STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት) ️
Photo
👉ለመሆኑ የተማሪዎቹ ጉዳይ ከሕግ አንጻር እንዴት ይታያል❓
በጅማ ዩኒቨርሲቲ የሕግ መምህር የሆኑት ሃብታሙ ለገሰ የማይገባቸውን ገንዘብ ወጪ ያደረጉት ግለሰቦች በወንጀል እንደሚጠየቁ ይናገራሉ።
የሕግ መምህሩ፤ “የሲስተም ችግሩን መሠረት በማድረግ ለራስ ወይም ለሌሎች የማይገባን ጥቅም ለማግኘት የተፈጸመው ተግባር የኮምፒዩር ወንጀልን ለመደንገግ በወጣ አዋጅ ሊታይ የሚችል የወንጀል ድርጊት ነው” ይላሉ።
ንግድ ባንክ ካጋጠመው ክስተት ጋር በተያያዘ የተፈጸመው ተግባር በዚህ የኮምፒዩር ወንጀልን ለመደንገግ በወጣው አዋጅ ሊታይ አይችልም ቢባል እንኳ ጉዳዩ በመደበኛው የስርቆት ወንጀል ሊዳኝ እንደሚችል ሃብታሙ ይናገራሉ።
የሕግ መምህሩ እንደሚሉት የራሳቸው ያልሆነን ገንዘብ ያወጡ ተማሪዎች በ3 ዓመት የቀላል እስራት እና ከ30ሺህ ብር ባልበለጠ የገንዘብ ቅጣት ሊቀጡ ይችላሉ ይላሉ።
“ወንጀሉን የተፈጸመበትን ሁኔታ ከግምት በማስገባት ብዙ ርቀት ሄደው ብዙ ገንዘብ የወሰዱ ግለሰቦች ቅጣት ከዚህም በላይ ከባድ ቅጣት ሊጠብቃቸው ይችላል”
ከእውቅናቸው ውጪ ገንዘብ ገቢ የተደረገላቸውም ግለሰቦች ቢሆኑ የራሳቸው ያልሆነን ገንዘብ ወይም የወንጀል ድርጊት ውጤት የሆነን ገንዘብ ይዞ በማቆየት በወንጀል ተጠያቂ እንደሚሆኑ ጨምረው አስረድተዋል።
የንግድ ባንክ የሲስተም ችግርን እንደ መልካም አጋጣሚ ተጠቅመው ገንዘብ የወሰዱ ተማሪዎች የማይገባቸውን ገንዘብ በአስቸኳይ ተመላሽ እንዲያደርጉ አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ማስጠንቀቂያ አዘል ማስታወቂያዎችን ማውጣታቸው ይታወሳል።
የሕግ መምህሩ ግን ዩኒቨርሲቲዎች ይህን የወንጀል ጉዳይ የመመልከት ሥልጣን የላቸውም ይላሉ።
“ዩኒቨርሲቲዎች መመልከት የሚችሉት የባሕሪ ወይም የዲስፕሊን ግድፈቶችን እንጂ የወንጀል ጉዳዮችን ማየት አይቻላቸውም። ሊያደርጉ የሚችሉት ከሚመለከተው አካል ጋር ትብብር ማድረግ ነው” ይላሉ።
ምንም እንኳ ጥሬ ገንዘብን በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ጊቢዎች ውስጥ ከሚገኙ ገንዘብ መክፈያ ማሽኖች (ኤቲኤም) ወጪ ቢያደርጉም ተማሪዎች ያለ አግባብ የተጠቀሙት የንግድ ባንክ ሥርዓትን እንጂ የኤቲኤም ማሽኑን አይደለም ይላሉ።
[ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው]
@NATIONALEXAMSRESULT
በጅማ ዩኒቨርሲቲ የሕግ መምህር የሆኑት ሃብታሙ ለገሰ የማይገባቸውን ገንዘብ ወጪ ያደረጉት ግለሰቦች በወንጀል እንደሚጠየቁ ይናገራሉ።
የሕግ መምህሩ፤ “የሲስተም ችግሩን መሠረት በማድረግ ለራስ ወይም ለሌሎች የማይገባን ጥቅም ለማግኘት የተፈጸመው ተግባር የኮምፒዩር ወንጀልን ለመደንገግ በወጣ አዋጅ ሊታይ የሚችል የወንጀል ድርጊት ነው” ይላሉ።
ንግድ ባንክ ካጋጠመው ክስተት ጋር በተያያዘ የተፈጸመው ተግባር በዚህ የኮምፒዩር ወንጀልን ለመደንገግ በወጣው አዋጅ ሊታይ አይችልም ቢባል እንኳ ጉዳዩ በመደበኛው የስርቆት ወንጀል ሊዳኝ እንደሚችል ሃብታሙ ይናገራሉ።
የሕግ መምህሩ እንደሚሉት የራሳቸው ያልሆነን ገንዘብ ያወጡ ተማሪዎች በ3 ዓመት የቀላል እስራት እና ከ30ሺህ ብር ባልበለጠ የገንዘብ ቅጣት ሊቀጡ ይችላሉ ይላሉ።
“ወንጀሉን የተፈጸመበትን ሁኔታ ከግምት በማስገባት ብዙ ርቀት ሄደው ብዙ ገንዘብ የወሰዱ ግለሰቦች ቅጣት ከዚህም በላይ ከባድ ቅጣት ሊጠብቃቸው ይችላል”
ከእውቅናቸው ውጪ ገንዘብ ገቢ የተደረገላቸውም ግለሰቦች ቢሆኑ የራሳቸው ያልሆነን ገንዘብ ወይም የወንጀል ድርጊት ውጤት የሆነን ገንዘብ ይዞ በማቆየት በወንጀል ተጠያቂ እንደሚሆኑ ጨምረው አስረድተዋል።
የንግድ ባንክ የሲስተም ችግርን እንደ መልካም አጋጣሚ ተጠቅመው ገንዘብ የወሰዱ ተማሪዎች የማይገባቸውን ገንዘብ በአስቸኳይ ተመላሽ እንዲያደርጉ አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ማስጠንቀቂያ አዘል ማስታወቂያዎችን ማውጣታቸው ይታወሳል።
የሕግ መምህሩ ግን ዩኒቨርሲቲዎች ይህን የወንጀል ጉዳይ የመመልከት ሥልጣን የላቸውም ይላሉ።
“ዩኒቨርሲቲዎች መመልከት የሚችሉት የባሕሪ ወይም የዲስፕሊን ግድፈቶችን እንጂ የወንጀል ጉዳዮችን ማየት አይቻላቸውም። ሊያደርጉ የሚችሉት ከሚመለከተው አካል ጋር ትብብር ማድረግ ነው” ይላሉ።
ምንም እንኳ ጥሬ ገንዘብን በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ጊቢዎች ውስጥ ከሚገኙ ገንዘብ መክፈያ ማሽኖች (ኤቲኤም) ወጪ ቢያደርጉም ተማሪዎች ያለ አግባብ የተጠቀሙት የንግድ ባንክ ሥርዓትን እንጂ የኤቲኤም ማሽኑን አይደለም ይላሉ።
[ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው]
@NATIONALEXAMSRESULT
👍24🤪9
#Update
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች ምዝገባ ማድረጋቸውን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በቅርቡ መግለፃቸው ይታወሳል፡፡
የፀጥታ ችግር ካለባቸው አካባቢዎች በስተቀር በአብዛኛው የአገሪቱ አካባቢዎች የተማሪዎች ምዝገባ መጠናቀቁም ተገልጿል።
የፈተናው ሕትመት በቀጣይ ቀናት እንደሚጀመር ለኢሳት የገለፁት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥም አረጋግጠዋል፡፡
ለ3ኛ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጠው ብሔራዊ ፈተናው፤ ዘንድሮ ለተፈጥሮ ሳይንስ እና ማኅበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስኮች ለእያንዳንዳቸው በስድስት የትምህርት አይነቶች እንዲሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር መወሰኑ አይዘነጋም።
@NATIONALEXAMSRESULT
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች ምዝገባ ማድረጋቸውን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በቅርቡ መግለፃቸው ይታወሳል፡፡
የፀጥታ ችግር ካለባቸው አካባቢዎች በስተቀር በአብዛኛው የአገሪቱ አካባቢዎች የተማሪዎች ምዝገባ መጠናቀቁም ተገልጿል።
የፈተናው ሕትመት በቀጣይ ቀናት እንደሚጀመር ለኢሳት የገለፁት ዋና ዳይሬክተሩ፤ የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሰኔ ወር እንደሚሰጥም አረጋግጠዋል፡፡
ለ3ኛ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚሰጠው ብሔራዊ ፈተናው፤ ዘንድሮ ለተፈጥሮ ሳይንስ እና ማኅበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስኮች ለእያንዳንዳቸው በስድስት የትምህርት አይነቶች እንዲሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር መወሰኑ አይዘነጋም።
@NATIONALEXAMSRESULT
👍23❤5
የእርዳታ ተማጽኖ
ዲያቆን ሱራፌል ገረመው መኮንን የ24 ዓመት ወጣት ሲሆን፤ የግራፊክስ ባለሙያ ነው።
እንዲሁም በረጲ መካነ ጎልጎታ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በድቁና አገልጋይ ነው።
ባለፉት ስድስት ወራት በገጠመው ከባድ የጉበት ህመም ምክንያት በተለያዩ ሆስፒታሎች የህክምና ክትትል ሲያደርግ ቢቆይም፤ ህመሙ ከፍተኛ ደረጃ ላይ በመድረሱ አስቸኳይ የጉበት ንቅለ ተከላ ማድረግ እንደሚገባው የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህክምና ቦርድ ወስኗል።
የጉበት ንቅለ ተከላ ህክምናው በሀገር ውስጥ የማይሰጥ ሲሆን፤ በውጭ ሀገር ህክምናውን ለማግኘት እስከ ስድስት ሚሊየን ብር እንደሚያስፈልግ ተጠይቋል።
ይህ ወጪ ከቤተሰብ አቅም በላይ በመሆኑ የወገኖቻችንን ድጋፍ መጠየቅ ግድ ብሎናል።
በመሆኑም በወጣት ሱራፌል ገረመው የህክምና ድጋፍ አስተባባሪዎች፤ መሰረት ፀጋዬ፣ አለልኝ ዋለ እና ሎንያስ ገዛኸኝ ስም በጋራ በተከፈቱ አካውንቶች፤
1000610015585 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
2957769765811 ዳሸን ባንክ
177682853 አቢሲኒያ ባንክ
የተቻላችሁን ወገናዊ ድጋፍ እንድታደርጉልን እንጠይቃለን።
ለተጨማሪ መረጃ
+251947328673 ኤልሳቤጥ ገረመው
+251946727171 ሎንያስ ገዛኸኝ
ዲያቆን ሱራፌል ገረመው መኮንን የ24 ዓመት ወጣት ሲሆን፤ የግራፊክስ ባለሙያ ነው።
እንዲሁም በረጲ መካነ ጎልጎታ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በድቁና አገልጋይ ነው።
ባለፉት ስድስት ወራት በገጠመው ከባድ የጉበት ህመም ምክንያት በተለያዩ ሆስፒታሎች የህክምና ክትትል ሲያደርግ ቢቆይም፤ ህመሙ ከፍተኛ ደረጃ ላይ በመድረሱ አስቸኳይ የጉበት ንቅለ ተከላ ማድረግ እንደሚገባው የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህክምና ቦርድ ወስኗል።
የጉበት ንቅለ ተከላ ህክምናው በሀገር ውስጥ የማይሰጥ ሲሆን፤ በውጭ ሀገር ህክምናውን ለማግኘት እስከ ስድስት ሚሊየን ብር እንደሚያስፈልግ ተጠይቋል።
ይህ ወጪ ከቤተሰብ አቅም በላይ በመሆኑ የወገኖቻችንን ድጋፍ መጠየቅ ግድ ብሎናል።
በመሆኑም በወጣት ሱራፌል ገረመው የህክምና ድጋፍ አስተባባሪዎች፤ መሰረት ፀጋዬ፣ አለልኝ ዋለ እና ሎንያስ ገዛኸኝ ስም በጋራ በተከፈቱ አካውንቶች፤
1000610015585 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
2957769765811 ዳሸን ባንክ
177682853 አቢሲኒያ ባንክ
የተቻላችሁን ወገናዊ ድጋፍ እንድታደርጉልን እንጠይቃለን።
ለተጨማሪ መረጃ
+251947328673 ኤልሳቤጥ ገረመው
+251946727171 ሎንያስ ገዛኸኝ
😢32👍22
https://www.tg-me.com/notcoin_bot?start=r_573809_33060966
🎁 +2.5k Notcoin as a first-time gift
🎁🎁🎁 +50k Notcoin if you have Telegram Premium @PremiumBot
🎁 +2.5k Notcoin as a first-time gift
🎁🎁🎁 +50k Notcoin if you have Telegram Premium @PremiumBot
Telegram
Notcoin
Probably nothing @notcoin
👍2
በቅርቡ መክፈል ይጀምራል ተብሎ በብዙዎች ዘንድ እየተጠበቀ ያለውና Bitcoin የተባለውን መገበያያ ይገዳደራል የተባለው notcoin የቴሌግራም bot ይህ ነው።
ስንት Coin ሰራችሁ? እውን ይከፍላል ብላችሁ ታስባላችሁ?
ቦቱ አሁን ላይ ታብ በማድረግ ብቻ ለተጠቃሚዎች coin እያጠራቀመ ይገኛል።
ለመጠቀም 👇
https://www.tg-me.com/notcoin_bot?start=r_573809_33060966
ከዚያም Start ማለትና የወርቅ ሳንቲሟን ታፕ ታፕ በማድረግ coin ማጠራቀም ይቻላል።
ምንም እንኳ ብዙዎች በቅርቡ እንደ ቢትኮይን መገበያያ ይሆናል ቢሉም በዚያው ልክ ደግሞ ተቃራኒውን የሚያነሱ አልጠፉም። በተመሳሳይ ደግሞ ለማንኛውም በሚል ቦቱን አስጀምረው ከ1,000,000 በላይ coin ያጠራቀሙም ብቅ እያሉ ነው። ሩሲያውያን የቦቱ ባለቤቶችም በቅርቡ ጠብቁን ብለዋል።
በቅርቡ እናያለን
ስንት Coin ሰራችሁ? እውን ይከፍላል ብላችሁ ታስባላችሁ?
ቦቱ አሁን ላይ ታብ በማድረግ ብቻ ለተጠቃሚዎች coin እያጠራቀመ ይገኛል።
ለመጠቀም 👇
https://www.tg-me.com/notcoin_bot?start=r_573809_33060966
ከዚያም Start ማለትና የወርቅ ሳንቲሟን ታፕ ታፕ በማድረግ coin ማጠራቀም ይቻላል።
ምንም እንኳ ብዙዎች በቅርቡ እንደ ቢትኮይን መገበያያ ይሆናል ቢሉም በዚያው ልክ ደግሞ ተቃራኒውን የሚያነሱ አልጠፉም። በተመሳሳይ ደግሞ ለማንኛውም በሚል ቦቱን አስጀምረው ከ1,000,000 በላይ coin ያጠራቀሙም ብቅ እያሉ ነው። ሩሲያውያን የቦቱ ባለቤቶችም በቅርቡ ጠብቁን ብለዋል።
በቅርቡ እናያለን
👍28❤12
በኢትዮጵያ ለተማሪዎች ዉጤት መቀነስ ምክንያቱ ‹‹ከፍተኛ የሙቀት መጠን ነዉ›› ሲል የዓለም ባንክ ገለጸ🤔
የዓለም ባንክ አደረግኩት ባለዉ ጥናት በኢትዮጵያ ለተማሪዎች ዉጤት መቀነስ ምክንያቱ ከፍተኛ የሙቀት መጠን መጨመር ነዉ ብሏል፡፡
ከፈረንጆቹ 2003-2019 በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና የወሰዱ ወደ 2.5 ሚሊየን የሚጠጉ ተማሪዎችን ዳታ ሰብስቦ ያገኘዉ ዉጤት መሆኑን ነዉ ይፋ ያደረገዉ፡፡
በትምህርት ዓመቱ ለከፍተኛ ሙቀት የተዳረጉ በተለይ ደግሞ በፈተና ወቅት ከባድ ሙቀት የሚያገኛቸዉ ተማሪዎች ፤ቀዝቃዛ አየር ባለባቸዉ ስፍራዎች ከሚማሩ ተማሪዎች ጋር ሲወዳደር ዉጤታቸዉ በእጅጉ ቀንሶ ተገኝቷል ነዉ ያለዉ፡፡
እንደዚህ ዓይነት ተጽዕኖ በተለይ በሰብ-ሰሃራ አፍሪካ አገራት ላይ የበረታ ነዉ የተባለ ሲሆን፤ የአየር ንብረት ለዉጡን ለመቋቋም የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎች በስፋት አለመኖራቸዉ ሁኔታዉን እንደሚያባብሰዉም ነዉ የተገለጸዉ፡፡
የጥናቱ መሰረታዊ ግኝት የሆነዉ በትምህርት ዘመኑ ከፍተኛ ሙቀት የሚስተናገድባቸዉ ቀናት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸዉ እንዲቀሩ የሚያደርግ መሆኑን ነዉ፡፡
ይህም በኮሌጅ መግቢያ ፈተናዎች ላይ ወደ 2.28 በመቶ ዝቅ ያለ ዉጤት እንዲመዘገብ እንደሚያደርግ ነዉ፡፡
በጥናቱ ይፋ እንደሆነዉ ግልጽ የሆነ ምክንያት ባይቀመጥለትም ወንዶች ከሴቶች በበለጠ በሙቀት መጨመሩ ምክንያት የፈተና ዉጤታቸዉ ዝቅ ያለ ሆኖ ተገኝቷል፡፡
ከወንዶች ጋር ሲነጻጸሩም ሴቶች በተሻለ መልኩ በትምህርት ገበታቸዉ ላይ የሚገኙ እና ለትምህርታቸዉም ከፍተኛ ቦታ ያላቸዉ ሆነዉ ተገኝተዋል፡፡
አሁን ላይ በተለያዩ የአለማችን አገራት ለተማሪዎች ዉጤት መቀነስ የሙቀት መጨመር ምክንያት መሆኑን ማስረጃ አለን ሲሉ በዓለም ባንክ የሪሰርቸሮች ግሩፕ ዋና ተመራማሪ ፓትሪክ ቤህረር ተናግረዋል፡፡
ፓትሪክ ጨምረዉም ከፍተኛ ሙቀት ከተማሪዎቹ በተጨማሪ በመምህራን የስራ እንቅስቃሴ ላይም የራሱ ተጽዕኖ ይኖረዋል ነዉ ያሉት፡፡
ፖሊሲ አዉጪዎች ይህንን ጉዳይ በደንብ ትኩረት ሊሰጡት ይገባል ያሉት ተመራማሪዉ ፤በመማሪያ ክፍሎች ዉስጥ ያለዉን የሙቀት መጠን በማስተካከል ለተማሪዎች ምቹ የመማሪያ ስፍራን መፍጠር አለባቸዉ ብለዋል፡፡
የተሻለዉ አማራጭ እንደየአከባቢዉ የሚለያይ ቢሆንም ግን አንድ ነገር ግልጽ ነዉ ሲሉ የሚጨምሩት ተመራማሪዉ ፤ይህም ተማሪዎች ለከፍተኛ ሙቀት ያልተጋለጡ አከባቢዎች ላይ እጅግ በተሻለ ሁኔታ መማር እንደሚችሉ ነዉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በ2022 ዘ ጋርዲያን ይዞት በወጣዉ አንድ ጽሁፍ ከፍተኛ የሙቀት መጨመር በጥራት እንዳናስብ በማድረግ ፣ የማሰላሰል እና የማመዛዘን ችሎታችን ላይ ተጽዕኖ ስለሚኖረዉ ስህተት የመስራት ዕድላችንን ከፍ ያደርገዋል ሲል አስታዉቆ ነበር፡፡
@NATIONALEXAMSRESULT
የዓለም ባንክ አደረግኩት ባለዉ ጥናት በኢትዮጵያ ለተማሪዎች ዉጤት መቀነስ ምክንያቱ ከፍተኛ የሙቀት መጠን መጨመር ነዉ ብሏል፡፡
ከፈረንጆቹ 2003-2019 በኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና የወሰዱ ወደ 2.5 ሚሊየን የሚጠጉ ተማሪዎችን ዳታ ሰብስቦ ያገኘዉ ዉጤት መሆኑን ነዉ ይፋ ያደረገዉ፡፡
በትምህርት ዓመቱ ለከፍተኛ ሙቀት የተዳረጉ በተለይ ደግሞ በፈተና ወቅት ከባድ ሙቀት የሚያገኛቸዉ ተማሪዎች ፤ቀዝቃዛ አየር ባለባቸዉ ስፍራዎች ከሚማሩ ተማሪዎች ጋር ሲወዳደር ዉጤታቸዉ በእጅጉ ቀንሶ ተገኝቷል ነዉ ያለዉ፡፡
እንደዚህ ዓይነት ተጽዕኖ በተለይ በሰብ-ሰሃራ አፍሪካ አገራት ላይ የበረታ ነዉ የተባለ ሲሆን፤ የአየር ንብረት ለዉጡን ለመቋቋም የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎች በስፋት አለመኖራቸዉ ሁኔታዉን እንደሚያባብሰዉም ነዉ የተገለጸዉ፡፡
የጥናቱ መሰረታዊ ግኝት የሆነዉ በትምህርት ዘመኑ ከፍተኛ ሙቀት የሚስተናገድባቸዉ ቀናት ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸዉ እንዲቀሩ የሚያደርግ መሆኑን ነዉ፡፡
ይህም በኮሌጅ መግቢያ ፈተናዎች ላይ ወደ 2.28 በመቶ ዝቅ ያለ ዉጤት እንዲመዘገብ እንደሚያደርግ ነዉ፡፡
በጥናቱ ይፋ እንደሆነዉ ግልጽ የሆነ ምክንያት ባይቀመጥለትም ወንዶች ከሴቶች በበለጠ በሙቀት መጨመሩ ምክንያት የፈተና ዉጤታቸዉ ዝቅ ያለ ሆኖ ተገኝቷል፡፡
ከወንዶች ጋር ሲነጻጸሩም ሴቶች በተሻለ መልኩ በትምህርት ገበታቸዉ ላይ የሚገኙ እና ለትምህርታቸዉም ከፍተኛ ቦታ ያላቸዉ ሆነዉ ተገኝተዋል፡፡
አሁን ላይ በተለያዩ የአለማችን አገራት ለተማሪዎች ዉጤት መቀነስ የሙቀት መጨመር ምክንያት መሆኑን ማስረጃ አለን ሲሉ በዓለም ባንክ የሪሰርቸሮች ግሩፕ ዋና ተመራማሪ ፓትሪክ ቤህረር ተናግረዋል፡፡
ፓትሪክ ጨምረዉም ከፍተኛ ሙቀት ከተማሪዎቹ በተጨማሪ በመምህራን የስራ እንቅስቃሴ ላይም የራሱ ተጽዕኖ ይኖረዋል ነዉ ያሉት፡፡
ፖሊሲ አዉጪዎች ይህንን ጉዳይ በደንብ ትኩረት ሊሰጡት ይገባል ያሉት ተመራማሪዉ ፤በመማሪያ ክፍሎች ዉስጥ ያለዉን የሙቀት መጠን በማስተካከል ለተማሪዎች ምቹ የመማሪያ ስፍራን መፍጠር አለባቸዉ ብለዋል፡፡
የተሻለዉ አማራጭ እንደየአከባቢዉ የሚለያይ ቢሆንም ግን አንድ ነገር ግልጽ ነዉ ሲሉ የሚጨምሩት ተመራማሪዉ ፤ይህም ተማሪዎች ለከፍተኛ ሙቀት ያልተጋለጡ አከባቢዎች ላይ እጅግ በተሻለ ሁኔታ መማር እንደሚችሉ ነዉ ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በ2022 ዘ ጋርዲያን ይዞት በወጣዉ አንድ ጽሁፍ ከፍተኛ የሙቀት መጨመር በጥራት እንዳናስብ በማድረግ ፣ የማሰላሰል እና የማመዛዘን ችሎታችን ላይ ተጽዕኖ ስለሚኖረዉ ስህተት የመስራት ዕድላችንን ከፍ ያደርገዋል ሲል አስታዉቆ ነበር፡፡
@NATIONALEXAMSRESULT
😁77👍37
አዲስ ዓለም የልዩ-ፍላጎት አገልግሎት ዛሬ ማለትም ቅዳሜ ከምሽቱ2:30 ጀምሮ በtiktok አካውንቷ ብቅ ብላ ስለ ኦቲዝም ምንነት ትተነትናለች። በፕሮግራሙ ዶ/ር ስመኝ ተስፋዬ ስለ ኦቲዝም ምንነት ያዘጋጀችውን ካጋራችን በኋላ የውይይት ጊዜ ይኖረናል።
ዶ/ር ስመኝ በሐረማያ ዩኒቨርስቲ መምህርት ስትሆን፣ በማህበራዊ ገጿም ጤና ነክ ጉዳዮችን ለማህበረሰቡ በመልቀቅ ከሚመጡ ችግሮች ቀድመው ይጠነቀቁ ዘንድ ማህበራዊ ግዴታዋንም እየተወጣች ያለች እህታችን ናት። በዚህም በኦቲዝም ዙሪያ ትኩረት አድርጋ ለመስራት የምትሻ በመሆኗ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ከኦቲዝም ጋር በተያያዘ ተሳትፎ ታደርጋለች።
ዛሬ ምሽት የአዲስ ዓለም የልዩ-ፍላጎት አገልግሎት ታድማ ስለ ኦቲዝም ከቃረመችው ብሎም ለእናንተ የእውቀት ምንጭ የሚሆን መረጃ ይዛ ስለምትቀርብ በፕሮግራሙ በመታደም ብዙ ታተርፋላችሁ።
ወንድምና እህቶቼ ምናልባት እርስዎ በማጋራትዎት አንድ ሰው ሊጠቅሙ ይችላሉና ሳይሰስቱ የሚመለከታቸው ሰዎች ላይ ይደርስ ዘንድ ያጋሩ
ፕሮግራም ዛሬ ቅዳሜ ምሽት 2:30
ፕሮግራሙ የሚተላለፍባት ገጽ
👉http://tiktok.com/@belayzgetnet
👉http://tiktok.com/@simegn.tenachin
ዶ/ር ስመኝ በሐረማያ ዩኒቨርስቲ መምህርት ስትሆን፣ በማህበራዊ ገጿም ጤና ነክ ጉዳዮችን ለማህበረሰቡ በመልቀቅ ከሚመጡ ችግሮች ቀድመው ይጠነቀቁ ዘንድ ማህበራዊ ግዴታዋንም እየተወጣች ያለች እህታችን ናት። በዚህም በኦቲዝም ዙሪያ ትኩረት አድርጋ ለመስራት የምትሻ በመሆኗ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ከኦቲዝም ጋር በተያያዘ ተሳትፎ ታደርጋለች።
ዛሬ ምሽት የአዲስ ዓለም የልዩ-ፍላጎት አገልግሎት ታድማ ስለ ኦቲዝም ከቃረመችው ብሎም ለእናንተ የእውቀት ምንጭ የሚሆን መረጃ ይዛ ስለምትቀርብ በፕሮግራሙ በመታደም ብዙ ታተርፋላችሁ።
ወንድምና እህቶቼ ምናልባት እርስዎ በማጋራትዎት አንድ ሰው ሊጠቅሙ ይችላሉና ሳይሰስቱ የሚመለከታቸው ሰዎች ላይ ይደርስ ዘንድ ያጋሩ
ፕሮግራም ዛሬ ቅዳሜ ምሽት 2:30
ፕሮግራሙ የሚተላለፍባት ገጽ
👉http://tiktok.com/@belayzgetnet
👉http://tiktok.com/@simegn.tenachin
👍15👌2
የ8ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና የሚሰጥበት ቀን...
የ2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ሰኔ 4 - 5/2016 እንዲሰጥ ተወስኗል።
ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
የ2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ሰኔ 4 - 5/2016 እንዲሰጥ ተወስኗል።
ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
👍29❤3
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ የፃፈው ደብዳቤ ፡
ጉዳዩ፦ ያለአግባብ ገንዘብ ከባንክ ወጭ ያደረጉ ተማሪዎችን ይመለከታል፤
እንደሚታወቀው ባንካችን መጋቢት 06/2016ዓ.ም የሲስተም ማዘመን ስራ እየተሰራ በተፈጠረው የሲስተም ችግር ምክንያት ደንበኞች ያለአግባብ ገንዘብ ሳይኖራቸው ከሂሳባቸው ወጭ ማድረጋቸው ይታወቃል፡፡ በዚህም መሠረት ባንካችን ከአ/ምንጭ ዩኒቨርስቲ ጋር በትብብር በተሰራው የማስመለስ ስራ አብዛኛው ደንበኞች ያለአግባብ የወሰዱትን ገንዘብ መመለስ ችለዋል፡፡ ነገር ግን ጥቂት የሚባሉ ደንበኞች ዕዳቸውን ከፍለው በሚፈለገው ፍጥነት ሊመልሱ አልቻሉም፡፤
በመሆኑም ዩኒቨርስቲው ይህንን የሀገር ሃብት ለማስመለስ እስካሁን ድረስ ለሠራው ሥራ ምስጋናችንን እያቀረብን፣ የቀረውን ገንዘብ ማስመለስ ይቻል ዘንድ ከዚህ ደብዳቤ ጋር ባያያዝነው ሠንጠረዥ ላይ በተመለከተው ዝርዝር መሠረት ልክ እንደዚህ ቀደሙ በተቋሙ ለሚገኙ ተማሪዎች ያለአግባብ የወሰዱትን ገንዘብ #በ48 ሰዓት ጊዜ ውስጥ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ተመላሽ እንዲደረግ ልዩ የሆነ መመሪያ እንዲሰጣቸው በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
[የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ]
ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
ጉዳዩ፦ ያለአግባብ ገንዘብ ከባንክ ወጭ ያደረጉ ተማሪዎችን ይመለከታል፤
እንደሚታወቀው ባንካችን መጋቢት 06/2016ዓ.ም የሲስተም ማዘመን ስራ እየተሰራ በተፈጠረው የሲስተም ችግር ምክንያት ደንበኞች ያለአግባብ ገንዘብ ሳይኖራቸው ከሂሳባቸው ወጭ ማድረጋቸው ይታወቃል፡፡ በዚህም መሠረት ባንካችን ከአ/ምንጭ ዩኒቨርስቲ ጋር በትብብር በተሰራው የማስመለስ ስራ አብዛኛው ደንበኞች ያለአግባብ የወሰዱትን ገንዘብ መመለስ ችለዋል፡፡ ነገር ግን ጥቂት የሚባሉ ደንበኞች ዕዳቸውን ከፍለው በሚፈለገው ፍጥነት ሊመልሱ አልቻሉም፡፤
በመሆኑም ዩኒቨርስቲው ይህንን የሀገር ሃብት ለማስመለስ እስካሁን ድረስ ለሠራው ሥራ ምስጋናችንን እያቀረብን፣ የቀረውን ገንዘብ ማስመለስ ይቻል ዘንድ ከዚህ ደብዳቤ ጋር ባያያዝነው ሠንጠረዥ ላይ በተመለከተው ዝርዝር መሠረት ልክ እንደዚህ ቀደሙ በተቋሙ ለሚገኙ ተማሪዎች ያለአግባብ የወሰዱትን ገንዘብ #በ48 ሰዓት ጊዜ ውስጥ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ተመላሽ እንዲደረግ ልዩ የሆነ መመሪያ እንዲሰጣቸው በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡
[የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ]
ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
👍34😁19
#Update
የመውጫ ፈተና መቼ ይሰጣል?
ትምህርት ሚኒስቴር ሚያዝያ 9/2016 ዓ.ም ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፈው ደብዳቤ፤ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 14 እስከ 21/2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ የሚወስዱ የቅድመ ምረቃ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎችን መረጃ በማሰባሰብ በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በኩል አረጋግጠው ባሳለፍነው ሳምንት ለትምህርት ሚኒስቴር መላካቸውን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
የመውጫ ፈተና መቼ ይሰጣል?
ትምህርት ሚኒስቴር ሚያዝያ 9/2016 ዓ.ም ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፈው ደብዳቤ፤ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 14 እስከ 21/2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ የሚወስዱ የቅድመ ምረቃ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎችን መረጃ በማሰባሰብ በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በኩል አረጋግጠው ባሳለፍነው ሳምንት ለትምህርት ሚኒስቴር መላካቸውን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
👍25😭5
በመጪው ሰኔ የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች የአገልግሎት 500 ብር የመክፈል እና ደረሰኝ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው።
ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
👍25👎8
ተማሪ መመገብ ያልቻሉ ዩኒቨርስቲዎች እየበዙ ነው🤔
ዲላ ዩኒቨርስቲም የምግብ በጀት እጥረት እንደገጠመው ገልቷል፡፡
ቀደም ሲል የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ተመሳሳይ እጣፈንታ እንደገጠመው መዘገባችን ይታወሳል፡፡
አብዛሃኛዎቹ ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸውን ለመመገብ ችግር እንደገጠማቸው በዚህ ዘገባችን ስር ከተሰጡት አስተያየቶች መረዳት ችለናል፡፡
ለማሳያነትም ድላ፣ ሀዋሳ እና አምቦ ዩኒቨርስቲ በበጀት እጥረትና በምግብ ግብኣት ችግር ተማሪዎቻቸውን መመገብ እንዳልቻሉ ከተሰጡት አስተያየቶች መረዳት ችለናል፡፡
ዲላ ዩኒቨርስቲው በለጠፈው ማስታወቂያ እንደ ሀገር ባጋጠመን የምግብ በጀት እጥረትና የምግብ ዋጋ መጨመር ጋር በተያያዘ ተማሪዎች የምግብ በጀታቸው ሙሉ በሙሉ ካለቀ ወራት አስቆጥሯል ብሏል፡፡
ተማሪዎቼ ትምህርታቸውን አቋርጠው እንዳይወጡ አትክልት እንዲመገቡ እያደረኩ ነው ብሏል፡፡
በአስቸኳይ የምግብ ጥሬ ዕቃ ግዥ አቅርቦ እንዲሟላልን ጠይቂያለሁ ያለው የድላ ዩኒቨርስቲ የአቅርቦት ሁኔታው እስከሚስተካከል በትዕግስት ጠብቁ ሲል አስታውቋል፡፡
ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
ዲላ ዩኒቨርስቲም የምግብ በጀት እጥረት እንደገጠመው ገልቷል፡፡
ቀደም ሲል የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ተመሳሳይ እጣፈንታ እንደገጠመው መዘገባችን ይታወሳል፡፡
አብዛሃኛዎቹ ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎቻቸውን ለመመገብ ችግር እንደገጠማቸው በዚህ ዘገባችን ስር ከተሰጡት አስተያየቶች መረዳት ችለናል፡፡
ለማሳያነትም ድላ፣ ሀዋሳ እና አምቦ ዩኒቨርስቲ በበጀት እጥረትና በምግብ ግብኣት ችግር ተማሪዎቻቸውን መመገብ እንዳልቻሉ ከተሰጡት አስተያየቶች መረዳት ችለናል፡፡
ዲላ ዩኒቨርስቲው በለጠፈው ማስታወቂያ እንደ ሀገር ባጋጠመን የምግብ በጀት እጥረትና የምግብ ዋጋ መጨመር ጋር በተያያዘ ተማሪዎች የምግብ በጀታቸው ሙሉ በሙሉ ካለቀ ወራት አስቆጥሯል ብሏል፡፡
ተማሪዎቼ ትምህርታቸውን አቋርጠው እንዳይወጡ አትክልት እንዲመገቡ እያደረኩ ነው ብሏል፡፡
በአስቸኳይ የምግብ ጥሬ ዕቃ ግዥ አቅርቦ እንዲሟላልን ጠይቂያለሁ ያለው የድላ ዩኒቨርስቲ የአቅርቦት ሁኔታው እስከሚስተካከል በትዕግስት ጠብቁ ሲል አስታውቋል፡፡
ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
👍38😭19
" የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ይሰጣል " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ
የ2016 ዓ.ም 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፤ " ፈተናው ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ለመስጠት ባይቻልም በክልሎች በተመረጡ ከተሞች ለመስጠት እየተሠራ ነው " ብለዋል።
" በሁሉም ክልሎች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን ይወስዳሉ " ሲሉ አሳውቀዋል።
ቀሪዎቹ ደግሞ በተለመደው አግባብ ፈተናቸውን እንደሚወስዱ ገልጸዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር እሸቱ ከበደ በበኩላቸው ፤ " ፈተናው በኦንላይን ለመሥጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ ነው " ብለዋል።
ተፈታኝ ተማሪዎች በሙከራ ፈተና እንዲለማመዱ እንደሚደረግ ገልጸዋል።
የአሰልጣኞች ስልጠና በመስጠት ተማሪዎች ተደጋጋሚ ስልጠና እንደሚሰጣቸው አመልክተዋል።
ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ይጀመራል ብለዋል።
© ትምህርት ሚኒስቴር
ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
የ2016 ዓ.ም 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፤ " ፈተናው ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ለመስጠት ባይቻልም በክልሎች በተመረጡ ከተሞች ለመስጠት እየተሠራ ነው " ብለዋል።
" በሁሉም ክልሎች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን ይወስዳሉ " ሲሉ አሳውቀዋል።
ቀሪዎቹ ደግሞ በተለመደው አግባብ ፈተናቸውን እንደሚወስዱ ገልጸዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር እሸቱ ከበደ በበኩላቸው ፤ " ፈተናው በኦንላይን ለመሥጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ ነው " ብለዋል።
ተፈታኝ ተማሪዎች በሙከራ ፈተና እንዲለማመዱ እንደሚደረግ ገልጸዋል።
የአሰልጣኞች ስልጠና በመስጠት ተማሪዎች ተደጋጋሚ ስልጠና እንደሚሰጣቸው አመልክተዋል።
ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ይጀመራል ብለዋል።
© ትምህርት ሚኒስቴር
ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
👍43😁9