Telegram Web Link
TIKVAH-ETHIOPIA
#HoPR🇪🇹 " 3.5 ቢሊየን ዶላር ከዚህ ቀደም የነበሩ መንግስታት የተበደሩትን ገንዘብ ያለፉትን ሶስት እና አራት አመታት ተደራድረን የእዳ ሽግሽግ እንዲኖር አድርገናል የገንዘብ ሚንስቴር በትላንትናው እለት በፈረንሳይ ተፈራርሟል" - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከምክር ቤት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ። የበጀት አመቱን አፈጻጸም…
#Ethiopia 🇪🇹
#GERD 🇪🇹

" መስከረም ላይ ዝናብ ጋብ ሲል ህዳሴን እናስመርቃለን !!! "

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በሚመለከት ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምን አሉ ?

" ህዳሴ አልቋል። ህዳሴን እናስመርቃለን። ህዳሴ ከመመረቁ በፊት ' ብንረብሽ ' ብለው የሚያስቡ ሰዎች አሉ ፤ እናስመርቃለን።

ህዳሴን እንዳይመረቅ ለማድረግ የሚያስችል ነገር አሁን የለም። የሚመረቀውም አሁን ነው ነገ ክረምቱ ሲያልቅ።

ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ያለኝ መልዕክት ህዳሴ ለሱዳን ህዳሴ ለግብፅ በረከት ነው። በፍጹም ጉዳት አያመጣባቸውም። ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ልማት ልማታቸው ነው ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ኢነርጂ ለሁሉም ጎረቤቶች የሚዳረስ ነው።

የኛ ግድብ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራትን የሚጎዳ ቢሆን ኖሮ ቱርካና አጀንዳ አይሆንም ነበር። ታስታውሳላችሁ ግቤ 3 ሲሰራ 'ቱርካና ይደርቃል የሚል ከፍተኛ ችግር ነበር። እንኳን ሊደርው ከግድቡ በኋላ ይኸው ሞልቶ እያስቸገረ ነው ያለው።

አሁንም ግብፅ ብትሄዱ የግብፅ አስዋን ግድብ አንድ ሊትር ውሃ አልቀነሰም። ወደፊትም ኢትዮጵያ እስከበለጸገች ድረስ እስካለች ድረስ የግብፅ ወንድሞቻችንን ጉዳት እኛ አናይም ተባብረን ከወንድሞቻች ጋር ማደግ እንፈልጋለን።

ግብፅ እንድትጎዳ ፣ ሱዳን እንድትጎዳ አንፈልግም። ኢነርጂውን በጋራ እንጠቀማለን ውሃውን በጋራ እንጠቀማለን ልማት በጋራ ይመጣል። ንግግር ካስፈለገ እንነጋገራለን ችግር የለም።

እኛ ለረጅም ጊዜ ስናነሳ የነበረው ' አትስሩ ' አትበሉን ነው ያልነው እንጂ በኛ ገንዘብ በኛ ምድር የሚሰራውም ስራ አታግዱ ነው ያልነው እንጂ ያን እስካልከለከሉ ድረስ አሁንም ከግብፆች ጋር ለመነጋገር፣ ለመደራደር ፣ ለመስራት ኢትዮጵያ ዝግጁ ናት፤ምንም ችግር የለብንም።

በእርግጠኝነት የምናገረው ህዳሴ ለግብፅም ለሱዳንም ጉዳት አያመጣም።

በዚሁ አጋጣሚ በኢትዮጵያ ውስጥ ትልቁ የስልጣን ባለቤት ይህ የተከበረው ምክር ቤት ስለሆነ ለግብፅ መንግሥት ፣ ለሱዳን መንግሥት እንዲሁም ለተፋሰሱ ሀገራት መንግሥታት በሙሉ መስከረም ዝናብ ጋብ ሲል ህዳሴን ስናስመርቅ የደስታችን ተካፋይ እንዲሆኑ ግብዣ አቀርብላቸዋለሁ።

የጋራ ሃብታችን ነው ፤ በጋራ እናስመርቀዋለን በጋራ እናየዋለን፣ የሚታዩ ጉዳዮች ካሉ በጋራ እናያለን።

ከድርቅ ጋር ተያይዞ ግብፅ የሚነሳው ነገር ' ድርቅ በሚሆንበት ሰዓት ግብፅ ትጎዳለች ' ነው ፤ ድርቅ የሚባለው ኢትዮጵያ ነው ኢትዮጵያ ከደረቀች ውሃዋ የለም  ማለት ነው እዛ አይደለም ድርቅ የሚባለው፤ ኢትዮጵያ ደግሞ እንዳትደርቅ Green Legacy (አረንጓዴ አሻራ) እየሰራን ነው እኛ አንደርቅም ማለት ነው እኛ ዝናብ ካገኘን እኛም ግብፅም ሱዳንም ሌሎቹም ይጠቀማሉ። በቅንነት አይተን በጋራ ለልማት እንድንሰራ አደራ እላለሁ። "

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤2.36K😡335👏126🙏55🤔36🕊25😱16😭14🥰13😢9💔3
የፌዴራል መንግሥት በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ ፀደቀ።

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ ባካሄደው 6ኛው ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 42ኛ መደበኛ ጉባኤ የ2018 ዓ/ም የፌዴራል መንግስት በጀት 1.93 ትሪሊዮን ብር አድርጎ አፅድቋል።

@tikvahethiopia
😡1.12K❤508🤔133😭81😱46👏45🕊35🙏27😢25💔11🥰7
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia 🇪🇹 #GERD 🇪🇹 " መስከረም ላይ ዝናብ ጋብ ሲል ህዳሴን እናስመርቃለን !!! " የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በሚመለከት ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምን አሉ ? " ህዳሴ አልቋል። ህዳሴን እናስመርቃለን። ህዳሴ ከመመረቁ በፊት ' ብንረብሽ ' ብለው የሚያስቡ ሰዎች አሉ ፤ እናስመርቃለን። ህዳሴን እንዳይመረቅ ለማድረግ የሚያስችል ነገር አሁን የለም። የሚመረቀውም አሁን ነው…
" በዝቋላ አንድ አባት ተገድለዋል ማን እንደገደላቸው እየተጣራ ነው ያለው á‰°áŒŁáˆ­á‰ś ምላሽ እንደሚያገኝ ተስፋ አደርጋለሁ "- ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ባለው ደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ገዳም “የሸኔ ታጣቃዎች” ባህታውያን አባቶች በሚኖሩባቸው ዋሻዎች ተኩስ መክፈታቸውን ገዳሙ ማሳወቁ ይታወሳል።

ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ አንድ አባት መገደላቸውን እና ሟቹ አባት ባህታዊ አባ ኃይለሚካኤል እንደሚባሉ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከገዳሙ ባገኘው መረጃ መዘገቡ ይታወሳል።

በተደጋጋሚ በገዳሙ እያጋጠመው ስላለው የመነኮሳት ግድያ መንግስት ለምን ማስቆም ተሳነው ሲሉ በዛሬው እለት የምክር ቤት አባሉ አበባው ደሳለው (ዶ/ር) ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥያቄ አቅርበዋል።

የአብን አባሉ አቶ አበባው " በዝቋላ ምንም መሳሪያ ያልታጠቁ መናኞች እና የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን ከሞት እና ከድብደባ ለመታደግ አግባብ ያለው የጸጥታ ሃይል የማይመድበው ለምንድነው " ሲሉ ጥያቄያቸውን አንስተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ በዝቋላ አንድ መናኝ መገደላቸውን አረጋግጠዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዝርዝር በሰጡት ምላሽ ምን አሉ ?

" ' መሻቴን ፍላጎቴን በሃይል ማስፈጸም እችላለሁ ' የሚሉ ሃይል በብቸኝነት የመጠቀም ስልጣን የመንግስት ብቻ መሆኑን የማይቀበሉ ሰዎች ናቸዉ።

እንዳሉት በዝቋላ አንድ አባት ተገድለዋል ማን እንደገደላቸው እየተጣራ ነው ያለው  ተጣርቶ ምላሽ እንደሚያገኝ ተስፋ አደርጋለሁ።

የሃይማኖት ተቋማት የታጠቁ ሽፍቶች መሸሸጊያ ከሆኑ እንደዚህ አይነት አደጋ ሊፈጠር ይችላል የሃይማኖት ቦታ የሃይማኖት ብቻ መሆን አለበት ሲሸሹ የሚደበቁበት ከሆነ ሲከፋቸው ገድለው ሊሄዱ ስለሚችሉ።

የዝቋላው ምን ይገርማል 12 አመት ተምሮ ፈተና ሊፈተን የሚሄድ ሰው ላይ የሚተኩሱ ሰዎች ዝቋላ ላይ አንድ አባት ላይ ቢገድሉ ምን ይገርማል።

የግድያው እሳቤ ነው ችግር ያለው ፈተና አትፈተን፣ ማዳበሪያ አትውሰድ ፣ትምህርት አትማር ብሎ የሚገድል ሰዉ ኢትዮጵያ ውስጥ ካለ የትም ሞት አለ ማለት ነው።

'ልብ ሲያቅ ገንፎ ያንቅ ይባላል'  ልባችን ያውቀዋል እነማን እንደሆኑ፤ ድብብቆሽ አይደለም። እነማን ገዳይ እንደሆኑ ግልጽ ነው። 'ልብ ሲያቅ ገንፎ ያንቅ' የመባለው እያወቅነው የምናግበሰብሰው ጉዳይ ሲሆን ነው።

ግድያ ሽንፈት ብቻ ነው የሚያመጣው በመግደል አይሳካልኝም ብሎ ማመን ያስፈልጋል። ... በሃይል ፍላጎትን ማስፈጸም ማለቂያ የለውም መቆም አለበት። " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😡3.23K❤1.36K😭191💔86🕊56🙏34🤔33😢32👏25😱18🥰6
TIKVAH-ETHIOPIA
" በዝቋላ አንድ አባት ተገድለዋል ማን እንደገደላቸው እየተጣራ ነው ያለው á‰°áŒŁáˆ­á‰ś ምላሽ እንደሚያገኝ ተስፋ አደርጋለሁ "- ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ባለው ደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ገዳም “የሸኔ ታጣቃዎች” ባህታውያን አባቶች በሚኖሩባቸው ዋሻዎች ተኩስ መክፈታቸውን ገዳሙ ማሳወቁ ይታወሳል። ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ አንድ አባት መገደላቸውን…
" ጦርነት ከተጀመረ ከዚህ በፊት እንደምናቀው አይደለም ነገር ይበላሻል !! " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ዛሬ በነበረው የህ/ተ/ም/ቤት ጉባኤን አንድ አባል " በትግራይ ክልል ዳግም ጦርንት እንዳይነሳ ስጋት አለ " በማለት በክልሉ ስላለው አሁናዊ የፖለቲካ እና የጸጥታ ሁኔታ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ማብራርያ እና ምላሽ ጠይቀዋል።

" ህወሓት ለዳግም ግጭት ቅስቀሳ እያደረገ ነው "  በማለት " ከሰላም ወዳዱ የትግራይ ህዝብ፤ ምሁራን እና ወጣቶች ምን ይጠበቃል ? " ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምን መለሱ ?

" የሁሉም እምነት አባቶች እዚህ ተወካይዎች አላችሁ፣ ሌላ ምንም ስራ የላችሁም በፍጥነት ትግራይ ወደ ግጭት፣ ወደ ጦርነት እንዳይገባ ስራችሁን አሁን ጀምሩ፣ ከተጀመረ ወዲያ ብትናገሩ ዋጋ የለውም።

ባለሃብቶች፣ ምሁራን፣ ኤምባሲዎች ውጊያ እንዳይጀመር አሁን ሚናችሁን ተወጡ ምክንያቱም ከተጀመረ ከዚህ በፊት እንደምናቀው አይደለም ይበላሻል ነገር።

በእኛ በኩል በትግራይ ምድር እንድ ጥይት የመተኮስ ፍላጎት የለንም፣ ከቻልን ማልማት ነው የምንፈልገው።

ትግራይ ላሉ ሃይሎች ለትግራይ ህዝብም፣ ለኢትዮጵያ ህዝብም መታወቅ ያለበት ጦርነት አያስፈልገንም በሰላም እና በውይይት ጉዳያችንን መፍታት ይቻላል " ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
❤1.02K😡397🕊89😭24🤔23🙏13💔11👏10😢10🥰1
TIKVAH-ETHIOPIA
" ጦርነት ከተጀመረ ከዚህ በፊት እንደምናቀው አይደለም ነገር ይበላሻል !! " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ በነበረው የህ/ተ/ም/ቤት ጉባኤን አንድ አባል " በትግራይ ክልል ዳግም ጦርንት እንዳይነሳ ስጋት አለ " በማለት በክልሉ ስላለው አሁናዊ የፖለቲካ እና የጸጥታ ሁኔታ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ማብራርያ እና ምላሽ ጠይቀዋል። " ህወሓት ለዳግም ግጭት ቅስቀሳ እያደረገ ነው "  በማለት " ከሰላም…
" እነዚህ ሀገራት እንኳንስ እናተን እራሳቸውንም ማገዝ አይችሉም ! " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግራይ ጉዳይ ያነሷቸው ነጥቦች ምንድናቸው ?

- ፕሪቶሪያ ለትግራይ ህዝብ እፎይታ አምጥቷል።

- ትግራይ ቴሌኮሚኒኬሽን ፣ መብራት ፣ ባንክ ፣ የአየር ትራንስፖርት፣ ምርት  አልነበረም ፣ ፋብሪካዎችም ሾል አቁመው ነበር ይሄ ሁሉ ጀምሯል።

- ትግራይ ክልል መንግሥት አልነበረም መንግሥት ተቋቁሟል።

- የተፈናቀሉ ሰዎች ራያ ፣ ፀለምት ተመልሰዋል።

- ወልቃይት የተፈናቀሉ አልተመለሱም DDR አልተፈጸመም።

- የወልቃይት ተፈናቃዮች መመለስ አለባቸው መንግሥት የፀና አቋም አለው። DDR መፈጸም አለበት። በነዚህ ጉዳዮች የፌዴራል ችግር አስመስሎ ለመሳል ይሞከራል ስህተት ነው። የፌዴራል መንግሥት በትግራይ ያለውን ጉዳይ በሰላም የመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት አለው።

- ለአንዳንዶች ውጊያ ጨዋታ ሊሆን ይችላል ለህዝባችን ፃረሞት ነው።

- ለአንዳንዶች ስለውጊያ እያነሱ መናገር ምንም ላይመስል ይችላል ስለማይሞቱ ለወጣት ግን ጉዳት ነው።

- የትግራይ ህዝብ 100% ጦርነት አይደልግም አይቶታል ትርፍ የለውም።

- ዓለም ትግራይ እና ምናምን ቢዋጉ ደንታው አይደለም ብዙ ውግያ እያስተናገደ ስለሆነ፤ ጆሮም የለውም ጊዜም የለውም። ዓለም ጊዜ ቢኖረው ኖሮ ሱዳንን ያዳምጥ ነበር።

- የዘመኑን የውጊያ ስልት መገንዘብ ይገባል ፤ አሁን እንደ ድሮ ተራራ መያዝ ተራራ መልቀቅ ብቻ ማሰብ ትክክል አይደለም። ኢራንን እና እስራኤልን ያዋጋው ተራራ አይደለም። ዘመን ተቀይሯል።

- አንዳንዶች " መንግሥት ተወጥሯል በፋኖ ፣ በሸኔ ወታደሩ ተበታትኗል አሁን ነው ጊዜው " የሚሉ ሰዎች አሉ እነዚህ ሰዎች ታሪክን መለስ ብለው ማየት አለባቸው። ሶማሊያ ኢትዮጵያን ስትወር ኢትዮጵያ ወታደር አልነበራትም ፤ ጣልያን ኢትዮጵያን ስትወር ወታደር አልነበራትም። ስለዚህ ኢትዮጵያ ራሷን ለመከላከል የግድ ሰልፍ የያዘ ወታደር አያስፈልጋትም።

- " የሚያግዙን ሰዎች አሉ ፤ የሚያግዙን ሀገራት አሉ " ብሎ ማሰብ በጣም የሚያሳዝነው ሌላው ጉዳይ ነው። እነዚህ ሀገራት እንኳንስ እናተን እራሳቸውንም ማገዝ አይችሉም። ሞራል ቲፎዞነትና ማገዝ ለየብቻ ነው። በትላልቅ ውጊያ እንኳን መደጋገፍ ችግር ሆኗል፤ እንኳንስ በሰፈር ውጊያ። የዓለም ኢኮኖሚ ከራስ ተርፎ ሰው ለማገዝ የሚያስችል ነገር ብዙ የለም ካለም ጥቂት ብቻ ነው።

- ትግራይ የሚያስፈልገው ሰላም ነው በንግግርና ውይይት ችግር መፍታት ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
❤1.48K😡325🕊74🤔37👏33🙏27😢13😭12💔3😱1
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#NationalExam🇪🇹

ፆታዊ ትንኮሳ የፈፀሙ ሦስት ተማሪዎች ከሀገር አቀፍ ፈተና ታገዱ።

በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተሰጠ ባለው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመፈተን ወደ መቱ ዩንቨርስቲ ከገቡት ተማሪዎች ውስጥ ሦስት ተማሪዎች በሴት ተማሪዎች ላይ ዕፆታዊ ትንኮሳ በመፈፀማቸው ከፈተናው መታገዳቸውን የመቱ ዩንቨርስቲ አስታወቀ።

ዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት አለሙ ድሳሳ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ " በርካታ ተማሪዎች ወደ ግቢ ከገቡ በኃላ ወጣ ያለ ፀባይ እያሳዩ ነበር " ብለዋል።

ዩኒቨርስቲውም ለፈተናው ከተቋቋመ ኮማንድፖስት ጋር በመሆን የመቆጣጠር ሥራ ሲሰራ እንደነበር በማንሳት፤ ሦስቱ ተማሪዎች በሴት ተማሪዎች ላይ ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም አደባባይ ላይ ትንኮሳ መፈፀማቸውን ተበድለናል ብለው በመጡ ሴቶች ቅሬታ እና ዩንቨርስቲውም ባደረገው ማጣራትብ ድርጊቱን መፈፀማቸውን አረጋግጧል።

" ትንኮሳ አድራጊዎቹ በአደባባይ ሴቶችን በግድ መሳም፤ ልብሳቸውን መገለብ እና መንካት የማይፈቀድ የአካላቸውን ክፍል በመንካታቸው ሴቶቹ ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት ህጋዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል " ብለዋል።

በዚህ የተነሳ የትንኮሳ ወንጀል በፈፀሙ ወንዶች ላይ ከዘንድሮው አመት ፈተና እንዲታገዱ መደረጉን ገልጸዋል።

ተማሪዎቹ አንዱ ከኢሉ አባቦር ዞን በቾ ወረዳ ሁለቱ ደግሞ ከምስራቅ ወለጋ የመጡ መሆናቸውን ፕረዝዳንቱ አክለዋል።

እርምጃ ከተወሰደ በኃላ በግቢው ሲስተዋል የነበረው የተማሪዎች ሥነ ምግባር መሻሻሉንም ተናግረዋል።

ወደፊትን ተመሳሳይ ችግሮች እንዳይፈጠር ትምህርት ቤቶች የፈተና ሥነ ምግባር ላይ ለተማሪዎች ግንዛቤ መስጠት እንዳለባቸው የገለፁት አለሙ ድሳሳ (ዶ/ር) ሴት ተማሪዎችም ራሳቸውን እንዲጠብቁና ለትንኮሳ ራሳቸውን እንዳይጋብዙም ጠይቀዋል።

የመቱ ዩንቨርስቲ በዘንድሮው ለ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ14,000 በላይ ተማሪዎችን ለመፈተን መቀበሉንም ዩንቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር አለሙ ድሳሳ አክለው ገልፀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነቀምቴ
#TikvahEthiopiaFamliyNekemte

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
8❤2.59K👏976😡158🤔77😭73🕊40😱39💔25😢16🙏13🥰10
አፍሪካ ከአፍሪካውያን አልፎ ለዓለም የሚተርፍ የመልማት ፀጋ የተጎናፀፈች የወጣቶች አህጉር ናት!

ባለፉት ሁለት ዓመታት አፍሪካ ያላትን እምቅ አቅም ወደ ተጨባጭ ሀይል ለመቀየር፣ የሥራ አጥነት ትርጉም ባለው መልኩ ለመቀነስ፣ ፍትሃዊ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትንና አህጉራዊ ትስስርን ከፍ ለማድረግ በማለም የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም ተካሂዷል፡፡

ዘንድሮም ለ 3ኛ ጊዜ ሦስተኛው የአፍሪካ የሥራ ዕድል ፈጠራ ፎረም ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 2/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል፡፡

የፎረሙ ዋና አላማ በስራ ዕድል ፈጠራ መስክ የግብርና እሴት ሰንሰለት፣ ዲጂታላይዜሽንና የፋይናንስ አካታችነትን በማረጋገጥ ምቹና አስተማማኝ የሥራ ዕድል ለመፍጠር የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ትስስርን ማላቅ ነው፡፡

በዚህ ታላቅ የፓን አፍሪካን ፎረም መሪዎች፣ የፈጠራ ባለሙያዎች፣ ሥራ ፈጣሪዎች እና የዘርፉ ምሁራን በአፍሪካ የመጪው ዘመን ሥራ እና የጋራ ተጠቃሚነት ላይ ይመክራሉ፡፡

ከምክክሩ ጎን ለጎን አንድ መቶ የሚሆኑ ኢንተርፕራይዞች ምርትና አግልግሎታቸውን የሚያስተዋውቁበትና የገበያ ትስስር የሚፈጥሩበት ኢግዚቢሽንና ባዛር ይካሄዳል፡፡

በመሆኑም በአድዋ ድል መታሰቢያ በመገኘት ባዛሩን እንድትጎበኙና ሥራ ፈጣሪዎችን እንድታበረታቱ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል፡፡
❤400😡30🙏15😭11🕊8😱5😢3🥰2👏2🤔2
የትምህርት ቤት ክፍያዎን በቀላሉ በፀሐይ ባንክ በኩል ይክፈሉ!

እጅግ ዘመናዊ የሆነው የፀሐይ ኢ-ስኩል ሲስተም የሚሰጣቸው ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች ተጠቃሚ ይሁኑ!

ወቅቱ ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ምዝገባ የሚያደርጉበት ነው፡፡ ፀሐይ ባንክ የትምህርት ቤቶችን ምዝገባ እና ሌሎች ሥራዎችን የሚያቀላጥፍ ምርጥ መላ ይዞ መጥቷል፡፡

አሁኑኑ አቅራቢያዎ ወደሚገኝ የፀሐይ ባንክ ቅርንጫፍ በመሔድ የፀሐይ ኢ-ስኩል ሲስተም ተጠቃሚ ይሁኑ!

ሥራዎትን ያቀላጥፉ! ከባንካችን ጋር በመስራት የሚያገኙትን ጥቅም ያሳድጉ!

ፀሐይ ባንክ
ለሁሉ!


Telegram: https://www.tg-me.com/tsehaybanksc
❤129🤔6🙏5🥰2😢1
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#መቃ

ሰሞኑን " መቃ " ላይ ታጣቂዎች በሹፌሮች  ንፁሃን ዜጎችና የጸጥታ ኃይሎች ላይ አሰቃቂ ነው የተባለ ግድያ መፈጸማቸው ይታወሳል።

ከዛ በኋላ ምን ተፈጠረ ?

- ከታጣቂዎቹ ግድያ በኋላ በመንግሥት ጸጥታ ኃይል በተወሰደ እርምጃ ከ17 በላይ የአካባቢው አርሶ አደሮች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።

- በጫካ የሚገኘው የቅማንት ሀይል ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ " በእጀባ ላይ የነበሩ ሹፌሮች፤ ተሳፋሪዎችን እና የመንግስት ጸጥታ ኃይል ላይ ጥቃት ያደረሱት በውንብድና ተግባር የተሰማሩ ሽፍቶች ናቸው " ብሏል። " ሰኔ 16/2017 ዓ.ም የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ የመንግስት ታጣቂዎች በአካባቢው ያሉ በመጀመሪያው በሁለተኛው ቀናቶች ወደ áЍ17 በላይ ንፁሃን የአካባቢው ተወላጅ አርሶ አደሮችን ገድለዋል " ሲል ከሷል።

- የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ለጥቃቱ " ፅንፈኛው ቅማንት " ሲል የጠራውን ታጣቂ ኃይል ተጠያቂ ማድረጉ ይታወሳል።

- የብሄረሰቡ ተወላጅ የሆኑና በአካባቢው የሚኖሩ ስሜ አይጠቀስ ያሉ ግለሰብ " ጥቃቱን ተከትሎ የመንግስት ታጣቂዎች በወሰዱት እርምጃ ከ17 በላይ የአካባቢው ተወላጅ አርሶ አደሮች ተገድለዋል። ከተገደሉት መካከል ወንድሜ ይገኝበታል " ብለዋል።

- አንድ ሌላ ነዋሪ " የመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ታጣቂው የወሰደባቸውን የቡድን መሳሪያ ለማስመለስ ወደ መቃ ከተማ ተኩሰዋል፤ በርካታ ንፁሃን ተገድለዋል ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ የተገደሉትን ጨምሮ ከ17 በላይ ንፁሃን አርሶ አደሮች ተገለዋል " ሲሉ ተናግረዋል።

- በአሁኑ ሰዓት ቆስሎ ሆስፒታል የሚገኝ የዐይን እማኝ " ግጭቱ ከ10:30-11:00 ነበር የተካሄደው ታጣቂዎች አሽክርካሪዎችንና ተሳፋሪዎችን ተዟዙረው ገድለው ከጨረሱ በኃላ ተመልሰው ጫካ እስኪሄዱ ድረስ ከሞቱት ሰዎች ኪስ ግንዘብና ሞባይል እያወጡ ሲወስዱ በሞተ ሰው አስከሬን ተከልየ አይቻለሁ " ሲል ገልጿል። " ታጣቂዎቹ ወደ ጫካ ከሄዱ በኃላ መከላከያ መጥቶ አካባቢውን እስኪቆጣጠር እስከ ምሽቱ 2:30 ድረስ አስከሬን ሊያነሳ የመጣ ወጣት áŠ áˆ‹á‹¨áˆáˆ " ብሏል። የቆሰሉትን ሆነ የሞቱትን ሰዎች የመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ናቸው ከወደቁበት ያነሱት።

(ተጨማሪ ዝርዝሩ ከላይ ያንብቡ)

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ባሕር ዳር
#TikvahEthiopiaFamilyBahirdar

@tikvahethiopia
❤565😭154😡23🕊19🙏8😢7🤔5🥰4
TIKVAH-ETHIOPIA
" በፔይሮል የሚያገኘውን ብቻ በማሳደድ ሀገር ማሳደግ አይቻልም ! " የገንዘብ ሚኒስቴር ከሠራተኛ የሚቀነስ ግብርን ጨምሮ ሌሎች የገቢ ጉዳዮችን የሚመለከተውን የገቢ ግብር አዋጅ ለማሻሻል ባስደረገው ጥናት በየወሩ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ከግብር ነፃ የሚሆነው የትኛው የደሞዝ መጠን ላይ ነው ለሚለው ሦስት አማራጮችን አቅርቧል። እነዚህም 1,200፣ 1,600፣ ወይስ 2,000 ብር ከሚከፈላቸው ላይ ይሁን…
#Ethiopia🇪🇹

የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ እንደሚሻሻል ተገልጿል።

ዛሬ 48ኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ተካሂዶ የአዋጁ መሻሻል ላይ ውሳኔ አሳልፏል።

ምክር ቤቱ " ቀደም ሲል ሲሰራበት የነበረው የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ አሁን ከምንገኝበት ሀገራዊ እና አለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ አንጻር ሲታይ በርካታ ክፍተቶች ያሉበት ነው " ብሏል።

" የአዋጁን ድንጋጌዎች በማሻሻል የታክስ ስርአቱ መሠረታዊ የታክስ መርሆዎችን ለማሳካት በሚያስችል መልኩ እንዲቀረጽ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ የማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል " ሲል ገልጿል።

ምክር ቤቱ በማሻሻያ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ በሙሉ ድምጽ አጽድቆ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ መወሰኑን አሳውቋል።

ከሳምንታት በፊት የገንዘብ ሚኒስቴር ከሠራተኛ የሚቀነስ ግብርን ጨምሮ ሌሎች የገቢ ጉዳዮችን የሚመለከተውን የገቢ ግብር አዋጅ ለማሻሻል ባስደረገው ጥናት በየወሩ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ከግብር ነፃ የሚሆነው የትኛው የደሞዝ መጠን ላይ ነው ለሚለው ሦስት አማራጮችን አቅርቦ እንደነበር ፤ እነዚህም 1,200፣ 1,600፣ ወይስ 2,000 ብር ከሚከፈላቸው ላይ ይሁን የሚል እንደነበር መዘገቡ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማሕበራት ኮንፌደሬሽን በበኩሉ ዝቅተኛው ከግብር ነፃ መሆን ያለበት የደሞዝ መጠን 8,300 ብር ነው መሆን ያለበት በሚል ሲከራከር እንደነበር አይዘነጋም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤570😭85😡54🙏24😢9🥰5🤔3🕊1
" ሃይል እያቋረጥን ስራ ስንሰራ የነበረ በመሆኑ በምንፈልገው ደረጃ የሃይል መቆራረጡን እንዳንቀንስ የራሱን አስተዋጽኦ አድርጓል "- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

የኢትዮጵያ አሌክትሪክ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ሦስት ወራት ለክረምት ዝግጅት ሲያከናውን የቆያቸውን ስራዎች በሚመለከት በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥቷል።

አገልግሎቱ በከተማዋ ለሚያጋጥም የሃይል መቆራረጥ ምክንያት ናቸው ብሎ የለያቸውን የመስመሮች ከዛፍ ጋር የሚፈጥሩት ንክኪ እና የረገቡ መስመሮች ላይ የተለያዩ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን አሳውቋል።

ተቋሙ ባለፉት ሦስት ወራት ብቻም ከ 25 ሺ በላይ ለሃይል መቆራረጥ ምክንያት የሆኑ አነስተኛ እና ከፍተኛ ግኝቶች አግኝተናል ነው ያለው።

ለሃይል መቆራረጥ ምክንያት ናቸው ካላቸው ግኝቶች ውስጥም ተቋሙ መፍታት የቻለው 56 በመቶዎቹን ብቻ ነው።

የአገልግሎቱ የኔትወርክ ኢንፍራስትራክቸር እና ኮርፖሬሽን ኤክሰለንስ ዳይሬክተር አቶ ፈሪድ አብዱሰላም ምን አሉ ?

" በስታንዳርዱ መሰረት ሽቦዎች እርስ በእርስ ሊኖራቸው የሚገባው ርቀት ከ 40-60 CM ፣ ከግራ እና ከቀኝ ካሉ ህንጻዎች እና ዛፎች 3 ሜትር እንዲሁም ከመሬት ያለው ከፍታ 5.5 ሜትር ከፍ ማለት የሚጠበቅባቸው ቢሆንም ይህ ሳይሆን በመቅረቱ ብልሽት እና አልፎ አልፎም አደጋ እያጋጠመ ነው።

ባለፉት ሦስት ወራት ብቻም ከ 25 ሺ 973 በላይ ለሃይል መቆራረጥ ምክንያት የሆኑ አነስተኛ እና ከፍተኛ ግኝቶች አግኝተናል።

ከተገኘው ግኝት አብዛኛው ወይም 30 በመቶ የሚሆነው የ ሃይል መቆራረጥ ምክንያት ዛፎች ናቸው።

በመዲናዋ 7,277 የሚሆኑ መስመር ውስጥ የገቡ እና ከ ኤሌክትሪክ መስመር 3 ሜትር መራቅ ያለባቸው ዛፎች የተገኙ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 5 ሺ 585 የሚሆኑትን የማጽዳት ስራ ተሰርቷል።

ያረጁ እና መቀየር የሚያስፈልጋቸው የኤሌክትሪክ ገመድ ተሸካሚ ፖሎች ቁጥር ከ 6 ሺ 367 በላይ ናቸው እዚህም ላይ ስራዎች ተሰርተዋል ይህም ለ ሃይል መቆራረጥ 25 በመቶ ምክንያት ነው።

በተጨማሪም 2 ሺ 425 ከግንባታዎችና እርስ በእርስ የተቀራረቡ መሥመሮች፣ 6 ሺ 298 የረገቡ እና የተለያዩ የመስመር ችግር ያለባቸው ሆነው ተገኝተዋል።

ከ 25 ሺ ግኝቶች ውስጥ 56 በመቶ የሚሆነውን ችግር ፈተናል።

በከተማዋ 10 ሺ 498 ትራንስፎርመሮች ላይ በተደረገ ምርምራ መጠነኛ ችግርች አግኝተንባቸዋል ለዚህም መፍትሄ በመስጠት ላይ እንገኛለን።

ሃይል እያቋረጥን ስራ ስንሰራ የነበረ በመሆኑ በምንፈልገው ደረጃ የሃይል መቆራረጡን እንዳንቀንስ የራሱን አስተዋጽኦ አድርጓል።

የሃይል መቆራረጥ መንስኤዎች ለስራ በሚል የሚቋረጡ ፣በብልሽት እና በሃይል አቅራቢው በኩል የሚያጋጥሙ ችግሮች ተጨማሪ ምክንያት ናቸው " ብለዋል።

ተቋሙ 20 ሚሊየን ብር በመመደብ ከነገ ጀምሮ 100 ሺ ችግኞችን ለመትከል ማቀዱን በጋዜጣዊ መግለጫው ወቅት ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
❤512😡70😭22👏20🤔8🙏7🕊5😱4🥰2😢1
2025/07/09 15:31:58
Back to Top
HTML Embed Code: