Telegram Web Link
Audio
ብሉይ ኪዳን 3

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን

አዳምጡ አትርፉበት መስማትም ዕድል ነው!
19👏5
እግዚአብሔር ቢፈቅድ ብንኖር ነገ

እሑድ ጥቅምት 09 ቀን 2018 ዓ.ም. ከ ጠዋቱ 4፡00 ሰዓት  ላይ ትምህርታችን ይጀምራል ::

የትምህርታችን ርእስ " የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስደት

ክፍል 2


ልደቱና ስደቱ ይተነተናል

ማስታወሻ ብትይዙ ይመከራል።

ሌሎች ወገኖቻችንንም ጋብዙ

https://www.tg-me.com/Nolawii
13👏1
ልብ አድርጉ 4፡00 ሰዓት
👍98
Live stream started
Live stream finished (1 hour)
Audio
የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስደት 2

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
14👏4
Forwarded from Nolawi ኖላዊ
በዲያቆን አሸናፊ መኰንን የተጻፉትን ና በገበያ ላይ ያሉትን እነዚህን መጻሕፍት በሙሉ ለሚገዙ አዲስ አበባ ላይ ላሉ ወዳጆች ያሉበት ድረስ እናደርሳለን!

1- የእግዚአብሔር ትዕግሥት 400
2- የኑሮ መድኅን 200
3- ተንሥኡ ለጸሎት 60
4- ረጅሙ ፈትል 170
5- የጊዜው ቃል 200
6- ቅዱስ ጋብቻ 200
7- እንደ እኔ ከተሰማችሁ 150
8- የሕይወት መክብብ 150
9- አካላዊ ቃል 250
10- ቃና ዘገሊላ 250
11- ኒቆዲሞስ 170
12- ሳምራዊቷ ሴት 250
13-መጻጉዕ 250
14- የወዳጅ ድምፅ 180
15- ኅብስተ ሕይወት 250
16- የሕይወት ውኃ 250
17- ኦሪት ዘፍጥረት ትርጓሜ 300
18- ምዕራፈ ቅዱሳን 200
19- የደስታ ቋጠሮ 130
20- የዕለቱ መና 200
21- የበረሃ ጥላ 200
22- ወዳጄ ሆይ 200
23- የአገልግሎት ቱንቢ 250
24- ጴጥሮስ ወጳውሎስ 250
25- ሰንፔር 170
26- መንፈሳዊ በረከት 500
27- ጥበበኛው ድሀ 2ዐዐ

አጠቃላይ ድምር 5,980 ብር
በሚከተሉት የባንክ ሂሳብ በመላክ በ0911 699907 ላይ በቴሌግራም ደረሰኙን ይላኩ ፈጥኖ ይደርሰዎታል

የሕይወት ዘመን ስንቅ ያለባቸው ድንቅ መጻሕፍት!!!
አሸናፊ መኰንን ወርቁ
Ashenafi Mekonnen worku 
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000165078482

አቢሲንያ ባንክ
23202573

ወጋገን ባንክ
0870286030101

አዋሽ ባንክ
Awash Bank
01320034656200
15
የጌታ ስደት

“ንጉሡ ሄሮድስም ሰምቶ ደነገጠ፥ ኢየሩሳሌምም ሁሉ ከእርሱ ጋር፤” ማቴ. 2፡3።


ሰብአ ሰገል “የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው(” ብለው በታላቅ ናፍቆት በፈለጉት ጊዜ ሄሮድስና መላው የኢየሩሳሌም ነዋሪ ደነገጡ ። ሄሮድስ ለሥልጣኑ ሰግቶ ይደንግጥ ፣ ኢየሩሳሌም ለምን ደነገጠች ( ብለን መጠየቅ አለብን ። ሄሮድስ ለሥልጣኑ በጣም ስሱ ነበር ። ይህን ዜና ሲሰማ እንደ ቆሰለ አውሬ ሕዝቡን እንዳይፈጅ ፈርተው ነው ። መሢሕን የምትጠብቅ ኢየሩሳሌም መሢሕ ተወለደ ሲባል ለማየትም አልጓጓችም ። እንደውም ካለው ንጉሥ ጋር እንዳልጣላ ብላ ደነገጠች ። ታላቁ የምሥራች ለማያምኑት ታላቅ መርዶ ሆነ ። የሩቁ ያከበረውን ክርስቶስ የቅርቡ ሊያከብረው አቃተው ። ምን ጊዜም ክርስቶስን በሚመለከት ሦስት ዓይነት ወገኖች ይታያሉ ። ሄሮድስ ፣ ካህናትና ሰብአ ሰገል ናቸው ። ሄሮድስ ለክርስቶስ ጥላቻ የነበረው ሊገድለው የሚሻ ነው ። ካህናቱ ንቀት የነበራቸው ለአዳኙ ቸል ባዮች ነበሩ ። ሰብአ ሰገል ክርስቶስ የሚናፍቁት ፣ የሚወዱትና የሚሰግዱለት ናቸው ። ዛሬም እነዚህ ሦስት ወገኖች ይታያሉ ። ለክርስቶስ ፍቅርና ስግደት ከሌለን እንደ ካህናቱ ንቀትና ቸልተኝነት ፣ እንደ ሄሮድስ ጥላቻና ገዳይነት ይኖረናል ። የክርስቶስ የሆኑትን መጥላት ፣ መናቅ ዛሬም ካለ የማቴዎስ ምዕራፍ ሁለት ንባብ ሕያው ነው ።

ሰብአ ሰገል ከሩቅ አገር የሁለት ዓመት ጉዞ ተጉዘው የመጡ ናቸው ። ክርስቶስ በተወለደ ዕለት በቤተ ልሔም ሰማይ ላይ የነበረው የመላእክት ትእይንት በአገራቸው ሆነው ሳያዩት አልቀሩም ። ደግሞም በተፈጥሮና በከዋክብት እንቅስቃሴ ላይ ለውጥ ታይቷል ። ሰብአ ሰገል የተፈጥሮ ሳይንስ ፣ የሥነ ፈለክ ፣ የመድኃኒት ቅመማ ፣ የባሕረ ሐሳብ ፣ የሒሳብ ሊቃውንት ሲሆኑ የዓለምን ሁኔታ ለነገሥታትና ለዓለም ሕዝብ የማሳወቅ ኃላፊነት ነበረባቸው ። ከነቢዩ ከዳንኤል በባቢሎን በፋርስ ምድር የክርስቶስን የመምጣቱን የሱባዔ ቍጥር ፣ የትንቢት ድርድር የሰማው የዞሮአስተር ተከታዮች ናቸው ። ሰብአ ሰገል የክርስቶስን መምጣት በሱባዔ ፣ በትንቢት ፣ በተፈጥሮ ለውጥ ተረድተው እንደ ተወለደ አወቁ ። አውቀው ዝም አላሉም ፣ ሊሰግዱለት መጡ ። ክርስቶስ በተወለደ ጊዜ ለየት ያለ የከዋክብት እንቅስቃሴ እንደ ነበር አጥኚዎች ደርሰውበታል ። የሚገርመው ሰብአ ሰገል ሥልጣን የነበራቸው ጠቢባን ነበሩ ። ለምርምር ሥራም የሚሆንና የዝና ትርፍ የሆነው ሀብትም ነበራቸው ። ንጉሥ ቤተ መንግሥት ይወለዳል ፣ እነርሱ ግን በበረት ያገኙትን ሕፃኑን አከበሩት ። የቦታና የጌጥ አምላኪዎች አልነበሩም ማለት ነው ፣ ሊቅ የላይ መለኪያ ሳይሆን የውስጥ ውበትን የሚፈልግ ነው ። ንጉሥ በዙፋን ላይ ያዩታል ፣ ጌታችን ግን በከብቶች ሣር ላይ ተኝቶ ነበር ። ንጉሥ ሠራዊት አሉት ፣ ጌታ ግን አረጋዊው ዮሴፍና እናቱ ማርያም ብቻ አጠገቡ ነበሩ ። ሰብአ ሰገል ክርስቶስን የፈለጉት ተሞኝተው አይደለም ፣ ሁሉ ከንቱ መሆኑን ጨብጠው አይተውት ነው ።

በጌታችን ልደት ላይ አሕዛብ ተጋበዙ ። የቤተ ክርስቲያን የወደፊት መልክ ተገለጠ ። ቤተ ክርስቲያን ከሕዝብና ከአሕዛብ የተውጣጣች ናትና ። አዳም ምቾትን ፈልጎ ሞትን አመጣብን ፣ ክርስቶስ መስቀልን ተሸክሞ አዳነን ። ከመስቀሉ ምዕራፎች አንዱ በበረት መወለድ ነው ። ክርስቶስና መስቀል ተለያይው አያውቁም ።

በላቲን አሜሪካ ድሀ ስለ ሆኑት ፕሬዝዳንት ብዙ ተነግሯል ። እኒህ የዘመናችን መሪ የነበሩት አንዲት ቮልስ ዋገን መኪና የነበረቻቸው ያችንም የሚጠቀሙ ፣ በአነስተኛ የገጠር ቤታቸው የሚያድሩ ነበሩ ። ከመሪነትም ሲነሡም የዕለት ሥራ እየሠሩ መኖር ቀጥለዋል ። በዚህም ተከብረዋል ። ዓለም ራስዋ የምትፈልገው ጌጠኛ ልብስ የሚለብሱ ፣ ውድ ቤተ መንግሥት የሚገነቡትን ሳይሆን የድሀ መልክ ያላቸውን ነገሥታት ነው ። “የዓለማችን ድሀው ፕሬዝዳንት ብለው ይጠሩኛል እኔ ግን ድሀ እንደ ሆንሁ አይሰማኝም ፣ ድሀ የሚባሉት የተቀናጣ ኑሮ ለመኖር የሚስገበገቡ ናቸው” በማለት የኡራጓዩ ፕሬዝዳንተ ሆሴ ሙጂካ ተናግረዋል ። እኒህ ሰው ፕሬዝዳንት ከመሆናቸው በፊት ይኖሩበት በነበረው የገጠር ቤታቸው ኑሮአቸውን ቀጥለዋል። ጥይት በማይበሳው መኪና ሳይሆን የ1987 ዓ.ም ስሪት በሆነችው ቮልስ ዋገን መኪና የሚሄዱ ነበሩ ። በፕሬዝዳንትነት ከሚያገኙት ደመወዝ 90 ከመቶውን ለድሆች ይሰጡ ነበር ። እኒህ ፕሬዝዳንት በ89 ዓመታቸው አርፈዋል ። በወቅቱ የነበሩት የኡራጓዩ መሪ የእኒህን ድሀ ፕሬዝዳንት ሞት አስመልክተው የሰጡት የኀዘን መገለጫ፡- “ስለ ሰጠኸን ነገር ሁሉ ለሕዝብ ስለነበረህ ጥልቅ ፍቅር እናመሰግናለን” የሚል ነበር ። እኒህ ድሀ ፕሬዝዳንት በሙስና ያልተከሰሱ የዓለማችን ፕሬዝዳንት ሊባሉ ይችላሉ ፤ እርሳቸውም ከሞታቸው ከዓመት በፊት፡- “ሞት የማይቀር ነው ፣ ምናልባት የሕይወት ጨው ሊሆን ይችላል” ብለዋል ። ስግብግቡ ዓለም መናኝ ነገሥታትን ፣ ድህነትን የመረጡ መሪዎችን ይናፍቃል ። ክርስቶስ ቅንጡ ሳይሆን የሕማም ሰው ሆኖ መጣ ። ነገሥታት መጠነኛ ኑሮን ካልመረጡ የሕዝብ ስቃይ እየጨመረ ይመጣል ። ይህንን ሊያስተምር የአይሁድ ንጉሥ በበረት ተወለደ ።

ይቀጥላል

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም.
43👍1
ስደታችንን ተሰደደ

ለጌታችን ስደት ትልቅ ምክንያት የነበረው ሄሮድስ ሥልጣን አፍቃሪ ፣ አስመሳይ ፣ ተንኮለኛ ፣ የሕፃናት ገዳይ ፣ ሃይማኖት ያለው መሳይ ፣ ለሮማውያን ሰግዶ/ምቹ ሆኖ ሥልጣንን ያገኘ ፣ ልጆቹም በእርሱ መንገድ ሄደው የተበከሉበት ሰው ነው ። የካህናት አለቆችና የሕዝቡ ጻፎችም ለጌታችን ስደት ምክንያት ነበሩ ። እነዚህ በንቀት የተሞሉ ፣ ክርስቶስ በቤተ ልሔም እንደሚወለድ ትንቢትን ጠቅሰው እየተናገሩ የሆነውን ለማየት አልሄዱም ። የንጉሡ መደንገጥ ፣ የሰብአ ሰገል መምጣት አልነቀነቃቸውም ። እንዲሰግድለት ሳይሆን እንዲገድለው ትንቢት ጠቅሰው ነገሩት ። የዓለም ሁኔታ ሲለወጥ እነዚህ ካህናት አይደነግጡም ። ከሩቅ የመጡ የእነርሱን መጽሐፍ ሲያከብሩ ብዙም አይገርማቸውም ። ንጉሡን ያስደነገጠ ነገር ምንድነው ( ለማለትም ቸልተኛነታቸው ከለከላቸው ። እየጠቀሱ ነዋሪዎች ነበሩ ። ቅዱስ ማቴዎስ ራሱ አይሁዳዊ ሲሆን ወንጌሉን የጻፈው በቀጥታ ለእነርሱ ነው ። መልእክቱም አልተቀበላችሁትም የሚል ነው ። ስለ ክርስቶስ በመስቀል ላይ በሠራችሁት ስህተት ብቻ ሳይሆን ልደቱም ላይ ያደረጋችሁት ቸልታ ተገቢ አይደለም እያላቸው ነው ። ሰው ራሱንም ለማየት የወንጌል መስተዋት ያስፈልገዋል ። ስህተቱን ያላመነም የክርስቶስ መድኃኒትነት አይረባውም ። መድኃኒት ከእምነት ጋር በጣም የተያያዘ ነው ። መጀመሪያ በሽታን ቀጥሎ መድኃቱን ማመን ያስፈልጋል ።

ሄሮድስ ለመግደል አሰበ እንጂ ተሳክቶለት ጌታን አልገደለውም ። ንቀትና ቸልታ የሞላባቸው የአይሁድ ካህናት ግን በመጨረሻ ጌታን ሰቅለውታል ። ከአላውያን ነገሥታት ፣ ከጨካኝ መሪዎች ይልቅ ክርስቶስን ለመስቀል አቅም ያለን እኛ አገልጋዮች ነን ። አገልጋይ ስንሆን በንቀትና በቸልተኝነት እንዳንያዝ መጠንቀቅ አለብን ። የዚህ ነገር መጨረሻው ክርስቶስን መስቀል ነውና ። የአይሁድ ካህናትን ጥቅስን ያውቃሉ ፣ የሚጠቅሱት ግን ሰዎች ለክርስቶስ እንዲሰግዱ ሳይሆን እንዲገድሉት ነው ። ከእግዚአብሔር የመጣውን ግን ማጥፋት አይቻልም ። ጥቅሶቻችን ዛሬስ የሰላም መሣሪያ ናቸው ወይ ( ብለን መጠየቅ አለብን ። መጽሐፉም ውሾች ይላል በማለት ውሻ ብሎ የመሳደብ ጥሙን የሚያረካ አለ ። በደርግ ዘመን የሚወደድ ጥቅስ ነበር ። “በሦስት ነገር ምድር ትናወጣለች፥ …ባሪያ በነገሠ ጊዜ…” የሚል ነው ። ይህን ጥቅስ የወሰዱት ከምሳ. 30፡21 ላይ ነው ። ይህን ጥቅስ እየጠቀሱ ገዥውን የሚሳደቡ ፣ ለምን ሲባሉ በጥቅስ ውስጥ የሚደበቁ ነበሩ ። የእግዚአብሔር ቃል ለአምልኮተ እግዚአብሔር ብቻ መጠቀስ አለበት ።

በአይሁድ ላይ ዘራቸውን ለማጥፋት ሦስት ጊዜ ያህል ሞት ታውጆ ነበር ። በግብፅ በፈርዖን ፣ በፋርስ በሐማ ፣ በገዛ ምድራቸው በሄሮድስ ሞት ታውጆባቸው ነበር ። ዓላማው መሢሑ የሚወጣበትን ዘር አጥፍቶ የዓለምን መዳን ማስቀረት ነበር ። ሰይጣን የሚዋጋው የሰውን ባለጠግነት ሳይሆን መዳኑን ነው ። ሰብአ ሰገል ሁለት ዓመት ሙሉ በፍለጋ ላይ ነበሩ ፣ የፍለጋ ማብቂያው ክርስቶስን ሲያገኙ ሆነ ። ሰዎች ሰባ ሰማንያ ዓመት አስሰው የሚያርፉት እርሱን ሲያገኙ ነው ። እውነተኛው የሕይወት ምዕራፍ ክርስቶስ ነው ። ድንግል ማርያምና አረጋዊው ዮሴፍ በቤተ ልሔም ለሁለት ዓመታት ያህል የቆዩት በናዝሬት ነዋሪዎች ዘንድ የክርስቶስ ያለ አባት መወለድ ያሥነሣቸውን ትችት ለመሸሽ ነው ። ዮሴፍ ሙያው አናጢ ነበርና የትም ለመቆየት የሚሆን ሙያ ነበረው ። ስለ ክርስቶስ አረጋዊው ዮሴፍም ድንግል ማርያምም በሰማይ መገለጥ አርፈዋል ፣ ናዝሬት ግን ይተራመሳል ። እኛ ዐርፈን ሰዎች ሊተራመሱ ፣ ከተማው ሊያውካካ ይችላል ። ትንሽ መሰወር ተገቢ ሊሆን ይችላል ። ደግሞም ሁሉ ቦታ እንጀራ የሚያበላንን ሙያ መያዝ መልካም ነው ። አናጢነት መቼም ተፈላጊ ፣ የትም ቦታ ሥራ ያለው ሙያ ነው ።

ሰብአ ሰገል ከአሕዛብ ቀዳሚ አማንያን ሆኑ ። በጥበባቸው ሳይሆን በእምነታቸው የክርስቶስ ተከታይ ሆኑ ። ኮከቡ ለጥቂት ጊዜ ቢሰወራቸው ሰው ጥየቃ ገቡ ። ነገሩ ንጉሥ ዘንድ ደረሰ ። ኋላ ላይ ለክርስቶስ ስደት ምክንያት ሆነ ። ምሥጢርን መጠበቅ ተገቢ ነው ። ነገ ሊነገር የሚገባውን ዛሬ ላይ መናገር ራሱን የቻለ ጉዳት አለው ። ምሥጢር ሦስት ነገሮች ይፈልጋል፡- ሰው ፣ ሁኔታና ጊዜ ። ምሥጢር በባለቤቱ ልብ ውስጥ ሳለ ጠባቂው ነው ፣ ከእርሱ ከወጣ በኋላ ግን ካቴና ይዞ የሚከተለው ፖሊስ ነው ። እግዚአብሔር በሁሉ ይምራል ። ሰብአ ሰገል ለጌታችን ያቀረቡት እጅ መንሻ በማግሥቱ ለሚመጣው ስደት የስንቅ መግዣ ነበር ። እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጃል ። ሳይደግስ አይጣላም ይሉታል ። ደግሶ አብልቶ የሚጣላ ምን ዓይነት ወዳጅ ይሆን ! የሚመጣውን አይቶልም ያዘጋጀልን ብዙ ነገር አለ ! ጥንቃቄን በማጣት ፣ ምሥጢርን ባለመጠበቅ ፣ የቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ ለማን መንገር እንዳለብን ባለመገንዘብ የመከራ አምጪ ልንሆን እንችላለን ።

የሚገርመው ወደ ስደተኛዋ አፍሪካ ጌታ የዛሬ ሁለት ሺህ ዓመት በፊት መሰደዱ ትልቅ ትርጉም አለው ። አፍሪካውያን በስደት እየባከኑ ነው ። ብዙዎች በራቸውን ይዘጉባቸዋል ። የጌታችን ስደት ለስደተኞች መጽናኛ ነው ። ስደተኞች ሃይማኖት በጠፋበት የሰለጠነው ምድር የሃይማኖትን መልክ እያሳዩ ፣ በረከት እያመጡላቸው ነው ። ስደተኞች በረከቶች ናቸው ። ሰብአ ሰገል የአገርህ ሰው ካልተቀበለህ እኛ እንውሰድህ አላሉም ። የእግዚአብሔር መርሐ ግብር ከሆነ የንጉሥ ወዳጅነትም ሊረዳን አይችልም ። ንጉሥ የቆረጠው እጅ ካለ ይቆጠራል እንዲሉ ከእግዚአብሔር ከሆነ ማጣቱም ማግኘት ነው።

ስደተኛውን ጌታ ፣ ስደተኛይቱን ድንግል ስናስብ ስደተኞችን በማስጠጋት ሊሆን ይገባዋል ። ስደተኞች አካላዊ ፣ ስሜታዊ ፣ ሥነ ልቡናዊ ፣ ሃይማኖታዊ ጫና ይደርስባቸዋል ። ቤተ ክርስቲያን እየናፈቁ ላያገኙ ፣ የሃይማኖት አባት እያማራቸው ብርቅ ሊሆንባቸው ይችላል ። በስደት ምድር ላይ ለኢትዮጵያውያን መጽናኛ የሆኑ አባቶችና አገልጋዮች ሊመሰገኑ ጊዜው አሁን ነው ።

ከእውነት የተሰደድነውን በስደቱ ይመልሰን !

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም.
32🥰4
የናዝሬቱ ኢየሱስ

“በአባቱም በሄሮድስ ፈንታ አርኬላዎስ በይሁዳ እንደ ነገሠ በሰማ ጊዜ፥ ወደዚያ መሄድን ፈራ፤ በሕልምም ተረድቶ ወደ ገሊላ አገር ሄደ፤ በነቢያት፡- ናዝራዊ ይባላል የተባለው ይፈጸም ዘንድ፥ ናዝሬት ወደምትባል ከተማ መጥቶ ኖረ።” (ማቴ. 2 ፡ 22-23 ።)

ሄሮድስ የሚለው ስም ኋላ ላይ ስመ መንግሥት ሆኗል ። በአገራችን ዐፄ እንደሚባለው ሄሮድስም ስመ መንግሥት በመሆን አገልግሏል ። ሄሮድስ በሚለው ስም ብዙዎች ተጠርተዋል ። ዋነኛው ግን ታላቁ ሄሮድስ ተብሎ የሚጠራው ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ37 ዓመት ጀምሮ እስከ 4 ዓ.ም. ድረስ ሥልጣን ላይ የነበረው ፖለቲከኛ ሰው ነው ። ይህ ሰው ሮማውያን የአባቱን የአንቲጳስን ውለታ አስበው ከፍ ያደረጉት ሲሆን በይሁዳ የነበረውን ሥልጣን በተቃዋሚዎች አጥቶ ወደ ሮም በሄደ ጊዜ ንጉሥ አድርገው ለአጥቢያው ሾሙት ። ሄሮድስም አስመሳይ ነበርና ከሮማ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት እስከ ቤተ ጣዖት ድረስ መሥዋዕትን በመሠዋት ታማኝ መሆኑን ገለጠ ። በሮማውያን ወታደራዊ ኃይል ታግዞ ዳግም የእስራኤልን ምድር ተቆጣጠረ ። ታላቁ ሄሮድስ በዓለም ላይ በተለያዩ ሥራዎቹ ይታወቃል ። ለሮም ንጉሥ መቀመጫነትና ለክብሩ በመሠረታት ቂሣርያ ይታወቃል ። ደግሞም ሁለተኛውን መቅደስ በማደስም የታወቀ ነው ። ይህ የመቅደስ እድሳትና መስፋፋት በ19 ዓመት ቅድመ ልደተ ክርስቶስ የጀመረ ሲሆን የተጠናቀቀው በ64 ዓ.ም ነው ። በሚያሳዝን መልኩ 6 ዓመት አገልግሎት ሰጥቶ በ70 ዓ.ም. በሮማውያን ፈረሰ ። ሄሮድስ ፖለቲከኛ ስለነበር የሥልጣኑ ምንጭና ደጋፊ የነበሩትን ሮማውያንን እንዲሁም የሚገዛቸውን አይሁድን በእኩልነት ደስ ለማሰኘት ይሞክር ነበር ። ለሥልጣኑ በጣም የሚሳሳ በመሆኑ ሚስቱንና ሦስት ወንዶች ልጆቹን ፈጅቷል ።

ሄሮድስ ጌታችንን ለመግደል በመነሣቱ ይታወቃል ። ብዙ የቤተ ልሔም ሕፃናትንም አስጨፍጭፏል ። ጌታ ወደ ግብጽ ከተሰደደ በኋላ ሄሮድስ የቆየው ለ3 ዓመታት ያህል ነው ። ሲሞት መንግሥቱ ለሦስት ልጆቹ ተከፋፈለ ። ይሁዳን ወይም ዋናውን ደቡባዊ ግዛት አርኬላዎስ ሲገዛ ፣ በሰሜን ያሉትን ሁለት ግዛቶች ሄሮድስ ፊልጶስና ሄሮድስ አንቲጳስ ገዝተዋል ። እነዚህ ሦስት የሄሮድስ ልጆች ንግሥናን ፈልገው ወደ ሮም ቢሄዱም አስተዳዳሪነቱ ጸናላቸው እንጂ ንጉሥነቱን አላገኙም ነበር ። የአርኬላዎስ ከኢየሩሳሌም መሄድን ታሳቢ አድርገው አይሁድና ሳምራውያን ወኪል በመላክ አርኬላዎስ እንዲነሣ ጥያቄ አቀረቡ ። በተነሣውም ዓመፅ ለመቀጣጫ እንዲሆን ሁለት ሺህ ሰዎች በስቅላት ተቀጡ ። በአርኬላዎስ ላይ የነበረው ጥላቻ እያየለ መጥቶ ሮማዊ ወኪል በእርሱ ፈንታ ተሾመ ። አርኬላዎስም በ6 ዓ.ም. ሥልጣኑን አጣ ።

ታላቁን ሄሮድስ በመሸሽ ግብጽ የነበሩት ሕፃኑ ኢየሱስ ፣ እናቱ ማርያምና አረጋዊው ዮሴፍ ሞቱ እንደ ተሰማ ተመለሱ ። አባቱን በግብር ይመስል የነበረው የይሁዳው ገዥ አርኬላዎስ ስለነበረ ወደ ናዝሬት መሄድን መረጡ ። ምክንያቱን የአባቱን ሥራ እያስፈጸመ ፣ በሺህ የሚቆጠሩ የይሁዳ ነዋሪዎችን እየገደለ ነበርና ። የጌታን መመለስ ቢሰማ አባቱ ያልቻለውን ነገር ለመፈጸም ይነሣ ነበር ። ስለዚህ አርኬላዎስን ላለማነሣሣት ወደ ናዝሬት ሄዱ ። ቍጠኞችን ማነሣሣት ተጨማሪ እሳት በምድር ላይ መለኮስ ነው ። በዚህም የኃጢአት ብዛት መጨመርና የኃጢአት ሎሌ መሆን ይመጣል ። አርኬላዎስ ጌታን መግደል አይችልም ፣ እርሱን አገኘሁ ብሎ ግን ብዙዎችን ይገድላል ። በዚህም ለብዙዎች ማለቅ ምክንያት ላለመሆን ወደ ናዝሬት ሄዱ ። ጌታን አገኝ ብሎ ታላቁ ሄሮድስ የቤተ ልሔም ሕፃናትን ገደለ ፣ ዛሬም ኢየሱስን የምትጠላ ዓለም እርሱን ያገኘች እየመሰላት ተከታዮቹን ትገድላለች ።

ጌታችን ወደ ናዝሬት መሄዱ ትንቢትን ለመፈጸም ነው ። ትንቢት ከእርሱ የመጣ መገለጥ ሲሆን ፍጻሜና እውነት የሚያገኘው በራሱ በክርስቶስ ነው ። የነቢያት ዓይናቸው ፣ እውነተኛ ለመባልም ማኅተማቸው ምጽአተ ክርስቶስ ነው ። ናዝሬት በሰሜናዊው ገሊላ የምትገኝ በኮረብታ ላይ የተመሠረተች ፣ ታሪክ የሚታይባት ማማ ነበረች ። ጌታችን ለልደቱ ናዝሬትን አልመረጠም ። ያለ አባት በምድር ተወልዷልና የናዝሬት ነዋሪዎች ግራ ስለተጋቡ ከትችታቸው ዘወር ማለት ይገባል ። ጊዜ የማይሽረው ሐሜት የለምና ሰዎች በከንቱ ስማችንን ሲያጠፉ ባለመስማት ዘወር እንበል ። በእውነቱ በጌታ እንደ ታየው ከአምስት ዓመት በኋላ ማንም አያስታውሰንም ። ጉድ አንድ ሰሞን ነው ይባላል ። ጌታችን የናዝሬቱ ኢየሱስ ይባላል ። በብሉይ ኪዳን ራሳቸውን ለእግዚአብሔር የለዩ ናዝራውያን የሚባሉ አሉ ። ጌታችን ግን በናዝሬት በማደጉ ናዝራዊ ተባለ ። ናዝሬትን ለምን መረጠ (

ናዝሬት የንቁዎች ፣ የአትንኩኝ ባይ ኃይለኞች ከተማ ናት ። ሁሉም የዓለም ማኅበረሰብ የሚኖርባት ፣ ለሥልጣኔ ቅርብ የሆነ ሕዝብ ያለባት ከተማ ናት ። ናዝሬት ላይ መቆም ከመላው ዓለም ጋር መገናኘት ነው ። ናዝሬት ወደ ይሁዳ ወይም ወደ ደቡብ የሚወስደው መንገድ አውራ ጎዳናው ተዘርግቶባት ሰሜንና ደቡብ እስራኤልን ታገናኛለች ። ከግብጽ ወደ ደማስቆ የሚያልፉ ቃፊሮች ናዝሬት መሸጋገሪያቸው ነበረች ። ከምዕራብ ወደ ምሥራቅ የሮማ ወታደሮች የሚያልፉት በዚህች ከተማ ነው ። በመገናኛዋ ናዝሬት ሰማይና ምድርን ያስታረቀው ኢየሱስ አደገ ። ሰው ሠራሽ የሆነውን ትብታብ የማይወደው ፣ አስጨንቆ ሳይሆን አስደስቶ የሚገዛው ኢየሱስ ለውጥን በሚወዱ መካከል አደገ ። ዓለምን ያለ መዶሻ ያነጠው የአብ ልጅ የማርያም ልጅ ተብሎ በሥጋ በመጣ ጊዜ በናዝሬት መዶሻ የያዘ አናጢ ሁኖ አገለገለ ። ናዝሬት በአክራሪ አይሁዶች የተናቁ ፣ ደግ አይወጣባቸውም ተብለው ተስፋ የተቆረጠባቸው ሰዎች መኖሪያ ናት ። በናዝሬት የመልካሞች መልካም ኢየሱስ ክርስቶስ አደገ ። የናዝሬቱ ኢየሱስ ሲባል የዓለም ጌታ ነው ፣ የሕዝቦች ቋንቋ ነው ማለት ነው ። በናዝሬት ብዙ ቋንቋ ይነገራልና ። የናዝሬቱ ኢየሱስ ሲባል የኃጢአተኞች ወዳጅ ማለት ነው ። ሰዎች ለንቀት የሰየሙትን ስያሜ እርሱ የእውነት አደረገው ። ስድብን ወስደነው ስንጠቀምበት ተሳዳቢው መሣሪያዬ አልሠራም ብሎ ይተወዋል ።

ናዝሬት ዓለምን የምታገናኝ አውራ ጎዳና ናት ፣ ወደ አባቱ ለመድረስ ጎዳና ፣ ወደ ወለደው ለመግባት በሩ የሆነው ኢየሱስ በናዝሬት አደገ ። ልበ ሰፊው በልበ ሰፊዎች ከተማ አደገ ። ተቆርቋሪው አትንኩኝ በሚሉ ፣ ሊቀርቧቸው በማያስቸግሩ ቀናዎች መካከል አደገ ። ናዝሬት በሰዎች የተጠላች በጌታ የተወደደች ናት ፣ ኢየሱስም አናጢዎች የናቁት አባቱ የወደደው የማዕዘን ራስ ደንጊያ ነው ።

ክብር ምስጋና ለናዝሬቱ ኢየሱስ ይሁን ! አሜን ።

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም.
40🥰2
ሰባቱ የፈሪሳውያን ዓይነቶች

ፈሪሳውያን የስማቸው ትርጉም እንደሚያስረዳን ለእግዚአብሔር የተለዩ ማለት ነው ። ፓራሽ ከሚለው የዕብራይስጥ ቃል የተገኘ ይመስላል ። ትርጉሙ መራቅ መለየት ሲሆን ፈሪሳዊ ማለትም የተለዩ ማለት ነው ። ራሳቸውን ከመላው ዓለም ብቻ ሳይሆን ከአይሁዳውያንና ከተራው ሕዝብ የተለዩ እንደሆኑ ይቆጥሩ ነበር ። እነዚህ ፈሪሳውያን በቃል ኪዳን ወደዚህ ሕይወት ይገባሉ ። ቃል ኪዳናቸውም ሕጉንና ትርጓሜውን በዘመናቸው ሁሉ ለማጥናትና ለመጠበቅ ሲሆን እርስ በርሳቸውም እንደ ወንድማማች ለመተያየት በሦስት ሰው ፊት ቃል በመግባት ይጀምሩ ነበር ። ፈሪሳውያን አነሣሣቸው ከክርስቶስ ልደት 200 ዓመት ቀደም ብሎ ነው ። ግሪካዊው የመንግሥት ሥልጣን ቦታውን በለቀቀ ጊዜ የግሪክ ቋንቋና ሔለናዊ የተሰኘው የዘመናዊነት ባሕል መላውን ዓለም መግዛት ቀጥሎ ነበር ። አጭር የነበረው የታላቁ እስክንድር ዓለምን የመግዛት ራእይ የቀጠለው በግሪክ ቋንቋና ፍልስፍና ነው ። ፈሪሳውያን አዲሱ ትውልድ በባዕድ ጠባይ እንዳይወረር ማንነታቸው እንዳይጠፋ በጣም ይጨነቁ የነበሩ ስብስቦች አገርን ለመታደግ የጀመሩት እንቅስቃሴ ነው ። እነዚህ ፈሪሳውያን ከሥልጣን የራቁ ሲሆኑ ቤተ መቅደሱ አካባቢ ላሉት ካህናት ጥሩ አመለካከት የላቸውም ። እኛ እናጠብቃለን ብለው ስለሚያስቡ ሌላውን ሁሉ እንደ ሕግ አፍራሽና ግዴለሽ ያዩት ነበር ። ፈሪሳውያን አገራዊ ስሜት ከእኛ ውጭ ለሐሳር ብለው የሚያስቡ ፣ ከእኛ በላይ ፉጨት አፍ ማሞጥሞጥ የሚሉ ነበሩ ። ጌታችን በምድር ላይ በነበረ ጊዜ ቍጥራቸው ከስድስት ሺህ የማይበልጥ ቢሆንም በጣም ተጽእኖ ፈጣሪዎች ነበሩ ። የጌታችንን ስብከት በማወክ ፣ በመጨረሻ ለሞት አሳልፎ በመስጠት እጃቸው ረጅም ነበር ።

እነዚህ ፈሪሳውያን ሰባት ቡድኖች ወይም ዓይነት ነበራቸው ። ፈሪሳዊነት ጠባይ በመሆኑ በሁሉም ዘመን ያለ ነው ። በአዲስ ኪዳን ከዘጠና ስምንት ጊዜ በላይ በግልና በቡድን የተጠቀሱ ናቸውና ለእኛ ትምህርት ባይሆኑ ይህን ያህል ሽፋን አያገኙም ነበር ። ሰባቱ የፈሪሳውያን ዓይነቶች፡-

1- የታይታ ፈሪሳውያን

እነዚህ “የትከሻ ፈሪሳውያን” በመባልም ይታወቃሉ ፣ ሕጉ የተጻፈባቸውን ጥቅልሎች በእጃቸውና በግንባራቸው ላይ በማሰር ይታወቃሉ ። ሕጉ የተሰጠበት ዓላማ እንደ ጌጥ እንዲንጠለጠል ሳይሆን ለሕይወት ለውጥ ነው ። ፈሪሳውያን ግን ሕጉ ከልባችንና ከቤታችን ተርፎ በልብሳችን ላይ ተጽፏል የሚል መልእክት ለማስተላለፍ ይጥሩ ነበር ። እነዚህ ፈሪሳውያን ረጃጅም ቀሚሶችን በመልበስ ፣ ዘርፋቸውን በማስረዘም መንደር ለመንደር የሚዞሩ ፣ የምስኪኖችን መቀነት የሚያስፈቱ ነበሩ ። ጻድቅነታቸውን ሁሉ ሰው እንዲያውቅላቸው ይፈልጋሉ ። እዩልኝ ስሙልኝ ይላሉ ። በጎ ተግባርን የሚያደርጉት ለሰው እንጂ የተፈጠሩበት ዓላማ መሆኑን ተገንዝበው አይደለም ። ዛሬም በጥቅስ ቤታችንና መኪናችን ተንቆጥቁጧል ። አማኝ መሆናችንን ለማሳየት የመሐላ ብዛት እንደረድራለን ። አንዱ በኢየሱስ ስም ፣ በጌታ ይላል ፣ ሌላው መድዬን እመቤቴን ይላል ። የሰቀልነው ጥቅስ ግን በዕለታዊ ኑሮአችን ላይ ተጽእኖ አያሳድርም ። የኢየሩሳሌም ፣ የግሪክ እያልን እናጌጣለን ፣ በኃጢአት ግን ወይበናል ። “ጠጉራም ውሻ አለ ሲሉት ይሞታል” እንዲሉ ከእኛ ይልቅ ልብሱ አማኝ ነው ። ጭንቀታችን ጌጠኛ መስቀል ወይም አይከን በሺህ ዶላር ለማንጠልጠል እንጂ የሕዝብን ስቃይ ለመካፈል ፣ የክርስቶስ የሕማሙ ወዳጅ ለመሆን አይደለም ። የምናገለግለው ሕዝብ በችግር ሰክሮ የምንሰብከውን እንኳ መስማት አልቻለም ። እኛ ግን በዘመናት ሁሉ እንደ ታየው ከሟች ጋር ሳይሆን ከገዳይ ጋር የምንሰለፍ ሆነናል ። የቀረው ልብሳችን እንጂ ጨካኝነት ሙሉ በሙሉ ወርሶናል ። ሕገ ፍቅር ሳይሆን ሕገ አራዊት ሰልጥኖብናል ። ያሸነፈ ብቻ የሚኖርበት ዓለም መሥርተናል ። ግፈኛን ተው ለማለት ግፍን ስላልተውን አፍ እያለን ዱዳዎች ሆነናል ። በዋና ከተማ ላይ እንተራመሳለን ፣ የተወለድንበት መንደር በሁከት ሲናወጥ የመጸለይና ተዉ የማለት የሞራል ልዕልና እንኳ አጥተናል ። “እውነት መናገር ካልቻልህ ዝም በል” ይባላል ። እኛ ግን በቍስል ላይ ጥዝጣዜ ለመሆን ከንቱ ንግግር መናገርን አላቆምንም ። “በየቀኑ በግ የሚያስበላ እረኛ ከተሸለመ ፣ ሸላሚው ቀበሮ ነው” ይባላል ። ይህ ሁሉ ሸብ ረብ ፣ ይህ ሁሉ ውድድር በግ የሚያስበሉትን ከፍ ለማድረግ ነው ።

ወጣቱ ከቀይ ሽብር አንሥቶ ሜዳ ላይ ሲወድቅ እንደሌለ ሁነን አልፈናል ። በየዘመናቱ የፈሰሰው የልጆቻችን ደም ዛሬ የሚበላ ምግብ ተገኝቶ አላስበላ ብሎናል ። በየጎጆው በረሀብ የሚሞቱት ሊቃውንት ረሀባቸው እየተፋረደን በሰላም ቤት ውስጥ ሰላም አጥተናል ። ዝናብ የሌላቸው ደመናዎች ሁነን መጡ መጡ ከመባል ውጭ ምንም ትርጉም የማንሰጥ መሆናችን ያሳዝናል ። ቤተ ክርስቲያን የነፍስ ደጃፍ መሆንዋን ባንገነዘብ እንኳ የእንጀራዬ ገበታ ነች ብለን ብናከብራት መልካም ነበር ። አንድ ወጣት ለዚህ ቁመና እስኪበቃ የሚከፈለው ዋጋ ቀላል አይደለም ። ከፅንስ ጀምሮ ፣ በምጥ እስከ መወለድ ፣ በጣር እስከ ማደግ ድረስ ዋጋ የተከፈለበት ወጣት ሲሞት እንዴት በክርስቶስ ፍቅር ያለን ሰዎች ያስችለናል ( ወጣቱ ለማየት ሲያሳሳ ጦርነት ይቆርጠዋል ። ወላድም ቀኑ ጨልሞበት እንዳዘነ ያልፋል ። የዚህ ሁሉ ችግራችን ለባለጠግነት እንጂ ለወንጌል አለመሮጣችን ነው ። ለታይታው ፣ ለእዩኝ ስሙልኝ እንጂ ለእውነት አለመኖራችን ነው ። በዚህ ዘመን ቁመናውን የሚሸጥ አገልጋይ እያመረትን ፣ እየቀደሰ ፎቶ አንሺ የሚቀጥር ቀዳሽ እያበዛን ነው ። ጸሎቱ ባያርግ የሚደንቅ አይደለም ። የተሻለ ካገኘ ለመሄድ በጨረታው የማይገደድ አገልጋይ ሰብስበናል ። የመከረንን ስም ሰጥተን ፣ አላዋቂውን አነሣሥተንበት እናጠፋዋለን ። ግን ወደ ሥራችን ፍጻሜ እየተጓዝን መሆኑን እንዘነጋለን ። ነብር እንኳ ሲሞት ቆዳውን ትቶ ይሞታል ፣ እኛ ለትውልድ ምን ትተን እንሄድ ይሆን ?

አቤቱ በቤትህ ውስጥ የጠፋነውን አግኘን !

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም .
38😢3🥰1
ዛሬ ዓርብ ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም. ከምሽቱ 2:00 ሰዓት  ላይ ትምህርታችን ይጀምራል ::

የትምህርታችን ርእስ " ብሉይ ኪዳን"

ክፍል 4

የሚል ነው

ማስታወሻ ብትይዙ ይመከራል።

ሌሎች ወገኖቻችንንም ጋብዙ

https://www.tg-me.com/Nolawii
15
Live stream started
Live stream finished (1 hour)
Audio
ብሉይ ኪዳን 4

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
16👏1
ሰባቱ የፈሪሳውያን ዓይነቶች /2
አልምጥ ፈሪሳውያን

በሁለተኛ ምድብ የሚገኙት ፈሪሳውያን ከበጎ ነገር የዘገዩ ፣ ዳተኛ ምድብ ናቸው ። ለሌሎች መልካም ሥሩ ብለው ያስተምራሉ ፣ እነርሱ ግን አያደርጉትም ። በጎ ለማድረግ ያስባሉ ነገር ግን ዛሬ አይደለም ይላሉ ። አንድ በጎ ነገር በማድረግ ለነገ የሚቆይ ነገር ለመሥራት ምክንያት ይፈጥራሉ ። እነዚህ ፈሪውያን አድርጉ የማለት እምቅ ትምህርት አላቸው ፣ ትእዛዙ ግን እነርሱን የሚመለከታቸው አይደሉም ። ሐኪሙ ይህን አታድርጉ ብሎ ራሱ ግን ያደርገዋል ። እነዚህም ለሌሎች ጤና ቀና ምክር ይሰጣሉ ፣ ለራሳቸው በሽታ ግን መድኃኒት አይወስዱም ። ሰዎች ታማሚ እንደሆኑ ፈውስም እንደሚያስፈልጋቸው እርግጠኛ ናቸው ፣ የራሳቸውን በሽታ ስላላመኑ መድኃኒቱን አይፈልጉትም ። እነዚህ ፈሪሳውያን ጊዜው አሁን ነው የሚለውን የእግዚአብሔር መንግሥት መመሪያ አይከተሉም ፣ ነገ ይሆናል ብለው ይወረውሩታል ። ክፉ ከሚያደርጉት በላይ በጎ ባለማድረጋቸው እግዚአብሔርን ያሳዝናሉ ።

አይሁዳውያን እግዚአብሔር ሁለት ሚዛን እንዳለው ያስቡ ነበር ። የአይሁድ ጥፋትና የአሕዛብ ጥፋት አንድ ዓይነት ቢሆንም እግዚአብሔር እኩል አይቀጣንም ብለው ያስቡ ነበር ። ስህተታቸውን ቀላል ለማድረግ የሄዱበት ርቀት እግዚአብሔርን አባይ ሚዛን ያለው አስመስለው ሳሉት ። አይሁዳዊ መሆን በጎ ለማድረግ መመረጥ ነው የሚለውን አይሁዳዊ መሆን ክፉ ለማድረግ ፈቃድ ማግኘት ነው ብለው ተረጎሙት ። ነቢዩ ሳሙኤል፡- “ባሪያህ ይሰማልና ተናገር” አለ ። በዚህ ዘመን ያለን አማንያን “ባሪያህ ይናገራልና እግዚአብሔር ሆይ ስማ” የምንል ይመስላል ። አይሁዳውያን በስህተታቸው እንደሚቀጡ ብዙ ማሳያዎች አሉ ። ወንድማቸውን ዮሴፍን በመሸጣቸው ምክንያት በግብጽ ምድር ባሪያ ሆኑ ፣ የሐሰት ነቢያትን በመከተላቸው በባቢሎን ተጋዙ ። መሢሑን በመስቀላቸው በሮማውያን ተደመሰሱ ። እስካለፉት ሰባ ዓመታት ድረስ አገር አልባ ሆነው ለ1900 ዓመታት በዓለም ላይ ተበተኑ ። የፈለግነውን እየሠራን እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ጥሎ አይጥልም ማለት ግብዝነት እንጂ እምነት አይደለም ። በጎ እየሠራን ያንን ብንናገር ወይም ክፉ ነገር ሳይመጣብን ብንፎክር ያምር ነበር ። በዓለም የሌለ መከራና ጉድ ተሸክመን ከዚህ በላይ መጣልና መውደቅ አለ ወይ( በሚሊየን የሚቆጠር ወገን በጦርነት ሲያልቅ እነዚያ ኢትዮጵያውያን አይደሉም ወይ ( አጉል መመጻደቅ ንስሐ እንዳንገባና ለተጎዱት እንዳናዝን አድርጎናል ። ትንቢት የተነገረለትን ፣ ሱባዔ የተቆጠረለትን ፣ አንተ አትሠራውም ልጅህ ሰሎሞን ይሠራዋል የተባለውን መቅደስ ያፈረሰው ኃጢአት ነው ። እግዚአብሔር በዓላማው ጨካኝ ነው ፣ በፍርዱም አድልኦ የለውም ።

አንዳንድ ሰዎች የብሉይ ኪዳኑ እግዚአብሔርና የአዲስ ኪዳኑ እግዚአብሔር ልዩ እንደሆነ ያስተምራሉ ። የብሉይ ኪዳኑ ጨካኝ ፣ የአዲስ ኪዳኑ ሩኅሩኅ እንደሆነ ይገምታሉ ። እግዚአብሔር ግን ፍርዱ ምሕረቱን ሳያስቀርበት ፣ ምሕረቱም ፍትሑን ሳያጓድልበት ለዘላለም ይኖራል ። እግዚአብሔር በአንድ ጊዜ ፈራጅም መሐሪም ነው ። እናት ለልጅዋ መሐሪ ብትሆን ፍትሕን ረግጣ ነው ፣ መንግሥት ፍትሐዊ ቢሆን ፍቅር የሚባልን ነገር ላለማወቅ ወስኖ ነው ። እግዚአብሔር ግን የፍቅርም የፍትሕም አምላክ ነው ። ሁላችንም ብንሆን ደግ ሲጠቃ ክፉ ሲያጠቃ ማየት አንችልም ። ይህ ማለት እግዚአብሔር እንዲፈርድ እንከጅላለን ማለት ነው ። በሌሎች ስህተት ላይ የሚፈርደው በእኛም ስህተት ላይ እንዲፈርድ መፍቀድ አለብን ። የተቀበልሁት የሚገባኝን ነው ማለት ታላቅ ብፅዕና ነው ። በአዲስ ኪዳን የተገኘው ነጻነት እንደ ፈለግን የመኖር ሳይሆን እንደ ተፈቀደልን የመገኘት ነው ። ነጻነት ከባርነት በላይ ኃላፊነትን የሚጠይቅ ነው ። ነጻነትን ማስተዳደር አለመቻል ከባድ ነገር ነው ።
በዚህ ዘመን ያለን ሰባክያን ምናልባት አልምጥ ክርስቲያን ሆነን ይሆናል ። ቤተ ክርስቲያንን እነ እገሌ ጎዷት ብለን እንቆረቆራለን ፣ እኛ ስንጎዳት ግን አይሰማንም ። የአንዳንዶችን ነቁጥ ስህተት እናጎላለን ፣ የሌሎችን ተራራ የሚያህል ስህተት ደግሞ በአገር ልጅ ስሜት እናልፈዋለን ። እገሌ የተናገረውን ስህተት ስህተት ስንለው ፣ ወዳጅ ከሆነ ደግሞ የአንደበት ማዳለጥ ፣ ከፍቅር የተነሣ የተነገረ ነው ብለን እናልፈዋለን ። ቤተ ክርስቲያንን ዘረኝነት የሚወዘውዛትን ያህል ቤተ መንግሥትን አይወዘውዘውም ። የፖለቲከኞች ዘረኝነት ጠቅለል አድርጎ አራት ክፍለ አገርን ላንዱ ፣ አምስት ክፍለ አገርን ለሌላው ሰጥቶ ነው ። በእኛ ያለው እስከ ቤት ቍጥር ወርዶ እስከ ጎጥ ዘቅጦ ይታያል ። ፈሪሳዊነት አስመሳይነት ነው ።

ጌታችን ወደ ዓለም የላከው ሕይወታችን እንዲመሰክር እንጂ ቃላችን ብቻ እንዲመሰክር አይደለም ። አንድ ሰው፡- “የምትናገረውን የምትኖረው እያፈረሰብኝ ነውና ልሰማህ አልቻልኩም” እንዳለው እኛም ሆነናል ። በጎ ሥራ ምግባርን ሙሉ ያደርገዋል ። ባለ መስረቅ ብቻ ምግባር ሙሉ አይሆንም ፣ መስጠትም ያስፈልጋል ። ምግባር ሁለት እጆች አሉት፤ ክፉን ማቆምና በጎ መጀመር ናቸው ። የኃጢአት በጀታችን ለጽድቅ ካልዋለ ገና አላመንም ማለት ነው ። አለማመንዘር ብቻውን ብቂ አይደለም ፣ ለትዳር አጋር አሳቢ መሆንም ያስፈልጋል ። በጎ ሥራ ትላንት የሠራነውን ክፉ ነገር መካሻ ማጠቢያ ነው ። የበደሉትን መካስ ፣ የቀሙትን መመለስ እርሱ ንስሐ ይባላል ። በጎ ሥራ ዛሬን ኖርኩ የሚያሰኘን ነው ። ለነገው ትውልድ ቀሪ ሀብት ነው ። “የቄስ ልጅ እግዚአብሔር አጎቱ ይመስለዋል” እንዲሉ እኔን ምንም አይለኝም ብሎ ያውም በቤቱ በበደል መጽናት ተገቢ አይደለም ። ምክንያት አያድንም ። ወገን እያለቀ ምክንያት የሚደረድር ሹም ካለ ተባባሪ ነው ። ይህን ካላቆምሁ የእኔ መኖር ምን ጥቅም አለው ( የሚል ወኔያም ያስፈልጋል ። ዛሬ ማድረግ የሚገባንን ነገ ብናደርገው ከክፉ ሊቆጠር ይችላል ። ታሞ ያልረዳነውን የመቃብሩን ሐውልት ብንሠራለት ጥቅም የለውም ። ብዙዎች ስሞት አትቅበሩኝ ፣ ዛሬ አዳምጡኝ እያሉን ነው ። ፈሪሳዊነታችን ግን አልሰማቸውም ።

አንድ የበላይ ሰው አውቃለሁ ። ራበኝ የሚል ማመልከቻ ሲመጣላቸው በእሳቱ “ሰ” ሊጻፍ የሚገባውን በንጉሡ “ሠ” ጽፈሃልና አስተካክለህ አምጣ ይሉ ነበር ። ያ ረሀብ ዘመኑን እንዳያሳጥርበት የሚጨነቅ አገልጋይ “መቼ(” ሲል “ከዐሥር ቀን በኋላ ና” ይባላል ። ምክንያቱም ነገ የቦርድ ስብሰባ ፣ ተነገወዲያ የውጭ እንግዶች … እየተባለ ምክንያት ይሰጠዋል ። ረሀብተኛን ነገ ና ማለት አይቻልም ፣ ያለው ቀን ዛሬ ነውና ። ለፊደሉ ስንጨነቅ ለራበው ሰው ግን አንጨነቅም ። ጭካኔም ልክ አለው ።

አቤቱ ምን እየሆንን ነው ፣ እባክህ መልሰን !

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ጥቅምት 15 ቀን 2018 ዓ.ም.
21🥰2
እግዚአብሔር ቢፈቅድ ብንኖር ነገ

እሑድ ጥቅምት 15 ቀን 2018 ዓ.ም. ከ ጠዋቱ 4፡00 ሰዓት  ላይ ትምህርታችን ይጀምራል ::

የትምህርታችን ርእስ " የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስደት

ክፍል 3


ልደቱና ስደቱ ይተነተናል

ማስታወሻ ብትይዙ ይመከራል።

ሌሎች ወገኖቻችንንም ጋብዙ

https://www.tg-me.com/Nolawii
19👍2
Live stream started
Live stream finished (1 hour)
Audio
የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስደት 3
የመጨረሻው ክፍል
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
14
2025/10/27 05:07:31
Back to Top
HTML Embed Code: