Telegram Web Link
#HoPR🇪🇹

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያ ይሰጣሉ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመንግስታቸውን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡም ይጠበቃል።

በተጨማሪም የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን እንደሚያፀድቅ ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ጉባኤው ከጥዋት 2:30 ጀምሮ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን በቀጥታ ይሰራጫል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
😡885❤479😭41🙏24🤔23👏18🥰15💔15🕊12😱9😢3
TIKVAH-ETHIOPIA
" ትናንት የተሰጠውን የእንግሊዘኛ ትምህርት ፈተና ያልተፈተኑ ተማሪዎች ሌሎች ትምህርት ፈተናዎችን ከወሰዱ በኋላ ይፈተናሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ትናንት በተሰጠው የመጀመሪያ ቀን ፈተናዎች ላይ የተወሰነ የኃይል እና የሲስተም መቆራረጥ አጋጥሞ እንደነበር የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተናግረዋል። " ከሚመለከታቸው…
#NationalExam🇪🇹

ከሰኔ 23 እስከ 25/2017 ዓ/ም በበይነ መረብና በወረቀት ሲሰጥ የነበረው የአንደኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ዛሬ ተጠናቋል፡፡

ፈተናውን በወረቀት 231,761 በበይነ መረብ 43,367 በድምሩ 275,128 ተፈታኞች ወስደዋል፡፡

የመጀመሪያ ቀን የመጀመሪያ ክፍለ ጊዜ ላይ ፈተናውን በበይነ መረብ ሲወስዱ በተወሰኑ የፈተና ማዕከላት ላይ በተለያየ ምክንያት የእንግሊዘኛ ፈተና ያልወሰዱ ተፈታኞች አብዛኞቹ ነገ ሐሙስ ጥዋት ከሁለተኛ ዙር ተፈታኞች ጋር ያልወሰዱት ፈተና የሚሰጣቸው እንደሆነ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

በሁለተኛ ዙር ለመውሰድ ያልቻሉ ተፈታኞች ከሶስተኛውና ከአራተኛው ዙር ተፈታኞች ጋር እንደሚወስዱ አመልክቷል።

" ፈተናውን በተለያዩ ዙሮች መስጠት መቻላችን በተለያዩ ችግሮች ምክንያት በተመደቡበት ዙር መፈተን ያልቻሉ ተፈታኞች በሌሎቹ ዙሮች ከሚፈተኑ ተፈታኞች ጋር መፈተን እንዲችሉ ዕድል ፈጥሯል " ሲል አገልግሎቱ ገልጿል።

#EAES

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤492🙏59😡27😭25🕊18🤔5🥰4😢3👏1
TIKVAH-ETHIOPIA
" በተፈጠረው እሳት አደጋ ሁለት ሰዎች ሞተዋል፤ አንዱ ሆስፒታል ገብቷል " - የሲዳማ ክልል ጸጥታ ቢሮ በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተፈጠረ በተባለ የፍንዳታ አደጋ በሰዎች ላይ ሞትና የአካል ጉዳት መድረሱን የሲዳማ ክልል ጸጥታ ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል። የክልሉ ጸጥታ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሀሚድ አህመድ በሰጡን ቃል፣ "ትላንት ሁለት ሰዓት አካባቢ በተፈጠረው እሳት አደጋ…
" የውሃ ማሞቂያ ፈንድቶ ነው የሁለት ሰዎች ሕይወት ያልፈው " - የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ

➡️ " በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ከአደጋው ጋር ተያይዞ የሚዘዋወሩት መረጃዎች የተሳሳቱ ናቸው !! "


የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ስራ አስኪያጅ አቶ ማቴዎስ አሸናፊ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት ትናንት ጠዋት በፓርኩ ሼድ 40 የውሃ ማሞቂያ (ቦይሌር) ባለሙያ ሰራተኞች መደበኛ ስራቸውን እያከናወኑ ባሉበት ፈንድቶ የ62 እና 45 ዕድሜ ውስጥ ያሉ ሁለት ባለሙያዎች ሕይወታቸዉ ማለፉንና በሁሉት ሰራተኞች ላይ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።

ሕይወታቸዉ ያለፈዉ ሁለቱም ባለሙያዎች ወንዶች ሲሆኑ ለረጅም ዓመታት በዘርፉ የሰሩና ልምድ ያላቸዉ መሆናቸውን የገለፁት አቶ ማቴዎስ ጉዳት የደረሰባቸው ሁለት ሰራተኞችም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቪ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሕክምና ላይ መሆናቸዉን ገልጸዋል።

የአደጋውን ትክክለኛ መንስኤ እንዲያጣራ መርማሪ ቡድን መዋቀሩን የገለፁት የፓርኩ ስራ አስኪያጅ ከአደጋው ጋር ተያይዞ በተለያዩ ማህበራዊ ትስስር ገፆች " ክስተቱ የእሳት አደጋ እንደሆነና መንስኤዉም ባለሙያዎች የልምድ ማነስ " ተደርጎ የሚሰራጩ መረጃዎች ፍፁም የተሳሳቱና ባለሙያዎችም የረጅም ዓመታት ማለትም ከ6 ዓመታት በላይ በዘርፉ ልምድ ያላቸው ስለመሆናቸው ተነግረዋል።

በዚህ ልክ በሰዉና በንብረት ላይ ጉዳት የሚያደርስ የእሳት አደጋ ከዚህ ቀደም በፓርኩ ዉስጥ ተከስቶ እንደማያዉቅም አቶ ማቴዎስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
❤860😭424😢56🙏43🕊36😡16👏13😱13🥰8
#DStvEthiopia
#ሁሉምያለውእኛጋርነው

📣 ከእሁድ እስከ እሁድ አለንላችሁ!

❗️❗️ለአጭር ጊዜ የሚቆይ! ደንበኝነትዎን ከሰኔ 8 ጀምሮ ሲያራዝሙ ከፍ ወዳለው ፓኬጅ ከተጨማሪ ቻናሎች ጋር በስጦታ ያገኛሉ!!

አዲሱን እና የተሻሻለውን MyDStv መተግበሪያ ያውርዱ።
⬇️ https://mydstv.onelink.me/vGln/xepsjmo7

ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚነት አላቸው!

#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
❤153🙏5🥰4😱3😢3
ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት

የሁለት ወር የልጆች የክረምት ስልጠና ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ይጀመራል።

👉ስልጠናው ዕድሜያቸው ከ 5-18  ዓመት ላሉ ልጆች የሚሰጥ ነው።
👉 ልጆች ፕሮጀክቶች እየሰሩ የሚሰለጥኑበት
የስልጠናዎቹ ዓይነት:
👉 Computer Programming and Website Development
👉 AI and Robotics
👉 Graphic Design, Video Editing and Animation
👉 Art (Film Acting, Writing and Modeling)
👉 Painting, Drawing and Sculpture
👉 Language and Basic Computer

☎️  0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram
Tiktok
Linkedin
❤111🙏6🤔5😡5😢2👏1
" ለምሳሌ የካ ክፍለ ከተማ ወደ 100 የሚሆኑ ሰዎች መታሰራቸውን በማስረጃዎች አረጋግጠናል፤ ወደ ቦሌ ወደ 200 የሚሆኑ አሉ " - ድርጅቱ

" ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች ኢትዮጵያ " የመብት ተሟጋች የተሰኘው ድርጅት፣ " የትግራይ ተወላጆች በአዲስ አበባ በዘፈቀደ እየታሰሩ ነው " ሲል ለቲካቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡

ስለእስሩ በተጨባጭ ያላችሁ መረጃ ምንድን ነው ? ብለን የጠየቅናቸው የድርጅቱ ምክትል ዳይሬክተር አቶ መብሪሂ ብርሃነ፣ " በባለፉት ሁለት፣ ሦስት ሳምንታት ያለየፍርድ ቤት ትዕዛዝ፣ ያለበቂ ጥርጣሬ ሰዎች በማንነታቸው ብቻ እየታሰሩ ስለሆነ ይህን መሠረት አድረገን ክትትል ስናደርግ ቆይተናል " ብለዋል።

" ከክትትል ባለፈ ደግሞ ተጨባጭ ማስረጃ ካገኘን በኋላ እና ታስረው የወጡት፣ የታሳሪ ቤተሰቦችና ጓደኞችን ከጠየቅን በኋላ ሪፖርት አውጥተናል " ብለው፣ " ሰዎች ከሕግ ውጪ ሲታሰሩ ብቻ ሳይሆን ያለበቂ ጥርጣሬ ታስረው ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ሲቀር ይሄ የዘፈቀደ እስር ነው " ሲሉ ወንጅለዋል።

" ሰዎች ሊታሰሩ ይችላሉ። ግን ሕግ ቢተላለፉ እንኳ ወደ ፍርድ ቤት ነው እንጂ የሚቀርቡት ከ48 ሰዓታት በላይ ፓሊስ አስሮ ማቆየት አይችልም በወንጀል እንኳ የተጠረጠረውን። እነዚህ ግን የወንጀል ጥርጣሬም የላቸውም፣ ለምን እንደታሰሩም አይነገራቸውም " ነው ያሉት።

እስራቱ ከምን ጋር የተያያዘ እንደሆነ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ " እስሮች በየጊዜው ይፈጸማሉ አሁን በትግራይ ተወላጆች ትኩረቱን አደረገ እንጂ፤ ከዚህ በፊትም ማንነት ተኮር እስሮች አሉ። ምክንያቱን አሳሪዎቹ ናቸው የሚያውቁት " ብለዋል።

" አንድ ሰው ከታሰረ ፍርድ ቤት መቅረብ አለበት እንጂ አንድ ቦታ አጎሮ ሳምንት፣ ሁለት ሳምንት ማቆየት ሕገ ወጥ ድርጊት ነው በወንጀልም ያስጠይቃል። በቁጥጥር ሥር የሚያውሏቸው ሰዎች 'እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ ከላይ የመጣ ትዕዛዝ ነው' ነው የሚሉት " ብለዋል።

" ሰዎች በሕገ መግስቱ አንቀጽ 25 መሠረት በእኩልነት ነው መስተናገድ ያለባቸው " ያሉት ም/ዳይክተሩ፣ " የታሰሩ አንዳንድ ሰዎች ገንዘብ ከፍለው የወጡበት ሁኔታ አለ። ስለዚህ የሙስና ተግባራትም አለ ለማለት ያስችላል " ብለዋል።

በተጨባጭ ድርጅቱ ባለው መረጃ መሠረት ምን ያክል ሰዎች ታስረዋል ? የት ክፍለ ከተማስ ነው የታሰሩት ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረላቸው ጥያቄ፣ " በተጨባጭ በእያንዳንዱ ከተማ ምን ያህል ሰው እንደታሰረ መቁጠር ያስፈልጋል። ግን ለምሳሌ የካ ክፍለ ከተማ ወደ 100 ሰዎች መታሰራቸውን በማስረጃዎች አረጋግጠናል፤ ወደ ቦሌ ወደ 200 የሚሆኑ አሉ " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

" በመቶዎች ወይም እስከ 1000 ሊሆን ይችላል ብለን እንገምታለን አጠቃላይ በቁጥጥር ሥር ውለው የተፈቱትና አሁንም በእስር ላይ ያሉት" ያሉት አቶ መብሪሂ፣ "ሰዎቹ የታሰሩት ቦሌ፣ ሲኤምሲ፣ ሾላ፣ ልደታ እና ሌሎች ቦታዎች ላይ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

" ሰዎች ወንጀል ከሰሩ በሕግ አግባብ አይጠየቁ አንልም ነገር ግን በጅምላ እየተወሰዱ፣ አንዳንዴም ገንዘብ እየጠየቁ እየሆነ ያለ ተግባር ስለሆነ በማንም ተወላጅ ላይ ሊደረግ አይገባም። መንግስት አስቸኳይ መፍትሄ ይስጥበት " ሲሉም አሳስበዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ የጠየቀው አንድ ተቋም፣ ጉዳዩን እየተከታተለው መሆኑን የጠቆመ ሲሆን፣ ምላሽ ከሰጠ የምናቀርብ ይሆናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
❤438😭166🙏18😡15🤔14🕊12👏10😢10
" በጸጥታ ምክንያት የባሕርና ትራንስፓርት ሎጂስቲክ ደረቅ ጭነት እንዳይጓጓዝ ያቋረጠባቸው ቦታዎች አሉ። ለምሳሌ ወረታ ደረቅ ወደብ " - ጠያቂዎች ስለባሕር ዳር ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት

የባሕርና ትራንስፓርት ሎጂስቲክ አገልግሎት ድርጅት በጸጥታው ምክንያት ወደ ወረታ ወደብ ደረቅ ጭነት እንዳይጓጓዝ በማቋረጡ በባሕር ዳር ጉምሩክ ቅ/ጽሕፈት ቤት ቅሬታ መኖሩን የሚመለከት ጥያቄ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ቀረበበት።

ጥያቄው የቀረበው ከሰሞኑን ኮሚሽኑ፣ የ11 ወራት ሪፓርቱን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ነው።

በዚህም አንድ ጠያቂ፣ " በጸጥታ ምክንያት የባሕርና ትራንስፓርት ሎጂስቲክ ደረቅ ጭነት እንዳይጓጓዝ ያቋረጠባቸው ቦታዎች አሉ። ለምሳሌ 'በወረታ ደረቅ ወደብ አካባቢ እንዳይሄዱ በመደረጉ በገቢያችን ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አመጡብን' የሚል ቅሬታ አለ በቅ/ጽ/ቤቱ። ኮሚሽኑ በዚህ ዙሪያ ምን እየሰራ ነው ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

ሌላኛው ጠያቂም፣ ከወረታ ደረቅ ወደብ ጋር በተያያዘ የቅ/ጽሕፈት ቤቱ ቅሬታ ሲያስረዱ፣ "'ዩኒሞዳሉ (ግለሰቡ) ያስገባል፣ መልቲሞዳሉ (የመንግስቱ) ግን አቋርጧል። በተደጋጋሚ ብንጽፍም አድማጭ አልተገኘም። ይሄ በመሆኑ ገቢያችን ቀንሷል፤ አፈጻጻማችን ዝቅተኛ እንዲሆን አድርጎታል' የሚል ቅሬታ ስላለ የኮሚሽኑ ምላሽ ምንድን ነው?" ሲሉ ጠይቀዋል።

ጉምሩክ ኮሚሽን፣ "በመስክ ጉብኝታችሁ ካያችኋቸው መካከል ባሕር ዳር ጉምሩክ ቅ/ጽሕፈት ቤት በመልቲ ሞዳል የሚገቡ የእቃ ፍሰት መቀነስ ጋር የተነሳው እውነት ነው። የመልቲሞዳል ኦፕሬተሩ የመንግስት የባሕር የትራንስፓርትና ሎጂስቲክ አገልግሎት ድርጅት ነው" ሲል መልሷል።

"እቃ አገባብን በተመለከተ በክልሉ/በመስመሩ ያሉ የጸጥታ ችግሮች አልፎ፣ አልፎ የሚፈጸሙ ቢሆንም በሱ ስጋት መነሻ የመልቲሞዳል ሞደሉ እቃዎችን በፈለገው ደረጃ ቀደም ብሎ እንደነበረው ስሙዝሊ ለማማጓጓዝ ፍላጎት የለውም" ሲል አክሏል።

"በወደቡ የሚገባው የእቃ ፍሰት ከጸጥታ መነሻ በማድረግ የመልቲሞዳል ኦፕሬተሩ እቃ እያጓጓዘ አይደለም። ፍሰቱ የሚሻሻልበት ሁኔታ ይኖራል" ነው ያለው ኮሚሽኑ።

በሌላ በኩል ኮሚሽኑ፣ "የግብዓትና ሎጂስቱክስ ጉዳይ ቀለል ተደርጓል። ኤግሶስት አድርገናል ካገዛችሁን። 100 መኪና ይገዛልን ብለን ከጠየቅን ሁለት ዓመት አልፎታል። እስካሁን አልተገዛም። ዋጋ እየተከፈለ ሰው እየሞተ ነው፤ የጸጥታ ተቋማት ሰዎችም መዓት ነው የሚሞተው" ሲል ሪፓርት ባቀረበበት ወቅት ገልጿል።

ቋሚ ኮሚቴው በበኩሉ፣ ኮንትሮባንዲስቶችን ከመያዝ አኳያ በተደረገ ግምገማ፣ "መንግስት ያለው መኪና በጣም ደካማ፣ ችግር ያለበት፤ ኮንትሮባንዲስቶቹ የሚይዙት ደግሞ ዘመናዊ እንደሆነ በየጊዜው ሲነሳ ነበር" ብሎ፣ "ከመኪና ጋር ተያይዞ ሁልጊዜ አቅማችሁን እየተፈታተነ ያለ ነገር ስለሆነ ችግራችሁን በደንብ ብታስረዱን የኛ ቋሚ ኮሚቴም ለማገዝ ዝግጁ ነው" ብሏል።

"በዚህ ዘርፍ በሰው ሕይወት ጉዳት እየደረሰ እንዳለም እናውቃለን። እናንተም ራሳቸውን መስዋት ያደረጉ ሰዎችን ቤተሰቦች እየደገፋችሁ እንደሆነ ይታወቃል። ተቋሙ ስራውን እየሰራ ባለበት የጠየቀው የመኪና ግዥ ምላሽ የማይሰጥበት ችግሩ ምንድን ነው?" ሲልም ኮሚሽኑን ጠይቋል።

ኮሚሽኑም፣ "ግዢ ሂደት ላይም ደርሰው አሸናፊ ከተለየ በኋላ ክረምት ላይ በተደረገ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጪ ምንዛሬ ፍሎቴሽኑ ላይ ትልቅ ኢምፓክት ስለነበረው አቅራቢዎቹ የማቅረብ ፍላጎት አልነበራቸውም" የሚል ምላሽ ሰጥቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
❤368🤔7😡7👏5🕊5😭5🥰4🙏3😢2
TIKVAH-ETHIOPIA
#HoPR🇪🇹 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያ ይሰጣሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመንግስታቸውን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡም ይጠበቃል። በተጨማሪም የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ…
#HoPR🇪🇹

" የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ግሽበት ከፍተኛ ጫና እያሳደረባቸው ካሉ የህብረተሰብ ክፍሎች የመንግሥት ሰራተኛው ግንባር ቀደም ነው ! " - የምክር ቤት አባል

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተዋል።

የምክር ቤቱ አባላትም ጥያቄያቸውን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እያቀረቡ ይገኛሉ።

እስካሁን ከቀረቡ ጥያቄዎች መካከል ከኑሮ ውድነት፣ ከመንግሥት ሰራተኞች ፣ ጤና ባለሙያዎች እና መምህራን የደመወዝ ጭማሪ ጋር የተያያዘ ጥያቄ ይገኝበታል።

ጥያቄው የቀረበው በምክር ቤት አባሉ አቶ ግዛቸው አየለ ነው።

ምን አሉ ?

" የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ግሽበት ከፍተኛ ጫና እያሳደረባቸው ካሉ የህብረተሰብ ክፍሎች የመንግሥት ሰራተኛው በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል።

በዚህ ምክንያት የጤና ባለሙያዎችን እና መምህራንን ጨምሮ የተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ የመንግሥት ሰራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ እንዲደረግ ጥያቄ እያነሱ ይገኛሉ።

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር የመንግሥት ሰራተኛን የኑሮ ደረጃ ከማሻሻል አኳያ በመንግሥት ምላሽ ዙሪያ ማብራሪያ ቢሰጥበት።

በተጨማሪ መንግሥት የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ እንዳለ ይታወቃል ይሁን እንጂ ካለው የቤት ፈላጊ ቁጥር ጋር ተነጻጽሮ ሲታይ ገና ብዙ ስራ ይጠይቃል። መንግሥት በአጭር፣ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ በከተሞች የሚታየውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት ምን እየሰራ ይገኛል ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

የምክር ቤቱ ስብሰባ በብሔራዊ ቴሌቪዥን ቀጥታ እየተላለፈ ይገኛል።

በተጨማሪ በምክር ቤቱ የዩትዩብ ገጽ መከታተል ይቻላል ፦ https://www.youtube.com/live/yLIns-2_vZM?feature=shared

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤790🙏78😡52😭26🤔19👏11😱6😢6🥰3
TIKVAH-ETHIOPIA
#HoPR🇪🇹 " የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ግሽበት ከፍተኛ ጫና እያሳደረባቸው ካሉ የህብረተሰብ ክፍሎች የመንግሥት ሰራተኛው ግንባር ቀደም ነው ! " - የምክር ቤት አባል የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተዋል። የምክር ቤቱ አባላትም ጥያቄያቸውን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እያቀረቡ ይገኛሉ። እስካሁን ከቀረቡ ጥያቄዎች መካከል ከኑሮ ውድነት፣ ከመንግሥት ሰራተኞች…
#HoPR🇪🇹

" በዝቋላ አቦና በተለያዩ ገዳማት ምንም መሳሪያ ያልታጠቁ መናኞች እና የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን ከሞት እና ከድብደባ ለመታደግ አግባብ ያለው የጸጥታ ሃይል የማይመድበው ለምንድነው ? " - የምክር ቤት አባሉ አበባው ደሳለው (ዶ/ር)

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉና አማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አባሉ አበባው ደሳለው (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ን ምን ጠየቁ ?

አበባው ደሳለው (ዶ/ር) ፦

" የመንግሥት ሰራተኞች እና ዝቅተኛው የማህበረሰብ ክፍል በተደጋጋሚ በአሁን ሰዓት ያለውን የኑሮ ውድነት መቋቋም እንዳቃታቸው ይገልጻሉ።

እንደመገለጫም ፦
- እራሳቸውን እና ቤተሰባቸውን አብልቶ ማሳደር
- የቤት ኪራይ መክፈል
- የልብስ እና የትምህርት ወጪዎችን መሸፈን ዳገት እንደሆነባቸው ይዘረዝራሉ።

ከዚህ ጋር በተገናኘ የህክምና ባለሙያዎች የስራ ማቆም አድማ በማድረግ መሰረታዊ የዳቦ ጥያቄያቸው እንዲፈታ ጠይቀዋል። ሆኖም ግን መንግሥት ይህንን መሰረታዊ ጥያቄ የፖለቲካ ስም በመስጠት ጥያቄያቸው ሳይፈታ ተዳፍኖ ቀርቷል።

ለመሆኑ መንግሥት ' ድሃ ተኮር ኢኮኖሚ ሪፎርም አራማጅ ነኝ ' እያለ የመንግሥት ሰራተኛውን እና ዝቅተኛውን የማህበረሰብ ክፍሎችን ኑሮ ለማሻሻል ስራ የሚጀምረው መቼ ነው ?

ከዚህ ጋር በተገናኘ አጠቃላይ የኢኮኖሚው አካሄድ ላይ ጥያቄ ይነሳበታል። የኢኮኖሚክ ባላንሱ ችግር እንዳለበት ይነሳል። የተለያየ ጥረት እየተደረገ ነው inflation (የዋጋ ግሽበት) ለመቀነስ ግን IMF እኛን የሚደግፍ ኢኮኖሚክ ሪፎርሙን፣ ዓለም ባንክ ፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ አሶሴሽን  ሳይቀር በጣም ፈተናዎች እንዳሉ ከኢኮኖሚክ ሪፎርሙ ጋር በተያያዘ ይገልጻሉ። ለምሳሌ ፦
° ከፍተኛ የዋጋ ግሽበት እንዳለ፣
° ገበያ ተኮር ምንዛሬ በመጠቀማችን ምክንያት የብር ዶላር ልዩነት ከፍተኛ መሆኑ፣
° በህዝብ ስም የተበደርነው ዕዳ እጅግ ከፍተኛ እንደሆነ፣
° ከፍተኛ ስራ አጥነት እንዳለ በአሁን ሰዓት በየአመቱ 2 ሚሊዮን ስራ አጦች እንደሚቀላቀሉ ይገለጻልና ይሄንን ችግር እንዴት ነው የምንፈታው በተለመደው አዙሪት ውስጥ ነው ወይ የምንቀጥለው ? ከኢኮኖሚ ችግሩ ለመውጣት ምን የታሰበ ነገር አለ ?

ሁለተኛ በዝቋላ አቦና በተለያዩ ገዳማት ምንም ጦር መሳሪያ ያልታጠቁ የሰማይ ቤትን ታሳቢ ያደረጉ መናኞች ላይ በተደጋጋሚ ጥቃት እየተፈጸመ ለሞት፣ ለድብደባ እና እንግልት ሲዳረጉ ይታያል። ለመሆኑ መንግሥት እንደዚህ ያለ ተደጋጋሚ የንጹሃን የቤተክርስቲያን አገልጋዮችን ከሞት ፣ ከድብደባና እንግልት ለመታደግ አግባብ ያለው የጸጥታ ኃይል የማይመድበው ለምንድነው ?

ሶስተኛ መንግሥት ከፋኖ ፣ ከሸኔና ሌሎች የታጠቁ ኃይሎች ጋር ያለው የጸጥታ ችግር በድርድር እንዲፈታ ፣ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ (ከፖለቲካ እስረኞች ጋር ለተገናኘ በተደጋጋሚ ያቀረብነው ጥያቄ ነው) ጅምላ ጭፍጨፋ የመሩ የህወሓት ባለስልጣናት በቶሎ ነበር የተፈቱት ነገር ግን እንደዚህ አይነት ተሳትፎ (involvement) የሌላቸው የአማራ ፖለቲከኞች ፣ አንቂዎች፣ ጋዜጠኞች ከታሰሩ 2 ዓመት ሞልቷቸዋል።

የፍትህ ስርዓቱ በጣም ዘገምተኛ ነው፤ ቶሎ እየተፈታ አይደለም ፤ ምንም ምስክርም እየተሰማባቸው አይደለም በጄኖሳይድ ወይም በጦርነቱ ቀጥተኛ ተሳታፊ እንደሆኑ የሚያመለክት ነገር የለም ግን በእስር ቤት እየተሰቃዩ ይገኛሉ። አማራ ክልል ብቻ አይደለም ኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል፣ ደቡብ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ከተለያዩ የምክር ቤት አባላት ጋር ባደረግነው ንግግር እንደዚህ አይነት ተመሳሳይ ችግር አለ። ቶሎ ፍትህ የማግኘት ችግርን በኢትዮጵያ መቼ ነው የምንቀርፈው ? የረፈደ ፍትህ እንደተነፈገ ይቆጠራልነውና።

ሌላው ድሮንን ጨምሮ በሌሎች ከባድ መሳሪያዎች ጭምር ንጹሃን እንዳይጠፉ የምክር ቤት አባላት፣ የሰብዓዊ መብት ተቋማት ፣ኃያላን መንግሥታት አሜሪካን ጨምሮ ስንወተውት ቆይተናል። የተለያዩ መግለጫዎች ኃያላን መንግሥታት ጭምር ሲያወጡ ይታያል። ሆኖም ግን በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በተለይም በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል፣ ደቡብ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ የመሳሰሉ ክልሎች ላይ የጸጥታ ችግሩ እስካሁን አልተቀረፈም።

ከዚህ ጋር በተገናኘ ' አግዙን ' ባሉን መሰረትም ሰላሙን ለማምጣት ወደ እርሶ ቢሮ መልዕክተኛ ብንልክም አልተሳካልንም። እንጂ እኛ ፖለቲከኞች፣ ተቃዋሚዎች ችግር መፍጠር ሳይሆን ችግሩ እንዲፈታ ቀረብ ብለን መነጋገር እንፈልጋለን ነገር ግን ያን መድረክ ልናገኝ አልቻልንም። ከዚህ ጋር በተገናኘ ምን የሚሉን ነገር አለ ሰላሙን ለማምጣት።

አራተኛ በተለያዩ አዲስ አበባ አካባቢዎች በሌሎች ትላልቅ የክልል ከተሞች ላይም ይሄ ችግር አለ ከ1998 ዓ/ም ጀምሮ መኖሪያ ቤት ሰርተው ፣ ውሃና መብራት አስገብተው፣ በርካታ የልማት ስራዎችን የሰሩ፣ መንግሥትዎን በድጋፍ ያገለገሉ ዜጎችን ያለምንም ምትክ ቤት ፣ መሬትና የገንዘብ ካሳ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው አቤቱታቸውን ይዘው የተለያዩ ቢሮዎች ቢሄዱም ጥያቄያቸው ውድቅ ሆኗል።

እነዚህ ሰዎች የሚያመለክተት ' ነገር ከ1998 ጀምሮ ነው ህገወጥ ከሆንን እናፍርስና በኮንዶሚኒየም እንደራጅ ' ስንል አይ ' እናተ ሰነድ አልባ ናችሁ እንጂ ህገወጥ አይደላችሁም በቅርቡ ህጋዊ እናደርጋችኃለን ' ተብለው እንደነበር ነው የሚያስታውሱት። በቅርቡ ያወጣነው አዋጅ አለ ከከተማ መሬት ጋር በተገናኘ ከ2004 ዓ/ም በፊት የተሰሩ ህገወጥ ቤቶች ህጋዊ እንደሚሆኑ የሚያመለክትና እነዚህን ሰዎች ለምድንነው በአግባቡ የማይስተናገዱት። የተለያዩ ቢሮዎች ሄደዋል አልተሳካላቸውም። በመጨረሻም እርሶን እንድጠይቅላቸው በመቶዎች የሚቆጠሩ ከሁለት ቀበሌ የተፈናቀሉ ከሰነድ ጋር ነው ያቀረቡልኝ። አመሰግናለሁ። "

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
2❤2.22K👏267🙏97😭35😡21🤔14🥰11🕊11😢8😱4
TIKVAH-ETHIOPIA
#HoPR🇪🇹 " በዝቋላ አቦና በተለያዩ ገዳማት ምንም መሳሪያ ያልታጠቁ መናኞች እና የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን ከሞት እና ከድብደባ ለመታደግ አግባብ ያለው የጸጥታ ሃይል የማይመድበው ለምንድነው ? " - የምክር ቤት አባሉ አበባው ደሳለው (ዶ/ር) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉና አማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አባሉ አበባው ደሳለው (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ን ምን ጠየቁ…
#ኢትዮጵያ🇪🇹

" የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ በቅርቡ ይጀመራል፤ ከ40 ወራት በኋላም ተጠናቅቆ ስራ ይጀምራል " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምን አሉ ?

" ኢትዮጵያ ከፍተኛ የማዕድን አቅም ያላት ሀገር ናት፤ በአፍሪካ ውስጥ ትላልቅ የማዕድን አቅም ካላቸው ሀገራት አንዷ ናት ፤ እስካሁን የትክረት የአመራር፣ የዕይታ ማነስ ስለነበረ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ማገዝ ይችል ነበር። አሁን እያነቃቃነው ነው።

ወርቅ ባለፈው ዓመት በዚህ ዓመት 37 ቶን ወርቅ ኤክስፖርት አድርገነዋል። 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ኤክስፖርት ዓመት ያገኘነውም ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተን ስለሰራን ነው። ይህ በየትኛውም ዘመን ያልነበረ ስኬተ ነው። ሌላው ጋዝ ነው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ በጋዝ ላይ የሚሰማሩ ኩባንያወች ፈቃድ አውጥተው ወደ ተጨባጭ ስራ አይገቡም ነበር።

ኢትዮጵያ የጋዝ ምርት በቅርቡ ለገበያ ማቅረብ ትጀምራለች። በዚህም ሰርቶ አዳሪ እንጂ አውርቶ አዳሪ አለመሆናችንንም በተከታታይ እያሳየን እንቀጥላለን። የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ በቅርቡ ይጀመራል፤ ከ40 ወራት በኋላም ተጠናቅቆ ስራ ይጀምራል። "

Credit : PMO Ethiopia

@tikvahethiopia
😡917❤713😭54👏33🤔31🙏15🕊14😱13💔10🥰8😢5
2025/07/12 14:18:43
Back to Top
HTML Embed Code: