Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
❤133👍48👏37🥰10🔥4
ብዙዎች በውስጥ መሥመር በማለቁ ምክንያት ተወዳጁ የአንድሮሜዳ መጽሐፍን እንዳላገኛችኹ ተደጋጋሚ ጥያቄ አንባቢዎች ያቀርቡ ነበረ።
አሁን ግን በጣም ሰፈ ኢትዮጵያዊና ሳይንሳዊ የሥነ ፈለክ (Astronomy) ዕውቀት የያዘው ታላቅ መጽሐፍ የተወሰነ ኮፒ ጥራቱን በጠበቀ መልኩ በድጋሚ ታትሞ ለአንባብያን ቀረበ።
መጽሐፉ በሀሁ መጻሕፍት መደብር
አድራሻ አራት ኪሎ አብርሆት ጎን
ስልክ 0911006705/ 0924408461
ማግኘት ይቻላል።
አሁን ግን በጣም ሰፈ ኢትዮጵያዊና ሳይንሳዊ የሥነ ፈለክ (Astronomy) ዕውቀት የያዘው ታላቅ መጽሐፍ የተወሰነ ኮፒ ጥራቱን በጠበቀ መልኩ በድጋሚ ታትሞ ለአንባብያን ቀረበ።
መጽሐፉ በሀሁ መጻሕፍት መደብር
አድራሻ አራት ኪሎ አብርሆት ጎን
ስልክ 0911006705/ 0924408461
ማግኘት ይቻላል።
❤66👍29😁3🥰2
[በደብረ ምጥማቅ ከግንቦት 21-25 የአምላክ እናት የድንግል ማርያም መገለጥና ስለውበቷ በኢትዮጵያ ሊቃውንት የቀረበላት ድንቅ ውዳሴ]
✍ በመጋቤ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ (በድጋሚ የተለጠፈ)
♥ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በመዝ ፵፬፥፲፪ ላይ “ወለገጽኪ ይትመሐለሉ ኲሎሙ አሕዛብ ብዑላነ ምድር” (የምድር ባለጠጎች አሕዛብ ኹሉ በፊትሽ ይማለላሉ) በማለት ትንቢትን እንደተናገረላት ብዙዎች ቅዱሳን ቅድስት ድንግል ማርያምን ተገልጻላቸው የአምላካቸውን እናት ለማየት ተመኝተዋል፤ ብዙዎቹም ልመናቸው ተሰምቶላቸው የአምላክ እናት ተገልጻላቸው እጅግ አስደናቂ ውበቷን አይተዋል፡፡ ከነዚኽ ውስጥ በደብረ ምጥማቅ የነበሩ ምእመናን ሌሎችም ብዙዎች ንጹሓን ክርስቲያኖች ይገኙበታል፡፡
♥ ልጇ አስቀድሞ በዘመነ ሥጋዌዉ በደብረ ምጥማቅ እንደ ምትገለጽ በገባላት ቃል ኪዳን መሠረት ከኢትዮጵያ፣ ከግብጽ፣ ከአርመንያ፣ ከሶርያ፣ ከሮም፣ ከጽርዕ፣ ከፋርስ ሀገራት ተሰብስበው በደብረ ምጥማቅ ድንኳን ተክለው፤ አጐበር ጥለው ከግንቦት 21 ቀን ጀምረው እስከ 25 ቀን ድረስ በፍጹም ደስታ የድንግልን በዓሏን ያከብሩ ነበር።
♥ “ወድንግልሂ ታስተርእዮሙ በእሉ ኀምስ መዋዕል ዘእንበለ ጽርዐት ምስለ መላእክት ወጻድቃን ወሰማዕት ምስሌሃ” ይላል፤ እመቤታችን ከግንቦት 21-25 ያለማቋረጥ ከመላእክት ከሊቃነ መላእክት፤ በአካለ ነፍስ ካሉ ከነቢያት ከሐዋርያት፤ ከጻድቃን ከሰማዕታት፤ ከደናግል ከመነኮሳት ጋራ ኹና ትገለጽላቸው ነበር፤ አማኒውም ኢአማኒውም ያያት ነበር፤ ክርስትያኖች ይህንን ድንቅ ተአምር እያዩ እምነታቸው ሲጸናላቸው፤ ያላመኑት ደግሞ እያመኑ በመጠመቅ ሀብተ ውልድና ስመ ክርስትናን ይቀበሉ ነበር፡፡
♥ በጒልላቱ ላይ ስትገለጽ በውስጥ በአፍአ በነፍስ በሥጋ ንጽሕት የኾነችው የቅድስት ድንግል ማርያም የፊቷ ውበትና ብርሃን እጅግ ድንቅ ነበርና ካህናቱም ሕዝቡም ኹሉ ልክ እንደ ኤልሳቤጥ “የጌታችን እናት ለእኛ ትገለጪ ዘንድ እኛ ምንድን ነን?” እያሉ ይጮኹ ነበር፤ ርሷም ያለማቋረጥ ትባርካቸው ነበር፡፡
♥የእመቤታችን ፍቅር በእጅጉ የበዛለት አባ ጽጌ ድንግልም በደብረ ምጥማቅ በታላቅ ክብር ተገልጻ ለምእመናን የታየችው የአምላክ እናት ለርሱም ትገለጽለት ዘንድ በማሕሌተ ጽጌ መጽሐፉ ላይ፡-
“አመ ትበርቂ በደብረ ምጥማቅ ኀምሰ ዕለታተ
ትእምርተ ገጽኪ ይርአይ እስከ ይትነሣእ ዘሞተ
ሚ መጠነ ማርያም ታሥተፌሥሒ ትፍሥሕተ
ኅድጊሰ ጽጌ ፍቅርኪ በጊዜ ንቃሑ መዓልተ
ብፁዕ ዘርእየኪ በሕልሙ ሌሊተ”
✍ (የፊትሽን መልክ ያይ ዘንድ የሞተ ሰው እስኪነሣ ድረስ በደብረ ምጥማቅ ለዐምስት ቀናት ያኽል በተገለጽሽ ጊዜ ማርያም ምን ያኽል ደስ ታሰኚ ኖሯል! በቀን የታየው የፍቅርሽ አበባ ይቅርና ሌሊት በሕልሙ ያየሽ ምስጉን ነው) በማለት ተማፅኗታል፡፡
♥ ዳግመኛም ይኸው ኢትዮጵያዊ ሊቅ በተመስጦ፡-
“ሥዕልኪ ጽግይተ ላሕይ ዘከመዝ ትኤድም በዓለም
እፎ ይሤኒ በሰማይ ላሕየ ገጽኪ ማርያም
ሐሤተ ትእምርትኪ እጽገብ አስተርእዪኒ በሕልም
እስመ አውዐየኒ ነደ ፍቅርኪ ፍሕም
አጥፍኦቶ ዘኢይክል ዝናም”
✍ (ማርያም ሥዕልሽ በዓለም እንዲኽ የምታበራ ከኾነ በሰማይ የፊትሽ መልክ ምን ያምር! አንቺን ከማየት የሚገኘውን ደስታ እጠግብ ዘንድ በሕልም ተገለጪልኝ፤ ዝናብ ሊያጠፋው የማይቻለው የፍቅርሽ እሳት አንድዶኛልና) ብሏል፡፡
♥ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም ይኽነን መገለጧን በእንዚራ ስብሐት መጽሐፉ ላይ በአድናቆት ፡-
“ኦ ንግሥት ይገንዩ ለኪ ነገሥት ወለኪ ንግሥታት ይትቀነያ
ወኪያኪ የአኲታ ወለስምኪ ይገንያ
ወለኪ ይሰግዳ ወለክብርኪ የሐልያ
ጢሮስ ወሲዶና ሰብአ ግብጽ ወኢትዮጵያ
ፊንቂ ወሮምያ ማሮን ወአርማንያ
በሥነ ጸዳልኪ ይትፌሥሓ ወበላሕይኪ ይትሐሠያ”
✍ (ንግሥት ሆይ ነገሥታት ለአንቺ ያገለግላሉ፤ ንግሥታትም አንቺን ያመሰግናሉ፤ አንቺንም ያሞግሳሉ፤ ለስምሽም ያጐነብሳሉ፤ ለአንቺ የጸጋ ስግደትን ይሰግዳሉ፤ ለክብርሽም ምስጋናን ያቀርባሉ፡፡ ጢሮስና ሲዶና የግብጽና የኢትዮጵያ ሰዎች፣ ፊንቄና ሮምያ፣ ማሮንና አርማንያ በወጋገንሽ ውበት ደስ ይሰኛሉ፤ በደም ግባትሽም እሰይ ይላሉ) በማለት ገልጦታል፡፡
❤ ❖✔ ቅዱስ ያሬድ አባታችንም በማይ ኪራሕ ሳለ እመቤታችን ተገልጻለት ፊቷን ለማየት ታድሏልና ይኽነን በዐይኑ ያየውን ውበቷን በድጓው ላይ እንዲኽ ሲል ጽፎታል፡-
✍️ “አይ ይእቲ ዛቲ እንተ ትወርድ እምሰማይ፤ ብርህት ከመ ፀሓይ፤ አዳም ቆማ ወክሣዳ ከመ አርማስቆስ፤ መዐዛ አፉሃ ከመ ኮል”
(ከሰማይ የምትወርደው እንደ ፀሐይም የምታበራው ርሷ ማን ናት! አንገቷ እንደ ግንብ ቀጥ ያለ ነው፤ የአፏም መዐዛ እንደ እንኮይ ነው) በማለት በተመስጦ የተመለከተውን ውበቷን ተናገረ፡፡
❤ ❖✔ ይኽ የቤተ ክርስቲያን ጌጥ ቅዱስ ያሬድ በዚኽ ሳያበቃ በመላእክት እየተመሰገነች ስለተገለጸችለት ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ያየውን የውበቷን ነገር ሲናገር፦
✍ “እምኀበ መላእክት ትሴባሕ አዳም ሥና፤ መዐርዒር ቃላ ወኲሉ ነገራ በሰላም … እምወርኅ ወእምፀሓይ ይሤኒ ላሕያ …ከመ ፍሕሶ ቀይሕ ከናፍሪሃ ወከመ ኮል መዐዛ አፉሃ ወከመ ሮማን ቂሐተ መላትሒሃ … "
❤ (በመላእክት ትመሰገናለች፤ ደም ግባቷ ያማረ ነው፤ ቃሏ እንደ ማር የጣፈጠ፤ ነገሯ ኹሉ በሰላም የተመላ ነው … ውበቷ ደም ግባቷ ከጨረቃና ከፀሓይ ይልቅ ያምራል፤ ከንፈሮቿ ፍሕሶ እንደሚባል አበባ ቀይ ናቸው፤ የጒንጯ ቅላትም እንደ ሮማን ቅርፍት ነው) እያለ ሊቁ ማሕሌታይ በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ ይመሰክርላታል።
❤ የእመቤታችን ጣዕመ ውዳሴዋ የበዛለት ኢትዮጵያዊው ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም በእንዚራ ስብሐቱ ላይ ስለውበቷ በተመስጦ ሆኖ ያቀረበላትን ውዳሴ እነሆ፡-
☞ ☞ “ኦ ፍቅርት ውዕየ ልብየ በእሳተ ፍቅርኪ ወነደ ኅሊናየ እምኀልዮትኪ …” (ውዲቱ ሆይ በፍቅርሽ እሳት ልቤ ተቃጠለ፤ አንቺንም ከማሰብ የተነሣ ኅሊናዬ ነደደ፤ ለምስጋናሽ ቃሌን ከፍ ከፍ አደርጋለኊ፤ አንቺን ለማመስገንም አንደበቴን አከፍታለኊ፡፡ ንግሥት ሆይ አንደበቴ ቅንነትሽን በመናገር ደስ ይለዋል፤ ከንፈሮቼም በቸርነትሽ ጣዕም ነገር ደስ ይሰኛሉ፤ ሰላም እያልኹሽም ለስምሽ አጠራር እኔ እሰግዳለኊ (ኢሳ 49:23)፡፡
❤ንግሥት ሆይ የራስሽ ክፍክፋት ተፈጥሮ እንደ አሞራ ጥቁር የኾነ ጠጒርሽም እንደ ሐር የሚመስል ነው (መሓ 7:6)፤ የራስ ወርቅሽ የቃል ኪዳን ምልክት ነው፤ የንጽሕናሽ ብርሃንም እንደ ጧት ወገግታ ነው (መሓ 6:10)፡፡
❤ ግርምቲቱ ሆይ የቅንድቦችሽ ነበልባል (እሳት) የመብረቅ ፍንጣቂ ነው፤ ዐይኖችሽም እንደ ጨረቃ ምላት ብርሃንን የተመሉ ናቸው (መሓ 6:10)፤ ጆሮችሽም የደስታ በሮች ናቸው (ሉቃ 1:28)፤ የጒንጮችሽ ቅላትም እንደ ሮማን ቅርፍት ነው (መሓ 4:3)፡፡
❤ንግሥት ሆይ አፍሽ የበጎ መዐዛ መስኮት ነው፤ ከንፈሮችሽም የደስታ መፍሰሾች ናቸው (መሓ 4:9)፤ የአፍንጫሽ መዐዛም የበረሓ እንኮይ ነው (መሓ 7:9)፤ የጥርሶችሽ ንጣትም እንደሚያምር በረዶ ነው (መሓ 4:2)፡፡
❤ ምርጢቱ ሆይ የአንደበትሽ ሥር የወተት ምንጭ ነው፤ የንግግርሽ ቃልም እንደ ማር የጣፈጠ ነው (መሓ 4፡12)፤ የእስትንፋስሽ ቃልም የሽቱ ቅመም ብናኝ ነው፤ ጒረሮሽም፣ የማር ወለላ አረፋ ነው፡፡.
✍ በመጋቤ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ (በድጋሚ የተለጠፈ)
♥ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በመዝ ፵፬፥፲፪ ላይ “ወለገጽኪ ይትመሐለሉ ኲሎሙ አሕዛብ ብዑላነ ምድር” (የምድር ባለጠጎች አሕዛብ ኹሉ በፊትሽ ይማለላሉ) በማለት ትንቢትን እንደተናገረላት ብዙዎች ቅዱሳን ቅድስት ድንግል ማርያምን ተገልጻላቸው የአምላካቸውን እናት ለማየት ተመኝተዋል፤ ብዙዎቹም ልመናቸው ተሰምቶላቸው የአምላክ እናት ተገልጻላቸው እጅግ አስደናቂ ውበቷን አይተዋል፡፡ ከነዚኽ ውስጥ በደብረ ምጥማቅ የነበሩ ምእመናን ሌሎችም ብዙዎች ንጹሓን ክርስቲያኖች ይገኙበታል፡፡
♥ ልጇ አስቀድሞ በዘመነ ሥጋዌዉ በደብረ ምጥማቅ እንደ ምትገለጽ በገባላት ቃል ኪዳን መሠረት ከኢትዮጵያ፣ ከግብጽ፣ ከአርመንያ፣ ከሶርያ፣ ከሮም፣ ከጽርዕ፣ ከፋርስ ሀገራት ተሰብስበው በደብረ ምጥማቅ ድንኳን ተክለው፤ አጐበር ጥለው ከግንቦት 21 ቀን ጀምረው እስከ 25 ቀን ድረስ በፍጹም ደስታ የድንግልን በዓሏን ያከብሩ ነበር።
♥ “ወድንግልሂ ታስተርእዮሙ በእሉ ኀምስ መዋዕል ዘእንበለ ጽርዐት ምስለ መላእክት ወጻድቃን ወሰማዕት ምስሌሃ” ይላል፤ እመቤታችን ከግንቦት 21-25 ያለማቋረጥ ከመላእክት ከሊቃነ መላእክት፤ በአካለ ነፍስ ካሉ ከነቢያት ከሐዋርያት፤ ከጻድቃን ከሰማዕታት፤ ከደናግል ከመነኮሳት ጋራ ኹና ትገለጽላቸው ነበር፤ አማኒውም ኢአማኒውም ያያት ነበር፤ ክርስትያኖች ይህንን ድንቅ ተአምር እያዩ እምነታቸው ሲጸናላቸው፤ ያላመኑት ደግሞ እያመኑ በመጠመቅ ሀብተ ውልድና ስመ ክርስትናን ይቀበሉ ነበር፡፡
♥ በጒልላቱ ላይ ስትገለጽ በውስጥ በአፍአ በነፍስ በሥጋ ንጽሕት የኾነችው የቅድስት ድንግል ማርያም የፊቷ ውበትና ብርሃን እጅግ ድንቅ ነበርና ካህናቱም ሕዝቡም ኹሉ ልክ እንደ ኤልሳቤጥ “የጌታችን እናት ለእኛ ትገለጪ ዘንድ እኛ ምንድን ነን?” እያሉ ይጮኹ ነበር፤ ርሷም ያለማቋረጥ ትባርካቸው ነበር፡፡
♥የእመቤታችን ፍቅር በእጅጉ የበዛለት አባ ጽጌ ድንግልም በደብረ ምጥማቅ በታላቅ ክብር ተገልጻ ለምእመናን የታየችው የአምላክ እናት ለርሱም ትገለጽለት ዘንድ በማሕሌተ ጽጌ መጽሐፉ ላይ፡-
“አመ ትበርቂ በደብረ ምጥማቅ ኀምሰ ዕለታተ
ትእምርተ ገጽኪ ይርአይ እስከ ይትነሣእ ዘሞተ
ሚ መጠነ ማርያም ታሥተፌሥሒ ትፍሥሕተ
ኅድጊሰ ጽጌ ፍቅርኪ በጊዜ ንቃሑ መዓልተ
ብፁዕ ዘርእየኪ በሕልሙ ሌሊተ”
✍ (የፊትሽን መልክ ያይ ዘንድ የሞተ ሰው እስኪነሣ ድረስ በደብረ ምጥማቅ ለዐምስት ቀናት ያኽል በተገለጽሽ ጊዜ ማርያም ምን ያኽል ደስ ታሰኚ ኖሯል! በቀን የታየው የፍቅርሽ አበባ ይቅርና ሌሊት በሕልሙ ያየሽ ምስጉን ነው) በማለት ተማፅኗታል፡፡
♥ ዳግመኛም ይኸው ኢትዮጵያዊ ሊቅ በተመስጦ፡-
“ሥዕልኪ ጽግይተ ላሕይ ዘከመዝ ትኤድም በዓለም
እፎ ይሤኒ በሰማይ ላሕየ ገጽኪ ማርያም
ሐሤተ ትእምርትኪ እጽገብ አስተርእዪኒ በሕልም
እስመ አውዐየኒ ነደ ፍቅርኪ ፍሕም
አጥፍኦቶ ዘኢይክል ዝናም”
✍ (ማርያም ሥዕልሽ በዓለም እንዲኽ የምታበራ ከኾነ በሰማይ የፊትሽ መልክ ምን ያምር! አንቺን ከማየት የሚገኘውን ደስታ እጠግብ ዘንድ በሕልም ተገለጪልኝ፤ ዝናብ ሊያጠፋው የማይቻለው የፍቅርሽ እሳት አንድዶኛልና) ብሏል፡፡
♥ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም ይኽነን መገለጧን በእንዚራ ስብሐት መጽሐፉ ላይ በአድናቆት ፡-
“ኦ ንግሥት ይገንዩ ለኪ ነገሥት ወለኪ ንግሥታት ይትቀነያ
ወኪያኪ የአኲታ ወለስምኪ ይገንያ
ወለኪ ይሰግዳ ወለክብርኪ የሐልያ
ጢሮስ ወሲዶና ሰብአ ግብጽ ወኢትዮጵያ
ፊንቂ ወሮምያ ማሮን ወአርማንያ
በሥነ ጸዳልኪ ይትፌሥሓ ወበላሕይኪ ይትሐሠያ”
✍ (ንግሥት ሆይ ነገሥታት ለአንቺ ያገለግላሉ፤ ንግሥታትም አንቺን ያመሰግናሉ፤ አንቺንም ያሞግሳሉ፤ ለስምሽም ያጐነብሳሉ፤ ለአንቺ የጸጋ ስግደትን ይሰግዳሉ፤ ለክብርሽም ምስጋናን ያቀርባሉ፡፡ ጢሮስና ሲዶና የግብጽና የኢትዮጵያ ሰዎች፣ ፊንቄና ሮምያ፣ ማሮንና አርማንያ በወጋገንሽ ውበት ደስ ይሰኛሉ፤ በደም ግባትሽም እሰይ ይላሉ) በማለት ገልጦታል፡፡
❤ ❖✔ ቅዱስ ያሬድ አባታችንም በማይ ኪራሕ ሳለ እመቤታችን ተገልጻለት ፊቷን ለማየት ታድሏልና ይኽነን በዐይኑ ያየውን ውበቷን በድጓው ላይ እንዲኽ ሲል ጽፎታል፡-
✍️ “አይ ይእቲ ዛቲ እንተ ትወርድ እምሰማይ፤ ብርህት ከመ ፀሓይ፤ አዳም ቆማ ወክሣዳ ከመ አርማስቆስ፤ መዐዛ አፉሃ ከመ ኮል”
(ከሰማይ የምትወርደው እንደ ፀሐይም የምታበራው ርሷ ማን ናት! አንገቷ እንደ ግንብ ቀጥ ያለ ነው፤ የአፏም መዐዛ እንደ እንኮይ ነው) በማለት በተመስጦ የተመለከተውን ውበቷን ተናገረ፡፡
❤ ❖✔ ይኽ የቤተ ክርስቲያን ጌጥ ቅዱስ ያሬድ በዚኽ ሳያበቃ በመላእክት እየተመሰገነች ስለተገለጸችለት ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ያየውን የውበቷን ነገር ሲናገር፦
✍ “እምኀበ መላእክት ትሴባሕ አዳም ሥና፤ መዐርዒር ቃላ ወኲሉ ነገራ በሰላም … እምወርኅ ወእምፀሓይ ይሤኒ ላሕያ …ከመ ፍሕሶ ቀይሕ ከናፍሪሃ ወከመ ኮል መዐዛ አፉሃ ወከመ ሮማን ቂሐተ መላትሒሃ … "
❤ (በመላእክት ትመሰገናለች፤ ደም ግባቷ ያማረ ነው፤ ቃሏ እንደ ማር የጣፈጠ፤ ነገሯ ኹሉ በሰላም የተመላ ነው … ውበቷ ደም ግባቷ ከጨረቃና ከፀሓይ ይልቅ ያምራል፤ ከንፈሮቿ ፍሕሶ እንደሚባል አበባ ቀይ ናቸው፤ የጒንጯ ቅላትም እንደ ሮማን ቅርፍት ነው) እያለ ሊቁ ማሕሌታይ በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ ይመሰክርላታል።
❤ የእመቤታችን ጣዕመ ውዳሴዋ የበዛለት ኢትዮጵያዊው ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም በእንዚራ ስብሐቱ ላይ ስለውበቷ በተመስጦ ሆኖ ያቀረበላትን ውዳሴ እነሆ፡-
☞ ☞ “ኦ ፍቅርት ውዕየ ልብየ በእሳተ ፍቅርኪ ወነደ ኅሊናየ እምኀልዮትኪ …” (ውዲቱ ሆይ በፍቅርሽ እሳት ልቤ ተቃጠለ፤ አንቺንም ከማሰብ የተነሣ ኅሊናዬ ነደደ፤ ለምስጋናሽ ቃሌን ከፍ ከፍ አደርጋለኊ፤ አንቺን ለማመስገንም አንደበቴን አከፍታለኊ፡፡ ንግሥት ሆይ አንደበቴ ቅንነትሽን በመናገር ደስ ይለዋል፤ ከንፈሮቼም በቸርነትሽ ጣዕም ነገር ደስ ይሰኛሉ፤ ሰላም እያልኹሽም ለስምሽ አጠራር እኔ እሰግዳለኊ (ኢሳ 49:23)፡፡
❤ንግሥት ሆይ የራስሽ ክፍክፋት ተፈጥሮ እንደ አሞራ ጥቁር የኾነ ጠጒርሽም እንደ ሐር የሚመስል ነው (መሓ 7:6)፤ የራስ ወርቅሽ የቃል ኪዳን ምልክት ነው፤ የንጽሕናሽ ብርሃንም እንደ ጧት ወገግታ ነው (መሓ 6:10)፡፡
❤ ግርምቲቱ ሆይ የቅንድቦችሽ ነበልባል (እሳት) የመብረቅ ፍንጣቂ ነው፤ ዐይኖችሽም እንደ ጨረቃ ምላት ብርሃንን የተመሉ ናቸው (መሓ 6:10)፤ ጆሮችሽም የደስታ በሮች ናቸው (ሉቃ 1:28)፤ የጒንጮችሽ ቅላትም እንደ ሮማን ቅርፍት ነው (መሓ 4:3)፡፡
❤ንግሥት ሆይ አፍሽ የበጎ መዐዛ መስኮት ነው፤ ከንፈሮችሽም የደስታ መፍሰሾች ናቸው (መሓ 4:9)፤ የአፍንጫሽ መዐዛም የበረሓ እንኮይ ነው (መሓ 7:9)፤ የጥርሶችሽ ንጣትም እንደሚያምር በረዶ ነው (መሓ 4:2)፡፡
❤ ምርጢቱ ሆይ የአንደበትሽ ሥር የወተት ምንጭ ነው፤ የንግግርሽ ቃልም እንደ ማር የጣፈጠ ነው (መሓ 4፡12)፤ የእስትንፋስሽ ቃልም የሽቱ ቅመም ብናኝ ነው፤ ጒረሮሽም፣ የማር ወለላ አረፋ ነው፡፡.
Telegram
መጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ (ዶክተር) Dr Rodas Tadese
ትክክለኛው ቻናሌ ይሄ ብቻ ነው። በዚ ብቻ ትምህርተ ሃይማኖትንና የኢትዮጵያ ምስጢራትን ሳይንሳዊ ጉዳዮችን በጥልቀት እንዳስሳለን። ሌሎቹ ቻናሎች የእኔ አይደሉም
❤75👍21
❤ የተሸለምሽ ያጌጥሽ ሙሽሪት ሆይ፤ የአንገትሽ መገናኛ (ቅርጽ) እንደ ወርቅ ዘንግ ነው (መሓ 1:11)፤ ትከሾችሽም የሰላምና የቅንነት ማረፊያዎች ናቸው፤ የጀርባሽ ልብስም የብርሃን ሐር ነው (ራእ 12:1)፤ ደረትሽም የዕውቀት አዳራሽ ነው፤ ጉያሽ የመለኮት (የጌታ) ማረፊያ ናቸው፤ እጆችሽም በንጽሕና አንባር የተሸለሙ ናቸው፤ ክንዶችሽም የንጉሥ (የጌታ) መጠጊያዎች ናቸው፤ ክርንሽም የኀይል ረድኤት ቦታ ነው፤ ክንዶችሽም የእሳት ምሳግ ናቸው፤ መኻል እጆችሽም ለመስጠት የተዘረጉ ናቸው፤ በጥፍሮችሽ የተጋረዱ ጣቶችሽ እንደ ወርቅ ፍቅፋቂ ነው::
❤ ሙሽሪት ሆይ ጡቶችሽ እንደ ወይን ፍሬ የተወደዱና ያማሩ ናቸው (መሓ 7:8) ፡፡ ጐኖችሽም በወርቅ ሐመልማል የተሣሉ (ያጌጡ) ናቸው (መዝ 67(68):13)፡፡ የማሕፀንሽ መቅደስ በአበባ (በጸጋ መንፈስ ቅዱስ) የታጠረ ነው፣ (መሓ 7/3) የልቡናሽ ጥልቀትም በቸርነት ቃል፤ ኲላሊቶችሽ የትእዛዝ ጽላት ናቸው፤ ኅሊናሽም የጥበብ መሠረት ነው፤ አንጀትሽም የይቅርታ ሣጥን ነው፤ የውስጥ ሰውነትሽም የቅዱሳን ቅድስት ምልክት ነው፤ የዕንብርትሽ ዙሪያም እንደ ማኅተም ቅርጽ ነው (መሓ 7:3)፤ ማሕፀንሽም የምስጋና ዙፋን ነው::
❤ የድንግልናሽም ምሳሌ፤ የታተመ የነቢያት መጽሐፍ ነው (ኢሳ 29:11)፤ የወገብሽ ትጥቅም የቅድስና ጸጋ ነው፤ ጒልበትሽም የአርያም (የሰማይ) ወገን ናቸው፤ የጭኖችሽ (የእግሮችሽ) አነዋወርም እንደ እብነ በረድ ምሶሶች ነው፤ እግሮችሽም ምሕረትን ለማድረግ የተፋጠኑ ናቸው፤ የማይታበዩ ጫማዎችሽም የጥበብ መድረክ ናቸው፡፡ እግርሽም በቅንነት ጐዳና የጸኑ ናቸው፤ የእግርሽ ጣቶችም በጥፋት ደንጊያ የማይሰነካከሉ ናቸው፤ ጥፍሮችሽም በላያቸው እንደ ብርሃን ብልጭ የሚሉ ናቸው፡፡
❤ የቁመናሽ አካልም እንደ ዘንባባ ያማረ ነው (መሓ 7:8)፤ የመልክሽ ደም ግባትም ለዐይን የተወደደ ነው፤ ድንግል ሆይ እጅግ በጣም አማርሽ፤ ከራስሽ እስከ እግርሽ ክፉ ነገር የለብሽም (መሓ 4:7)፤ ደም ግባትሽን የሚመስለው የለም፤ ኹለንተናሽንም የሚተካከለው የለም፡፡ ምርጢቱ ሆይ መልካም በኾነውና በጎም በኾነው ኹሉ መሰልኹሽ ነገር ግን ምስጋናሽን መጨረሽ አልቻልኹም፡፡)፡፡ (አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ)
♥ የመልክአ ማርያም ደራሲም የአምላኩን እናት ቅድስት ድንግል ማርያምን ፊቷን ለማየት ሽቶ በናፍቆት ኾኖ፡-
“ሰላም ለመልክእኪ ዘተሠርገወ አሜረ
ዘያበርህ ወትረ
ፍቅርትየ አንቲ እንተ ታበድሪ ፍቅረ
አርእዪኒ ገጸ ዚኣኪ ማርያም ምዕረ
ዘኢይሰምዖ ካልእ እንግርኪ ነገረ”
♥ (ኹልጊዜ (ዘወትር) የሚያበራ ፀሓይን ጌጥ ላደረገ መልክሽ ሰላምታ ይገባል፤ ፍቅርን የምትመርጪ (የምታስቀድሚ) አንቺ ፍቅረኛዬ ማርያም ሌላ የማይሰማው ነገርን እነግርሽ ዘንድ አንድ ጊዜ ያንቺን ፊት ግለጪልኝ) በማለት ተማፅኗታል፡፡
♥ በመኾኑም በደብረ ምጥማቅ የተገለጠችላቸው ምእመናን የአምላክን እናት አይተው እንደተደሰቱ፤ ዛሬም ለእኛ በመስቀል ሥር ከልጇ ለተቀበለችን ለአደራ ልጆቿ በረድኤት ትገለጽ ዘንድ አበው ካህናት ሌሊቱን በሰዓታት ምስጋና፦
✍ “ንዒ ኀቤየ ኦ ድንግል ምስለ ወልድኪ ፍቁርኪ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ትባርኪ ላዕሌነ” (ድንግል ሆይ ከተወዳጅ ልጅሽ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋራ ወደ እኔ ነዪ እኛን ትባርኪ ዘንድ (በእኛ ላይ በረከትን እንድታሳድሪ) በማለት ይማፀኗታል።
[የአምላክ እናት ሆይ ዛሬም ለእኛም በእጅጉ ለምንወድሽ ለልጆችሽ በረድኤት ትገለጪልን ዘንድ እንማፀንሻለን፡፡]
❤ ሙሽሪት ሆይ ጡቶችሽ እንደ ወይን ፍሬ የተወደዱና ያማሩ ናቸው (መሓ 7:8) ፡፡ ጐኖችሽም በወርቅ ሐመልማል የተሣሉ (ያጌጡ) ናቸው (መዝ 67(68):13)፡፡ የማሕፀንሽ መቅደስ በአበባ (በጸጋ መንፈስ ቅዱስ) የታጠረ ነው፣ (መሓ 7/3) የልቡናሽ ጥልቀትም በቸርነት ቃል፤ ኲላሊቶችሽ የትእዛዝ ጽላት ናቸው፤ ኅሊናሽም የጥበብ መሠረት ነው፤ አንጀትሽም የይቅርታ ሣጥን ነው፤ የውስጥ ሰውነትሽም የቅዱሳን ቅድስት ምልክት ነው፤ የዕንብርትሽ ዙሪያም እንደ ማኅተም ቅርጽ ነው (መሓ 7:3)፤ ማሕፀንሽም የምስጋና ዙፋን ነው::
❤ የድንግልናሽም ምሳሌ፤ የታተመ የነቢያት መጽሐፍ ነው (ኢሳ 29:11)፤ የወገብሽ ትጥቅም የቅድስና ጸጋ ነው፤ ጒልበትሽም የአርያም (የሰማይ) ወገን ናቸው፤ የጭኖችሽ (የእግሮችሽ) አነዋወርም እንደ እብነ በረድ ምሶሶች ነው፤ እግሮችሽም ምሕረትን ለማድረግ የተፋጠኑ ናቸው፤ የማይታበዩ ጫማዎችሽም የጥበብ መድረክ ናቸው፡፡ እግርሽም በቅንነት ጐዳና የጸኑ ናቸው፤ የእግርሽ ጣቶችም በጥፋት ደንጊያ የማይሰነካከሉ ናቸው፤ ጥፍሮችሽም በላያቸው እንደ ብርሃን ብልጭ የሚሉ ናቸው፡፡
❤ የቁመናሽ አካልም እንደ ዘንባባ ያማረ ነው (መሓ 7:8)፤ የመልክሽ ደም ግባትም ለዐይን የተወደደ ነው፤ ድንግል ሆይ እጅግ በጣም አማርሽ፤ ከራስሽ እስከ እግርሽ ክፉ ነገር የለብሽም (መሓ 4:7)፤ ደም ግባትሽን የሚመስለው የለም፤ ኹለንተናሽንም የሚተካከለው የለም፡፡ ምርጢቱ ሆይ መልካም በኾነውና በጎም በኾነው ኹሉ መሰልኹሽ ነገር ግን ምስጋናሽን መጨረሽ አልቻልኹም፡፡)፡፡ (አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ)
♥ የመልክአ ማርያም ደራሲም የአምላኩን እናት ቅድስት ድንግል ማርያምን ፊቷን ለማየት ሽቶ በናፍቆት ኾኖ፡-
“ሰላም ለመልክእኪ ዘተሠርገወ አሜረ
ዘያበርህ ወትረ
ፍቅርትየ አንቲ እንተ ታበድሪ ፍቅረ
አርእዪኒ ገጸ ዚኣኪ ማርያም ምዕረ
ዘኢይሰምዖ ካልእ እንግርኪ ነገረ”
♥ (ኹልጊዜ (ዘወትር) የሚያበራ ፀሓይን ጌጥ ላደረገ መልክሽ ሰላምታ ይገባል፤ ፍቅርን የምትመርጪ (የምታስቀድሚ) አንቺ ፍቅረኛዬ ማርያም ሌላ የማይሰማው ነገርን እነግርሽ ዘንድ አንድ ጊዜ ያንቺን ፊት ግለጪልኝ) በማለት ተማፅኗታል፡፡
♥ በመኾኑም በደብረ ምጥማቅ የተገለጠችላቸው ምእመናን የአምላክን እናት አይተው እንደተደሰቱ፤ ዛሬም ለእኛ በመስቀል ሥር ከልጇ ለተቀበለችን ለአደራ ልጆቿ በረድኤት ትገለጽ ዘንድ አበው ካህናት ሌሊቱን በሰዓታት ምስጋና፦
✍ “ንዒ ኀቤየ ኦ ድንግል ምስለ ወልድኪ ፍቁርኪ ኢየሱስ ክርስቶስ ከመ ትባርኪ ላዕሌነ” (ድንግል ሆይ ከተወዳጅ ልጅሽ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋራ ወደ እኔ ነዪ እኛን ትባርኪ ዘንድ (በእኛ ላይ በረከትን እንድታሳድሪ) በማለት ይማፀኗታል።
[የአምላክ እናት ሆይ ዛሬም ለእኛም በእጅጉ ለምንወድሽ ለልጆችሽ በረድኤት ትገለጪልን ዘንድ እንማፀንሻለን፡፡]
❤133👍26👏11🥰10
ስለ ክርስቶስ ዕርገት የሊቁ የቅዱስ ያሬድ ትምህርት
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (ነገረ ክርስቶስ መጽሐፍ ገጽ 505)
💥 “ዮምሰ በሰማያት ይትፌሥሑ መላእክት እስመ በእንተ ሰብእ ዘሐመ ወሞተ በፍሥሐ ወበሰላም ዐርገ ሰማያት”
👉 (ስለ ሰው ልጆች የታመመው የሞተው በደስታና በሰላም ወደ ሰማይ ዐርጓልና ዛሬ በሰማያት መላእክት ይደሰታሉ) (ድጓ ዘሰንበት፤ ገጽ 454)
💥 “በፍሥሐ ወበሰላም ዐርገ ወልድ ውስተ ሰማያት ተኰነኑ ሎቱ መላእክት በይባቤ ዐርገ ወበቃለ ቀርን በከመ ዕርገቱ ዳግመ ምጽአቱ በስብሐት እንዘ ንሴፎ”
👉 (በደስታና በሰላምም ወልድ ወደ ሰማያት ውስጥ ዐረገ፤ ለርሱም መላእክት ተገዙለት፤ በእልልታና በመለከት ቃል ዐረገ፤ ተስፋ እንደምናደርገው እንደ ዕርገቱ ዳግመኛ ለፍርድ መምጣቱ በጌትነት ነው) ድጓ ዘሰንበት ገጽ 454
💥 “ዐርገ እግዚአብሔር ውስተ ማኅደሩ ግሩም፤ ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ ወበቃለ ቀርን፤ ዐርገ እግዚአብሔር በስብሐት ምስለ መላእክት፤ ንዑ ነሀሉ ኀበ አምላክነ ንዑ ነሀሉ ምስለ ንጉሥነ ወናክብር ሰንበቶ በጽድቅ”
👉 (እግዚአብሔር ወደ ግሩም ማደሪያው ዐረገ፤ እግዚአብሔር በእልልታና በመለከት ድምፅ ዐረገ፤ እግዚአብሔር በመላእክት ምስጋና ዐረገ፤ አምላካችን ወዳለበት ኑ እንኑር፤ ከንጉሣችን ጋር ኑ እንኑር፤ ሰንበቱን በእውነት እናክብር) (ድጓ ዘሰንበት ገጽ 458)
💥 “አምላከ ምሕረት ንጉሠ ነገሥት ወእግዚአ አጋእዝት አክሊለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት ወተስፋ መነኮሳት ክብሮሙ ለመላእክት ተንሢኦ ዐርገ ሰማያት”
👉 (የምሕረት አምላክ፣ የነገሥታት ንጉሥ፣ የጌቶች ጌታ፣ የሰማዕታት አክሊል፣ የካህናት ሿሚ፣ የመነኮሳት ተስፋ፣ የመላእክት ክብራቸው ተነሥቶ ወደ ሰማያት ዐረገ) (ድጓ ዘክብረ ቅዱሳን ገጽ 467)
💥 “አምላኩሰ ለአዳም ዐርገ ውስተ አርያም ሞገሶሙ ለጻድቃን በትንሣኤሁ ገብረ ፍሥሐ ወሰላም”
👉 (የአዳም አምላኩ ግን ወደ አርያም ዐረገ፤ የጻድቃን ሞገሳቸው በመነሣቱ ደስታና ሰላምን አደረገ) (ድጓ ዘክብረ ቅዱሳን ገጽ 470)
💥 “አውጽኦሙ አፍአ እስከ ቢታንያ ወአዕረጎሙ ውስተ ደብር ለሐዋርያት ወነገሮሙ ምስጢረ ኅቡአ ወልድ ዋሕድ እንዘ ሀሎ ምስሌሆሙ ወተናገሮሙ መጽአ ደመና ብሩህ ወሰወሮሙ፤ እለ ይለብሱ መብረቀ ስብሐት አስተርአይዎሙ ወይቤልዎሙ ለእመ ርኢክምዎ የዐርግ ሰማየ በስብሐት ይመጽእ ዳግመ”
👉 (እስከ ቢታንያ ድረስ ይዟቸው ወደ ውጪ አወጣቸው፤ ወደ ደብረ ዘይት ተራራ አወጣቸው፤ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው ወልድ ዋሕድ ከነርሱ ጋር እያለ ስዉር ምስጢርን ነገራቸው፤ ይኽነነም እየተናገራቸው ብሩህ ደመና መጥቶ ሰወረውም፤ የምስጋና መብረቅን የለበሱ ታይዋቸው፤ በምስጋና ወደ ሰማይ ሲያርግ እንዳያችኹት ዳግመኛ ይመጣል አሏቸው) እንዲል ቅዱስ ያሬድ (ድጓ ዘዘወትር ገጽ 464)
💥 በመኾኑም በቅዱስ ያሬድ ድንቅ ምስጋና ዓለም እስኪያልፍ ድረስ የክርስቶስን ዕርገት በቤተ ክርስቲያናችን ይሰበካል፡፡
💥 መልካም የአምላካችን የክርስቶስ የዕርገት በዓል ይኹንላችኹ።
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (ነገረ ክርስቶስ መጽሐፍ ገጽ 505)
💥 “ዮምሰ በሰማያት ይትፌሥሑ መላእክት እስመ በእንተ ሰብእ ዘሐመ ወሞተ በፍሥሐ ወበሰላም ዐርገ ሰማያት”
👉 (ስለ ሰው ልጆች የታመመው የሞተው በደስታና በሰላም ወደ ሰማይ ዐርጓልና ዛሬ በሰማያት መላእክት ይደሰታሉ) (ድጓ ዘሰንበት፤ ገጽ 454)
💥 “በፍሥሐ ወበሰላም ዐርገ ወልድ ውስተ ሰማያት ተኰነኑ ሎቱ መላእክት በይባቤ ዐርገ ወበቃለ ቀርን በከመ ዕርገቱ ዳግመ ምጽአቱ በስብሐት እንዘ ንሴፎ”
👉 (በደስታና በሰላምም ወልድ ወደ ሰማያት ውስጥ ዐረገ፤ ለርሱም መላእክት ተገዙለት፤ በእልልታና በመለከት ቃል ዐረገ፤ ተስፋ እንደምናደርገው እንደ ዕርገቱ ዳግመኛ ለፍርድ መምጣቱ በጌትነት ነው) ድጓ ዘሰንበት ገጽ 454
💥 “ዐርገ እግዚአብሔር ውስተ ማኅደሩ ግሩም፤ ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ ወበቃለ ቀርን፤ ዐርገ እግዚአብሔር በስብሐት ምስለ መላእክት፤ ንዑ ነሀሉ ኀበ አምላክነ ንዑ ነሀሉ ምስለ ንጉሥነ ወናክብር ሰንበቶ በጽድቅ”
👉 (እግዚአብሔር ወደ ግሩም ማደሪያው ዐረገ፤ እግዚአብሔር በእልልታና በመለከት ድምፅ ዐረገ፤ እግዚአብሔር በመላእክት ምስጋና ዐረገ፤ አምላካችን ወዳለበት ኑ እንኑር፤ ከንጉሣችን ጋር ኑ እንኑር፤ ሰንበቱን በእውነት እናክብር) (ድጓ ዘሰንበት ገጽ 458)
💥 “አምላከ ምሕረት ንጉሠ ነገሥት ወእግዚአ አጋእዝት አክሊለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት ወተስፋ መነኮሳት ክብሮሙ ለመላእክት ተንሢኦ ዐርገ ሰማያት”
👉 (የምሕረት አምላክ፣ የነገሥታት ንጉሥ፣ የጌቶች ጌታ፣ የሰማዕታት አክሊል፣ የካህናት ሿሚ፣ የመነኮሳት ተስፋ፣ የመላእክት ክብራቸው ተነሥቶ ወደ ሰማያት ዐረገ) (ድጓ ዘክብረ ቅዱሳን ገጽ 467)
💥 “አምላኩሰ ለአዳም ዐርገ ውስተ አርያም ሞገሶሙ ለጻድቃን በትንሣኤሁ ገብረ ፍሥሐ ወሰላም”
👉 (የአዳም አምላኩ ግን ወደ አርያም ዐረገ፤ የጻድቃን ሞገሳቸው በመነሣቱ ደስታና ሰላምን አደረገ) (ድጓ ዘክብረ ቅዱሳን ገጽ 470)
💥 “አውጽኦሙ አፍአ እስከ ቢታንያ ወአዕረጎሙ ውስተ ደብር ለሐዋርያት ወነገሮሙ ምስጢረ ኅቡአ ወልድ ዋሕድ እንዘ ሀሎ ምስሌሆሙ ወተናገሮሙ መጽአ ደመና ብሩህ ወሰወሮሙ፤ እለ ይለብሱ መብረቀ ስብሐት አስተርአይዎሙ ወይቤልዎሙ ለእመ ርኢክምዎ የዐርግ ሰማየ በስብሐት ይመጽእ ዳግመ”
👉 (እስከ ቢታንያ ድረስ ይዟቸው ወደ ውጪ አወጣቸው፤ ወደ ደብረ ዘይት ተራራ አወጣቸው፤ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው ወልድ ዋሕድ ከነርሱ ጋር እያለ ስዉር ምስጢርን ነገራቸው፤ ይኽነነም እየተናገራቸው ብሩህ ደመና መጥቶ ሰወረውም፤ የምስጋና መብረቅን የለበሱ ታይዋቸው፤ በምስጋና ወደ ሰማይ ሲያርግ እንዳያችኹት ዳግመኛ ይመጣል አሏቸው) እንዲል ቅዱስ ያሬድ (ድጓ ዘዘወትር ገጽ 464)
💥 በመኾኑም በቅዱስ ያሬድ ድንቅ ምስጋና ዓለም እስኪያልፍ ድረስ የክርስቶስን ዕርገት በቤተ ክርስቲያናችን ይሰበካል፡፡
💥 መልካም የአምላካችን የክርስቶስ የዕርገት በዓል ይኹንላችኹ።
❤184👍26👏8😁7
💥❖ለአብርሃም የተገለጠ ምስጢረ ሥላሴ ❖💥
✍ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥❖ “በቀትርም ጊዜ እርሱ በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በመምሬ የአድባር ዛፍ ተገለጠለት።”
— ዘፍጥረት 18፥1
👉 መምሬ በኬብሮን ያለች ሲኾን አብርሃም ለእግዚአብሔር መሠዊያ የሠራባት የተቀደሰች ቦታ ናት (ዘፍ 13:18)
👉 በዕብራይስጥ "መምሬ" ማለት ጥንካሬ ወይም የሰባ ማለት ነው። ይኽም የተትረፈረፈ እና መለኮታዊ ጸጋን ያመለክታል።
💥❖ የተገለጡለት ሰዓቱ ቀትር (ስድስት) ሰዓት በዕንጨት ሥር በሰው አምሳል መኾኑ ቀደምት ሊቃውንት ሲያራቅቁት በአብ፣ በመንፈስ ቅዱስ፣ በራሱም ፈቃድ ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል ወልድ ዘመኑ ሲፈጸም የአብርሃምን ባሕርይ ተዋሕዶ ፍጹም ሰው ኾኖ በስድስት ሰዓት በዕንጨት መስቀል ላይ ለቤዛ ዓለም የሚሰቀል መኾኑን ያጠይቃል ይላሉ፨
💥❖ ይኽነን ይዞ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በሕማማት ሰላምታው፦
"ለአብርሃም አብ ቀዳሚ ዘአስተርአይኮ ክርስቶስ
ቀትረ ታሕተ ዕፀ ድርስ
ተሰቀልከ ከመ እቡስ ስብሐት ለከ"
(ምስጋና የተገባኽ ጌታ ድርስ በሚባል የዛፍ ዐይነት ሥር በስድስት ሰዓት ለአባታችን አብርሃም ቀድሞ የተገለጥኽለት ክርስቶስ ሆይ እንደ በደለኛ ተሰቀልኽ) ይላል፨
💥 ሌላው ቀትር (እኩለ ቀን) የፀሐይ ግለት ይበረታል። እግዚአብሔርም በእሳት እንደተፈተነ ወርቅ እምነቱ ተፈትኖ የጠራውን አብርሃምን የጎበኘው በቀዝቃዛ ጊዜ ሳይኾን እንደ እሳት በሚያቃጥል ሰዓት ነው።
👉 ያልታዘዘው አዳምን በሠርክ ሰዓት እግዚአብሔር በአትክልት ስፍራ ሊጎበኘው ሲመጣ በዛፍ ውስጥ ተደበቀ። ታዛዡ አብርሃም ግን በቀትር (ከቀኑ 6 ሰዓት) በዛፍ አጠገብ ሳለ እግዚአብሔር ወደ ርሱ ሲመጣ ቢያየው ለመቀበል ሮጠ።
💥 እኩለ ቀን ፀሐይ በአናታችን ትክክል ከፍተኛው ልዕልናዊ ቦታዋ ላይ የምትደርስበት ሰዓት ሲኾን ሙሉ ብርሃን ሰጥታ ጥላን የምታባርርበት ሰዓት ላይ የክሕደት ጥላ ባላጣላበት አማናዊ ፀሐይ ሥሉስ ቅዱስ ተገልጸውለታል።
👉 በሐዲስ ኪዳንም በተመሳሳይ መልኩ ቅዱስ ጳውሎስን የመለሰው ከሰማይ የታየው ብርሃን በስድስት ሰዓት (ቀትር) ላይ ነበረ (የሐዋ 22:6)።
✍️ “ዐይኑንም አነሣና እነሆ፥ ሦስት ሰዎች በፊቱ ቆመው አየ፤ ባያቸውም ጊዜ ሊቀበላቸው ከድንኳኑ ደጃፍ ተነሥቶ ሮጠ፥ ወደ ምድርም ሰገደ”
— ዘፍጥረት 18፥2
👉 ሥላሴ በአምሳለ ዕደው ቆመው ቢያይ መሮጡ ድንቅ ነው። አርጅቶ 100 ዓመት መልቶት ከግዝረት ቁስል ያገገመ ሲኾን እስኪቀርቡ ሳይጠብቅ መሮጡ የመንፈስ ጥንካሬው፣ እንግዳ ማፍቀሩ፣ በመንፈስ የነቃ መኾኑን ያመለክታል (ዘፍጥረት 17፡24)።
👉 በዚኽ ደጉ አብርሃም አምላክን በመውደድ ፈጣን መንፈሳዊ ሩጫን ለሚሮጡ አብነት ነው።
✍️ “ሳበኝ፥ ከአንተም በኋላ እንሮጣለን፤ ንጉሡ ወደ ቤቱ አገባኝ” እንዲል
— መሓልይ. 1፥4
💥❖ ስላቀረበው ስግደት ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ሰለዚኽ ነገር በድጓው ላይ፦
"ዮም አብርሃም ሰገደ ለፈጣሪሁ
ሶበ ነጸረ ዋሕደ በሥላሴሁ"
(ዋሕደ ባሕርይ የኾነ እግዚአብሔርን በአካላዊ ሦስትነቱ ባየው ጊዜ አብርሃም ዛሬ ለፈጣሪው ሰገደ) ይላል፨
💥❖ ከዚኽ በኋላ "አቤቱ በፊትኽስ ሞገስ አግኝቼ እንደኾነ ባሪያኽን አትለፈኝ ብዬ እለምናለኍ፤ ጥቂት ውሃ ይምጣላችኍ፤ እግራችኹን ታጠቡ፤ ከዚኽችም ዛፍ በታች ዕረፉ…" በማለት ተናግሯል፡፡
✔"በፊትኽ ሞገስን አግኝቼ" ብሎ አንድነታቸውን፤
✔"ውሃ ይምጣላችኍ፣ ዕረፉ፣ ትኼዳላችሁ" ብሎ የሦስትነታቸውን ምስጢር ገልጾአል፡፡
💥❖ ይኽቺ አንድነቱ ሦስትነቱን ሳይጠቀልለው ሦስትነቱ አንድነቱን ሳይከፍለው በአንድነት በሦስትነት የሚመሰገን እግዚአብሔር የተገለጠባት ዛፍ፤ አንድነት ሦስትነት በጐላ በተረዳ ነገር የታወቀባት ከሦስቱ አካል አንዱ አካል እግዚአብሔር ወልድን በድንግልና የወለደች የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ መኾኗን፤ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ እንዚራ ስብሐት መጽሐፉ ላይ፦
"አንቲ ውእቱ ዕፀ ድርስ ዘለአብርሃም በርስአኒሁ
ዘብኪ አጽለለ እግዚአብሔር በሥላሴሁ"
(ለአብርሃው በእርጅናው ወቅት፤ እግዚአብሔርን በሦስትነት ያስጠለለብሽ የወይራ ዕንጨት አንቺ ነሽ) በማለት ሲገልጥ፦
💥❖ ዳግመኛም በዚኹ መጽሐፉ፡-
"እንቲ ውእቱ ዕፀት ዘነበርኪ ጥቃ ኀይመት፣
ዘብኪ አጽለሉ ሠለስቱ አጋዕዝት"
(ባንቺ ሦስቱ ጌቶች (ሥላሴ) የተጠለሉብሽ በድንኳን አጠገብ የቆምሽ ዕንጨት አንቺ ነሽ) በማለት በአንድነቱ ምንታዌ (ኹለትነት)፣ በሦስትነቱ ርባዔ (አራትነት) ለሌለበት አምላክ የሦስትነቱ የአንድነቱ ምስጢር መገለጫ የሥላሴ ማደሪያ መኾኗን መስክሯል፡፡
💥❖ ከዚኽም ምስጢር የተነሣ አብርሃምም ሳራን “ሦስት መስፈሪያ የተሠለቀ ዱቄት ፈጥነሽ አዘጋጂ፤ ለውሺውም እንጎቻም አድርጊ” በማለት የተገለጸለትን የሦስትነት የአንድነት ምስጢርን አጒልቶ ተናግሯል፡፡
💥❖ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ይኽነን ይዞ በሕማማት ሰላምታው ላይ፦
"ግናይ ለክሙ ሥሉስ ቅዱስ ነገሥተ ሰብዐቱ አብያት
እለ በላዕክሙ ውሣጤ ኀይመት
አሐደ ኅብስተ ትሥልስት"
(ከሦስት መስፈሪያ ዶቄት የተጋገረ አንድነት ያለው ኅብስትን በድንኳን ውስጥ የተመገባችሁ የሰባት ቤቶች (ሰማያት) ነገሥት ሆይ ለእናንተ መገዛት (ምስጋና) ይገባል) ይላል፨
💥❖ አብርሃምም በደስታ ኾኖ መዐር፣ ወተት፣ ያዘጋጀውን ጥጃ አመጣላቸው፤ እነርሱም ደስ ይበለው ብለው በግብር አምላካዊ ተመግበዋል፤ መላእክት ሎጥ ቤት፤ ቅዱስ ሩፋኤል ጦቢት ቤት ተመገበ የተባለው አንድ ነው፤ እሳት ቅቤ በላ እንደማለት ብቻ ነው፨
💥❖ ይኸውም ወተትና መዐር መመገባቸው ኦሪትን ወንጌልን መሥራታቸውን ሲያጠይቁ ነው፤ መዐር የኦሪት፤ ቅቤ የወንጌል ምሳሌ ነው፨ ማር ለጊዜው ሲይዝ የሚለቅ አይመስልም፤ ግን ይለቃል ኦሪትም ስትሠራ የምታልፍ አትመስልም ነበር ግን በኽዋላ ዐልፋለች፨ ወተት የወንጌል ምሳሌ ነው፤ ይኽ ወተት ለጊዜው የሚለቅቅ ይመስላል በኽዋላ ሲያጥቡት አይለቅም ወንጌልም ለጊዜው ስትሠራ የምታልፍ ትመስል ነበር፤ በኽዋላ ግን ጸንታ የምትኖር ኾናለችና በማለት መተርጉማን ያራቅቁታል፡
💥 ከሦስቱ አንዱ እግዚአብሔር ወልድ አብርሃምን "የዛሬ ዓመት እንደዛሬው ጊዜ ወደ አንተ በእውነት እመለሳለኍ፤ ሚስትኽ ሳራም ልጅን ታገኛለች" በማለት ዘመኑ ሲፈጸም እግዚአብሔር ወልድ ከቤተ አብርሃም ከተገኘች ከእመቤታችን የመወለዱንና፤ በሳራ የተመሰለች ወንጌል ምእመናንን እንደምታስገኝ በምስጢር ገልጾለታል፤ ቅዱስ ጳውሎስም አካላዊ ቃል በሰጠው ተስፋ መሠረት ከነገደ አብርሃም የመወለዱን ነገር ለዕብራውያን ሰዎች በጻፈው መልእክቱ ላይ "በሕይወታቸው ኹሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ኹሉ ነጻ እንዲያወጣ፤ በሥጋና በደም እንዲኹም ተካፈለ፣ የአብርሃምን ዘር ይዞአል እንጂ የያዘው የመላእክትን አይደለም" በማለት ገልጾታል (ዕብ ፪፥፲፭-፲፮)፡፡
💥❖ ይኽቺ ሥላሴ የገቡባት ኀይመተ አብርሃም (የአብርሃም ድንኳን) የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት፤ ይኸውም ሥላሴ ወደ አብርሃም ድንኳን እንደገቡ ኹሉ፤ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያምም፤ አብ ለአጽንኦ፣ መንፈስ ቅዱስ ለአንጽሖ፣ ወልድ በተለየ አካሉ ሥጋን ለመዋሐድ ዐድረዋል (ሉቃ ፩፥፴፭)፤ በመኾኑም አማናዊቷ የሥላሴ ማደሪያ የአብርሃም ድንኳን እመቤታችን ብቻ ናት፡፡
✍ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥❖ “በቀትርም ጊዜ እርሱ በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በመምሬ የአድባር ዛፍ ተገለጠለት።”
— ዘፍጥረት 18፥1
👉 መምሬ በኬብሮን ያለች ሲኾን አብርሃም ለእግዚአብሔር መሠዊያ የሠራባት የተቀደሰች ቦታ ናት (ዘፍ 13:18)
👉 በዕብራይስጥ "መምሬ" ማለት ጥንካሬ ወይም የሰባ ማለት ነው። ይኽም የተትረፈረፈ እና መለኮታዊ ጸጋን ያመለክታል።
💥❖ የተገለጡለት ሰዓቱ ቀትር (ስድስት) ሰዓት በዕንጨት ሥር በሰው አምሳል መኾኑ ቀደምት ሊቃውንት ሲያራቅቁት በአብ፣ በመንፈስ ቅዱስ፣ በራሱም ፈቃድ ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል ወልድ ዘመኑ ሲፈጸም የአብርሃምን ባሕርይ ተዋሕዶ ፍጹም ሰው ኾኖ በስድስት ሰዓት በዕንጨት መስቀል ላይ ለቤዛ ዓለም የሚሰቀል መኾኑን ያጠይቃል ይላሉ፨
💥❖ ይኽነን ይዞ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በሕማማት ሰላምታው፦
"ለአብርሃም አብ ቀዳሚ ዘአስተርአይኮ ክርስቶስ
ቀትረ ታሕተ ዕፀ ድርስ
ተሰቀልከ ከመ እቡስ ስብሐት ለከ"
(ምስጋና የተገባኽ ጌታ ድርስ በሚባል የዛፍ ዐይነት ሥር በስድስት ሰዓት ለአባታችን አብርሃም ቀድሞ የተገለጥኽለት ክርስቶስ ሆይ እንደ በደለኛ ተሰቀልኽ) ይላል፨
💥 ሌላው ቀትር (እኩለ ቀን) የፀሐይ ግለት ይበረታል። እግዚአብሔርም በእሳት እንደተፈተነ ወርቅ እምነቱ ተፈትኖ የጠራውን አብርሃምን የጎበኘው በቀዝቃዛ ጊዜ ሳይኾን እንደ እሳት በሚያቃጥል ሰዓት ነው።
👉 ያልታዘዘው አዳምን በሠርክ ሰዓት እግዚአብሔር በአትክልት ስፍራ ሊጎበኘው ሲመጣ በዛፍ ውስጥ ተደበቀ። ታዛዡ አብርሃም ግን በቀትር (ከቀኑ 6 ሰዓት) በዛፍ አጠገብ ሳለ እግዚአብሔር ወደ ርሱ ሲመጣ ቢያየው ለመቀበል ሮጠ።
💥 እኩለ ቀን ፀሐይ በአናታችን ትክክል ከፍተኛው ልዕልናዊ ቦታዋ ላይ የምትደርስበት ሰዓት ሲኾን ሙሉ ብርሃን ሰጥታ ጥላን የምታባርርበት ሰዓት ላይ የክሕደት ጥላ ባላጣላበት አማናዊ ፀሐይ ሥሉስ ቅዱስ ተገልጸውለታል።
👉 በሐዲስ ኪዳንም በተመሳሳይ መልኩ ቅዱስ ጳውሎስን የመለሰው ከሰማይ የታየው ብርሃን በስድስት ሰዓት (ቀትር) ላይ ነበረ (የሐዋ 22:6)።
✍️ “ዐይኑንም አነሣና እነሆ፥ ሦስት ሰዎች በፊቱ ቆመው አየ፤ ባያቸውም ጊዜ ሊቀበላቸው ከድንኳኑ ደጃፍ ተነሥቶ ሮጠ፥ ወደ ምድርም ሰገደ”
— ዘፍጥረት 18፥2
👉 ሥላሴ በአምሳለ ዕደው ቆመው ቢያይ መሮጡ ድንቅ ነው። አርጅቶ 100 ዓመት መልቶት ከግዝረት ቁስል ያገገመ ሲኾን እስኪቀርቡ ሳይጠብቅ መሮጡ የመንፈስ ጥንካሬው፣ እንግዳ ማፍቀሩ፣ በመንፈስ የነቃ መኾኑን ያመለክታል (ዘፍጥረት 17፡24)።
👉 በዚኽ ደጉ አብርሃም አምላክን በመውደድ ፈጣን መንፈሳዊ ሩጫን ለሚሮጡ አብነት ነው።
✍️ “ሳበኝ፥ ከአንተም በኋላ እንሮጣለን፤ ንጉሡ ወደ ቤቱ አገባኝ” እንዲል
— መሓልይ. 1፥4
💥❖ ስላቀረበው ስግደት ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ሰለዚኽ ነገር በድጓው ላይ፦
"ዮም አብርሃም ሰገደ ለፈጣሪሁ
ሶበ ነጸረ ዋሕደ በሥላሴሁ"
(ዋሕደ ባሕርይ የኾነ እግዚአብሔርን በአካላዊ ሦስትነቱ ባየው ጊዜ አብርሃም ዛሬ ለፈጣሪው ሰገደ) ይላል፨
💥❖ ከዚኽ በኋላ "አቤቱ በፊትኽስ ሞገስ አግኝቼ እንደኾነ ባሪያኽን አትለፈኝ ብዬ እለምናለኍ፤ ጥቂት ውሃ ይምጣላችኍ፤ እግራችኹን ታጠቡ፤ ከዚኽችም ዛፍ በታች ዕረፉ…" በማለት ተናግሯል፡፡
✔"በፊትኽ ሞገስን አግኝቼ" ብሎ አንድነታቸውን፤
✔"ውሃ ይምጣላችኍ፣ ዕረፉ፣ ትኼዳላችሁ" ብሎ የሦስትነታቸውን ምስጢር ገልጾአል፡፡
💥❖ ይኽቺ አንድነቱ ሦስትነቱን ሳይጠቀልለው ሦስትነቱ አንድነቱን ሳይከፍለው በአንድነት በሦስትነት የሚመሰገን እግዚአብሔር የተገለጠባት ዛፍ፤ አንድነት ሦስትነት በጐላ በተረዳ ነገር የታወቀባት ከሦስቱ አካል አንዱ አካል እግዚአብሔር ወልድን በድንግልና የወለደች የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ መኾኗን፤ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ እንዚራ ስብሐት መጽሐፉ ላይ፦
"አንቲ ውእቱ ዕፀ ድርስ ዘለአብርሃም በርስአኒሁ
ዘብኪ አጽለለ እግዚአብሔር በሥላሴሁ"
(ለአብርሃው በእርጅናው ወቅት፤ እግዚአብሔርን በሦስትነት ያስጠለለብሽ የወይራ ዕንጨት አንቺ ነሽ) በማለት ሲገልጥ፦
💥❖ ዳግመኛም በዚኹ መጽሐፉ፡-
"እንቲ ውእቱ ዕፀት ዘነበርኪ ጥቃ ኀይመት፣
ዘብኪ አጽለሉ ሠለስቱ አጋዕዝት"
(ባንቺ ሦስቱ ጌቶች (ሥላሴ) የተጠለሉብሽ በድንኳን አጠገብ የቆምሽ ዕንጨት አንቺ ነሽ) በማለት በአንድነቱ ምንታዌ (ኹለትነት)፣ በሦስትነቱ ርባዔ (አራትነት) ለሌለበት አምላክ የሦስትነቱ የአንድነቱ ምስጢር መገለጫ የሥላሴ ማደሪያ መኾኗን መስክሯል፡፡
💥❖ ከዚኽም ምስጢር የተነሣ አብርሃምም ሳራን “ሦስት መስፈሪያ የተሠለቀ ዱቄት ፈጥነሽ አዘጋጂ፤ ለውሺውም እንጎቻም አድርጊ” በማለት የተገለጸለትን የሦስትነት የአንድነት ምስጢርን አጒልቶ ተናግሯል፡፡
💥❖ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ይኽነን ይዞ በሕማማት ሰላምታው ላይ፦
"ግናይ ለክሙ ሥሉስ ቅዱስ ነገሥተ ሰብዐቱ አብያት
እለ በላዕክሙ ውሣጤ ኀይመት
አሐደ ኅብስተ ትሥልስት"
(ከሦስት መስፈሪያ ዶቄት የተጋገረ አንድነት ያለው ኅብስትን በድንኳን ውስጥ የተመገባችሁ የሰባት ቤቶች (ሰማያት) ነገሥት ሆይ ለእናንተ መገዛት (ምስጋና) ይገባል) ይላል፨
💥❖ አብርሃምም በደስታ ኾኖ መዐር፣ ወተት፣ ያዘጋጀውን ጥጃ አመጣላቸው፤ እነርሱም ደስ ይበለው ብለው በግብር አምላካዊ ተመግበዋል፤ መላእክት ሎጥ ቤት፤ ቅዱስ ሩፋኤል ጦቢት ቤት ተመገበ የተባለው አንድ ነው፤ እሳት ቅቤ በላ እንደማለት ብቻ ነው፨
💥❖ ይኸውም ወተትና መዐር መመገባቸው ኦሪትን ወንጌልን መሥራታቸውን ሲያጠይቁ ነው፤ መዐር የኦሪት፤ ቅቤ የወንጌል ምሳሌ ነው፨ ማር ለጊዜው ሲይዝ የሚለቅ አይመስልም፤ ግን ይለቃል ኦሪትም ስትሠራ የምታልፍ አትመስልም ነበር ግን በኽዋላ ዐልፋለች፨ ወተት የወንጌል ምሳሌ ነው፤ ይኽ ወተት ለጊዜው የሚለቅቅ ይመስላል በኽዋላ ሲያጥቡት አይለቅም ወንጌልም ለጊዜው ስትሠራ የምታልፍ ትመስል ነበር፤ በኽዋላ ግን ጸንታ የምትኖር ኾናለችና በማለት መተርጉማን ያራቅቁታል፡
💥 ከሦስቱ አንዱ እግዚአብሔር ወልድ አብርሃምን "የዛሬ ዓመት እንደዛሬው ጊዜ ወደ አንተ በእውነት እመለሳለኍ፤ ሚስትኽ ሳራም ልጅን ታገኛለች" በማለት ዘመኑ ሲፈጸም እግዚአብሔር ወልድ ከቤተ አብርሃም ከተገኘች ከእመቤታችን የመወለዱንና፤ በሳራ የተመሰለች ወንጌል ምእመናንን እንደምታስገኝ በምስጢር ገልጾለታል፤ ቅዱስ ጳውሎስም አካላዊ ቃል በሰጠው ተስፋ መሠረት ከነገደ አብርሃም የመወለዱን ነገር ለዕብራውያን ሰዎች በጻፈው መልእክቱ ላይ "በሕይወታቸው ኹሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ኹሉ ነጻ እንዲያወጣ፤ በሥጋና በደም እንዲኹም ተካፈለ፣ የአብርሃምን ዘር ይዞአል እንጂ የያዘው የመላእክትን አይደለም" በማለት ገልጾታል (ዕብ ፪፥፲፭-፲፮)፡፡
💥❖ ይኽቺ ሥላሴ የገቡባት ኀይመተ አብርሃም (የአብርሃም ድንኳን) የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት፤ ይኸውም ሥላሴ ወደ አብርሃም ድንኳን እንደገቡ ኹሉ፤ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያምም፤ አብ ለአጽንኦ፣ መንፈስ ቅዱስ ለአንጽሖ፣ ወልድ በተለየ አካሉ ሥጋን ለመዋሐድ ዐድረዋል (ሉቃ ፩፥፴፭)፤ በመኾኑም አማናዊቷ የሥላሴ ማደሪያ የአብርሃም ድንኳን እመቤታችን ብቻ ናት፡፡
❤29
💥❖ ሊቁም በነገረ ማርያም ይኽነን ምስጢር ሲገልጽ "ወይእቲ ኀይመት ትትሜሰል በድንግል ወዕደው አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ እሙንቱ፤ አብ አጽንኣ፣ ወወልድ ተሰብአ እምኔሃ፣ ወመንፈስ ቅዱስ ቀደሳ ከመ ትጹር አምላከ በከርሣ" (ያቺ ድንኳንም በድንግል ትመሰላለች፤ ሰዎቹም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ናቸው፤ አብ አጸናት፣ ወልድም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ሰው ኾነ፣ መንፈስ ቅዱስ አካላዊ ቃል አምላክን ትሸከም ዘንድ ለያት) በማለት ተርጉሞታል፨
💥❖ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ በሰላምታ መጽሐፉ ላይ መጽሐፉ፦ "ኀይመተ አብርሃም አብ ሰላም ለኪ፤
ዘኮንኪ ከመ ተድባብ ሰላም ለኪ"
(እንደ ጥላ የኾንሽ የአባት አብርሃም ድንኳን ሰላምታ ይገባሻል) በማለት አመስግኗታል፡፡
💥❖ ይኽ አብርሃም የተቀበለውን የተስፋ ቃል ሊቃውንት ሲተረጒሙት "ኦ አኃውየ በይነ መኑ እንከ ዘይቤ እግዚአብሔር ለአብርሃም አመ ከመ ዮም እገብእ ኀቤከ አኮኑ እግዝእትነ ማርያም ይእቲ ዘወፅአት እምነ ሥርው ለአዳም ..." (ወንድሞቼ ሆይ እግዚአብሔር አብርሃምን እንደዛሬው ኹሉ ወደአንተ ተመልሼ እመጣለኍ ያለው ስለማን ይመስላችኋል? ከአዳም ሥር ወጥታ፤ ከኖኅ አብራክ ተገኝታ፤ ወደ አብርሃም አብራክ ልትከፈል፤ ሥላሴ በአብርሃም ቤት በእንግድነት ተገኝተው፤ ከአብርሃም ዘር ከእመቤታችን የእግዚአብሔርን ልጅ ሰው መኾን ስለርሷ የተናገሩላት እመቤታችን ድንግል ማርያም አይደለችምን፤ ስለዚኽ እግዚአብሔር ስለ እመቤታችን ጥንታዊ የልደቷን አመጣጥ በየጊዜው ምልክት እንደሚሰጥ ልብ አድርገን ማስተዋል ይገባናል) በማለት አብራርተው ተርጒመዋል፡፡
💥❖ ሊቁ አባ ሕርያስቆስም በቅዳሴው በቊ ፴፪ ላይ "ተናግዶቱ ለአብርሃም" (የአብርሃም እንግድነቱ አንቺ ነሽ) በማለት ምስጢሩን ጠቅልሎ የገለጠውን ይኽነን ድንቅ ምስጢር፤ ሊቁ በነገረ ማርያም ላይ በስፋትና በጥልቀት፡-
♥ "ወዓዲ ኀይመት ዘአብርሃም ዘውስቴታ ተአንገደ እግዚአብሔር አኮ ከማሁ ዘኮነቶ ምጽላለ በእንተ ምዕር አላ ኮነቶ እመ ወተከድነ ሥጋሃ ወረሰዮ አሐደ ምስለ መለኮቱ"
(ዳግመኛም እግዚአብሔር (በሦስትነት) በዕንግድነት ያረፈባት የአብርሃም ድንኳን አንቺ ነሽ፤ ለጥቂት ጊዜ ብቻ መጠለያን፣ መጠጊያን የኾነቺው አይደለም፤ እናትን ኾናው ሥጋዋን ተዋሕዶ ከመለኮቱ አንድ አደረገው እንጂ) በማለት በአብርሃም ድንኳን ብትመሰልም እንኳ ክብሯ ከፍ ያለ፤ ለዘላለም የአምላክ ማረፊያውና እናቱ መኾኗን አብራርቶ ገልጧል፡፡
💥❖ ሊቅነትን ከንግሥና ጋር ያስተባበረው ዐጼ ዘርዐ ያዕቆብ በመጽሐፈ ሥላሴ መጽሐፉ ላይ፦
👉 "ኦ ብእሲ ዘትትከሓድ አይኑ ዕለት ለአግዚአብሔር ሰገዱ ሎቱ ምስለ መላእክቲሁ በዕሪና እምነ ኩሉ ፍጡራኒሁ..."
(ሥላሴን የምትክድ አንተ ሰው ሆይ ከፍጡሮች ወገን በመላ እግዚአብሔርን ከመላእክቱ ጋር በአንዲት ዕሪና የሰገዱለት በማናቸው ዕለት ነው? በማናቸው ዕለት እግዚአብሔር ከፈጠራቸው መላእክቱ ጋር ተካክሎ እግሩን ታጠበ? በማናቸው ዕለት በሰው መጠለያ በታች ከፈጠራቸው መላእክት ጋር ተካክሎ ተጠለለ? በማናቸው ዕለት ከፈጠራቸው መላእክት ጋር ተካክሎ እግዚአብሔር በላ? በማናቸው ዕለት ከአዳም ልጆች ወገን ሰው ወደ ፈጣሪው በለመነ ጊዜ መላእክቱ ከፈጣሪያቸው ከእግዚአብሔር ጋር ተካክለው እንዲኽ አድርግ መቼ አሉ? አንተ ሥላሴን የካድኽ ከሓዲ ፍጡራን መላእክትን ፈጣሪ ከኾኑ ከሥላሴ ጋር በመተካከል እንዲሰገድላቸው ለምን ታመጣቸዋለኽ? ፈጡራን መላእክትን ፈጣሪ ከኾኑ ከሥላሴ ጋር ተካክለው በአብርሃም ቤት እንደተጠለሉ፤ እግራቸውን እንደታጠቡ፤ ዐብረው እንደበሉ አድርገኽ ለምን ታስተካክላለኽ? አንተ ከእኛ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን አንድነት የኾንኽ ክርስቲያን አንዱ እግዚአብሔር ነው፤ ኹለቱ መላእክት ናቸው አትበል) በማለት አስፍቶ ይጽፋል፨
✔❖በቤተ አብርሃም የገቡ ሥሉስ ቅዱስ ሆይ ዘወትር በቤተ ልቡናችን ውስጥ ግቡልን፨❖✔
[ለበለጠ ምስጢር "መልክአ ሥላሴ ንባቡና ትርጓሜው" መጽሐፌን ያንብቡ]፨
✍ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥❖ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ በሰላምታ መጽሐፉ ላይ መጽሐፉ፦ "ኀይመተ አብርሃም አብ ሰላም ለኪ፤
ዘኮንኪ ከመ ተድባብ ሰላም ለኪ"
(እንደ ጥላ የኾንሽ የአባት አብርሃም ድንኳን ሰላምታ ይገባሻል) በማለት አመስግኗታል፡፡
💥❖ ይኽ አብርሃም የተቀበለውን የተስፋ ቃል ሊቃውንት ሲተረጒሙት "ኦ አኃውየ በይነ መኑ እንከ ዘይቤ እግዚአብሔር ለአብርሃም አመ ከመ ዮም እገብእ ኀቤከ አኮኑ እግዝእትነ ማርያም ይእቲ ዘወፅአት እምነ ሥርው ለአዳም ..." (ወንድሞቼ ሆይ እግዚአብሔር አብርሃምን እንደዛሬው ኹሉ ወደአንተ ተመልሼ እመጣለኍ ያለው ስለማን ይመስላችኋል? ከአዳም ሥር ወጥታ፤ ከኖኅ አብራክ ተገኝታ፤ ወደ አብርሃም አብራክ ልትከፈል፤ ሥላሴ በአብርሃም ቤት በእንግድነት ተገኝተው፤ ከአብርሃም ዘር ከእመቤታችን የእግዚአብሔርን ልጅ ሰው መኾን ስለርሷ የተናገሩላት እመቤታችን ድንግል ማርያም አይደለችምን፤ ስለዚኽ እግዚአብሔር ስለ እመቤታችን ጥንታዊ የልደቷን አመጣጥ በየጊዜው ምልክት እንደሚሰጥ ልብ አድርገን ማስተዋል ይገባናል) በማለት አብራርተው ተርጒመዋል፡፡
💥❖ ሊቁ አባ ሕርያስቆስም በቅዳሴው በቊ ፴፪ ላይ "ተናግዶቱ ለአብርሃም" (የአብርሃም እንግድነቱ አንቺ ነሽ) በማለት ምስጢሩን ጠቅልሎ የገለጠውን ይኽነን ድንቅ ምስጢር፤ ሊቁ በነገረ ማርያም ላይ በስፋትና በጥልቀት፡-
♥ "ወዓዲ ኀይመት ዘአብርሃም ዘውስቴታ ተአንገደ እግዚአብሔር አኮ ከማሁ ዘኮነቶ ምጽላለ በእንተ ምዕር አላ ኮነቶ እመ ወተከድነ ሥጋሃ ወረሰዮ አሐደ ምስለ መለኮቱ"
(ዳግመኛም እግዚአብሔር (በሦስትነት) በዕንግድነት ያረፈባት የአብርሃም ድንኳን አንቺ ነሽ፤ ለጥቂት ጊዜ ብቻ መጠለያን፣ መጠጊያን የኾነቺው አይደለም፤ እናትን ኾናው ሥጋዋን ተዋሕዶ ከመለኮቱ አንድ አደረገው እንጂ) በማለት በአብርሃም ድንኳን ብትመሰልም እንኳ ክብሯ ከፍ ያለ፤ ለዘላለም የአምላክ ማረፊያውና እናቱ መኾኗን አብራርቶ ገልጧል፡፡
💥❖ ሊቅነትን ከንግሥና ጋር ያስተባበረው ዐጼ ዘርዐ ያዕቆብ በመጽሐፈ ሥላሴ መጽሐፉ ላይ፦
👉 "ኦ ብእሲ ዘትትከሓድ አይኑ ዕለት ለአግዚአብሔር ሰገዱ ሎቱ ምስለ መላእክቲሁ በዕሪና እምነ ኩሉ ፍጡራኒሁ..."
(ሥላሴን የምትክድ አንተ ሰው ሆይ ከፍጡሮች ወገን በመላ እግዚአብሔርን ከመላእክቱ ጋር በአንዲት ዕሪና የሰገዱለት በማናቸው ዕለት ነው? በማናቸው ዕለት እግዚአብሔር ከፈጠራቸው መላእክቱ ጋር ተካክሎ እግሩን ታጠበ? በማናቸው ዕለት በሰው መጠለያ በታች ከፈጠራቸው መላእክት ጋር ተካክሎ ተጠለለ? በማናቸው ዕለት ከፈጠራቸው መላእክት ጋር ተካክሎ እግዚአብሔር በላ? በማናቸው ዕለት ከአዳም ልጆች ወገን ሰው ወደ ፈጣሪው በለመነ ጊዜ መላእክቱ ከፈጣሪያቸው ከእግዚአብሔር ጋር ተካክለው እንዲኽ አድርግ መቼ አሉ? አንተ ሥላሴን የካድኽ ከሓዲ ፍጡራን መላእክትን ፈጣሪ ከኾኑ ከሥላሴ ጋር በመተካከል እንዲሰገድላቸው ለምን ታመጣቸዋለኽ? ፈጡራን መላእክትን ፈጣሪ ከኾኑ ከሥላሴ ጋር ተካክለው በአብርሃም ቤት እንደተጠለሉ፤ እግራቸውን እንደታጠቡ፤ ዐብረው እንደበሉ አድርገኽ ለምን ታስተካክላለኽ? አንተ ከእኛ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን አንድነት የኾንኽ ክርስቲያን አንዱ እግዚአብሔር ነው፤ ኹለቱ መላእክት ናቸው አትበል) በማለት አስፍቶ ይጽፋል፨
✔❖በቤተ አብርሃም የገቡ ሥሉስ ቅዱስ ሆይ ዘወትር በቤተ ልቡናችን ውስጥ ግቡልን፨❖✔
[ለበለጠ ምስጢር "መልክአ ሥላሴ ንባቡና ትርጓሜው" መጽሐፌን ያንብቡ]፨
✍ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
❤81👍13🔥3