Telegram Web Link
ቅዱስነታቸው የደቡብ አፍሪካ ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን አጠናቀው አዲስ አበባ ገቡ።
**

ብፁ
ዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ
ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዮንቨርሲቲ ፕሬዝዳንት፣የደቡብ ኦሞና
አሪ ዞኖች ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የዳውሮ-ኮንታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች በደቡብ አፍሪካ ሲያካሒዱት የቆዩትን ሐዋርያዊ አገልግሎት አጠናቀው ዛሬ ከቀትር በኋላ አዲስ አበባ ገብተዋል።

ቅዱስነታቸውና ከቅዱስ ፓትርያርኩ ጋር ወደ ደቡብ አፍሪካ የተጓዙት የልዑካን ቡድን አባላት ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ብፁዕ አቡነ አብሮሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የባህርዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ክቡር መልአከ ሕይወት ቆሞስ አባ ኃይለ ገብርኤል ነጋሽ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ፣የጠቅላይ ቤተክህነት መምሪያ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገው
ላቸዋል።

በመቀጠልም በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም የእንኳን ደህና መጡ አቀባበል መርሐ ግብር የሚካሔድ ሲሆን በዚሁ መርሐ ግብር ላይም ቅዱስ ፓትርያርኩ ትምህርተ ወንጌል፣ቃለ ምዕዳንና ቃለ ቡራኬ ሰጥተው የአቀባበል መርሐ ግብሩ የሚጠናቀቅ ይሆናል።

ምንጭ: የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

@ortodoxtewahedo
"አትጨነቁ ያሳያችሁኝ ፍቅር ጥንካሬ ሰጥቶኛል ብለዋል።" በኩረ መዘምራን ኪነጥበብ

ቤተክርስቲያን ያሳደገቻቸው በአለም ዘሪያ ያሉ ያልደወሉለት ፕሮፌሰሮች እና ዶክተሮች የሉም...የሆነው ሆኖ መቅረዝ ሆስፒታል በVIP አቀባበል ተቀብሎ በኩረ መዘምራን ሕክምናውን ጀምረዋል። ቤተክርስትያን ያፈራቻቸው ዶክተሮች እና ነርሶች ተረባርበው... "የሚቻል ቢሆን ከእድሜአችንም እየቀነስን በጨመርንልህ" ብለው እንደ ህመምተኛ ሳይሆን እንደ ንጉስ ተቀብለው አስተናግደውታል። አሉ የተባሉ ስፔሻሊስቶች አይተውታል ክትትል እያደረጉለት ነው።

ሁላችሁም መቅረዝ ሆስፒታል እንድትጎበኙት ተጋብዛችሁዋል። በዛውም ህሙማንን የመጎብኘት ልማድን እናካብት።

አብርሀም ሀይሉ

@ortodoxtewahedo
ሩስያ ሐገረ እግዚአብሔር
"በሩስያ ዮሽካር ግዛት የሚገኝ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ገዳም
በረከቱ ይደርብን ::

@ortodoxtewahedo
#እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የምህረት ቃል ኪዳን የተቀበለችበት ወርሃዊ መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ

#እንጦጦ ሀመረ ኖህ ኪዳነ ምህረት ገዳም

በአዲስ አበባ ከተማ በስተሰሜን ምሥራቅ በጉለሌ ክፍለ ከተማ የምትገኝ ስመጥርና ታሪካዊ ገዳም ስትሆን በተራራ፣በሸለቆና በወንዞች የተከበበች በመሆኑዋ በተፈጥሮ አቀማመጧ አረንጓዴ የተላበሰች ናት፡፡ ይህም ለቤተክርስቲያኗ ውበትና ግርማ ሞገስ ከመስጠት አልፎ በሚያስደስት ፀጥታ የአዕዋፍ ዝማሬ ተሞልታ ጸጋን እንድትላበስ አድርጓታል፡፡
ይህች ቦታ የተቆረቆረችው በ484 ዓ/ም ሲሆን በ500 ዓ.ም በአባ ሊባኖስ የአንድነት ገዳም ሆና ተቋቋመች፡፡ አባ ሊባኖስ ወደ ሌላ መንፈሳዊ ተልእኮ ለመሄድ መነኮሳቱን ሲሰናበቱ እንዲህ የሚል ትንቢት ተናግረው ነበር ‹‹ልጆቼ ሆይ በሉ ይህችን ቅድስት ቦታ አደራ ሰጥቻችኋለሁ በኋላ ዘመን ታላቅ ቦታ ትሆናለች' አጋንንት ይወገዱባታል' የብዙ ቅዱሳን አፅም ያርፍባታል' ነገስታት ጳጳሳት ይሰግዱባታል' ብዙ መናንያን መጠጊያ ያደርጋታል ቤተ መቅደሷም በወርቅ በብር ተጊጣ ትታነጻለች የአንድነቱም ገዳም ተሻሽሎ ይቋቋምባታል››፡፡ በ9ኛ መቶ ክ/ዘመን ዮዲት ጉዲት የአክሱም ጽዮንን ቤተ መቅደስ ለማቃጠል ስትነሳ ንጉሡ አንበሣ ውድም ታቦተጽዮንን በምሥጢር በማስያዝ ወደ ሸዋ መጥተው በእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነምሕረት ገዳም ታቦተ ጽዮንን አሳድረው ወደ ዝዋይ ደሴት ሲሄዱ ለገዳሟ ንዋየ ቅድሰት ስጦታ አበርክተዋል ጸበሏን ተጠምቀው ቦታውን መርቀው ሄደዋል፡፡
በ12ኛው መቶ ክ/ዘመን ጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ከንጉሥ ላሊበላ ጋር ወደ ዝቋላ አምባ ሲመጡ በዚህች ገዳም በእንግድነት አድረው በጸበሏ ተጠምቀው ቦታውን ባርከዋል፡፡ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስም ለመነኮሳቱ እንዲህ ብለው ነበር ‹‹ይህች ገዳም ታላቅ ስመጥር ገዳም ትሆናለች ከእርሷ በታች የሚታየው ጫካና ዱር መናገሻ ከተማ ይሆናል፡፡››
አፄ ዘርዓ ያዕቆብም ወደዚህች ገዳም መጥተው አቀማመጧንና የጸበሏን ፈዋሽነት ተመልክተዋል ‹‹ዳሯ እሳት መሐሏ ገነት ይሁን›› ብለው ብዙ ስጦታ አበርክተዋል፡፡ አፄ ልብነ ድንግልም ወደ ገዳሟ መጥተው ተማህጽኖ አድርገው በጸበሏ ተጠምቀው ታቦተ ልደታንና ብዙ ንዋየቅድሳት ሰጥተው ሄደዋል፡፡ በንግስት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት ይህች ገዳም ሐመረ ኖኅ ኪዳነምህረት ገዳም ተብላ ተሰይማለች፡፡
ይህች ቦታ እንደተነገረላት ትንቢት ብዙ ቅዱሳንና ነገሥታት መጥተው የሰገዱባት የባረኳት' ጸበሏ የአጋንንት ድል መንሻ' የብዙ መነኮሳት መጠጊያ 'የህሙማን መፈወሻ' የእመቤታችንን ቃል ኪዳን ለማግኘት ብዙን ጊዜ ለሱባኤ ከሚመረጡ ቦታዎች አንዷ ናት፡፡ ይህች ደብር በ1957 ዓ/ም የተመሠረተ ሰንበት ት/ቤት ሲኖራት በ1984 ዓ/ም በብፁዓን ጳጳሳት ‹‹መርሶ ሕይወት›› /የሕይወት ወደብ/ የሚለውን ስያሜ አግኝቷል፡፡ የገዳሟ ስያሜ ሐመረ ኖኅ ( የኖኅ መርከብ ) እንደሆነ ሁሉ መርሶ ሕይወት ( የሕይወት ወደብ ) በመባሉ ሁለቱ ተዛማችነት አላቸው ፡፡ ይህ ሰንበት ት/ቤት ለየት የሚያደርገው በግል መኖሪያ ቤት በጋሞኛ ቋንቋ ይሰጥ የነበረውን ትምህርት ከ1986 ጀምሮ በሰ/ት/ቤቱ ስር በማቀፍ የወንጌል ትምህርቱን ከመማር ባሻገር ለጋሞ ሕዝብ መንፈሳዊ እንቅስቃሴን በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
አዘጋጅ፡- እህተ ማርያም (በሰ/ት/ቤታችን ሰሌዳ መጽሔት ቀርቦ የነበረ)

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ለዘለአለም ትኑር!!!

ሰው ሁሉ ለመናገር የዘገየ ለመስማት የፈጠነ ይሁን !
(ያዕቆብ 1፥19)

< ወስብሐት ለእግዚአብሔር

@ortodoxtewahedo
Today,s Best photo
የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ካቴድራል
በሩስያዋ መስኮቭ (ሞስኮ) ከተማ
በረከቱ ይደርባችሁ

@ortodoxtewahedo
Audio
ስመለስ እከፍልሃለሁ

Size:-28.2MB
Length:-1:21:02

    በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

@ortodoxtewahedo
Audio
በወርቅ መቅረዞች መሐል ያለው
ራእይ 1÷13
👉በአዲስ አበባ ደ/ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ ግንቦት 16/2013ዓ.ም የተሰጠ ትምህርት

Size:- 27.2MB
Length:-1:58:56

በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

@ortodoxtewahedo
Audio
አትባክኑ|| ተነሡ ከዚህ እንሂድ

Size:-33MB
Length:-1:34:46

    በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

@ortodoxtewahedo
የድንግል ማርያም ዓበይት በዓላት የምንላቸው ወር በገባ 21 ሳይጨመር

🔘መስከረም 10
🔸ጸዴንያ ማርያም

🔘መስከረም 21
🔸ግሸን ማርያም

🔘ህዳር 6
🔸ቁስቋም ማርያም

🔘ህዳር 21
🔸ጽዮን ማርያም

🔘ታህሳስ 3
🔸በዓታ ለማርያም

🔘ታህሳስ 22
🔸ብስራተ ገብርኤል

🔘ታህሳስ 28/29
🔸ልደት

🔘ጥር 21
🔸የእመቤታችን በዓለ ዕረፍት

🔘የካቲት 16
🔸ኪዳነምህረት ቃል ኪዳን የተቀበለችበት

🔘ግንቦት 1
🔸ልደታ ለማርያም

🔘ግንቦት 24
🔸ስደት የጀመረችበት

🔘ግንቦት 21-25
🔸ለአምስት ቀናት ደብረ ምጥማቅ የተገለጠችበት

🔘ሰኔ 8
🔸ስለ ኃዘኗ ጌታችን ከደረቀ ዓለት ላይ ውኃ ያፈለቀበት

🔘ሰኔ 20
🔸ሕንጸተ ቤተከርስቲያን

🔘ሐምሌ 26
🔸ዕረፍቱ ለዮሴፍ አረጋዊ

🔘ነሐሴ 7
🔸ጽንሰታ ለማርያም

🔘ነሐሴ 16
🔸ዕርገተ ለማርያም

http://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
#ደብረ ምጥማቅ
ጻድቃኔ ማርያም ገዳም

💠በሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃና ወደራ ወረዳ የሚገኘው የደብረ ምጥማቅ ማርያምና የጻድቃኔ ቅድስት ማርያም መካነ ቅዱሳን አንድነት ገዳም በ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በንጉሥ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ አማካይነት እንደተመሠረተ የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡

💠ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ቤተ ክርስቲያኑን ሊያሠሩ የቻሉበት ዋነኛ ምክንያትም፤ በግብፅ ሀገር ሃይማኖት፤ ዘር፤ ቀለም ሳትለይ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስትገለጽ የነበረችበት ቤተ ክርስቲያን እሰላሞች በማቃጠላቸው እጅግ አዝነው ስለነበር በኢትዮጵያ ውስጥ ሰሜን ሸዋ ላይ ቤተ ክርስቲያኑን እንዳሠሩ የታሪክ መዛግብት ያስረዳሉ፡፡

💠በኢትዮጲያ ከሚገኙ የተባህትዎ ቦታዎች አንዷ የሆነችው ይህች ጻድቃኔ ማርያም ገዳም ከጥንት ጀምሮ ነገሥታት፣ ካህናትና ምእመናን ደጅ የጠኑባት፤ ሥጋቸውን ለነብሳቸው ያስገዙባት፤ ቃለ እግዚአብሔርን የሚማሩባት ነበረች፤ ለ500 ዓመታት ያህል ገዳሟ መናንያን የማይኖሩባት በቅዱሳን የምትጠበቅ ሆና ኖራለች፡፡

💠ከ500 ዓመታት በኋላ ጊዜ ገቢር ለእግዚአብሔር እንዲሉ በ20ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጨረሻና በ21ኛው መቶ ክፈለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ገዳሟ ዳግም አንሰራራች፤ ገዳሟ ምእመናን ፈቃደ ሥጋቸውን ለፈቃደ ነፍሳቸው የሚያስገዙባት፤ ፈውስ ሥጋዊ ወመንፈሳዊ የሚያገኙባት፤ ሱባኤ ይዘው ከእግዚአብሔር መልስ የሚያገኙባት፤ መናንያን እንደ መላእክት የሚኖሩባት፤ የጽድቅ ተግባራት የሚከናወንባት፤ የእግዚአብሔር ቸርነቱ የበዛባት፤ የእመቤታችን ፍቅሯና ምልጃዋ የነገሰባት ቦታ ናት፡፡

💠በንጉሥ ዘርዐ ያዕቀብ የተመሠረተው ይህ ገዳም አሁንም ባለንበት ዘመን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በሕልም፤ በራዕይና በተከስቶ እየተገለጸች ምእመናንን እየተራዳች፤ በስሟ ከፈለቀው ጸበል እየጠጡና እየተጠመቁ ከተለያዩ ደዌያት በመፈወስ ላይ ናቸው፡፡

💠አሁን ላይ የጻድቃኔ ማርያም ቤተ ክርስቲያን እሰከ 25 ሚሊዮን ብር በሚደርስ ወጪ የቤተ ክርስቲያኑን ሕንፃ እየተገነባ ነው፤  የጽድቅ በር፤ የደኀንነት መድን የሆነችውን ቦታ ጠብቆና አስጠብቆ ማቆየት ደግሞ የሁሉም ክርስቲያን ግዴታ ነው፡፡

💠ዛሬ ከምናየውና ከምንሰማው መልካም ጅምር ተነስተን ለወደፊቱም ታስቦበት ገዳሙ ሰፍቶ፤ ምእመናን ተጽናንተውና ተፈውሰው የሚመለሱባት ቦታ እንድትሆን ማድረግ ኃላፊነት ስላለብን የበኩላችንን አስተዋኦ ማበርከት ይኖርብናል፡፡

   ከእናታች ከንጽህት ድንግል ማሪያም ረድኤት በከረት ይክፈለን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
          ይቆየን

http://www.tg-me.com/ortodoxtewahedo
2024/05/29 08:27:18
Back to Top
HTML Embed Code: