[በ40 ምንጭና በተለያዩ አካባቢዎች በሰማይ ላይ እየነደደ የሚጓዘው ምን ይኾን? በሳይንስና በሃይማኖት]
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 ዛሬ ጥር 1/ 2017 ዓ.ም. በሀገራችን በተለያዩ ቦታዎች የታየ በሰማይ እየተቀጣጠለ የሚኼድ በጣም በርካታ ፎቶዎችና ቪዲዮዎች በውስጥ መሥመር እየተላኩልኝ ነበርና ምልከታዬን ለማስቀመጥ እሞክራለኹ።
💥 ከሰማይ ላይ አብርተው ስለሚታዩ ስለሚወድቁ የተፈጥሮና ሰው ሠራሽ አካላት መረዳት ግድ ይላል።
የተፈጥሮ የሕዋ ዐለቶችን አስቀድመን እንመልከት፦
1. አስትሮይድ
2. ሜትዮራይድ
3. ሚትዮር
4. ሜትሮይት
መካከል ያለውን ልዩነት አንድነት መረዳት ያስፈልጋል፡-
1. አስትሮይድ
💥 በዋነኛነት በማርስ እና በጁፒተር መካከል ባለው የአስትሮይድ ቀበቶ ውስጥ የሚገኙት ዐለታማ ሥሪትነት ያላቸው አካላት ናቸው። መጠናቸውን ለመረዳት ለምሳሌ አስትሮይድ ቬስታ መጠኑ 329 ማይል (530 ኪሎ ሜትር) ዲያሜትር ያለው ሲኾን ከታናናሾቹ ውስጥ ከ33 ጫማ (10 ሜትር) በታች የኾኑም ይገኙበታል። የኹሉም አስትሮይድ አጠቃላይ ክብደት ግን ከምድር ጨረቃ ያነሰ ነው።
👉 በዚኹ አጋጣሚ በኢትዮጵያ አቆጣጠር ዐርብ ሚያዝያ 5/ 2021 ዓ.ም ወይም እንደ ጎርጎርዮሳዊ አቆጣጠር ኤፕሪል 13/ 2029 አፖፊስ የተባለው አስትሮይድ ከምድር በላይ 30,600 ኪሎ ሜትር (19,000 ማይል) ርቀት ላይ የሚያልፍ ሲኾን ቢሊዮኖች በዐይናቸው ያዩታል። መሬትን የመመታት ዕድሉ 2.7 ፐርሰንት ብቻ ነው። (አንድሮሜዳ ክፍል 2 ገጽ 388 - 394 )
2. ሜትዮራይድ
💥 ሜትዮራይዶች በሕዋ ያሉ ትናንሽ ዐለቶች ሲኾኑ መጠናቸው ከከሸዋ ቅንጣት እስከ 1 ሜትር አካባቢ ይደርሳሉ። አንዳንድ ሜትዮራይድ ዐለቶች ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ ብረታ ብረት ወይም የድንጋይ እና የብረት ውሕዶች ናቸው። ሜትዮራይድ ብዙ ጊዜ ከአስትሮይድ ወይም ከኮሜት ወይም ከሌሎች ፕላኔቶች ጭምር የሚመጡ ናቸው። በአጠቃላይ ሜትዮራይድ ስንል ገና በሕዋ ላይ ያሉትን ነው።
3. ሚትየር
💥 ከላይ እንዳየነው ሜትዮራይድ ወደ ምድር ከባቢ አየር ወይም ወደ ሌላ ፕላኔት በከፍተኛ ፍጥነት ሲገቡ እና ሲቃጠሉ ሚትዮር ይባላሉ። በሌላ አጠራር “ተወርዋሪ ኮከቦች” ብለን የምንጠራቸው ሲኾን አንዳንድ ጊዜ ሜትየሮች ከቬኑስ የበለጠ ብሩህ ኾነው ሊታዩ ይችላሉ። ያን ጊዜ “የእሳት ኳሶች” ተብለው ይጠራሉ። ብዙ ተወርዋሪ ከዋክብት በአንድ ላይ በሰዓታት ሲታዩ "ሜትየር ሻወር" በመባል ይታወቃሉ።
4. ሜትሮይት
💥 ሳይቃጠል የምድርን ከባቢ አየር ዐልፎ በምድር ላይ የሚያርፍ የሜትሮይድ ቁራጭ መጠሪያ ነው። በሰዓት በዐሥር ሺዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን በመጓዝ በኃይለኛ ግፊት ወድቆ ሲበታተን ብሩህ ነበልባል ይመስላል።
ሜትሮይትስ በሦስት ዋና ዋና ዓይነቶች ይከፈላሉ፡-
1) ድንጋያማ ሜትሮይትስ (በዋነኛነት ከሲልኬት) ማዕድናት የተውጣጡ ናቸው)፣
2) የብረት ሜትሮዮይትስ (በአብዛኛው ከብረት-ኒኬል ውሕዶች የተውጣጡ ናቸው)
3) ድንጋያማ ብረት ሜትሮይትስ (በግምት እኩል መጠን ያላቸው የሲሊኬት ማዕድናት እና ብረት ኒኬል ይዘዋል)
👉 ሜትሮይቶች ሲታዩ የምድር ዐለቶችን ሊመስሉ ይችላሉ፣ ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜ የሚያብረቀርቅ ሊመስል የሚችል የተቃጠለ ውጫዊ ክፍል አላቸው። ይኸውም በከባቢ አየር ውስጥ በሚያልፉበት ጊዜ የሜትሮይት ውጫዊ ገጽታ ሲቀልጥ የሚፈጠር ነው።
👉በምድር ላይ ከ 50,000 በላይ ሜትሮይትስ ተገኝተዋል.
ከእነዚህ ውስጥ 99.8% የሚሆኑት ከአስትሮይድ የሚመጡ ናቸው።
👉 በየቀኑ 48.5 ቶን የሜትሮይት ቁስ አካል ወደ ምድር ይወድቃል። ይህም በዓመት 17,000 ሚቴዮራይትስ እንደማለት ነው። አብዛኛው ግን በከባቢ አየር ውስጥ ተንኖ ተወርዋሪ ኮከብ ይኾናል።
👉 በቅርብ የተከሰቱ አደገኛ ከሚባሉት የሜትሮይትስ ክስተቶች ውስጥ ኹለቱን በማንሣት ጽሑፌን ልቋጭ፦
1ኛ) በዘመናዊ ታሪክ ውስጥ አንድ ትልቅ ሜትሮይድ ወደ ምድር ከባቢ አየር ውስጥ የገባው እኤአ በ1908 ሲኾን የቱንጉስካ ክስተት በመባል ይታወቃል። ይህ ሜትዮር በሩሲያ በሳይቤሪያ ላይ የተከሰተ ሲኾን ምድሩን ሳይመታ በፊት በአየር ላይ ጥቂት ማይል ርቀት ላይ ፈነዳ።
👉 የፍንዳታው ኃይል በመቶዎች የሚቆጠሩ ማይሎች ስፋት ባለው ክልል ውስጥ ዛፎችን ለማውደም የሚያስችል ኃይለኛ ነበር። ሜትዮሩ 120 ጫማ (37 ሜትር) ስፋት ያለው እና 220 ሚሊዮን ፓውንድ (100 ሚሊዮን ኪሎ ግራም) ይመዝን ነበረ። በአካባቢው በመቶዎች የሚቆጠሩ አጋዘኖች ሲሞቱ ነገር ግን ማንም ሰው በፍንዳታው መሞቱን የሚያሳይ ቀጥተኛ መረጃ የለም።
2ኛ) እ.ኤ.አ. በ 2013 በቼልያቢንስክ ሩሲያ ሰማይ ላይ ቤትን የሚያህል ሜትሮይድ በሰከንድ ከ11 ማይል (18 ኪሎ ሜትር) በላይ ወደ ከባቢ አየር በመግባት ከመሬት በላይ 14 ማይል (23 ኪሎ ሜትር) ላይ ፈነዳ። ፍንዳታው ወደ 440,000 ቶን የሚገመተውን የቲኤንቲ ኃይል በመልቀቁ ከ200 ስኩዌር ማይል (518 ስኩዌር ኪሎ ሜትር) በላይ መስኮቶችን የሰባበረ እና ሕንፃዎችን ያበላሽ አስደንጋጭ ኹኔታን ፈጠረ። በፍንዳታው ይልቁኑ በመስታወት ስብርባሪ ከ1,600 በላይ ሰዎች ቆስለዋል።
💥 ሌላው በሰማይ እየተቃጠሉ ሲሄዱ ሊታዪ የሚችሉት ሰው ሠራሽ ነገሮች
👉 ከአሁን በኋላ የማይሠሩ በጠፈር ውስጥ ያሉ ሰው ሠራሽ ነገሮች Space debris, space junk, orbital debris በመባል ይታወቃሉ።
ለምሳሌ፡-
👉 የድሮ ሳተላይቶች
👉 የሮኬት ክፍልፋዮች
👉 የፈነዱ ወይም የተጋጩ ተሽከርካሪዎች ወይም የተቆራረጡ ቁርጥራጮች ይገኙበታል።
👉 ከጠፈር ተልእኮ በኋላ የተጣሉ ቁሶች ናቸው።
💥 በግምት ከ10 ሴንቲ ሜትር በላይ ከ36,500 በላይ ቁሶች ሲኖሩ፤ ከ1-10 ሴ.ሜ በላይ 1 ሚሊዮን ቁርጥራጮች እና ከ1 130 ሚሊዮን የሚጠጉ ትናንሽ ቁርጥራጮች ይገኛሉ።
ሊያመጡ የሚችሉት አደጋዎች፡-
1) የሚሠሩ ሳተላይቶችን፣ ዐለም ዐቀፍ የጠፈር ጣቢያ (አይኤስኤስ) ወይም የጠፈር መንኮራኩሮችን በመግጨት ሊጎዳ ይችላል።
👉 አንዳንድ ቁርጥራጮች ወደ ምድር ከባቢ አየር ውስጥ ከገቡ መሬት ላይ አደጋ ሊፈጥሩ ይችላሉ።
👉 ለምሳሌ ሰኞ ታኅሣሥ 21/ 2017 ወይም December 30, 2024, በኬንያ፣ ሙኩኩ መንደር ውስጥ ከሮኬት የመለያያ ቀለበት በመባል የሚታወቅ አንድ ትልቅ ብረታማ ነገር የተከሰከሰ ሲኾን ቀለበቱ በግምት 2.5 ሜትር ዲያሜትር እና 500 ኪሎ ግራም ይመዝናል። እንደ እድል ሆኖ ግን ምንም ጉዳት አልደረሰም።
💥 ሌላው በተለያዩ ሀገራት ታዩ የሚባሉት የማይታወቁ በራሪ አካላት (UFO ወይም UAP) ዙሪያ ብዙ ቪዲዮዎች በYoutube ላይ የሠራሁትን ማየት ይቻላል።
💥 በሃይማኖት መጻሕፍት ስንመለከት በተለይ በዮሐንስ ራእይ ላይ ለቁጣ የሚወድቁ እንደ ችቦ የተቃጠለ የሚመስል እንደሚወድቅ እንዲህ ይጽፋል፦
✍️ “ሦስተኛውም መልአክ ነፋ፤ እንደ ችቦም የሚቃጠል ታላቅ ኮከብ ከሰማይ ወደቀ፥ በወንዞችና በውኃም ምንጮች ሲሶ ላይ ወደቀ። የኮከቡም ስም እሬቶ ይባላል። የውሃውም ሲሶ መራራ ሆነ መራራም ስለተደረገ በውሃው ጠንቅ ብዙ ሰዎች ሞቱ።”
— ራእይ 8፥10-11
✍️ “ሁለተኛውም መልአክ ነፋ፤ በእሳት የሚቃጠል ታላቅ ተራራን የሚመስል ነገር በባሕር ተጣለ፤ የባሕርም ሲሶው ደም ሆነ”
— ራእይ 8፥8
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 ዛሬ ጥር 1/ 2017 ዓ.ም. በሀገራችን በተለያዩ ቦታዎች የታየ በሰማይ እየተቀጣጠለ የሚኼድ በጣም በርካታ ፎቶዎችና ቪዲዮዎች በውስጥ መሥመር እየተላኩልኝ ነበርና ምልከታዬን ለማስቀመጥ እሞክራለኹ።
💥 ከሰማይ ላይ አብርተው ስለሚታዩ ስለሚወድቁ የተፈጥሮና ሰው ሠራሽ አካላት መረዳት ግድ ይላል።
የተፈጥሮ የሕዋ ዐለቶችን አስቀድመን እንመልከት፦
1. አስትሮይድ
2. ሜትዮራይድ
3. ሚትዮር
4. ሜትሮይት
መካከል ያለውን ልዩነት አንድነት መረዳት ያስፈልጋል፡-
1. አስትሮይድ
💥 በዋነኛነት በማርስ እና በጁፒተር መካከል ባለው የአስትሮይድ ቀበቶ ውስጥ የሚገኙት ዐለታማ ሥሪትነት ያላቸው አካላት ናቸው። መጠናቸውን ለመረዳት ለምሳሌ አስትሮይድ ቬስታ መጠኑ 329 ማይል (530 ኪሎ ሜትር) ዲያሜትር ያለው ሲኾን ከታናናሾቹ ውስጥ ከ33 ጫማ (10 ሜትር) በታች የኾኑም ይገኙበታል። የኹሉም አስትሮይድ አጠቃላይ ክብደት ግን ከምድር ጨረቃ ያነሰ ነው።
👉 በዚኹ አጋጣሚ በኢትዮጵያ አቆጣጠር ዐርብ ሚያዝያ 5/ 2021 ዓ.ም ወይም እንደ ጎርጎርዮሳዊ አቆጣጠር ኤፕሪል 13/ 2029 አፖፊስ የተባለው አስትሮይድ ከምድር በላይ 30,600 ኪሎ ሜትር (19,000 ማይል) ርቀት ላይ የሚያልፍ ሲኾን ቢሊዮኖች በዐይናቸው ያዩታል። መሬትን የመመታት ዕድሉ 2.7 ፐርሰንት ብቻ ነው። (አንድሮሜዳ ክፍል 2 ገጽ 388 - 394 )
2. ሜትዮራይድ
💥 ሜትዮራይዶች በሕዋ ያሉ ትናንሽ ዐለቶች ሲኾኑ መጠናቸው ከከሸዋ ቅንጣት እስከ 1 ሜትር አካባቢ ይደርሳሉ። አንዳንድ ሜትዮራይድ ዐለቶች ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ ብረታ ብረት ወይም የድንጋይ እና የብረት ውሕዶች ናቸው። ሜትዮራይድ ብዙ ጊዜ ከአስትሮይድ ወይም ከኮሜት ወይም ከሌሎች ፕላኔቶች ጭምር የሚመጡ ናቸው። በአጠቃላይ ሜትዮራይድ ስንል ገና በሕዋ ላይ ያሉትን ነው።
3. ሚትየር
💥 ከላይ እንዳየነው ሜትዮራይድ ወደ ምድር ከባቢ አየር ወይም ወደ ሌላ ፕላኔት በከፍተኛ ፍጥነት ሲገቡ እና ሲቃጠሉ ሚትዮር ይባላሉ። በሌላ አጠራር “ተወርዋሪ ኮከቦች” ብለን የምንጠራቸው ሲኾን አንዳንድ ጊዜ ሜትየሮች ከቬኑስ የበለጠ ብሩህ ኾነው ሊታዩ ይችላሉ። ያን ጊዜ “የእሳት ኳሶች” ተብለው ይጠራሉ። ብዙ ተወርዋሪ ከዋክብት በአንድ ላይ በሰዓታት ሲታዩ "ሜትየር ሻወር" በመባል ይታወቃሉ።
4. ሜትሮይት
💥 ሳይቃጠል የምድርን ከባቢ አየር ዐልፎ በምድር ላይ የሚያርፍ የሜትሮይድ ቁራጭ መጠሪያ ነው። በሰዓት በዐሥር ሺዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን በመጓዝ በኃይለኛ ግፊት ወድቆ ሲበታተን ብሩህ ነበልባል ይመስላል።
ሜትሮይትስ በሦስት ዋና ዋና ዓይነቶች ይከፈላሉ፡-
1) ድንጋያማ ሜትሮይትስ (በዋነኛነት ከሲልኬት) ማዕድናት የተውጣጡ ናቸው)፣
2) የብረት ሜትሮዮይትስ (በአብዛኛው ከብረት-ኒኬል ውሕዶች የተውጣጡ ናቸው)
3) ድንጋያማ ብረት ሜትሮይትስ (በግምት እኩል መጠን ያላቸው የሲሊኬት ማዕድናት እና ብረት ኒኬል ይዘዋል)
👉 ሜትሮይቶች ሲታዩ የምድር ዐለቶችን ሊመስሉ ይችላሉ፣ ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜ የሚያብረቀርቅ ሊመስል የሚችል የተቃጠለ ውጫዊ ክፍል አላቸው። ይኸውም በከባቢ አየር ውስጥ በሚያልፉበት ጊዜ የሜትሮይት ውጫዊ ገጽታ ሲቀልጥ የሚፈጠር ነው።
👉በምድር ላይ ከ 50,000 በላይ ሜትሮይትስ ተገኝተዋል.
ከእነዚህ ውስጥ 99.8% የሚሆኑት ከአስትሮይድ የሚመጡ ናቸው።
👉 በየቀኑ 48.5 ቶን የሜትሮይት ቁስ አካል ወደ ምድር ይወድቃል። ይህም በዓመት 17,000 ሚቴዮራይትስ እንደማለት ነው። አብዛኛው ግን በከባቢ አየር ውስጥ ተንኖ ተወርዋሪ ኮከብ ይኾናል።
👉 በቅርብ የተከሰቱ አደገኛ ከሚባሉት የሜትሮይትስ ክስተቶች ውስጥ ኹለቱን በማንሣት ጽሑፌን ልቋጭ፦
1ኛ) በዘመናዊ ታሪክ ውስጥ አንድ ትልቅ ሜትሮይድ ወደ ምድር ከባቢ አየር ውስጥ የገባው እኤአ በ1908 ሲኾን የቱንጉስካ ክስተት በመባል ይታወቃል። ይህ ሜትዮር በሩሲያ በሳይቤሪያ ላይ የተከሰተ ሲኾን ምድሩን ሳይመታ በፊት በአየር ላይ ጥቂት ማይል ርቀት ላይ ፈነዳ።
👉 የፍንዳታው ኃይል በመቶዎች የሚቆጠሩ ማይሎች ስፋት ባለው ክልል ውስጥ ዛፎችን ለማውደም የሚያስችል ኃይለኛ ነበር። ሜትዮሩ 120 ጫማ (37 ሜትር) ስፋት ያለው እና 220 ሚሊዮን ፓውንድ (100 ሚሊዮን ኪሎ ግራም) ይመዝን ነበረ። በአካባቢው በመቶዎች የሚቆጠሩ አጋዘኖች ሲሞቱ ነገር ግን ማንም ሰው በፍንዳታው መሞቱን የሚያሳይ ቀጥተኛ መረጃ የለም።
2ኛ) እ.ኤ.አ. በ 2013 በቼልያቢንስክ ሩሲያ ሰማይ ላይ ቤትን የሚያህል ሜትሮይድ በሰከንድ ከ11 ማይል (18 ኪሎ ሜትር) በላይ ወደ ከባቢ አየር በመግባት ከመሬት በላይ 14 ማይል (23 ኪሎ ሜትር) ላይ ፈነዳ። ፍንዳታው ወደ 440,000 ቶን የሚገመተውን የቲኤንቲ ኃይል በመልቀቁ ከ200 ስኩዌር ማይል (518 ስኩዌር ኪሎ ሜትር) በላይ መስኮቶችን የሰባበረ እና ሕንፃዎችን ያበላሽ አስደንጋጭ ኹኔታን ፈጠረ። በፍንዳታው ይልቁኑ በመስታወት ስብርባሪ ከ1,600 በላይ ሰዎች ቆስለዋል።
💥 ሌላው በሰማይ እየተቃጠሉ ሲሄዱ ሊታዪ የሚችሉት ሰው ሠራሽ ነገሮች
👉 ከአሁን በኋላ የማይሠሩ በጠፈር ውስጥ ያሉ ሰው ሠራሽ ነገሮች Space debris, space junk, orbital debris በመባል ይታወቃሉ።
ለምሳሌ፡-
👉 የድሮ ሳተላይቶች
👉 የሮኬት ክፍልፋዮች
👉 የፈነዱ ወይም የተጋጩ ተሽከርካሪዎች ወይም የተቆራረጡ ቁርጥራጮች ይገኙበታል።
👉 ከጠፈር ተልእኮ በኋላ የተጣሉ ቁሶች ናቸው።
💥 በግምት ከ10 ሴንቲ ሜትር በላይ ከ36,500 በላይ ቁሶች ሲኖሩ፤ ከ1-10 ሴ.ሜ በላይ 1 ሚሊዮን ቁርጥራጮች እና ከ1 130 ሚሊዮን የሚጠጉ ትናንሽ ቁርጥራጮች ይገኛሉ።
ሊያመጡ የሚችሉት አደጋዎች፡-
1) የሚሠሩ ሳተላይቶችን፣ ዐለም ዐቀፍ የጠፈር ጣቢያ (አይኤስኤስ) ወይም የጠፈር መንኮራኩሮችን በመግጨት ሊጎዳ ይችላል።
👉 አንዳንድ ቁርጥራጮች ወደ ምድር ከባቢ አየር ውስጥ ከገቡ መሬት ላይ አደጋ ሊፈጥሩ ይችላሉ።
👉 ለምሳሌ ሰኞ ታኅሣሥ 21/ 2017 ወይም December 30, 2024, በኬንያ፣ ሙኩኩ መንደር ውስጥ ከሮኬት የመለያያ ቀለበት በመባል የሚታወቅ አንድ ትልቅ ብረታማ ነገር የተከሰከሰ ሲኾን ቀለበቱ በግምት 2.5 ሜትር ዲያሜትር እና 500 ኪሎ ግራም ይመዝናል። እንደ እድል ሆኖ ግን ምንም ጉዳት አልደረሰም።
💥 ሌላው በተለያዩ ሀገራት ታዩ የሚባሉት የማይታወቁ በራሪ አካላት (UFO ወይም UAP) ዙሪያ ብዙ ቪዲዮዎች በYoutube ላይ የሠራሁትን ማየት ይቻላል።
💥 በሃይማኖት መጻሕፍት ስንመለከት በተለይ በዮሐንስ ራእይ ላይ ለቁጣ የሚወድቁ እንደ ችቦ የተቃጠለ የሚመስል እንደሚወድቅ እንዲህ ይጽፋል፦
✍️ “ሦስተኛውም መልአክ ነፋ፤ እንደ ችቦም የሚቃጠል ታላቅ ኮከብ ከሰማይ ወደቀ፥ በወንዞችና በውኃም ምንጮች ሲሶ ላይ ወደቀ። የኮከቡም ስም እሬቶ ይባላል። የውሃውም ሲሶ መራራ ሆነ መራራም ስለተደረገ በውሃው ጠንቅ ብዙ ሰዎች ሞቱ።”
— ራእይ 8፥10-11
✍️ “ሁለተኛውም መልአክ ነፋ፤ በእሳት የሚቃጠል ታላቅ ተራራን የሚመስል ነገር በባሕር ተጣለ፤ የባሕርም ሲሶው ደም ሆነ”
— ራእይ 8፥8
💥 ስለዚኽ አንባቢዎች የራሳችሁን ምልከታ በአስተያየት መስጫው ላይ ማስቀመጥ ትችላላችኹ።
(ስለ ሥነ ፈለክ ለመረዳት አንድሮሜዳ ክፍል 1፤ አንድሮሜዳ ክፍል 2፤ ማዛሮት መጽሐፍን ያንብቡ)
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
(ስለ ሥነ ፈለክ ለመረዳት አንድሮሜዳ ክፍል 1፤ አንድሮሜዳ ክፍል 2፤ ማዛሮት መጽሐፍን ያንብቡ)
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
የ6 ፕላኔቶች ሰልፍ ደረሰ
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
👉 በመላው ዓለም የምትገኙ የከዋክብት ተመልካቾች በጥር ወር በ2017 ዓ.ም. የ6 ፕላኔቶች፦
በኢትዮጵያዊ ሥነ ፈለክ አጠራር
👉 መሪህ፣ መሽተሪ፣ ዝሁራ፣ ሳተርን ወይም በውጪው አጠራር ማርስ፣ ጁፒተር፣ ቪነስ፣ ሳተርን፣ ዩራነስ፣ ኔፕቱን
ድንቅ ሰልፍን በሰማይ ላይ የምታዩበት ምርጥ ምሽት መጣ።
👉 ያለምንም መሣሪያ በቀላሉ በዐይን ማየት የምንችለው ማርስ፣ ጁፒተር፣ ቬኑስ እና ሳተርን ናቸው።
👉 ዩራኑስ እና ኔፕቱን ለመመልከት ግን ቴሌስኮፕ ያስፈልገናል።
💥 በመኾኑም ፀሓይ ከጠለቀች በኋላ ወደ ደቡብ ምዕራብ አድማስ ስንመለከት ፕላኔት ቬኑስ እና ሳተርን ተቀራርበው ሲታዩ ያለምንም መሣሪያ በዐይን ብቻ ማየት ትችላላችሁ። ከሁለቱም ብሩህ የሆነችው ደግሞ ኮከበ ምዕራብ ወይም በአቡሻሕር አጠራር አስታርቦ ሸሽ ቬነስ ስትኾን በብርሃን አነስ ብሎ የሚታየን ሳተርን ነው።
👉 በሰማይ ላይ ከፍ ብለን በዐይናችን ስንመለከት ከቬኑስ ቀጥሎ በምሽት ሰማይ ላይ ሁለተኛው ደማቅ ብርሃን በኢትዮጵያዊ የሥነ ፈለክ አጠራር መሽተሪ ወይም ፕላኔት ጁፒተር በሠውር (ታውረስ) መናዝል በቀንዶቹ መኻከል በቀዩ የሠውር ዐይን በአልዴባራን ትይዩ ደምቆ በዐይን ይታያል።
👉 በምሥራቃዊው አድማስ አቅራቢያ ደግሞ ቀዩ ፕላኔት በኢትዮጵያ የሥነ ፈለክ ሥያሜ "መሪህ" ወይም ፕላኔት ማርስ በቀይ ቀለም በድምቀት አብርቶ ለሁሉም በዐይን ይታያል።
💥 በተለይ ኀሙስ ጥር 8 (January 16) ቀይ ፕላኔቱ ወደ ምድር በጣም ቅርብ በሆነ አቀራረብ ላይ ስለሚኾን መልክአ ማርስ በፀሐይ ሙሉ በሙሉ ያበራል። በዓመቱ ውስጥ ከየትኛውም ጊዜ የበለጠ ብሩህ ይሆናል እናም ሌሊቱን ሙሉ ይታያል። ክቡራን የከዋክብት ተመልካቾችና አድናቂዎች ማርስን ለማየት እና ፎቶግራፍ ለማንሣት ይህ በጣም ጥሩው ጊዜ ነው። መካከለኛ መጠን ያለው ቴሌስኮፕ ካላችሁ በፕላኔቱ ብርቱካንማ ገጽ ላይ አንዳንድ ጥቁር ዝርዝሮችን እንድታዩ ያስችላችኋልና ምሽታችሁን ተጠቀሙበት።
👉 በቴሌስኮፕ ከኾነ በዐይን ባይተዩም ፕላኔት ዩራነስ በጁፒተር አቅራቢያ ሲኾን ኔፕቲዩን ደግሞ ወደ ቬኑስ እና ሳተርን ቅርብ በመሆን አስደናቂ ሰልፍን ይሠራሉ።
👉 ፕላኔቶች ሁል ጊዜ በሰማይ ማየት የተለመደ ነው። ብዙም ያልተለመደው ግን ስድስት ብሩህ ፕላኔቶችን በአንድ ጊዜ ማየት ነው። ይህም በየዓመቱ የማይከሰት መኾኑ ነው። በሳይንስ "አሰላለፍ" (alignment) ይባላል።
👉 በተለይ ጥር 9 እና 10 (January 17 - 18) የፕላኔት ዝሁራ ወይም ቪነስ እና የፕላኔት ዙሀል ወይም ሳተርን ግጥጥሞሽ በሰማይ ላይ (በ2 ዲግሪ አካባቢ) ማለት ምድር ላይ ኾነን ስንመለከት በኹለት የጣት ስፋቶች ርቀት ተቀራርበው ለዐይይ ይታዩናል እንደማለት ነው።
👉 ከሳይንስ ዕይታ በተጨማሪ የፕላኔት ሰልፍ እጅግ ብዙ መንፈሳዊ ዝርዝር ፍቺዎችን የያዘ ሲኾን በዐጭሩ ለመግለጽ የጠፈር ስምምነትን፣ ዐዲስ ጅምርን እና መንፈሳዊ መነቃቃትን፣ የሰማያዊ ሥርዐት ፍጹምነትን፣ የሥጋ የነፍስ የመንፈስ ጽምረታዊ ሰልፍን፣ ያንጸባርቃል። በተለይ መንገዳችንን አጽናፈ ዓለምን ወደፈጠረ ወደ የብርሃን አምላክ ወደ እግዚአብሔር እንድናደርግ ምልክት ይኾናሉ። በተለይ እያንዳንዱ ፕላኔት ያላቸው ፍቺ እጅግ በርካታ በመኾኑ በዚህ ውሱን ጽሑፍ ላይ መግለጽ አይቻልም።
በዚህ ላይ ያለውን ሰፊ መንፈሳዊ ምሳሌ ከፈለጋችሁ "ማዛሮት" የሚለውን መጽሐፌን ሳይንሳዊ ትርጉም ከፈለጋችሁ "አንድሮሜዳ 1 እና 2 መጻሕፍትን አንብቡ።
👉 እኔም በነዚሁ ቀናት ከወዳጆቼ ጋር በመኾን የሰማይ ምልከታ በማድረግ ምሽታችንን ተፈጥሮን በማድነቅ የፈጠራቸውን አምላክ በማመስገን የምናመሸ ሲሆን ለዐዳዲስ የሰማይ ተመልካቾች በቴሌስኮፕ የጁፒተርን 4 ጨረቃዎች፣ የሳተርንን ቀለበትን በማሳየት ያላቸውን ሳይንሳዊና መንፈሳዊ ጉዳዮችን ለሚመጡ ተመልካቾች በማስረዳት ምርጥ ምሽቶች ይኾኑልናል።
✍️ መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
👉 በመላው ዓለም የምትገኙ የከዋክብት ተመልካቾች በጥር ወር በ2017 ዓ.ም. የ6 ፕላኔቶች፦
በኢትዮጵያዊ ሥነ ፈለክ አጠራር
👉 መሪህ፣ መሽተሪ፣ ዝሁራ፣ ሳተርን ወይም በውጪው አጠራር ማርስ፣ ጁፒተር፣ ቪነስ፣ ሳተርን፣ ዩራነስ፣ ኔፕቱን
ድንቅ ሰልፍን በሰማይ ላይ የምታዩበት ምርጥ ምሽት መጣ።
👉 ያለምንም መሣሪያ በቀላሉ በዐይን ማየት የምንችለው ማርስ፣ ጁፒተር፣ ቬኑስ እና ሳተርን ናቸው።
👉 ዩራኑስ እና ኔፕቱን ለመመልከት ግን ቴሌስኮፕ ያስፈልገናል።
💥 በመኾኑም ፀሓይ ከጠለቀች በኋላ ወደ ደቡብ ምዕራብ አድማስ ስንመለከት ፕላኔት ቬኑስ እና ሳተርን ተቀራርበው ሲታዩ ያለምንም መሣሪያ በዐይን ብቻ ማየት ትችላላችሁ። ከሁለቱም ብሩህ የሆነችው ደግሞ ኮከበ ምዕራብ ወይም በአቡሻሕር አጠራር አስታርቦ ሸሽ ቬነስ ስትኾን በብርሃን አነስ ብሎ የሚታየን ሳተርን ነው።
👉 በሰማይ ላይ ከፍ ብለን በዐይናችን ስንመለከት ከቬኑስ ቀጥሎ በምሽት ሰማይ ላይ ሁለተኛው ደማቅ ብርሃን በኢትዮጵያዊ የሥነ ፈለክ አጠራር መሽተሪ ወይም ፕላኔት ጁፒተር በሠውር (ታውረስ) መናዝል በቀንዶቹ መኻከል በቀዩ የሠውር ዐይን በአልዴባራን ትይዩ ደምቆ በዐይን ይታያል።
👉 በምሥራቃዊው አድማስ አቅራቢያ ደግሞ ቀዩ ፕላኔት በኢትዮጵያ የሥነ ፈለክ ሥያሜ "መሪህ" ወይም ፕላኔት ማርስ በቀይ ቀለም በድምቀት አብርቶ ለሁሉም በዐይን ይታያል።
💥 በተለይ ኀሙስ ጥር 8 (January 16) ቀይ ፕላኔቱ ወደ ምድር በጣም ቅርብ በሆነ አቀራረብ ላይ ስለሚኾን መልክአ ማርስ በፀሐይ ሙሉ በሙሉ ያበራል። በዓመቱ ውስጥ ከየትኛውም ጊዜ የበለጠ ብሩህ ይሆናል እናም ሌሊቱን ሙሉ ይታያል። ክቡራን የከዋክብት ተመልካቾችና አድናቂዎች ማርስን ለማየት እና ፎቶግራፍ ለማንሣት ይህ በጣም ጥሩው ጊዜ ነው። መካከለኛ መጠን ያለው ቴሌስኮፕ ካላችሁ በፕላኔቱ ብርቱካንማ ገጽ ላይ አንዳንድ ጥቁር ዝርዝሮችን እንድታዩ ያስችላችኋልና ምሽታችሁን ተጠቀሙበት።
👉 በቴሌስኮፕ ከኾነ በዐይን ባይተዩም ፕላኔት ዩራነስ በጁፒተር አቅራቢያ ሲኾን ኔፕቲዩን ደግሞ ወደ ቬኑስ እና ሳተርን ቅርብ በመሆን አስደናቂ ሰልፍን ይሠራሉ።
👉 ፕላኔቶች ሁል ጊዜ በሰማይ ማየት የተለመደ ነው። ብዙም ያልተለመደው ግን ስድስት ብሩህ ፕላኔቶችን በአንድ ጊዜ ማየት ነው። ይህም በየዓመቱ የማይከሰት መኾኑ ነው። በሳይንስ "አሰላለፍ" (alignment) ይባላል።
👉 በተለይ ጥር 9 እና 10 (January 17 - 18) የፕላኔት ዝሁራ ወይም ቪነስ እና የፕላኔት ዙሀል ወይም ሳተርን ግጥጥሞሽ በሰማይ ላይ (በ2 ዲግሪ አካባቢ) ማለት ምድር ላይ ኾነን ስንመለከት በኹለት የጣት ስፋቶች ርቀት ተቀራርበው ለዐይይ ይታዩናል እንደማለት ነው።
👉 ከሳይንስ ዕይታ በተጨማሪ የፕላኔት ሰልፍ እጅግ ብዙ መንፈሳዊ ዝርዝር ፍቺዎችን የያዘ ሲኾን በዐጭሩ ለመግለጽ የጠፈር ስምምነትን፣ ዐዲስ ጅምርን እና መንፈሳዊ መነቃቃትን፣ የሰማያዊ ሥርዐት ፍጹምነትን፣ የሥጋ የነፍስ የመንፈስ ጽምረታዊ ሰልፍን፣ ያንጸባርቃል። በተለይ መንገዳችንን አጽናፈ ዓለምን ወደፈጠረ ወደ የብርሃን አምላክ ወደ እግዚአብሔር እንድናደርግ ምልክት ይኾናሉ። በተለይ እያንዳንዱ ፕላኔት ያላቸው ፍቺ እጅግ በርካታ በመኾኑ በዚህ ውሱን ጽሑፍ ላይ መግለጽ አይቻልም።
በዚህ ላይ ያለውን ሰፊ መንፈሳዊ ምሳሌ ከፈለጋችሁ "ማዛሮት" የሚለውን መጽሐፌን ሳይንሳዊ ትርጉም ከፈለጋችሁ "አንድሮሜዳ 1 እና 2 መጻሕፍትን አንብቡ።
👉 እኔም በነዚሁ ቀናት ከወዳጆቼ ጋር በመኾን የሰማይ ምልከታ በማድረግ ምሽታችንን ተፈጥሮን በማድነቅ የፈጠራቸውን አምላክ በማመስገን የምናመሸ ሲሆን ለዐዳዲስ የሰማይ ተመልካቾች በቴሌስኮፕ የጁፒተርን 4 ጨረቃዎች፣ የሳተርንን ቀለበትን በማሳየት ያላቸውን ሳይንሳዊና መንፈሳዊ ጉዳዮችን ለሚመጡ ተመልካቾች በማስረዳት ምርጥ ምሽቶች ይኾኑልናል።
✍️ መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 Ethiopia’s Epiphany
✍️ Dr Rodas Tadese
💥 A Sacred Celebration of Baptism In the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, the Feast of Epiphany, known as Timkat, stands as a glorious celebration of Christ’s baptism, marking the moment when the Holy Trinity Spirit — was revealed in perfect unity.
👉 The celebrations begin on the eve of Epiphany, an evening that overflows with hymns, praises and anticipation. The Church opens with a hymn that sets the tone for the holy night:
✍️ "The Pilot of the righteous’ soul, the Hope of the hopeless, Jesus Christ has been revealed to the world; born of the Virgin, He grew in obedience to His family; He became fully man and was baptized in the River Jordan."
👉 This chant and many others, echo through the Church, recounting Christ’s journey from heaven to earth, His humble birth and His revelation as the Son of God at His baptism. These hymns, filled with the language of mystery and wonder, prepare the faithful for the full glory of Epiphany. As evening deepens, the Church embarks on a powerful reenactment that mirrors Christ’s journey from Galilee to the Jordan.
👉 The Ark of the Covenant (Tabot) — a consecrated replica of the tablets of stone representing God’s covenant with humanity — is brought out from each parish church. The Ark, symbolizing the presence of God, is adorned with vibrant, sacred cloths and carefully carried to a nearby body of water.
👉 The clergies, with candles and incense, form a solemn procession, chanting and singing with reverence as they accompany the Ark. Spiritual songs fill the air, proclaiming:
✍️ "The Son of God, who descended from heaven, entered the waters of baptism with joy and peace."
👉 This procession, symbolizing Jesus’ humble journey to be baptized, is a moving image of devotion and faith. Multitudes gather along the path, their voices rising in ancient hymns and the Ark is surrounded by priests and deacons, draped in robes of white and gold, symbolizing the purity and majesty of Christ. As night falls, the clergy and faithful keep a sacred vigil, filling the hours with prayers, hymns and scripture readings that immerse the congregation in the profound mystery of Christ’s baptism.
👉 The Church honors this moment with reverent praises, proclaiming:
✍️ "Christ was born; Christ was baptized; He has given us new birth through water and the Holy Spirit. Truly and firmly believed is the revelation of Christ, the Sun of Righteousness; glorious indeed is the splendor of His baptism."
👉 The Church vibrates with devotion as ancient hymns are sung, including melodies by St. Yared, the great Ethiopian hymnologist, whose compositions elevate the spirit and remind the faithful of the timeless nature of Christ’s love. It is a night where heaven and earth seem to meet and the faithful feel united with their Savior in His act of humble obedience. At midnight, the Church reaches the pinnacle of its celebration with the Eucharistic Liturgy.
👉 As the Liturgy begins, a profound silence and awe descend over the faithful. They gather, their hearts prepared by fasting, prayer and reflection, to receive the Body and Blood of Christ. The Eucharist is a personal encounter with the One who was
baptized to sanctify the waters of the world and in this moment, the faithful experience His presence within them.
✍️ Dr Rodas Tadese
💥 A Sacred Celebration of Baptism In the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, the Feast of Epiphany, known as Timkat, stands as a glorious celebration of Christ’s baptism, marking the moment when the Holy Trinity Spirit — was revealed in perfect unity.
👉 The celebrations begin on the eve of Epiphany, an evening that overflows with hymns, praises and anticipation. The Church opens with a hymn that sets the tone for the holy night:
✍️ "The Pilot of the righteous’ soul, the Hope of the hopeless, Jesus Christ has been revealed to the world; born of the Virgin, He grew in obedience to His family; He became fully man and was baptized in the River Jordan."
👉 This chant and many others, echo through the Church, recounting Christ’s journey from heaven to earth, His humble birth and His revelation as the Son of God at His baptism. These hymns, filled with the language of mystery and wonder, prepare the faithful for the full glory of Epiphany. As evening deepens, the Church embarks on a powerful reenactment that mirrors Christ’s journey from Galilee to the Jordan.
👉 The Ark of the Covenant (Tabot) — a consecrated replica of the tablets of stone representing God’s covenant with humanity — is brought out from each parish church. The Ark, symbolizing the presence of God, is adorned with vibrant, sacred cloths and carefully carried to a nearby body of water.
👉 The clergies, with candles and incense, form a solemn procession, chanting and singing with reverence as they accompany the Ark. Spiritual songs fill the air, proclaiming:
✍️ "The Son of God, who descended from heaven, entered the waters of baptism with joy and peace."
👉 This procession, symbolizing Jesus’ humble journey to be baptized, is a moving image of devotion and faith. Multitudes gather along the path, their voices rising in ancient hymns and the Ark is surrounded by priests and deacons, draped in robes of white and gold, symbolizing the purity and majesty of Christ. As night falls, the clergy and faithful keep a sacred vigil, filling the hours with prayers, hymns and scripture readings that immerse the congregation in the profound mystery of Christ’s baptism.
👉 The Church honors this moment with reverent praises, proclaiming:
✍️ "Christ was born; Christ was baptized; He has given us new birth through water and the Holy Spirit. Truly and firmly believed is the revelation of Christ, the Sun of Righteousness; glorious indeed is the splendor of His baptism."
👉 The Church vibrates with devotion as ancient hymns are sung, including melodies by St. Yared, the great Ethiopian hymnologist, whose compositions elevate the spirit and remind the faithful of the timeless nature of Christ’s love. It is a night where heaven and earth seem to meet and the faithful feel united with their Savior in His act of humble obedience. At midnight, the Church reaches the pinnacle of its celebration with the Eucharistic Liturgy.
👉 As the Liturgy begins, a profound silence and awe descend over the faithful. They gather, their hearts prepared by fasting, prayer and reflection, to receive the Body and Blood of Christ. The Eucharist is a personal encounter with the One who was
baptized to sanctify the waters of the world and in this moment, the faithful experience His presence within them.
👉 This sacred communion draws the faithful into the mystery of Epiphany, where each heart becomes a living witness to the truth that God Himself descended into the waters of creation to bring salvation to all. At dawn, the celebration continues with readings from the four Gospels, each recounting aspects of Christ’s life and His divine mission.
👉 The Church conducts the sprinkling of holy water, a symbol of the baptismal waters of the Jordan and as this holy water touches each person, they are reminded of their own rebirth in Christ, their hearts renewed in the grace of baptism. Throughout the morning, the Church praises Christ with jubilant hymns. Scholarly singers, chanting with profound skill, proclaim:
✍️ "He came down from heaven; born of Mary; baptized in the Jordan at the age of 30. The Lord, foretold by the prophets, was revealed openly to the world."
The Church then joyfully sings:
✍️ "Today, a great joy fills the earth because of the birth and baptism of Christ. Hallelujah, Hallelujah, Hallelujah! He left the ninetynine hosts of angels, and rose again in peace." descended into the waters These chants, filled with reverence and awe, resonate through the Church, as the faithful are reminded of Christ’s humility and His profound act of love for humanity. As the celebrations conclude, the Ark of the Covenant is brought back to the Church in a procession as reverent and joyful as when it first began.
👉 This return journey symbolizes Christ’s departure into the wilderness after His baptism, where He fasted, prayed and prepared for His ministry on earth. It is a solemn reminder that, just as Christ withdrew to the wilderness so too are the faithful called to a life of prayer, fasting and spiritual preparation. Through this feast, the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church brings the life and teachings of Jesus into vivid, living color. The entire event becomes a powerful and moving Christological sermon, not just spoken but lived and experienced.
👉 The faithful are not mere spectators; they are drawn into the mystery, embodying the journey of Christ and embracing His presence in every moment. In celebrating Epiphany, the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church reaffirms that Christ is the Light, the Savior and the Redeemer who came to sanctify the waters, reveal the Trinity and invite humanity into the mystery of the divine.
👉 Through each hymn, procession and ritual, the Church reminds the faithful of the profound truth that Jesus is one Nature of God, the Incarnate Logos, humbling Himself to be baptized for the sake of all. This feast, with its rich symbols, sacred songs and the unity of the faithful, stands as a testament to the Church’s dedication to Christ. It is a call to each believer to journey with Him, to be renewed in spirit and to celebrate the mystery of salvation with hearts full of love, devotion and awe.
Source The Sun of Righteousness
Page 201 - 204
Order your book on Amazon
https://a.co/d/himSUfb
👉 The Church conducts the sprinkling of holy water, a symbol of the baptismal waters of the Jordan and as this holy water touches each person, they are reminded of their own rebirth in Christ, their hearts renewed in the grace of baptism. Throughout the morning, the Church praises Christ with jubilant hymns. Scholarly singers, chanting with profound skill, proclaim:
✍️ "He came down from heaven; born of Mary; baptized in the Jordan at the age of 30. The Lord, foretold by the prophets, was revealed openly to the world."
The Church then joyfully sings:
✍️ "Today, a great joy fills the earth because of the birth and baptism of Christ. Hallelujah, Hallelujah, Hallelujah! He left the ninetynine hosts of angels, and rose again in peace." descended into the waters These chants, filled with reverence and awe, resonate through the Church, as the faithful are reminded of Christ’s humility and His profound act of love for humanity. As the celebrations conclude, the Ark of the Covenant is brought back to the Church in a procession as reverent and joyful as when it first began.
👉 This return journey symbolizes Christ’s departure into the wilderness after His baptism, where He fasted, prayed and prepared for His ministry on earth. It is a solemn reminder that, just as Christ withdrew to the wilderness so too are the faithful called to a life of prayer, fasting and spiritual preparation. Through this feast, the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church brings the life and teachings of Jesus into vivid, living color. The entire event becomes a powerful and moving Christological sermon, not just spoken but lived and experienced.
👉 The faithful are not mere spectators; they are drawn into the mystery, embodying the journey of Christ and embracing His presence in every moment. In celebrating Epiphany, the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church reaffirms that Christ is the Light, the Savior and the Redeemer who came to sanctify the waters, reveal the Trinity and invite humanity into the mystery of the divine.
👉 Through each hymn, procession and ritual, the Church reminds the faithful of the profound truth that Jesus is one Nature of God, the Incarnate Logos, humbling Himself to be baptized for the sake of all. This feast, with its rich symbols, sacred songs and the unity of the faithful, stands as a testament to the Church’s dedication to Christ. It is a call to each believer to journey with Him, to be renewed in spirit and to celebrate the mystery of salvation with hearts full of love, devotion and awe.
Source The Sun of Righteousness
Page 201 - 204
Order your book on Amazon
https://a.co/d/himSUfb
[እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ]
✍ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (በድጋሚ ፓስት የተደረገ)
💥 ጥምቀት ማለት ቃሉ የግእዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙም “መነከር፣ መዘፈቅ፣ ውሃ ውስጥ ገብቶ መውጣት” ማለት ነው፡፡
💥 ምስጢረ ጥምቀትን የመሠረተልን ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ሲመሠርትም በማዘዝ ብቻ ሳይሆን በሥራ በማሳየት ጭምር ነው (ማቴ 3፡17፤ ማር 1፡9፤ ሉቃ 3፡21፤ ዮሐ 1፡31)፡፡
💥 ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እከብር አይል ክቡር የባሕርይ አምላክ ሆኖ ሳለ በዮርዳኖስ ወንዝ በአገልጋዩ (በፍጡሩ) በዮሐንስ የተጠመቀበት ምክንያት፦
1) አንድነቱን ሦስትነቱን ለመግለጽ
2) የዕዳ ደብዳቤያችንን ለመደምሰስ (ቆላ 2:14)
3) በእርሱ ጥምቀት የእኛን ጥምቀት ለመቀደስ
4)ለጥምቀታችን ኀይልን ለመስጠት
5) ለአብነት ርሱ ተጠምቆ እናንተም ተጠመቁ ብሎ አርአያና ምሳሌ ለመሆን ከቅድስት ድንግል ማርያም በተወለደ በ30 ዘመኑ ጥር 11 ከሌሊቱ በ10ኛው ሰዓት፤ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ፡፡
💥 ጌታችን በዮርዳኖስ እንደሚጠመቅና የዮርዳኖስ ወንዝ ጌታን ስታይ እንደምትሸሽ ነቢዩ ዳዊት በመዝ 113፡3-5፦
✍️ “ባሕር አየች ሸሸችም፥ ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ፤ ተራሮች እንደ ኮርማዎች፥ ኮረብቶችም እንደ ጠቦቶች ዘለሉ፤ አንቺ ባሕር የሸሸሽ፥ አንቺም ዮርዳኖስ ወደ ኋላሽ የተመለስሽ ምን ሆናችኋል?” በማለት ከ1000 ዓመት አስቀድሞ ትንቢት የተናገረ ሲሆን፤ ብዙ ምሳሌም አለውና ከትርጓሜ ወንጌል ይመልከቱ፨
💥 ዮሐንስ ወደ ጌታችን መምጣት ሲገባው ጌታችን ወደ ዮሐንስ የሄደበት ምክንያት የመጀመሪያው ትሕትናን ለማስተማር ነው።
✍️ ሁለተኛው ለአብነት ለምሳሌ ነው፤ ይኸውም ዮሐንስ ሄዶ አጥምቆት ቢሆን ዛሬ ባለሥልጣናቱ ካህናትን ቤታችን ድረስ መጥታችሁ አጥምቁን ይሏቸው ነበርና ሰማያዊ ንጉሥ እኔ ከሄድኩ እናንተም ሄዳችሁ ቤተ ክርስቲያን ተጠመቁ ለማለት ሄዷል።
💥 ዮሐንስ ግን ወደርሱ በትሕትና የመጣው አምላኩ ክርስቶስ መሆኑን ተረድቶ “እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን?” ሲል ጌታችንም “ጽድቅን ልንፈጽም” ይገባናል ብሎ ትንቢተ ነቢያትን ሊፈጽም እንደመጣ ሲነግረው ዮሐንስ እሺ አለ።
💥 ከዚያም ተያይዘው ወደ ዮርዳኖስ ሲወርዱ የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት እንደሚያስተምሩት የዮርዳኖስ ወንዝ ወደ ኋላዋ ሸሽታለች በዚህም ዳዊት በመዝ 77፡16 ላይ፦
✍️ “አቤቱ፥ ውሆች አዩህ ውሆችም አይተውህ ፈሩ ጥልቆች ተነዋወጡ፥ ውሆችም ጮኹ” ብሎ የተናገረው ትንቢት ተፈጸመ።
💥 ጌታችንም ተጠምቆ ከውሃው ከወጣ በኋላ ሰማይ ተከፈተ ይላል። መተርጉሙ ሲያመሰጥረው፦
1) "ከመ ተጠምቀ ሰማያዊ ናሁ ወረደ እምሰማይ ወሀለዎ ከመ ይዕርግ ውስተ ሰማይ" (ሰማያዊው እንደተጠመቀ ከሰማይ እንደወረደ ወደሰማይ እንደሚያርግ ለማስረዳት)
2) "ወዳግም እስመ አናቅጸ ሰማያት ተዐጽዉ በምክንያተ ዕልወተ አዳም ..." (በአዳምና በሰዎች በደል ምክንያት የሰማያት ደጆች ተዘግተው ነበር። ገነትም ተዘግታ በእሳት ጦር ትጠበቅ ነበር። ጌታችን በተጠመቀ ጊዜ በጥምቀቱ ምክንያት የሰማይ ደጃፎች ተከፈቱ)።
3) "ሣልስ ያጠይቀነ ከመ እለ ይጠመቁ ይትረኃው ሎሙ አናቅጸ ሰማያት ..." (ለሚጠመቁ ሰዎች የሰማያት ደጃፎች እንደሚከፈቱላቸውና ከሞት ከተነሡ በኋላ ወደ ሰማይ እንደሚወጡ ያስረዳል)።
4) ሰማያት ተከፈቱ መባሉ ደጃፍ በተከፈተ ጊዜ በውስጥ ያለው ዐዲስ ነገር እንዲገለጥ በጥምቀትም ዐዲስ ምስጢር ይገለጣልና ነው።
💥 አብ በሰማይ ኹኖ “ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር ዘቦቱ ሠመርኩ” (በርሱ ደስ የሚለኝ የምወድደው ልጄ ይኽ ነው) ብሎ ሲመሰክር፤ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ በራሱ ላይ ተቀመጠ፤ አካላዊ ቃል ክርስቶስም በጽንፈ ዮርዳኖስ ቁሞ ታየ፡፡
💥 መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ለምን ወረደ? ቢባል
✍️ ርግብ ኀዳጊተ በቀል (በቀልን የምትተው) ናት፤ መንፈስ ቅዱስም ኀዳጌ በቀል፤ ቸር ነኝ ሲል፡፡
✍️ ርግብ ልጆቿን ተከባክባ እንድታሳድግ፤ መንፈስ ቅዱስም ለምእመናን ልሕቀት መንፈሳዊ እሰጣለኊ ሲል፡፡
✍️ ርግብ በኖኅ ጊዜ የጥፋት ውሃ መጒደሉን የወይራ ቅርንጫፍ ይዛ ብሥራተ ፍሥሐ የምሥራችን እንደገለጸች፤ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል በመውረድ ከርሱ ጋር የሥልጣን አንድነት ባለው በወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ራስ ላይ በመቀመጥ የፍዳ ዘመን ማክተሙን ተስፋ መስቀልን አብሥሯል፡፡
✍️ ርግብ ክንፏን ቢመቷት፤ ዕንቊላሏን ቢሠብሩባትም ቤቷን ካላፈረሱባት በቀር አትኼድም፤ መንፈስ ቅዱስም ምንም ኀጢአትን ቢሠራም፤ ጨርሰው ካልካዱት በስተቀር አይለይምና፡፡
💥 ይኸውም በምስጢረ ሥላሴ ትምህርት እንደምንረዳው ከሰማይ ኾኖ የመሰከረው የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ በቃልነት መንፈስ ቅዱስ በእስትንፋስነት ያሉበት (ሕልው የኾኑበት) አብ ነው።
✍️ ወርዶ በወልድ ራስ የተቀመጠው አብ በልቡናነት አካላዊ ቃል ክርስቶስ በቃልነት ሕልው የኾኑበት መንፈስ ቅዱስ ነው።
✍️ በጽንፈ ዮርዳኖስ ቆሞ የታየው አብ በልቡናነት መንፈስ ቅዱስ በእስትንፋስነት ሕልው የኾኑበት አካላዊ ቃል ክርስቶስ ነው፤ እንዲኽ አድርገው የአካል ሦስትነታቸውን የፈቃድ አንድነታቸውን ለማስረዳት አብ በደመና ኾኖ መሰከረ፤ መንፈስ ቅዱስ በአምሳለ ርግብ ወርዶ ታየ፤ አካላዊ ቃል ክርስቶስ በጽንፈ ዮርዳኖስ ቆሞ ታየ።
♥ በዚኽም የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት በሚገባ ሲታወቅ በተጨማሪም “በርሱ ደስ የሚለኝ የምወድደው ልጄ ይኽ ነው” ብሎ እግዚአብሔር አብ በመመስከሩ ቅድመ ዓለም ከአብ ያለ እናት የተወለደው በኋለኛው ዘመን ከእመቤታችን ያለ አባት በኅቱም ድንግልና የተወለደው እግዚአብሔር ወልድ ተቀዳሚና ተከታይ የሌለው አንድ ብቻ መኾኑ በሚገባ ተረጋግጧል፤ ዕለቱም በጽርዕ ቋንቋ ኤጲፋንያ ሲባል በግእዝ አስተርእዮ በዐማርኛም የመታየት የመገለጥ ጊዜ ተብሏል፡፡
♥ ኢትዮጵያ ሀገራችን ስለ ነገረ ጥምቀት የሰማችው ከሌላው ዓለም አስቀድማ ጌታችን ባረገ በጥቂት ወራት (በ34 ዓ.ም) በኢትዮጵያው ጀንደረባ አማካይነት ነው (የሐዋ 8፥26-39)፤ ይህም በዐል ከዘጠኙ ዐበይት በዐላት አንደኛው ሲሆን ጌታችን ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ ስላመራ ይህንን ለማሰብ ታቦታቱ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ ያመራሉ።
♥ በዚህ መልኩ መከበር እንዴት ተጀመረ? የሚለውን ሊቀ ትጉኃን ኃይለ ጊዮርጊስ በጻፉት የነገረ ሃይማኖት መጽሐፍ ላይ የጻፉትን ለአንባብያን ለማካፈል ወደድኩ። ይኸውም ከ515-529 ዓ.ም ለ14 ዓመት ኢትዮጵያን በመሩት በአጼ ገብረ መስቀል ዘመን ሲሆን በጊዜው ቅዱስ ያሬድ የነበረበት ጊዜ በመሆኑ ከዝማሬው በመነሣት ታቦታቱ ጥር 11 ጠዋት ከመንበረ ክብራቸው ተነሥተው ወደ ባሕረ ጥምቀቱ አምርተው አመሻሹ ላይ ይመለሱ ነበር ብለዋል፡፡
♥ ጸሐፊው በመቀጠል ሲያብራሩ ከዚያም ከ1157-1197 ዓ.ም ድረስ ለ40 ዓመት ኢትዮጵያን በመራው በታላቱ ጻድቅ ንጉሥ በላሊበላ ዘመን በአንድ አካባቢ ያሉ አብያተ ክርስትያናት ታቦታቱ ባንድ ላይ እንዲያከብሩ ንጉሥ ላሊበላ ታላቅ መንፈሳዊ ዐዋጅን አሳውጆ በአንድ አካባቢ፣ ወረዳ፣ ያሉ በአንድ ላይ ማክበር ጀመሩ፤ በርሱ ዘመን የነበሩት ታላቁ ጻድቅ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በአክሱም፣ በጎንደር፣ በሸዋ፣ በአንኮበር፣ በመርጡለ ማርያም እየሄዱ ባሕረ ጥምቀቱን እንደባረኩ ይጽፋሉ፡፡
✍ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (በድጋሚ ፓስት የተደረገ)
💥 ጥምቀት ማለት ቃሉ የግእዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙም “መነከር፣ መዘፈቅ፣ ውሃ ውስጥ ገብቶ መውጣት” ማለት ነው፡፡
💥 ምስጢረ ጥምቀትን የመሠረተልን ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን ሲመሠርትም በማዘዝ ብቻ ሳይሆን በሥራ በማሳየት ጭምር ነው (ማቴ 3፡17፤ ማር 1፡9፤ ሉቃ 3፡21፤ ዮሐ 1፡31)፡፡
💥 ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እከብር አይል ክቡር የባሕርይ አምላክ ሆኖ ሳለ በዮርዳኖስ ወንዝ በአገልጋዩ (በፍጡሩ) በዮሐንስ የተጠመቀበት ምክንያት፦
1) አንድነቱን ሦስትነቱን ለመግለጽ
2) የዕዳ ደብዳቤያችንን ለመደምሰስ (ቆላ 2:14)
3) በእርሱ ጥምቀት የእኛን ጥምቀት ለመቀደስ
4)ለጥምቀታችን ኀይልን ለመስጠት
5) ለአብነት ርሱ ተጠምቆ እናንተም ተጠመቁ ብሎ አርአያና ምሳሌ ለመሆን ከቅድስት ድንግል ማርያም በተወለደ በ30 ዘመኑ ጥር 11 ከሌሊቱ በ10ኛው ሰዓት፤ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ፡፡
💥 ጌታችን በዮርዳኖስ እንደሚጠመቅና የዮርዳኖስ ወንዝ ጌታን ስታይ እንደምትሸሽ ነቢዩ ዳዊት በመዝ 113፡3-5፦
✍️ “ባሕር አየች ሸሸችም፥ ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ፤ ተራሮች እንደ ኮርማዎች፥ ኮረብቶችም እንደ ጠቦቶች ዘለሉ፤ አንቺ ባሕር የሸሸሽ፥ አንቺም ዮርዳኖስ ወደ ኋላሽ የተመለስሽ ምን ሆናችኋል?” በማለት ከ1000 ዓመት አስቀድሞ ትንቢት የተናገረ ሲሆን፤ ብዙ ምሳሌም አለውና ከትርጓሜ ወንጌል ይመልከቱ፨
💥 ዮሐንስ ወደ ጌታችን መምጣት ሲገባው ጌታችን ወደ ዮሐንስ የሄደበት ምክንያት የመጀመሪያው ትሕትናን ለማስተማር ነው።
✍️ ሁለተኛው ለአብነት ለምሳሌ ነው፤ ይኸውም ዮሐንስ ሄዶ አጥምቆት ቢሆን ዛሬ ባለሥልጣናቱ ካህናትን ቤታችን ድረስ መጥታችሁ አጥምቁን ይሏቸው ነበርና ሰማያዊ ንጉሥ እኔ ከሄድኩ እናንተም ሄዳችሁ ቤተ ክርስቲያን ተጠመቁ ለማለት ሄዷል።
💥 ዮሐንስ ግን ወደርሱ በትሕትና የመጣው አምላኩ ክርስቶስ መሆኑን ተረድቶ “እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን?” ሲል ጌታችንም “ጽድቅን ልንፈጽም” ይገባናል ብሎ ትንቢተ ነቢያትን ሊፈጽም እንደመጣ ሲነግረው ዮሐንስ እሺ አለ።
💥 ከዚያም ተያይዘው ወደ ዮርዳኖስ ሲወርዱ የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት እንደሚያስተምሩት የዮርዳኖስ ወንዝ ወደ ኋላዋ ሸሽታለች በዚህም ዳዊት በመዝ 77፡16 ላይ፦
✍️ “አቤቱ፥ ውሆች አዩህ ውሆችም አይተውህ ፈሩ ጥልቆች ተነዋወጡ፥ ውሆችም ጮኹ” ብሎ የተናገረው ትንቢት ተፈጸመ።
💥 ጌታችንም ተጠምቆ ከውሃው ከወጣ በኋላ ሰማይ ተከፈተ ይላል። መተርጉሙ ሲያመሰጥረው፦
1) "ከመ ተጠምቀ ሰማያዊ ናሁ ወረደ እምሰማይ ወሀለዎ ከመ ይዕርግ ውስተ ሰማይ" (ሰማያዊው እንደተጠመቀ ከሰማይ እንደወረደ ወደሰማይ እንደሚያርግ ለማስረዳት)
2) "ወዳግም እስመ አናቅጸ ሰማያት ተዐጽዉ በምክንያተ ዕልወተ አዳም ..." (በአዳምና በሰዎች በደል ምክንያት የሰማያት ደጆች ተዘግተው ነበር። ገነትም ተዘግታ በእሳት ጦር ትጠበቅ ነበር። ጌታችን በተጠመቀ ጊዜ በጥምቀቱ ምክንያት የሰማይ ደጃፎች ተከፈቱ)።
3) "ሣልስ ያጠይቀነ ከመ እለ ይጠመቁ ይትረኃው ሎሙ አናቅጸ ሰማያት ..." (ለሚጠመቁ ሰዎች የሰማያት ደጃፎች እንደሚከፈቱላቸውና ከሞት ከተነሡ በኋላ ወደ ሰማይ እንደሚወጡ ያስረዳል)።
4) ሰማያት ተከፈቱ መባሉ ደጃፍ በተከፈተ ጊዜ በውስጥ ያለው ዐዲስ ነገር እንዲገለጥ በጥምቀትም ዐዲስ ምስጢር ይገለጣልና ነው።
💥 አብ በሰማይ ኹኖ “ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር ዘቦቱ ሠመርኩ” (በርሱ ደስ የሚለኝ የምወድደው ልጄ ይኽ ነው) ብሎ ሲመሰክር፤ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወርዶ በራሱ ላይ ተቀመጠ፤ አካላዊ ቃል ክርስቶስም በጽንፈ ዮርዳኖስ ቁሞ ታየ፡፡
💥 መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ለምን ወረደ? ቢባል
✍️ ርግብ ኀዳጊተ በቀል (በቀልን የምትተው) ናት፤ መንፈስ ቅዱስም ኀዳጌ በቀል፤ ቸር ነኝ ሲል፡፡
✍️ ርግብ ልጆቿን ተከባክባ እንድታሳድግ፤ መንፈስ ቅዱስም ለምእመናን ልሕቀት መንፈሳዊ እሰጣለኊ ሲል፡፡
✍️ ርግብ በኖኅ ጊዜ የጥፋት ውሃ መጒደሉን የወይራ ቅርንጫፍ ይዛ ብሥራተ ፍሥሐ የምሥራችን እንደገለጸች፤ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል በመውረድ ከርሱ ጋር የሥልጣን አንድነት ባለው በወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ራስ ላይ በመቀመጥ የፍዳ ዘመን ማክተሙን ተስፋ መስቀልን አብሥሯል፡፡
✍️ ርግብ ክንፏን ቢመቷት፤ ዕንቊላሏን ቢሠብሩባትም ቤቷን ካላፈረሱባት በቀር አትኼድም፤ መንፈስ ቅዱስም ምንም ኀጢአትን ቢሠራም፤ ጨርሰው ካልካዱት በስተቀር አይለይምና፡፡
💥 ይኸውም በምስጢረ ሥላሴ ትምህርት እንደምንረዳው ከሰማይ ኾኖ የመሰከረው የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ በቃልነት መንፈስ ቅዱስ በእስትንፋስነት ያሉበት (ሕልው የኾኑበት) አብ ነው።
✍️ ወርዶ በወልድ ራስ የተቀመጠው አብ በልቡናነት አካላዊ ቃል ክርስቶስ በቃልነት ሕልው የኾኑበት መንፈስ ቅዱስ ነው።
✍️ በጽንፈ ዮርዳኖስ ቆሞ የታየው አብ በልቡናነት መንፈስ ቅዱስ በእስትንፋስነት ሕልው የኾኑበት አካላዊ ቃል ክርስቶስ ነው፤ እንዲኽ አድርገው የአካል ሦስትነታቸውን የፈቃድ አንድነታቸውን ለማስረዳት አብ በደመና ኾኖ መሰከረ፤ መንፈስ ቅዱስ በአምሳለ ርግብ ወርዶ ታየ፤ አካላዊ ቃል ክርስቶስ በጽንፈ ዮርዳኖስ ቆሞ ታየ።
♥ በዚኽም የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት በሚገባ ሲታወቅ በተጨማሪም “በርሱ ደስ የሚለኝ የምወድደው ልጄ ይኽ ነው” ብሎ እግዚአብሔር አብ በመመስከሩ ቅድመ ዓለም ከአብ ያለ እናት የተወለደው በኋለኛው ዘመን ከእመቤታችን ያለ አባት በኅቱም ድንግልና የተወለደው እግዚአብሔር ወልድ ተቀዳሚና ተከታይ የሌለው አንድ ብቻ መኾኑ በሚገባ ተረጋግጧል፤ ዕለቱም በጽርዕ ቋንቋ ኤጲፋንያ ሲባል በግእዝ አስተርእዮ በዐማርኛም የመታየት የመገለጥ ጊዜ ተብሏል፡፡
♥ ኢትዮጵያ ሀገራችን ስለ ነገረ ጥምቀት የሰማችው ከሌላው ዓለም አስቀድማ ጌታችን ባረገ በጥቂት ወራት (በ34 ዓ.ም) በኢትዮጵያው ጀንደረባ አማካይነት ነው (የሐዋ 8፥26-39)፤ ይህም በዐል ከዘጠኙ ዐበይት በዐላት አንደኛው ሲሆን ጌታችን ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ ስላመራ ይህንን ለማሰብ ታቦታቱ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ ያመራሉ።
♥ በዚህ መልኩ መከበር እንዴት ተጀመረ? የሚለውን ሊቀ ትጉኃን ኃይለ ጊዮርጊስ በጻፉት የነገረ ሃይማኖት መጽሐፍ ላይ የጻፉትን ለአንባብያን ለማካፈል ወደድኩ። ይኸውም ከ515-529 ዓ.ም ለ14 ዓመት ኢትዮጵያን በመሩት በአጼ ገብረ መስቀል ዘመን ሲሆን በጊዜው ቅዱስ ያሬድ የነበረበት ጊዜ በመሆኑ ከዝማሬው በመነሣት ታቦታቱ ጥር 11 ጠዋት ከመንበረ ክብራቸው ተነሥተው ወደ ባሕረ ጥምቀቱ አምርተው አመሻሹ ላይ ይመለሱ ነበር ብለዋል፡፡
♥ ጸሐፊው በመቀጠል ሲያብራሩ ከዚያም ከ1157-1197 ዓ.ም ድረስ ለ40 ዓመት ኢትዮጵያን በመራው በታላቱ ጻድቅ ንጉሥ በላሊበላ ዘመን በአንድ አካባቢ ያሉ አብያተ ክርስትያናት ታቦታቱ ባንድ ላይ እንዲያከብሩ ንጉሥ ላሊበላ ታላቅ መንፈሳዊ ዐዋጅን አሳውጆ በአንድ አካባቢ፣ ወረዳ፣ ያሉ በአንድ ላይ ማክበር ጀመሩ፤ በርሱ ዘመን የነበሩት ታላቁ ጻድቅ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በአክሱም፣ በጎንደር፣ በሸዋ፣ በአንኮበር፣ በመርጡለ ማርያም እየሄዱ ባሕረ ጥምቀቱን እንደባረኩ ይጽፋሉ፡፡
Telegram
መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ (ዶክተር) Dr Rodas Tadese
ትክክለኛው ቻናሌ ይሄ ብቻ ነው። በዚ ብቻ ትምህርተ ሃይማኖትንና የኢትዮጵያ ምስጢራትን ሳይንሳዊ ጉዳዮችን በጥልቀት እንዳስሳለን። ሌሎቹ ቻናሎች የእኔ አይደሉም
♥ በመቀጠልም ከ1245-1268 ዓ.ም ለ23 ዓመት ኢትዮጵያን በመሩት በዐጼ ይኩኖ አምላክ ዘመነ መንግሥት በጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አሳሳቢነት ታቦታቱ በባሕረ ጥምቀት ሲውሉ ምእመናን በታላቅ ድምቀት እግዚአብሔርን እያመሰገኑ እንዲውሉ መንፈሳዊ ዐዋጅ አሳወጁ በማለት ገልጸዋል፡፡
♥ በመቀጠል ከ1426-1460 ዓ.ም ለ34 ዓመት ኢትዮጵያን በመሩት በታላቁ ንጉሥ በዐጼ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥትም ንጉሡ ከሊቃውንት ጋር በመወያየት የበዐሉን ታሪክ ተከትሎ ታቦታቱ ጥር 10 ከመንበረ ክብራቸው ተነሥተው ወደ ባሕረ ጥምቀት እንዲወርዱና ጥር 11 እንዲመለሱ መወሰኑን ሊቀ ትጉኃን ኀይለ ጊዮርጊስ በመጽሐፋቸው ላይ ይተነትናሉ።
💥 እንደሚታወቀው ታቦተ ጽዮን በሄደችበት ሁሉ በረከትን ትሰጥ እንደነበር የአቢዳራን ቤት በበረከት እንደሞላች፤ የዮርዳኖስን ባህር እንደከፈለች፣ የኢያሪኮን ቅጽር እንዳፈረሰች፣ የፍልስጤማውያን ጣዖት ዳጎንን ቀጥቅጣ እንዳጠፋች ሀገሪቱ ትባረክ ዘንድ ርኲሳን መናፍስት ይርቁ ዘንድ ምድሪቱ በቃል ኪዳኑ ታቦታት ትቀደስ ዘንድ ታቦታቱ በመጡበት መንገድ እንዳይመለሱ ታላቅ ዐዋጅ አሳውጀው በዐዋጁ መሠረት ዛሬ ድረስ በደመቀ መልኩ በዓሉ እየተከበረ ይገኛል ብለው ታሪካዊ ዳራውን ጽፈዋል፡፡
💥 ከባሕር ማዶ ጸሐፍያን ውስጥ ቼሩሊ በዐጼ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን ቁመቱ 14 ወርዱ 8 ክንድ የኾነ ባሕረ ጥምቀት እንደተዘጋጀ ሲጽፍ፤ በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዐጼ ልብነ ድንግል በተገኙበት እጅግ ታላቅ ድንኳን በባሕረ ጥምቀቱ ዙሪያ እንዴት ተተክሎ እንደተከበረ ፍራንቺስኮ አልቫሬዝ ገልጿል፤ በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረውን የበዓለ ጥምቀት አከባበር ደግሞ ፔድሮ ፔየዝ ዘግቦት ነበር።
💥 አሁን ባለንበት ጊዜም ዳዊት በመዝ 44፡16 ላይ “በአባቶችሽ ፋንታ ልጆች ተወለዱልሽ” በማለት እንደተናገረ ከመቼውም በበለጠ እግዚአብሔር የወጣቱን ልብ በረድኤት ጎብኝቶት "አልፋ ወዖ ቤጣ የውጣ ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው ወወልደ ማርያም ሥግው" ተብሎ ሕይወት የሆነው የአምላካችን የኢየሱስ ስም ለተጻፈበት ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ ለሚሠዋበት ለቃል ኪዳኑ ታቦታት ክብር አካባቢውን እያስዋበ፣ ታቦታቱ የሚሄዱበትን መንገድ እየጠረገ፤ ታላላቅ ምንጣፎችን ታቦታቱ በሚሄዱበት መንገድ እያነጠፈ ለቃል ኪዳኑ ታቦት እንደ ነቢዩ ዳዊት ከፍተኛ ክብር በመስጠት እግዚአብሔርን እያገለገለ ይገኛል (1ኛ ነገሥት 6፡1-23)፡፡
“የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን ታቦትና ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ፥ ከሰፈራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት” (ኢያ 3፡3)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
♥ ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ [በድጋሚ ፓስት የተደረገ]
የቴሌግራም ቻናል፦ https://www.tg-me.com/Rodas9
የYoutube Channel:- https://youtube.com/channel/UCFKnpmDyWe3LQ_9Gx3TMnAg
♥ በመቀጠል ከ1426-1460 ዓ.ም ለ34 ዓመት ኢትዮጵያን በመሩት በታላቁ ንጉሥ በዐጼ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመነ መንግሥትም ንጉሡ ከሊቃውንት ጋር በመወያየት የበዐሉን ታሪክ ተከትሎ ታቦታቱ ጥር 10 ከመንበረ ክብራቸው ተነሥተው ወደ ባሕረ ጥምቀት እንዲወርዱና ጥር 11 እንዲመለሱ መወሰኑን ሊቀ ትጉኃን ኀይለ ጊዮርጊስ በመጽሐፋቸው ላይ ይተነትናሉ።
💥 እንደሚታወቀው ታቦተ ጽዮን በሄደችበት ሁሉ በረከትን ትሰጥ እንደነበር የአቢዳራን ቤት በበረከት እንደሞላች፤ የዮርዳኖስን ባህር እንደከፈለች፣ የኢያሪኮን ቅጽር እንዳፈረሰች፣ የፍልስጤማውያን ጣዖት ዳጎንን ቀጥቅጣ እንዳጠፋች ሀገሪቱ ትባረክ ዘንድ ርኲሳን መናፍስት ይርቁ ዘንድ ምድሪቱ በቃል ኪዳኑ ታቦታት ትቀደስ ዘንድ ታቦታቱ በመጡበት መንገድ እንዳይመለሱ ታላቅ ዐዋጅ አሳውጀው በዐዋጁ መሠረት ዛሬ ድረስ በደመቀ መልኩ በዓሉ እየተከበረ ይገኛል ብለው ታሪካዊ ዳራውን ጽፈዋል፡፡
💥 ከባሕር ማዶ ጸሐፍያን ውስጥ ቼሩሊ በዐጼ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን ቁመቱ 14 ወርዱ 8 ክንድ የኾነ ባሕረ ጥምቀት እንደተዘጋጀ ሲጽፍ፤ በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዐጼ ልብነ ድንግል በተገኙበት እጅግ ታላቅ ድንኳን በባሕረ ጥምቀቱ ዙሪያ እንዴት ተተክሎ እንደተከበረ ፍራንቺስኮ አልቫሬዝ ገልጿል፤ በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረውን የበዓለ ጥምቀት አከባበር ደግሞ ፔድሮ ፔየዝ ዘግቦት ነበር።
💥 አሁን ባለንበት ጊዜም ዳዊት በመዝ 44፡16 ላይ “በአባቶችሽ ፋንታ ልጆች ተወለዱልሽ” በማለት እንደተናገረ ከመቼውም በበለጠ እግዚአብሔር የወጣቱን ልብ በረድኤት ጎብኝቶት "አልፋ ወዖ ቤጣ የውጣ ኢየሱስ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው ወወልደ ማርያም ሥግው" ተብሎ ሕይወት የሆነው የአምላካችን የኢየሱስ ስም ለተጻፈበት ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ ለሚሠዋበት ለቃል ኪዳኑ ታቦታት ክብር አካባቢውን እያስዋበ፣ ታቦታቱ የሚሄዱበትን መንገድ እየጠረገ፤ ታላላቅ ምንጣፎችን ታቦታቱ በሚሄዱበት መንገድ እያነጠፈ ለቃል ኪዳኑ ታቦት እንደ ነቢዩ ዳዊት ከፍተኛ ክብር በመስጠት እግዚአብሔርን እያገለገለ ይገኛል (1ኛ ነገሥት 6፡1-23)፡፡
“የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን ታቦትና ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ፥ ከሰፈራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት” (ኢያ 3፡3)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
♥ ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ [በድጋሚ ፓስት የተደረገ]
የቴሌግራም ቻናል፦ https://www.tg-me.com/Rodas9
የYoutube Channel:- https://youtube.com/channel/UCFKnpmDyWe3LQ_9Gx3TMnAg
Telegram
መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ (ዶክተር) Dr Rodas Tadese
ትክክለኛው ቻናሌ ይሄ ብቻ ነው። በዚ ብቻ ትምህርተ ሃይማኖትንና የኢትዮጵያ ምስጢራትን ሳይንሳዊ ጉዳዮችን በጥልቀት እንዳስሳለን። ሌሎቹ ቻናሎች የእኔ አይደሉም
በጥበብ እንድመቅ
እጅግ ድንቅና እርስዎን ወደ ጥበብ ከፍታ የሚያደርሶት በብዙ ምስጢር የተመላው "የግእዝ ቀመረ ፊደል" (Geez Gematria) የኦንላይን ትምህርት
👉 በዶክተር ሮዳስ ታደሰ ሊጀመር ነው።
💥 ትምህርቱ፦ ቅዳሜ ለ1 ሰዓት ተኩል
💥 ሰዓት፦ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ አቆጣጠር
👉 1 PM EST (NY) Time
👉 10 AM PST (LA) Time
💥 የመጀመሪያው ሴሚስተር የካቲት 22 (March 1) - ግንቦት 23 (May 31)
💥 አስትሮኖሚ (ሥነ ፈለክ፤ ሥነ ከዋክብት)
✍️ በዶክተር ጌትነት ፈለቀ
✍️ እሑድ ሰዓቱ በተመሳሳይ
💥 ለበለጠ መረጃ (ለምዝገባ) በሰሜን አሜሪካ ላሉ፦
(202) 643-3620 ይደውሉ።
በሀገር ውስጥ ላሉ ስልክ፦ 0911827336 ወይም 0925354271
👉 ለምዝገባ፦
🔥 *Considering the high volume of future Students who have expressed interest to take these Online Courses, we are happy to extend some discounts to our future students*
🔥 *For those who are applying from overseas [Europe, America, Canada, etc] ... PLEASE use these links shown below. Each link Registers you to the corresponding course, or courses.*
👉 *1. This Link gives you a $30 Discount for Numerology [Qemere Geez]*
https://buy.stripe.com/4gw2bA32V7Qy4hi001
👉 *2. This Link gives you a $30 Discount is for Astronomy [Sine-Feleg]*
https://buy.stripe.com/bIYdUi5b35Iq8xyeUW
👉 *3. This Link gives a $90 Discount for those who are taking both Courses*
https://buy.stripe.com/00g5nM6f75Iqg003cf
ይጠቀሙ።
👉 በሕይወት ዘመንዎ ከጥበብ ጋር የሚገናኙባት ዕለት ምርጥ ናት። ይመዝገቡ ለጥበብ ወዳጆችም ሼር ያድርጉ።
እጅግ ድንቅና እርስዎን ወደ ጥበብ ከፍታ የሚያደርሶት በብዙ ምስጢር የተመላው "የግእዝ ቀመረ ፊደል" (Geez Gematria) የኦንላይን ትምህርት
👉 በዶክተር ሮዳስ ታደሰ ሊጀመር ነው።
💥 ትምህርቱ፦ ቅዳሜ ለ1 ሰዓት ተኩል
💥 ሰዓት፦ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኢትዮጵያ አቆጣጠር
👉 1 PM EST (NY) Time
👉 10 AM PST (LA) Time
💥 የመጀመሪያው ሴሚስተር የካቲት 22 (March 1) - ግንቦት 23 (May 31)
💥 አስትሮኖሚ (ሥነ ፈለክ፤ ሥነ ከዋክብት)
✍️ በዶክተር ጌትነት ፈለቀ
✍️ እሑድ ሰዓቱ በተመሳሳይ
💥 ለበለጠ መረጃ (ለምዝገባ) በሰሜን አሜሪካ ላሉ፦
(202) 643-3620 ይደውሉ።
በሀገር ውስጥ ላሉ ስልክ፦ 0911827336 ወይም 0925354271
👉 ለምዝገባ፦
🔥 *Considering the high volume of future Students who have expressed interest to take these Online Courses, we are happy to extend some discounts to our future students*
🔥 *For those who are applying from overseas [Europe, America, Canada, etc] ... PLEASE use these links shown below. Each link Registers you to the corresponding course, or courses.*
👉 *1. This Link gives you a $30 Discount for Numerology [Qemere Geez]*
https://buy.stripe.com/4gw2bA32V7Qy4hi001
👉 *2. This Link gives you a $30 Discount is for Astronomy [Sine-Feleg]*
https://buy.stripe.com/bIYdUi5b35Iq8xyeUW
👉 *3. This Link gives a $90 Discount for those who are taking both Courses*
https://buy.stripe.com/00g5nM6f75Iqg003cf
ይጠቀሙ።
👉 በሕይወት ዘመንዎ ከጥበብ ጋር የሚገናኙባት ዕለት ምርጥ ናት። ይመዝገቡ ለጥበብ ወዳጆችም ሼር ያድርጉ።