንዲሁም ተጠቃሚነታቸዉን ለማረጋገጥ ለሴት ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በቢሾፍቱ ከተማ እየሰጠ ይገኛል።
ወ/ሮ ማህሌት በቀለ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ስልጠናዉ በጾታ፣ ስርአተ ጾታ እና አስቻይ ህጎች ዙሪያ ለተቋሙ ሴት ሰራተኞች የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል።
አላማዉም ስርአተ ጾታንና የሴቶችን ጉዳይ በሁሉም ስራ ላይ ለማካተት፣ የሴቶችን አደራጃጀትና ተሳትፎ ለማሳደግ ነዉ ብለዋል።
ወ/ሮ ማህሌት አያይዘዉም ይህ ስልጠና በተለይም ሴቶች በተናጠል ከሚደረገዉ እንቅስቃሴ ይልቅ ተደራጅተዉ ያላቸዉን ችሎታ፣ እዉቀትና አቅም በጋራ በመንቀሳቀስ የተሻለ ዉጤት ለማስመዝገብ እንዲሁም ተጠቃሚነታቸዉን ለማረጋገጥና ተሳትፎቸዉን ለማሳደግ የሚረዳ ነዉ ብለዋል።
በስልጠናዉ የተቋሙ ሴት አመራሮች፣ ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ ።
=====================================
(መስከረም 22/2014ዓ.ም) የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የሴት ሰራተኞችን አቅም፣ ክህሎትና ተሳታፊነት ለማሳደግ እንዲሁም ተጠቃሚነታቸዉን ለማረጋገጥ ለሴት ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በቢሾፍቱ ከተማ እየሰጠ ይገኛል።
ወ/ሮ ማህሌት በቀለ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ስልጠናዉ በጾታ፣ ስርአተ ጾታ እና አስቻይ ህጎች ዙሪያ ለተቋሙ ሴት ሰራተኞች የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል።
አላማዉም ስርአተ ጾታንና የሴቶችን ጉዳይ በሁሉም ስራ ላይ ለማካተት፣ የሴቶችን አደራጃጀትና ተሳትፎ ለማሳደግ ነዉ ብለዋል።
ወ/ሮ ማህሌት አያይዘዉም ይህ ስልጠና በተለይም ሴቶች በተናጠል ከሚደረገዉ እንቅስቃሴ ይልቅ ተደራጅተዉ ያላቸዉን ችሎታ፣ እዉቀትና አቅም በጋራ በመንቀሳቀስ የተሻለ ዉጤት ለማስመዝገብ እንዲሁም ተጠቃሚነታቸዉን ለማረጋገጥና ተሳትፎቸዉን ለማሳደግ የሚረዳ ነዉ ብለዋል።
በስልጠናዉ የተቋሙ ሴት አመራሮች፣ ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ ።
አዲስ ምዕራፍ
New Beginning
መስከረም 24, 2014 ዓ.ም
October_4_ 2021
ለክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ አሊ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር !! መልካም የስራ ዘመን እንመኛለን!
New Beginning
መስከረም 24, 2014 ዓ.ም
October_4_ 2021
ለክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ አሊ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር !! መልካም የስራ ዘመን እንመኛለን!