🌓አራቱ ተከታታይ የሰማይ ክስተቶች መንፈሳዊ አምሳል🌒
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
🌟 በሉቃስ 21፡25 -28 ላይ ✍️ “በፀሐይና በጨረቃም በከዋክብትም ምልክት ይሆናል ...ይኽም ሊኾን ሲጀምር ቤዛችኹ ቀርቦአልና አሻቅባችኹ ራሳችሁን አንሡ።”
በማለት ጌታችን እንዳስተማረ እነዚኽ ሰማያዊ አካላት በየጊዜው የሚያሳዩት ታላላቅ መንፈሳዊ ምልክት አለና በሰማይ ላይ በተከታታይ ስለታዩት አራት ታላላቅ መንፈሳዊ የጊዜያችን ምልክቶች በስሱ ለማለት ወደድኊ፡፡

💥 በጳጒሜን 2/ 2017 ዓ.ም. “ርኅወተ ሰማይ” (የሰማይ መከፈት) በሚደረግበት በዕለተ እሑድ ምሽት በሑት (ዓሣዎች) (ፓይሲስ) መናዝል ውስጥ የ2017 ዓ.ም. የዓመቱ የመጨረሻዋ የሙሉ ጨረቃ ዕለት ታላቅ የደም ጨረቃ (ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ) ተከናውኖ ኹላችንም በዐይናችን ያየንበት ድንቅ ዕለት ነበረ፡፡

💥 ፀሓይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብትን እግዚአብሔር ከተፈጠረበት ዋና ዓላማ የመዠመሪያው ለምልክት ነውና “በርኅወተ ሰማይ” (በሰማይ መከፈት) ዕለት መከናወኑ ግጥጥሞሽ ሳይኾን ሥርዓት ነው።
☄️ በማጠናቀቂያ የጳጉሜን ወር ዳግመኛም በመናዝል ማጠቃለያ በፓይሲስ (ሑት - ዓሣዎች) ውስጥ የተከናወነ የደም ጨረቃ በፍጻሜው ጊዜ ለዓሣዎች (የሰው) ልጆች ሕይወት የፈሰሰውን የክርስቶስን የመሥዋዕት ደምና በዕለቱ የጨረቃን ደም መምሰል እንድናስታውስ በሚገባ ያደርገናል።

☄️ በዓሉም የቅዱስ ሩፋኤል ከመኾኑ ጋር ተያይዞ "ሩፋ" ማለት "ፈውስ" ኤል "እግዚአብሔር" ነውና አቅንተው ለተማፀኑ ፈውሰ እግዚአብሔር ለተማፀኑ ኹሉ የተሰጠበት ዕለት ነው።

💥 ሑት (ዓሣ - ፓይሲስ) ብዙ ምስጢር በመያዙ በመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ኹሉ ዋና መግባቢያ ነበረ፡፡
🌟 “ዓሣ” ኢክተስ ΙΧΘΥΣ (Ichthys) ሲባል ፍቺውም በምሕጻረ ቃል “ኢየሱስ ክርስቶስ፣ የእግዚአብሔር ልጅ፣ አዳኝ” ማለት ነበረ።

☄️ በተመሳሳይ የውሃ ጠባይዕ በኾነው በዓሣዎቹ መናዝል ቀይ የደም ጨረቃ በዚኽ ዕለት ሲታይ ለመጀመሪያ ጊዜም በግብጽ በዐባይ ውሃ ላይ በሙሴ በትር የተደረገው ተአምር የውሃው ደም መኾንና የዓሣዎቹ መሞት ነበረ። ተመሳሳይ ምልክት በሰማይ በታየ በኹለተኛው ቀን ጳጉሜን 4 የዐባይ ግድብ በመጠናቀቅ የኢትዮጵያ ታላቅ ዑደት ጀምሯል።
💥💥💥
🌒 እሑድ መስከረም 11/ 2018 ዓ.ም. በዐዲሱ ዓመታችን የመዠመሪያዋ ጠፍ ጨረቃ በምትውልበት ዕለት ደግሞ በደቡብ ፓሲፊክ፣ ኒውዝላንድ፣ ምሥራቅና ደቡብ አውስትራሊያ፣ አንታርክቲካ ያሉ ቀለበታማ የፀሓይ ግርዶሽ ይታያል፡፡
🌟 ፀሓይ በዚኽ ግርዶሽ ጊዜ በሰንቡላ (ድንግል - ቪርጎ) መናዝል ውስጥ በመኾን በእሳት ቀለበት 🌚 ተሞሽራ ትታያለች፡፡
☄️ በመንፈሳዊ ትርጓሜ ሰንቡላ (ቪርጎ) በቅድስት ድንግል ማርያም እና በቤተልሔም የምትመሰል ናት፡፡
🌟 በእኛ “ሰንቡላ” በዕብራይስጥ “ቤቱላህ” ትባላላች፤ ፍቺውም “ድንግል” ማለት ነው፡፡ በግሪክም “ሴሬስና ፓርቴኖስ” ስትባል ፍቺውም “ንጽሕት ብላቴና ድንግል” ማለት ነው፡፡
☄️ በዐረቢክም “አዳራህ” ሲሏት ፍቺዋም “ንጽሕት ድንግል” ማለት ነው፡፡ ይኽችን መናዝል አምላክ በሰማይ ማኖሩ የመሲሑን ከድንግል መወለድ የሚያመለክት ሕያው ምልክት ነበረ፡፡
🌟 ፀሓይ በመስከረም 10 በመስከረም 11 ዕለት በዚኽ ግርዶሽ ወቅት በዚኽች ሰንቡላ ውስጥ እንደምታበራ በዮሐንስ ራእ 12፡1 ✍️“ወአስተርአየ ተአምር ዐቢይ በውስተ ሰማይ ብእሲት እንተ ትለብስ ፀሓየ” (“ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናጽፋ ጨረቃ ከእግሮችዋ በታች ያላት በራስዋም ላይ የአሥራ ሁለት ከዋክብት አክሊል የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች።”
— ራእይ 12፥1
ያለውን ምልክቱ ያሳያል፡፡

☄️ መስከረም 10 ሲነሣ ከ33ቱ የእመቤታችን በዓላት አንዱ ነው፤ የቅድስት ድንግል ማርያም ልደትን ጳጒሜን 3 (September 8th) አብዛኞቹ የዓለማት ሀገራትና አብያተ ክርስቲያናት ያስባሉ፡፡ ሌላው መስከረም 10 ሲኾን፤ መጨረሻው ግንቦት 1 ይከበራል፡፡

🌟 በተአምሯ መቅድም ላይ “ቦ እለ ይቤሉ አመ ዐሡሩ ለመስከረም ልደታ ወንሕነሰ ንብል ጥዩቀ በከመ መሀሩነ አበዊነ ሊቃውንት አመ አሚሩ ለግንቦት ልደታ” (መስከረም ዐሥር ቀን ልደቷ ነው የሚሉም አሉ፤ እኛ ግን በተረዳ ነገር አባቶቻችን ሊቃውንት እንዳስተማሩን ልደቷን ግንቦት 1 ቀን ነው እንላለን) ይላል፡፡
💥💥💥
✍️ ሰኞ መስከረም 12/ 2018 ዓ.ም. ፀሐይ ልክ የምድር ወገብ ላይ ኾና በመላው ዓለም “ዕሪና መዓልት ወሌሊት” (ቀኑና ሌሊቱ እኩል የሚኾንበት) ቀን ሲኾን እኩሌ” (Autumn Equinox) ይባላል፡፡ ይህ ዕለት ፀሐይ የሰማያዊውን ሉል ወገብ አቋርጣ ወደ ደቡብ አቅጣጫ የምትሄድበት ጊዜ ሲሆን ፀሐይ ልክ የምድር ወገብ ላይ ሆና ቀንና ሌሊቱ እኩል የሚሆንበት ጊዜ ነው፡፡

✍️ ዲድስቅልያ የወቅቶችን መለወጫ ሲያይ “እስመ ይዔሪ መዓልት ወሌሊት አመ ዕሥራ ወኀሙሱ” (ቀንና ሌሊት በ25 ይተካከላልና) ይላል እንጂ መስከረም 12 – 14 ውስጥ ይመላለሳል፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በግእዝ መዝገበ ቃላት ገጽ 577 ላይ በደቃይቅ ቊጥር አራት ቀን ወደ ታች ወርዶ “አመ ዕሥራ ወአሚሩ” (በ21) ኹኗል፡፡ በኛም ብተት “አመ ዐሡሩ ወሠሉሱ” (በ13ኛው ዕለት) ወይም “ወረቡዑ” (በ14ኛው ዕለት) ኹኗል በማለት የቀመሩን ስልት ጽፈዋል፡፡ ይኽ መተካከል በየ182 ቀን የሚከናወን ሲኾን ይኸውም በግእዝ ፊደላት ቊጥር ስደራ ልክ ነው (26 ፊደላት x 7 = 182)፡፡
💥💥💥
✍️ ሰኞ መስከረም 12 - ረቡዕ 14/ 2018 ዓ.ም ሮሽ ሀሻናህ የቀንደ መለከት በዓል ይኾናል፡፡ “ሮሽ ማለት እራስ “ሀሻናህ” (ዐውደ ዓመት) ማለት ነው፡፡ በዕብራውያን ትውፊትና በቤዛንታይን ባሉት ኹሉ ትውፊት “ልደተ ዓለም” (ዓለም የተፈጠረበት ወር) ተብሎ ይታሰባል፡፡

🌟 እንደ አለቃ ኪዳነ ወልድ ትንታኔ ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ ድረስ ቀዳማዊ ወር ኤታኒም ነበር በኋላ ግን ከግብጽ የወጡበት ኔሣን (ሚያዝያ) ስለነበር “ዝንቱ ወርኅ ይኩንክሙ ቀዳማየ አውራኅ” (ይህ ወር የወሮች መጀመሪያ ይሁናችኊ የዓመቱም መጀመሪያ ወር ይሁናችኊ) ተብለው በእነርሱ የጥቅምትን ቅድምና ለሚያዝያ የሚያዝያን 7ተኛነት ለጥቅምት (በእኛ ለመስከረም) እንዲሰጡ ታዘው ነበር ይላሉ (ዘፀ 12፡2)።

☄️ እስራኤላውያን ከግብጽ የወጡበትን ሚያዝያን ዐዲስ ዓመታቸውን እንዲያከብሩ ቢታዘዙም ግን ዓለም የተፈጠረበትን የኤታኒም 7ተኛ ወርን እንዲያከብሩ “አመ ርእሰ ሳብዕ ሠርቀ ወርኅ ግበሩ መጥቅዐ” (በሰባተኛው ወር በመጀመሪያው ቀን ዕረፍት በመለከት ድምፅ መታሰቢያ የተቀደሰ ጉባኤ ይሁንላችኊ) ተብለው ታዘው ነበርና ቀንደ መለከት እየነፉ ዓለም የተፈጠረበት ወር ያከብሩ ነበር፡፡ (ዘሌዋ 23፡24)፡፡

💥 ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው ላይ
✍️ “ንፍሑ ቀርነ በጽዮን ወስብኩ በደብረ መቅደስየ ዛቲ ዕለት በዓለ እግዚአብሔር እስመ ይቤ ዛቱ በዓለ እግዚአሔር” (በጽዮን ቀንደ መለከትን ንፉ፤ በመቅደሴ ተራራ ስበኩ፤ ይኸቺ ዕለት የእግዚአብሔር በዓል ናት ብሏልና) በማለት የገለጻት ይኽቺ በዓል በብሉይ ይከበሩ ከነበሩት በዓላት አንደኛዋ ስትኾን በዘመነ ሐዲስ ደግሞ ክርስቶስ ለፍርድ ሲመጣ የሚነፋውን ቀንደ መለከት ጠቋሚ ናት፡፡
69👍2👎1
☄️ ይኸውም 7 ፍጹም ነው = ፍጻሜ ዓለምን
☄️ 7 የዕረፍት ቀን ነው = ዕረፍት መምጣቱን፤
☄️ የቀንደ መለከት መነፋት - በሊቃነ መላእክት የሚነፋውን ቀንደ መለከት ይገልጻል፡-
✍️ “መላእክቱንም ከታላቅ መለከት ድምፅ ጋር ይልካቸዋል፥ ከሰማያትም ዳርቻ እስከ ዳርቻው ከአራቱ ነፋሳት ለእርሱ የተመረጡትን ይሰበስባሉ።”
— ማቴዎስ 24፥31
✍️“አንድ ምሥጢር እነግራችኋለሁ፤ ሁላችን አናንቀላፋም ነገር ግን የኋለኛው መለከት ሲነፋ ሁላችን በድንገት በቅጽበተ ዓይን እንለወጣለን፤ መለከት ይነፋልና ሙታንም የማይበሰብሱ ሆነው ይነሣሉ እኛም እንለወጣለን።”
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥51-52
✍️ “ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ”
— 1ኛ ተሰሎንቄ 4፥16
☄️ በመኾኑም በሰማይ መከፈት የተደረገው የጨረቃ ግርዶሽ - የአሮጌ ዑደት መጠናቀቅ
☄️ የቀለበታማ የፀሓይ ግርዶሽ - የዐዲስ ዑደት ዥማሮን
☄️ በሚዛን ወቅት ያለ የቐንና የሌሊት መተካከል - የፍርድ ሚዛንን
☄️ የቀንደ መለከት ድምፅ - ንቃተ ኅሊና በመላው ዓለም መታወጅን ይወክላል
💥 በመጨረሻም የ2018 ዓ.ም. የመጀመሪያዋ የመስከረም ሙሉ ጨረቃ ማግሰኞ መስከረም 28/ 2018 ዓ.ም. ከምሽቱ 12፡26 ላይ ደምቃ በመውጣት እስከ ሌሊቱ 12፡!2 ድረስ ሰማዩን አድምቃው ትውላለችና ለዚያ ዕከት በሰላም ያድርሰን፡፡
ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ መስከረም 10 ተጻፈ።
125👍20👏7🔥2👎1
🌟 መስከረም 12 ኢትዮጵያ የጠበቀችው ድንቅ ዕለት🌟
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 መስከረም 12 ለፕላኔታችን መሬት በሙላ ታላቅ ዕለት ናት፤ ይኽነን ጥበብ በዘመን ቀመሯና በፊደሏ የያዘችውና የምትምሰክረው ንግሥተ ጥበብ ኢትዮጵያ ናት፤ በእኛ በኢትዮጵያ አቈጣጠር መስከረም 12 በሌላው ዓለም አቈጣጠር ደግሞ እንደ ኹኔታው መስከረም (September) 21 ወይም 21 አንዳንዴም 22 ይኾናል።
🌟 በዚኽ ቀን ፀሓይ ልክ የምድር ወገብ ላይ ኾና ቀኑና ሌሊቱ በመላው ዓለም እኩል የሚኾንበት ወቅት “ዕሪና መዓልት ወዕሪና ሌሊት ዘመፀው" (የመፀው እኩሌ (Autumnal /fall equinox) ይባላል፡፡
🌟 ይኽ ዕለት ፀሐይ የሰማያዊውን ሉል ወገብ አቋርጣ ወደ ደቡብ አግጣጫ የምትኼድበት ጊዜ ሲኾን በሰሜናዊው ንፍቀ ክበብ መፀው የሚዠምርበት ዕለት ነው፡፡ በዚኽ ጊዜ ፀሓይ ልክ በምሥራቅ ትክክለኛ አቅጣጫ ላይ ወጥታ በምዕራብ ትክክለኛ አግጣጫ ላይ ትጠልቃለች፡፡

🌟 የኢትዮጵያ ዐዲሱ ዓመት መግቢያ “መስከረም” ከኾነባቸው በርካታ ምክንያት ውስጥም አንደኛው በ182 ቀን አንዴ “ዕሪና መዓልት ወዕሪና ሌሊት ዘመፀው” (የመፀው የቀንና የሌሊት መተካከል) (Autumnal /fall equinox) የሚኾንበት ወርም ጭምር በመኾኑ ነው፡፡
🌟 መጽሐፍ ስንክሳርም የዓመቱ መዠመሪያ ስለኾነው የመስከረም ወር እንዲኽ ይተነትነዋል፡-
✍️ “ወርኃ መስከረም ቡሩክ ርእሰ አውራኅ ዓመታት ዘግብጽ ወኢትዮጵያ ሰዓተ መዓልቱ ፲ወ፪ቱ ዕሩይ ምስለ ሌሊቱ ወእምዝ የሐጽጽ”
(የተባረከ የመስከረም ወር የግብጽና የኢትዮጵያ ዓመታት ወሮች ራስ ነው፤ የቀኑ ሰዓትም ከሌሊቱ ሰዓት የተስተካከለ ዐሥራ ኹለት ነው፤ ከዚኽ በኋላ እያነሰ ይኼዳል) በማለት የመፀው እኩሌ የሚደረግበት ወር እንደኾነ አስቀምጧል፡፡

💥 91 ዕለት ከ15 ኬክሮስ የአራቱ ወቅታት የዘመን ቀመር ላለን በዲድስቅልያ 30 ላይ ✍️ “እስመ ይዔሪ መዓልት ወሌሊት አመ ዕሥራ ወኀሙሱ” (መዓልትና ሌሊት በመጋቢት 25 ይተካከላል) ይላል፡፡
🌟 አለቃ ኪዳነ ወልድ በመዝገበ ቃላታቸው ገጽ 577 ላይ ሲያብራሩ በ25 ያለው የድሮውን ነው፤ ዛሬ ግን በደቃይቅ ቊጥር 4 ቀን ወደ ታች ወርዶ “አመ ዕሥራ ወአሚሩ” (በ21) ኹኗል፡፡ በእኛ ብተት ደግሞ “አመ ዐሡሩ ወሠሉሱ ወይም ወረቡዑ” (በ12 ወይም በ13) ይኾናል ብለዋል፡፡
ኹለተኛው በ182 ቀን የሚኾነው የቀንና ሌሊት መተካከል

🌟 በኢትዮጵያ አቈጣጠር መጋቢት 12 በፈረንጆች ደግሞ መጋቢት (ማርች 20 ወይም 21) ላይ የሚውለው እና ፀሓይ ልክ የምድር ወገብ ላይ ኾና ቀንና ሌሊቱ እኩል የሚኾንበት ጊዜ (ወቅት) “ዕሪና መዓልት ወዕሪና ሌሊት ዘጸደይ” (የጸደይ የቀንና ሌሊት መተካከል) (Vernal/spring equinox) ይባላል፡፡

🌟 ይኽ ዕለት ፀሓይ የሰማያዊውን ሉል ወገብ አቋርጣ ወደ ሰሜን አግጣጫ የምትኼድበት ጊዜ ሲኾን ለሰሜናዊው ንፍቀ ክበብ ላሉ ጸደይ የሚዠምሩበት ቀን ነው፡፡ በዚኽ ጊዜ ፀሓይ ልክ በምሥራቅ ትክክለኛ አቅጣጫ ላይ ወጥታ በምዕራብ ትክክለኛ አግጣጫ ላይ ትጠልቃለች፡፡ በየ182 ቀናቱ የሚኾነውን የዕሪና መዓልት ወሌሊት (ኢኪውኖክስ) ሳይንስን በሚገባ በመረዳታቸው ነበር ይኽነን መተካከል የሚደረግበት ሌላኛውን ወር “መጋቢት” ብለው ሠይመውታል፡፡

🌟 መጋቢት የሚለው ቃል “መግቦ መግቦት” ከሚለው የግእዝ ንኡስ አንቀጽ የወጣ ቃል ሲኾን ትርጒሙም የመዓልትና የሌሊት ምግብና እንደ መስከረም ትክክል የሚኾንበት ቀንና ሌሊቱ እኩል የሚመጋገብበት ወርኀ ዕሪና (የመተካከል ወር) ማለት ነው፡፡

💥 በኢትዮጵያ የሥነ ከዋክብት ትምህርት በ12ቱ ወራት የስፍረ ሰዓት የሠንጠረዥ ትምህርት ላይ የመስረምና የመጋቢት ወር ሠንጠረዥ አንድ ሲኾን ቀኑና ሌሊቱ 12 ዐሥራ ኹለት ነው፡፡በምድር ወገብ በየትኛውም ወቅት ቢኾን የሰዓተ መዓልቱ ጊዜ በዚኽ ዕለት 12 ሰዓታት ያኽል ነው፡፡

🌟 ከመጋቢት እኩሌ (March equinox) እስከ መስከረም እኩሌ (September equinox)፤ ፀሓይ በ23.5° ዲግሪ በሰሜን ምሥራቅ በኩል በመውጣት በ23.5° ዲግሪ በሰሜን ምዕራብ በኩል ትጠልቃለች፡፡

🌟 ከመስከረም እኩሌ እስከ መጋቢት እኩሌ፤ ፀሓይ በ23.5° ዲግሪ በደቡብ ምሥራቅ በኩል በመውጣት፤ በ23.5° ዲግሪ በደቡብ ምዕራብ በኩል ትጠልቃለች፡፡

🌟 በመጋቢት እና በመስከረም (ኹለቱ እኩሌዎች) የመዓልቱ ርዝማኔ 12 ሰዓታት ያኽል ነው፡፡ይኽነን ጥበብ በታላቁ የፊደል ቀመራችን ውስጥ በጥበብ ተሠናሥሎ ተዋሕዶና ተጋምዶ የተቀመጠባት ብቸኛዋ የምድራችን ሀገር ንግሥተ ጥበብ ኢትዮጵያ ናት፡፡

💥 ከፊደል [አ] እስከ ፊደል [ፐ] ከላይ ወደ ታች የተደረደሩት 26ት የግእዝ ፊደላት ናቸው፡፡
☄️ወደ ጐን ያሉት [አ] [ቡ] [ጊ] [ዳ] [ሄ] [ው] [ዞ] ደግሞ 7 ናቸው፡፡
☄️ በአጠቃላይ ለማወቅ 26 × 7 =182 ይኾናሉ፡፡
☄️ ይኸውም 365 የዓመት ቀናት ÷ 2 = 182.5 በመምጣት የዓመቱን የግማሽ ዕለት ቀመርን ፊደላቱ ይዘዋል፡፡ በምንኖርባት ምድር ላይ በግእዝ ፊደላችን ቊጥር ልክ በየ182ት ቀናት የሚከሰቱትን፡-
💥 ዕሪና መዓልት ወዕሪና ሌሊት ዘመፀው
💥 ዕሪና መዓልት ወዕሪና ሌሊት ዘጸደይ
ናቸው፡፡

🌟 በዚኽች ቀንና ሌሊቷ እኩል በሚኾንበት ሰኞ መስከረም 12 በ2018 ዓ.ም ሮሽ ሀሻናህ רֹאשׁ הַשָּׁנָה የቀንደ መለከት በዓል ይኾናል፡፡ “ሮሽ ማለት እራስ “ሀሻናህ” (ዐውደ ዓመት) ማለት ነው፡፡

☄️ በዕብራውያን ትውፊትና በቤዛንታይን ባሉት ኹሉ ትውፊት “ልደተ ዓለም” (ዓለም የተፈጠረበት ወር) Έτη Γενέσεως Κόσμου κατά 'Ρωμαίους ተብሎ ይታሰባል፡፡
https://orthochristian.com/97046.html

💥 እንደ አለቃ ኪዳነ ወልድ ትንታኔ ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ ድረስ ቀዳማዊ ወር ኤታኒም ነበር በኋላ ግን ከግብጽ የወጡበት ኔሣን (ሚያዝያ) ስለነበር “ዝንቱ ወርኅ ይኩንክሙ ቀዳማየ አውራኅ” (ይህ ወር የወሮች መጀመሪያ ይሁናችኊ የዓመቱም መጀመሪያ ወር ይሁናችኊ) ተብለው በእነርሱ የጥቅምትን ቅድምና ለሚያዝያ የሚያዝያን 7ተኛነት ለጥቅምት (በእኛ ለመስከረም) እንዲሰጡ ታዘው ነበር ይላሉ (ዘፀ 12፡2)።

💥 እስራኤላውያን ከግብጽ የወጡበትን ሚያዝያን ዐዲስ ዓመታቸውን እንዲያከብሩ ቢታዘዙም ግን ዓለም የተፈጠረበትን የኤታኒም 7ተኛ ወርን እንዲያከብሩ፡-
✍️ “አመ ርእሰ ሳብዕ ሠርቀ ወርኅ ግበሩ መጥቅዐ” (በሰባተኛው ወር በመጀመሪያው ቀን ዕረፍት በመለከት ድምፅ መታሰቢያ የተቀደሰ ጉባኤ ይሁንላችኊ) ተብለው ታዘው ነበርና ቀንደ መለከት እየነፉ ዓለም የተፈጠረበት ወር ያከብሩ ነበር፡፡ (ዘሌዋ 23፡24)፡፡

💥 ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው ላይ
✍️ “ንፍሑ ቀርነ በጽዮን ወስብኩ በደብረ መቅደስየ ዛቲ ዕለት በዓለ እግዚአብሔር እስመ ይቤ ዛቱ በዓለ እግዚአሔር” (በጽዮን ቀንደ መለከትን ንፉ፤ በመቅደሴ ተራራ ስበኩ፤ ይኸቺ ዕለት የእግዚአብሔር በዓል ናት ብሏልና) በማለት የገለጻት ይኽቺ በዓል በብሉይ ይከበሩ ከነበሩት በዓላት አንደኛዋ ስትኾን በዘመነ ሐዲስ ደግሞ ክርስቶስ ለፍርድ ሲመጣ በሊቃነ መላእክት የሚነፋውን የቀንደ መለከት ጠቋሚ ናት፡፡

💥 በተለይ ቢሊየኖች ከተመለከቱት በርኅወት ሰማይ (በሰማይ መከፈት) ከጳጉሜን 2 እሑድ ምሽት በዓሣዎች (ሑት፣ ፓይሲስ) ከተከናወነው የደም ጨረቃ ግርዶሽ ተከናወነ።
85👍7
💥 መስከረም 11/1/2018 (2+0+1+8 = 11) 11/1/11 ቀመር ከተከናወነው ቀለበታማ የፀሓይ ግርዶሽ በሰንቡላ (ቪርጎ) ከታየ በኋላ፤ መላው ዓለም ቀንና ሌሊቱ እኩለ በሚኾንበት መስከረም 12 ዕለት በዋለው በሮሽ ሀሻናህ ዕለት 100 ጥንታዊ የኾኑ ቀንደ መለከት በኢየሩሳሌም ሲነፉ ለመጀመሪያ ጊዜ መላው ዓለም የቀጥታ ሥርጭት እንዲተላለፍ መወሰኑ እንዲኾን መደረጉ እንዲኹ የኾነ አይደለም። በዓለማችን ታላቅ ጉዳይና አንድ ታላቅ የትንቢት ቀጠሮ ጊዜ በጊዜያችን እንደተቃረበ አመላካች ሊኾን ይችላልና በጣም ብዙ ያልተጠበቁ ክንውኖች በዜናም ይኹን በሌላ በሚቀጥሉት ጊዜያቶች ልናይ እንደምንችል በመረዳት ኅሊናችንን ሰብሰብ ማረግ ጥሩ ነው፡፡
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ 11/1/2018 ዓ.ም. (2+0+1+8 = 11) 11/1/11 ተጻፈ
113👍27
💥የመስከረም ወር ሙሉ ጨረቃ እና የሴቶች አበባ
✍️ በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
💥 ዛሬ ማግሰኞ መስከረም 27 የ2018 ዓ.ም. የዐዲሱ ዓመት የመስከረም ወር የመጀመሪያዋ ሙሉ ጨረቃ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 12፡26 ጀምራ በመውጣት ጠፈሩን አድምቃው አምሽታ ታነጋለች፡፡

🌚 ያለፈው ዓመት የ2017 ዓ.ም. የመጨረሻዋ ሙሉ ጨረቃ በሙሉ የደም ጨረቃ ግርዶሽን ጳጉሜን 2 ሸኝተን የዐዲሱን ዓመት የ2018 ዓ.ም. ደማቅ፣ ውብ፣ ያማረች ጨረቃን በዛሬው ምሽት የምናያት ይኾናል፡፡

💥 እንደሚታወቀው ክረምቱን መስከረም 25 ሸኝተን መስከረም 26 ላይ ዘመነ መፀውን ተቀብለናል፡፡ በሀገራችን በኢትዮጵያ የመፀው ወቅት ከመስከረም 26 እስከ ታኅሣሥ 25 ያለው ሲኾን የነፋስ ወቅትም ይባላል፡፡
🌺 መፀው የሚለውን የግእዝ ቃል ወደ ዐማርኛ ሲፈታ “መፀወ” ማለት (ጸገየ፣ ጼነወ፣ መጠወ) “አበበ 🌼 ፣ አበባ ያዘ 🌸 ፣ የአበባ መዐዛ ሸተተ 💐 ” ማለት ነውና ወርኀ ጽጌ፣ ዘመነ ጽጌ (የአበባ ወር፣🌸 የአበባ ዘመን🌻) ማለት ነው፡፡

🌾 ታዲያ በዚኽ የአበባ ወቅትና በመስከረም የዐዲሱ ዓመት የመዠመሪያ ሙሉ ጨረቃን ከሴቶች 🤰ተፈጥሯዊ ኩነት ጋር “ማዛሮት” የሚለው መጽሐፌ ገጽ 312 ላይ ያለውን አጋራችኋለኊ፡፡

💥 ኢትዮጵያን ጨምሮ የጥንት ሥልጡን ሕዝቦች የሴቶች የወርኀዊ ደምና 🌺 ጨረቃ ግንኙነት እንዳላቸው ይገልጹ ነበር፡፡ በእኛም አጠራር “የወር አበባ” ማለት “የጨረቃ አበባ” ማለት ነው፡፡ “ወር” የሚለው የዐማርኛ ቃል “ወርኅ” ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲኾን ፍቺውም “ጨረቃ🌛” ማለት ነው፡🌛ምክንያቱም አንድ ወር ማለት ጨረቃ ምድርን የምትዞርበትና የጨረቃ ሰሌዳዎች (phases) የሚቀያየሩበት የ29.5 ቀናት ዑደት ስለኾነ “ዐውደ ወርኅ” ተብሎ በጨረቃ ተሰይሟል፡፡ 🌻 አበባ ማለት ደግሞ አንድ ተክል ካበበ ፍሬ ለመያዝ መድረሱን አመላካች እንደሆነ 🤰ሴቶቹም ፍሬ ጽንስ የሚቋጥሩበት ጊዜ መቃረቡን አመልካች ነው፡፡

🤰በእንግሊዝኛ “ሜኑስትሬሽን (menstruation) እና “ሜንስስ” (menses) የሚለው ቃል ጥንቱኑ የመጣው “ሙን፣ ሜኔ” (moon (mene)) ከሚለው የላቲንና የግሪክ ቃል ሲኾን ፍቺውም “የጨረቃ ወር የያዘ የሴቶች ዑደት” ማለት ነው፡፡

🌓 ጨረቃና የጨረቃ የሴቶች አበባ የሚለው ዑደት የተሳሰረው የቀናቱ የርዝመት አማካይ ቅርርቦች፣ የጨረቃ በየደረጃው ያሉ ሰሌዳዎቿ፣ የዑደታቱ የድርጊት ግጥጥሞሽ መሠናሠል ነው፡፡
🌓 የወር አበባ ስንል ወርኅ ማለት ጨረቃ ማለት ነውና የሴቷ ዑደት የጀመረው በመጀመሪያው ቀን እንደኾነ ብናስብ በአማካይ አብዛኛው የሴቶች ዑደቱ 28 እስከ 29 ቀናት ውስጥ ነው፡፡ ነገር ግን ዐልፎ ዐልፎ በልዩነት ከ21-35 ዕለት ሊረዝም ይችላል፡፡
🌓 በተመሳሳይ መልኩ ጨረቃ መሬት ለመዞር የሚፈጅባት 27.3 ቀናት (27 ቀናት፤ ከ7 ሰዓት፤ ከ43 ደቂቃ) ሲሆን ወይም ከጠፍ ጨረቃ 🌚 ወደ ሙሉ ጨረቃ 🌝 ከዚያ መልሶ ወደ ጠፍ ጨረቃ 🌑 ለመሆን የሚፈጅባት ዑደት በ29 እና በ30 ማለትም በአማካይ 29.5 ቀናት እንደማለት ነው፡፡ ይኽንን ስናይ በአማካይ ምን ያህል የተቀራረቡ እንደኾነ እንረዳለን፡፡
👩‍🦱 ሌላው የሴቶች ወር አበባ (የጨረቃ አበባ) ዑደት አራት ዋና ዋና የዑደት ደረጃዎች አሉት፡፡ እነዚኽም፡-
1. ሜንስትሩአል
2. የፎሊኪውላር
3. ኦቪውሌሽን (ኦቪውላቶሪ)
4. ሉቴዬል ይባላሉ፡፡
🌝 ወደ ጨረቃ ስንመጣም አራት ታላላቅ ዋና ገጾች (4 major phases) አሏት፡፡ እነዚህም፡-
1. ጠፍ (በክ) ጨረቃ - የማትታይ ጨረቃ (new moon)
2. መንፈቀ ወርኅ - ግማሽ ጨረቃ (first quarter)
3. ምልአተ ወርኅ - ሙሉ ጨረቃ (full moon)
4. ሕፀፀ ወርኅ - የጎደለች ጨረቃ (last quarter)

🤰 እነዚህም ርስ በርሳቸው ዑደታቱ እንዴት እንደሚነጻጸሩና ተፈጥሮን አምላክ እንዴት ውብ አድርጎ እንዳያያዘው ከዚኽ ቀጥለን እንመለከታለን፡፡
🌑🤰1ኛ) ሜንስትሩአል ዑደትና የጨረቃ ልደት
🤰 በመጀመሪያው “ሜንስትሩአል ፌዝ” ጊዜ በአማካይ ከ3 እስከ 7 ቀናት የሴቶች ወርኀዊ ደም ፍሳሽ መታየት (መውጣት) ይጀምራል፡፡
🌛 ወደ ጨረቃ ስንመጣም ጠፍ ጨረቃ (new moon) ከኾነች ከአንድ አራት ቀን በኋላ ግን የተወሰነ ብርሀን ያረፈበት አካሏን በማጭድ ቅርጽ መልክ እናየዋለን፡፡ እኛም ጨረቃ ተወለደች፣ ወጣች እንላለን፡፡ ይኽንን የኹለቱንም የመታየት የመውጣት ቀንን ማነጻጸር የበለጠ እንድንረዳው ያስችላል፡፡

🤰🌓 2ኛ) ፎሊኪውላር ዑደትና ግማሽ ጨረቃ
🤰ከአንድ ሳምንት በኋላ ባለው በዚኽ የወር አበባ ዑደት ጊዜ በተለይ በሴቶች የመራቢያ ሕዋስ በአንዱ እንቁላል ማደግ የሚጀምርበት እድገቱን የሚያፋጥን ሆርሞን የሚመረትበት ጊዜ ነው፡፡
🌓 ወደ ጨረቃ ስንመጣም በተመሳሳይ መልኩ ከሰባት ቀን ወይም ከአንድ ሳምንት በኋላ ደግሞ የፀሐይ ብርሃን ያገኘው ክፍሏ ይጨምርና ግማሽ አካሏ ብርሀን ያርፍበታል በግእዝ “መንፈቀ ወርኅ” (እኩሌታ ጨረቃ) ትባላለች፡፡
ስለዚኽ ግማሽ ጨረቃ ሆና አድጋ ትታየናለች ማለት ነው፡፡ ይኽ የደረሰችበት የቅርጽ ደረጃ ደግሞ እንደ ሳይንሱ የመጀመሪያ ሩብ (first quarter) ይባላል፡፡
ይህም ምን ያህል በወር አበባና በጨረቃ ሰሌዳዎች ያለውን የዕድገት ጭማሪ ደረጃ መመሳሰል በግልጽ የሚያሳይ ነው፡፡

🤰💥 3ኛ) ኦቪውሌሽንና ሙሉ ጨረቃ (14ኛ ቀን)
💥 ከ2 ሳምንት በኋላ ወይም በ14ኛው ቀን ጨረቃ ከፀሓይ በተቃራኒ በኩል ትሆንና የፀሐይ ብርሃን ሙሉ ለሙሉ ሲያርፍባት ደምቃ ታበራለች፤ ይኽም ደረጃ ሙሉ ጨረቃ “ምልአተ ወርኅ” (full moon) ይባላል፡፡
🤰 በተመሳሳይ መልኩ በሴቶች የወር አበባ ዑደት 14ኛው ቀን ሴት በተለይ ፅንስ መቋጠር የምትችልበት ሲሆን በዚህ ጊዜ ከመራቢያ ሕዋሳቷ በአንዱ ያደገው እንቁላል (ፅንስ ሊሆን የሚችለው ደም) ወደ ማሕፀን ይወርዳል፡፡
ልክ እንደ ፀሓይ ምሳሌ ከወንድ ዘር ጋር ሲገናኝ ሕይወት ይጀምራል፤ ብርሃን ነፍስ ያለችው ፍሬ ጽንስ በማሕፀኗ ይቋጠራል፡፡ አበባነቱ ወደ ፍሬ ይደርሳል፡፡

🤰🌒 4ኛ) ሉቴዬልና የጨረቃ ጒድለት (ከ17-28)
🤰🌒 ከ17-28 ቀናት ባለው በዚህ የሉቴዬል የወር አበባ ዑደት ጊዜ በማሕፀን ውስጥ የሚመረተውን የሆርሞን መጠን እየቀነሰ የሚሄድበት ነው፡፡
🌛 ወደ ጨረቃ ዑደት ስንመጣ በ14ኛው ወይም በ15ኛው ቀን ሙሉ በመሆን በምሥራቅ ወጥታ ሌሊቱን ሁሉ ደምቃ ታበራለች፤ ከዚያም በተከታታይ እስከ 14 ቀን ድረስ አንድ አንድ እጅ ብርሃን እየተነሣት (እያጣች) እየጐደለች በሌሊት የመውጫዋ ጊዜ እየዘገየ ጠፍ ወደ መሆን ታዘግማለች፡፡ ይህም ሕጸጸ ወርኅ (የጨረቃ ጉድለት) ይባላል፡፡

😍 ከዚኹ ጋር ተያይዞ በኢትዮጵያውያኑ የሥነ ፈለክ ጥበባዊ ትምህርት ፀሓይ ከወንድ ጋር ጨረቃ ከሴት ጋር በስፋት ይነጻጸራሉ፡፡ ሴቶች ሰማይን ቢመረምሩና እንደ ጨረቃ ሳቢ ተፈጥሮን እግዚአብሔር እንደሰጣቸው ቢረዱ ኖሮ ከፍተኛ ኃይል ይኖራቸው ነበረ። ዳሩ ግን ዓለም የምታሸክመው ብዙ የማይጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ኃይላቸውን እንዲያባክኑ በማድረግ ለአንክሮ ለማድነቅ ለተዘክሮ ለማሰብ የተፈጠሩትን ፍጥረታት እንዳያስቡ በማድረግ ሙሉ ጨረቃ ኾነው እንዳይደምቁ ትፈትናቸዋለች።
94👍18🔥5
🌒 ይኽነን በስፋት በሌላ ጊዜ የምጽፍላችኍ ሲኾን በዛሬው መስከረም 27 ምሽት ላይ ጨረቃን በማየት ተፈጥሮን በማድነቅ የፍጥረታት ፈጣሪ እግዚአብሔርን በማመስገን ወራችኹ በሙሉ እንደ ሙሉዋ ጨረቃ የበራ፣ የደመቀ እንዲኾን በመማፀን የምታነሡትን ፎቶዎች ደግሞ በቴሌግራም ቻናሌ https://www.tg-me.com/Rodas9 እና https://www.tg-me.com/+xN518gdGKvswNzE0
ላይ እንድታጋሩኝ እጠይቃለኍ፡፡
መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
መስከረም 27/ 2018 ዓ.ም.
112👍18🔥5👏3
የመስከረም ሙሉ ጨረቃ
330👍81👏17🔥7😁7👎4🥰2
2025/10/17 23:05:15
Back to Top
HTML Embed Code: