#ሴጅ_ማሰልጠኛ_ኢንስቲትዩት
የሁለት ወር የጋዜጠኝነት የክረምት ስልጠና የፊታችን ሰኞ ሐምሌ 07/2017 ዓ.ም ይጀመራል።
በስልጠናው፦
👉 መሠረታዊ የጋዜጠኝነት መርሖች
👉 የመዝናኛ ፕሮግራም ጋዜጠኝነት፣ የፕሮግራም ዝግጅት እና ዶክመንተሪ ዝግጅት
👉 የሞባይል ጋዜጠኝነት እና YouTube Journalism አካቷል፡፡
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram Tiktok Linkedin
የሁለት ወር የጋዜጠኝነት የክረምት ስልጠና የፊታችን ሰኞ ሐምሌ 07/2017 ዓ.ም ይጀመራል።
በስልጠናው፦
👉 መሠረታዊ የጋዜጠኝነት መርሖች
👉 የመዝናኛ ፕሮግራም ጋዜጠኝነት፣ የፕሮግራም ዝግጅት እና ዶክመንተሪ ዝግጅት
👉 የሞባይል ጋዜጠኝነት እና YouTube Journalism አካቷል፡፡
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram Tiktok Linkedin
❤117🙏3😭2
#Tinsae #IDEXX
ትንሳኤ ኢንተርናሽናል ቢዝነስ ኢንተርፕራይዝ ከአይዴክስ (IDEXX) ላቦራቶሪስ ጋራ በጋራ በመሆን የውሃ ጥራት መመርመሪያ መሳሪያዎች ላይ ያተኮረ ዎርክሾፕ ከሰሞኑን አካሂዶ ነበር።
ወርክሾፑ ላይ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግስት እና የግል ተቋማት ተሳታፊ እንደነበሩ ድርጅቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
" መሳሪያዎቹ እጅግ በጣም ቀላል፣ ጊዜ ቆጣቢና በቀላሉ በአጭር ጊዜ ስልጠና በቀላሉ ለመስራት የሚያስችሉ " ናቸው ያለ ሲሆን " በተለይ Tecta B4 እና Teta B6 የተባሉት መሳሪያዎች እጅግ ዘመናዊ ከእጅ ንኪኪ ውጪ የሆኑ፣ ባንድ ጊዜ አራት ወይም ስድስት ናሙናዎችን ለመመርመር የሚያስችሉና ውጤቱንም በኢሜል ለሚመለከተው አካል የመላክ አቅም ያላቸው " ናቸው ሲል ገልጧል።
" ይኼንን የመሳሰሉት መሳሪያዎች በስፋት ወደ ስራ በሚገቡበት ጊዜ የሀገሪቱን የንፁህ ውሃ አቅርቦት እና ተደራሽነት ከፍ በማድረግ በተለይም በውሃ ወለድ የሚመጡ በሽታዎችን በከፍተኛ ደረጃ የሚቀንሱ ይሆናሉ " ብሏል።
ትንሳኤ ኢንተርናሽናል ከአይዴክስ (IDEXX) በተጨማሪ ሀክ (HACH) እና ሌሎች አለማቀፍ የውሃ መመርመሪያ አምራች ድርጂቶች ጋር ብቸኛ አቅራቢ በመሆን የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳለውና በዚህ ረገድ በሃገሪቱ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ላይ የራሱን አሻራ እያሳረፈ ያለ ተቋም መሆኑም አመልክቷል።
@tikvahethiopia
ትንሳኤ ኢንተርናሽናል ቢዝነስ ኢንተርፕራይዝ ከአይዴክስ (IDEXX) ላቦራቶሪስ ጋራ በጋራ በመሆን የውሃ ጥራት መመርመሪያ መሳሪያዎች ላይ ያተኮረ ዎርክሾፕ ከሰሞኑን አካሂዶ ነበር።
ወርክሾፑ ላይ ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግስት እና የግል ተቋማት ተሳታፊ እንደነበሩ ድርጅቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
" መሳሪያዎቹ እጅግ በጣም ቀላል፣ ጊዜ ቆጣቢና በቀላሉ በአጭር ጊዜ ስልጠና በቀላሉ ለመስራት የሚያስችሉ " ናቸው ያለ ሲሆን " በተለይ Tecta B4 እና Teta B6 የተባሉት መሳሪያዎች እጅግ ዘመናዊ ከእጅ ንኪኪ ውጪ የሆኑ፣ ባንድ ጊዜ አራት ወይም ስድስት ናሙናዎችን ለመመርመር የሚያስችሉና ውጤቱንም በኢሜል ለሚመለከተው አካል የመላክ አቅም ያላቸው " ናቸው ሲል ገልጧል።
" ይኼንን የመሳሰሉት መሳሪያዎች በስፋት ወደ ስራ በሚገቡበት ጊዜ የሀገሪቱን የንፁህ ውሃ አቅርቦት እና ተደራሽነት ከፍ በማድረግ በተለይም በውሃ ወለድ የሚመጡ በሽታዎችን በከፍተኛ ደረጃ የሚቀንሱ ይሆናሉ " ብሏል።
ትንሳኤ ኢንተርናሽናል ከአይዴክስ (IDEXX) በተጨማሪ ሀክ (HACH) እና ሌሎች አለማቀፍ የውሃ መመርመሪያ አምራች ድርጂቶች ጋር ብቸኛ አቅራቢ በመሆን የረጅም ጊዜ ልምድ እንዳለውና በዚህ ረገድ በሃገሪቱ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ላይ የራሱን አሻራ እያሳረፈ ያለ ተቋም መሆኑም አመልክቷል።
@tikvahethiopia
❤208🤔5🙏5🕊3🥰2😢1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ጥቆማ
(ለሚመለከተው አካል - አዲስ አበባ)
" በሰውና መኪና ላይ ወድቆ ጉዳት እንዳይደርስ መፍትሄ ይፈለግለት ! "
" ይህ በቪድዮው ላይ የምትመለከቱት የመብራት ኮንክሪት ፖል ታቹ ተበልቶ አልቆ ለመውደቅ ጫፍ ላይ ደርሷል። ከጎኑ ትራንስፎርመርንም አለ።
ቦታው ከጋርመንት ወደ ጀሞ አንድ ሲኬድ መብራት ተሻግሮ (ቫርኔሮ የመኖሪያ መንደር አካባቢ) ዘመን ማደያ ጋር ነው ሲሆን ብዙ ሰው የሚመላለስበት መኪናም የሚንቀሳቀስበት ነው።
ፖሉ ወድቆ በሰው እና በመኪና ጉዳት ሳያደርስ በፊት መፍትሄ ይፈለግለት። ወቅቱም ክረምት በመሆኑ ዝናቡና ንፋሱ ኃይለኛነውና ፈጣን መፍትሄ ይፈለግለት። " - ዮሴፍ (ከአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
(ለሚመለከተው አካል - አዲስ አበባ)
" በሰውና መኪና ላይ ወድቆ ጉዳት እንዳይደርስ መፍትሄ ይፈለግለት ! "
" ይህ በቪድዮው ላይ የምትመለከቱት የመብራት ኮንክሪት ፖል ታቹ ተበልቶ አልቆ ለመውደቅ ጫፍ ላይ ደርሷል። ከጎኑ ትራንስፎርመርንም አለ።
ቦታው ከጋርመንት ወደ ጀሞ አንድ ሲኬድ መብራት ተሻግሮ (ቫርኔሮ የመኖሪያ መንደር አካባቢ) ዘመን ማደያ ጋር ነው ሲሆን ብዙ ሰው የሚመላለስበት መኪናም የሚንቀሳቀስበት ነው።
ፖሉ ወድቆ በሰው እና በመኪና ጉዳት ሳያደርስ በፊት መፍትሄ ይፈለግለት። ወቅቱም ክረምት በመሆኑ ዝናቡና ንፋሱ ኃይለኛነውና ፈጣን መፍትሄ ይፈለግለት። " - ዮሴፍ (ከአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤645🙏209👏37😭37🕊18😱13🤔1
" ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች አርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ተወስደው ሕክምና እየተደረገላቸው ይገኛል" - ፖሊስ
በጋሞ ዞን ቦረዳ ወረዳ የጅብ መንጋ በሰዎች ላይ ጉዳት አደረሰ።
የቦረዳ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ም/ኮማንደር ስምዖን ለንበቦ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ትናንት ምሽት 1 ሰዓት ገደማ የጅብ መንጋ በወረዳዉ ወይደ መላቶ ቀበሌ በሰዎች ላይ ጉዳት ሰንዝሮ ስድስት ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።
በአከባቢው ከከተማ በቅርብ ርቀት ጥብቅ ደኖች መኖራቸውን የገለፁት ፖሊስ አዛዡ ጅቦች በጫካዉ ዉስጥ እንዳሉ ቢታወቅም እስካሁን በሰዉ ላይ ጉዳት አድርሰው እንደማያውቅና የትናንት ምሽቱ ጥቃት ድንገተኛ እንደሆነ ገልጸዋል።
በጥቃቱ ጉዳት የደረሰባቸው ስድስት ሰዎች ወደ አርባ ምንጭ ሆስፒታል ተወስደዉ ሕክምና እየተደረገላቸው መሆኑን አዛዡ ገልጸው ማምሻዉን ጥንቃቄና ጥበቃ ሲደረግ ማደሩንና ከዛሬ ማለዳ ጀምሮ የፀጥታ አባላት ከአከባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን አሰሳ እያደረጉ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
በጋሞ ዞን ቦረዳ ወረዳ የጅብ መንጋ በሰዎች ላይ ጉዳት አደረሰ።
የቦረዳ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ም/ኮማንደር ስምዖን ለንበቦ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ትናንት ምሽት 1 ሰዓት ገደማ የጅብ መንጋ በወረዳዉ ወይደ መላቶ ቀበሌ በሰዎች ላይ ጉዳት ሰንዝሮ ስድስት ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።
በአከባቢው ከከተማ በቅርብ ርቀት ጥብቅ ደኖች መኖራቸውን የገለፁት ፖሊስ አዛዡ ጅቦች በጫካዉ ዉስጥ እንዳሉ ቢታወቅም እስካሁን በሰዉ ላይ ጉዳት አድርሰው እንደማያውቅና የትናንት ምሽቱ ጥቃት ድንገተኛ እንደሆነ ገልጸዋል።
በጥቃቱ ጉዳት የደረሰባቸው ስድስት ሰዎች ወደ አርባ ምንጭ ሆስፒታል ተወስደዉ ሕክምና እየተደረገላቸው መሆኑን አዛዡ ገልጸው ማምሻዉን ጥንቃቄና ጥበቃ ሲደረግ ማደሩንና ከዛሬ ማለዳ ጀምሮ የፀጥታ አባላት ከአከባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን አሰሳ እያደረጉ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
❤407😭142😢25😱24🙏21🤔10🕊10👏8🥰7
TIKVAH-ETHIOPIA
" አንድ ሃገር ለመብረር ፈቃድ ያስፈልጋል ያንን ፈቃድ ጠይቀን ሲፈቀድልን ነው የምንበረው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቬትናም የሚያደርገውን የመጀመሪያውን በረራ በዛሬው ዕለት ምሽት ያስጀምራል። አየር መንገዱ አፍሪካን ከ ኤዥያ ጋር ያገናኘው የዛሬ 52 አመት እ.ኤ.አ በ 1973 ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ቻይናዋ ከተማ ሻንጋይ በመብረር እንደነበር የአየር መንገዱ ዋና…
" አካባቢው ላይ ያሉ ገበሬዎች ተነስተው የሚሰፍሩበት ቦታ ግንባታ በሰፊው እየተከናወነ ነው መስከረም ውስጥ ለማጠናቀቅ እየሰራን ነው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ አቡሴራ አካባቢ አዲስ ለሚያስገነባው ግዙፉ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ 2,500 አባወራዎች እንደሚነሱ መገለጹ ይታወሳል።
3,500 ሔክታር መሬት ላይ የሚያርፈው አዲሱ የአየር ማረፊያ ስራ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አየር መንገዱ አሳውቋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በአሁኑ ሰአት ለ2,500 አባውራዎች መኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ መሆኑን እና በመስከረም ወር ለማስረከብ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ስለ አዲሱ አየር መንገድ እና በሃገር ውስጥ ያሉ መዳረሻዎችን ለማስፋት እየተሰራ ስላለው ስራ በዝርዝር ምን አሉ ?
" አካባቢው ላይ ያሉ ገበሬዎች ተነስተው የሚሰፍሩበት ቦታ ግንባታ በሰፊው እየተከናወነ ነው መስከረም ውስጥ ለማጠናቀቅ እየሰራን ነው እንደተጠናቀቀ ወደ ተሰራላቸው ዘመናዊ መኖሪያ ቤቶች ይዘዋወራሉ ስራቸውንም በአዲስ መልክ ይጀምራሉ።
ቦታው ሲለቀቅልን የግንባታ ስራ እንጀምራለን የአየር መንገዱ ዲዛይንም በብዙ አድቫንስ አድርጓል እየቆራረጥን በቅደም ተከተል ነው የምንሰራው የመጀመሪያውን ዙር ስራ ህዳር ውስጥ ለመጀመር እቅድ ይዘናል።
የሃገር ውስጥ በረራን ለማስፋት እና የአገልግሎት ጥራቱን ከፍ ለማድረግ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት ጥቂት አመታት በርካታ ስራ ሲሰራ ቆይቷል።
ከስራዎቹ መሃል ዛሬ ላይ ያሉን የአውሮፕላን ጣቢያዎች ማሻሻል ነው የአውሮፕላን መንደርደሪያው ጥሩ ካልሆነ እሱን በአዲስ መልክ መስራት።
መንገደኞች የሚስተናገዱባቸው ተርሚናሎችም አንዳንዶቹ ደረጃቸውን ያልጠበቁ እና አሮጌ ፣ ወይም በቆርቆሮ የተሰሩ ነበሩ እነሱን እያፈረስን በዘመናዊ መንገድ እየሰራን ነው ሁሉንም በአንድ ጊዜ ስለማይቻል በቅደም ተከተል ነው የምንሰራው።
ባለፈው አንድ አመት ውስጥ ብቻ እንደ ጎዴ እና ጂንካ ያሉ 3 ተርሚናሎችን ሰርተን ስራ ላይ አውለናል።
አገልግሎቱን ለማስፋትም አዳዲስ ኤርፖርቶችን በመስራት ላይ እንገኛለን በአሁኑ ሰአት ስድስት ተርሚናሎች እየተሰሩ ይገኛሉ አንዳንዶቹ ለምረቃ ደርሰዋል።
ለምሳሌ ፦ ያቤሎ መንደርደሪያው አልቋል በሁለት ወር ውስጥ በረራ እምጀምራለን እሱ 23ኛው የሃገር ውስጥ መዳረሻችን ይሆናል ማለት ነው።
ነገሌ ቦረና፣ መቱ ፣ሚዛን አማን እና ደብረ ማርቆስም በመገንባት ላይ ናቸው በሚመጡት ወራት ውስጥ ይጠናቀቃሉ ተብሎ ይጠበቃል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ አቡሴራ አካባቢ አዲስ ለሚያስገነባው ግዙፉ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ 2,500 አባወራዎች እንደሚነሱ መገለጹ ይታወሳል።
3,500 ሔክታር መሬት ላይ የሚያርፈው አዲሱ የአየር ማረፊያ ስራ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አየር መንገዱ አሳውቋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በአሁኑ ሰአት ለ2,500 አባውራዎች መኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ መሆኑን እና በመስከረም ወር ለማስረከብ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ስለ አዲሱ አየር መንገድ እና በሃገር ውስጥ ያሉ መዳረሻዎችን ለማስፋት እየተሰራ ስላለው ስራ በዝርዝር ምን አሉ ?
" አካባቢው ላይ ያሉ ገበሬዎች ተነስተው የሚሰፍሩበት ቦታ ግንባታ በሰፊው እየተከናወነ ነው መስከረም ውስጥ ለማጠናቀቅ እየሰራን ነው እንደተጠናቀቀ ወደ ተሰራላቸው ዘመናዊ መኖሪያ ቤቶች ይዘዋወራሉ ስራቸውንም በአዲስ መልክ ይጀምራሉ።
ቦታው ሲለቀቅልን የግንባታ ስራ እንጀምራለን የአየር መንገዱ ዲዛይንም በብዙ አድቫንስ አድርጓል እየቆራረጥን በቅደም ተከተል ነው የምንሰራው የመጀመሪያውን ዙር ስራ ህዳር ውስጥ ለመጀመር እቅድ ይዘናል።
የሃገር ውስጥ በረራን ለማስፋት እና የአገልግሎት ጥራቱን ከፍ ለማድረግ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት ጥቂት አመታት በርካታ ስራ ሲሰራ ቆይቷል።
ከስራዎቹ መሃል ዛሬ ላይ ያሉን የአውሮፕላን ጣቢያዎች ማሻሻል ነው የአውሮፕላን መንደርደሪያው ጥሩ ካልሆነ እሱን በአዲስ መልክ መስራት።
መንገደኞች የሚስተናገዱባቸው ተርሚናሎችም አንዳንዶቹ ደረጃቸውን ያልጠበቁ እና አሮጌ ፣ ወይም በቆርቆሮ የተሰሩ ነበሩ እነሱን እያፈረስን በዘመናዊ መንገድ እየሰራን ነው ሁሉንም በአንድ ጊዜ ስለማይቻል በቅደም ተከተል ነው የምንሰራው።
ባለፈው አንድ አመት ውስጥ ብቻ እንደ ጎዴ እና ጂንካ ያሉ 3 ተርሚናሎችን ሰርተን ስራ ላይ አውለናል።
አገልግሎቱን ለማስፋትም አዳዲስ ኤርፖርቶችን በመስራት ላይ እንገኛለን በአሁኑ ሰአት ስድስት ተርሚናሎች እየተሰሩ ይገኛሉ አንዳንዶቹ ለምረቃ ደርሰዋል።
ለምሳሌ ፦ ያቤሎ መንደርደሪያው አልቋል በሁለት ወር ውስጥ በረራ እምጀምራለን እሱ 23ኛው የሃገር ውስጥ መዳረሻችን ይሆናል ማለት ነው።
ነገሌ ቦረና፣ መቱ ፣ሚዛን አማን እና ደብረ ማርቆስም በመገንባት ላይ ናቸው በሚመጡት ወራት ውስጥ ይጠናቀቃሉ ተብሎ ይጠበቃል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤1.44K😡160👏93😭35🥰32🙏30🕊20🤔16😢12💔2
TIKVAH-ETHIOPIA
" ካምፓኒዎቹን መቀመቅ የሚከት እብደት እንዲቆም የሚመለከተው አካል ሃላፊቱን ይወጣ " - አቶ በየነ ምክሩ አሁን ላይ በአዲስ አበባ የሚገኙትና የትእምት (EFFORT) ዋና ስራ አስፈፃሚ መሆናቸውን የሚናገሩት አቶ በየነ መክሩ ' ላዛ ትግርኛ ' ለተባለ የዩቱብ ሚድያ ቃለ መጠይቅ ሰጥተው ነበር። በዚህም " ህገ-ወጥ " ሲሉ የጠሩት የደብረፅን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ህወሓት በትእምት ካምፓኒዎች ላይ ከፍተኛ…
#EFFORT
" ነባሩ ቦርድ ህጋዊ ነው ፤ በትእምት ስም የተካሄደው የምክር ቤት ጉባኤ ህጋዊ አይደለም " የሚል ውሳነ መሰጠቱ ተሰማ።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ታማኝ ምንጮች በላኩት መረጃ ነባሩ የትእምት ኢንቨስትመንት አመራር " ህገ-ወጥ የምክር ጉባኤ አካሂዶ ህገ-ያልተከተሉ አመራሮች መርጦ በተቋሙ ላይ የጀመረው ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ ይታገድልኝ " ሲል ለክልሉ የፍትህ ቢሮ ያቀረበው ክስ ተቀባይነት አግኝቷል።
" በስራ ላይ ያለው ህጋዊ የትእምት ኢንቨስትመንት አመራር ነኝ " የሚል አካል ለፍትህ ቢሮ ያቀረበው ክስ ምን ይመስላል ?
በአቶ ቴድሮስ ሓጎስ የሚመራው የትእምት ባለ አደራ ቦርድ አመራር " በትእምት ስም የተካሄደው የምክር ቤት ጉባኤ ህገ-ወጥ ነው ፤ በጉባኤው የተመረጠ በኣብራሃም ተከስተ (ዶ/ር) የሚመራ ቦርድ በተቋሙ ላይ እያካሄደ የሚገኘው እንቅስቃሴም ህገ-ወጥ መሆኑ ተጣርቶ ይታገድልኝ " ሲል ለፍትህ ቢሮ አቤታቱ አቅርቧል።
ሦስት አጣሪ አባላት ያሉት ኮሚቴ በማቋቋም ላለፉት 10 ቀናት የቀረበለት አቤቱታ ሲመረምር የቆየው የፍትህ ቢሮ " በኣብራሃም ተከስተ (ዶ/ር) የሚመራ ቦርድ ህጋዊ አይደለም " በማለት በትእምት ላይ የሚያደርገው እንቅስቃሴ እንዲያቆም የእግድ ውሳኔ ሰጥቷል።
" የትእምት ምክር ቤት ባለፈው የካቲት 2017 ዓ.ም ባካሄደው ጉባኤ መርጦኛል " በሚል በመንቀሳቀስ ላይ ያለውና የተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ በየነ መክሩ ህጋዊ ርክክብ ባላካሄዱበት ሁኔታ በላያቸው ላይ አዲስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ለመቅጠር በሚድያዎች እስከማስነገር የደረሰው በኣብራሃም ተከስተ (ዶ/ር) የሚመራው አካል " ህጋዊ አይደለህም " የሚል የፍትህ ቢሮ ውሳኔ ያከብር ይሆን ? የብዙዎች ጥያቄ ነው።
ባለፈው መጋቢት 2017 ዓ.ም በተፈጠረው የፓለቲካ ቀውስ ምክንያት የቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከትግራይ መውጣታቸው ተከትሎ የትእምት ኢንቨስትመንት ዋና ስራ አስፈፃሚና የባለ አደራ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ በየነ መክሩና አቶ ቴድሮስ ሓጎስ ከክልሉ ውጪ ናቸው።
የትእምት ዋና ስራ ስፈፃሚ በየነ መክሩ በያዝነው ሳምንት መጀመሪያ ላዛ ትግርኛ ለተባለው ሚድያ ከአዲስ አበባ በሰጡት ቃለ-መጠይቅ " ህገ-ወጥ ቡድኑ በሃይል ካስቀመጣቸው አመራሮች የተደረገ ርክክብ የለም ፤ ዋና ስራ አስፈፃሚና ቦርድ የነበረው ነው ያለው " ማለታቸው ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ነባሩ ቦርድ ህጋዊ ነው ፤ በትእምት ስም የተካሄደው የምክር ቤት ጉባኤ ህጋዊ አይደለም " የሚል ውሳነ መሰጠቱ ተሰማ።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ታማኝ ምንጮች በላኩት መረጃ ነባሩ የትእምት ኢንቨስትመንት አመራር " ህገ-ወጥ የምክር ጉባኤ አካሂዶ ህገ-ያልተከተሉ አመራሮች መርጦ በተቋሙ ላይ የጀመረው ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ ይታገድልኝ " ሲል ለክልሉ የፍትህ ቢሮ ያቀረበው ክስ ተቀባይነት አግኝቷል።
" በስራ ላይ ያለው ህጋዊ የትእምት ኢንቨስትመንት አመራር ነኝ " የሚል አካል ለፍትህ ቢሮ ያቀረበው ክስ ምን ይመስላል ?
በአቶ ቴድሮስ ሓጎስ የሚመራው የትእምት ባለ አደራ ቦርድ አመራር " በትእምት ስም የተካሄደው የምክር ቤት ጉባኤ ህገ-ወጥ ነው ፤ በጉባኤው የተመረጠ በኣብራሃም ተከስተ (ዶ/ር) የሚመራ ቦርድ በተቋሙ ላይ እያካሄደ የሚገኘው እንቅስቃሴም ህገ-ወጥ መሆኑ ተጣርቶ ይታገድልኝ " ሲል ለፍትህ ቢሮ አቤታቱ አቅርቧል።
ሦስት አጣሪ አባላት ያሉት ኮሚቴ በማቋቋም ላለፉት 10 ቀናት የቀረበለት አቤቱታ ሲመረምር የቆየው የፍትህ ቢሮ " በኣብራሃም ተከስተ (ዶ/ር) የሚመራ ቦርድ ህጋዊ አይደለም " በማለት በትእምት ላይ የሚያደርገው እንቅስቃሴ እንዲያቆም የእግድ ውሳኔ ሰጥቷል።
" የትእምት ምክር ቤት ባለፈው የካቲት 2017 ዓ.ም ባካሄደው ጉባኤ መርጦኛል " በሚል በመንቀሳቀስ ላይ ያለውና የተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ በየነ መክሩ ህጋዊ ርክክብ ባላካሄዱበት ሁኔታ በላያቸው ላይ አዲስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ለመቅጠር በሚድያዎች እስከማስነገር የደረሰው በኣብራሃም ተከስተ (ዶ/ር) የሚመራው አካል " ህጋዊ አይደለህም " የሚል የፍትህ ቢሮ ውሳኔ ያከብር ይሆን ? የብዙዎች ጥያቄ ነው።
ባለፈው መጋቢት 2017 ዓ.ም በተፈጠረው የፓለቲካ ቀውስ ምክንያት የቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከትግራይ መውጣታቸው ተከትሎ የትእምት ኢንቨስትመንት ዋና ስራ አስፈፃሚና የባለ አደራ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ በየነ መክሩና አቶ ቴድሮስ ሓጎስ ከክልሉ ውጪ ናቸው።
የትእምት ዋና ስራ ስፈፃሚ በየነ መክሩ በያዝነው ሳምንት መጀመሪያ ላዛ ትግርኛ ለተባለው ሚድያ ከአዲስ አበባ በሰጡት ቃለ-መጠይቅ " ህገ-ወጥ ቡድኑ በሃይል ካስቀመጣቸው አመራሮች የተደረገ ርክክብ የለም ፤ ዋና ስራ አስፈፃሚና ቦርድ የነበረው ነው ያለው " ማለታቸው ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
❤364🕊16😡12👏8🥰6🤔5😭2
#ዙሪያ
ንግድ ላይ የተሰማሩ ዜጎች ይዘዋቸው የምናያቸውን በርካታ ፖስ ማሽኖች በማስቀረት ወደ አንድ የተቀናጀ ስርአት እንዲገቡ ያስችላቸዋል የተባለ ሲስተም ይፋ ተደርጓል።
ኢትዮ ቴሌኮም፣ ከዳሽን ባንክ እና ኤታ ሶሉሽንስ በአጋርነት በጋራ በመሆን የቀረበው "ዙሪያ" የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲስተም በአስመጪና ላኪ፣ በማኑፋክቸሪንግ እና ችርቻሮ ንግድ ዘርፍ ለተሰማሩ ድርጅቶችና ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጣቸውን ለማዘመን ያግዛቸዋል ተብሏል።
"ዙሪያ" የኢ.አር.ፒ (ERP)፣ የፒ.ኦ.ኤስ (POS) እና ካሽ ሬጂስተር (Cash Register) አገልግሎቶችን በአንድ ላይ ለመስጠት የሚያስችል የቢዝነስ አውቶሜሽ ሶሉሽን የያዘ ሲስተም ነው፡፡
መተግበሪያው የተለያየ ንግድ ላይ የተሰማሩ ዜጎች ይዘዋቸው የምናያቸውን በርካታ ፖስ ማሽኖች በማስቀረት ወደ አንድ የተቀናጀ ስርአት እንዲገቡ የሚያስችል ነው።
"ዙሪያ" ሁሉንም የሀገር ውስጥና አለም አቀፍ ካርዶች መቀበል እንደሚችል የተገለጸ ሲሆን በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ኮሚሽን ዕውቅና እንደተሰጠው ይፋ በማድረጊያ ስነ ስርአቱ ላይ ተገልጿል።
ይህ ሲስተም የሂሳብ ምዝገባ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን ነጋዴዎች የሚያንቀሳቅሱትን ሃብት ለማስተዳደር እና ማንኛውንም የክፍያ መረጃዎች በአንድ ያካተተ ደረሰኝ ለማግኘት ያስችላል ነው የተባለው፡፡
አገልግሎቱን ለማቅረብ ኢትዮ ቴሌኮም የቴሌክላውድ (TeleCloud) መሠረተ ልማት በማቅረብ የተሳተፈ ሲሆን ለዚህ አገልግሎት የሚውለውን ማሽን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት በማመቻቸት ዳሽን ባንክ አስተዋጽኦ ማድረጉን ተነግሯል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ንግድ ላይ የተሰማሩ ዜጎች ይዘዋቸው የምናያቸውን በርካታ ፖስ ማሽኖች በማስቀረት ወደ አንድ የተቀናጀ ስርአት እንዲገቡ ያስችላቸዋል የተባለ ሲስተም ይፋ ተደርጓል።
ኢትዮ ቴሌኮም፣ ከዳሽን ባንክ እና ኤታ ሶሉሽንስ በአጋርነት በጋራ በመሆን የቀረበው "ዙሪያ" የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲስተም በአስመጪና ላኪ፣ በማኑፋክቸሪንግ እና ችርቻሮ ንግድ ዘርፍ ለተሰማሩ ድርጅቶችና ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጣቸውን ለማዘመን ያግዛቸዋል ተብሏል።
"ዙሪያ" የኢ.አር.ፒ (ERP)፣ የፒ.ኦ.ኤስ (POS) እና ካሽ ሬጂስተር (Cash Register) አገልግሎቶችን በአንድ ላይ ለመስጠት የሚያስችል የቢዝነስ አውቶሜሽ ሶሉሽን የያዘ ሲስተም ነው፡፡
መተግበሪያው የተለያየ ንግድ ላይ የተሰማሩ ዜጎች ይዘዋቸው የምናያቸውን በርካታ ፖስ ማሽኖች በማስቀረት ወደ አንድ የተቀናጀ ስርአት እንዲገቡ የሚያስችል ነው።
"ዙሪያ" ሁሉንም የሀገር ውስጥና አለም አቀፍ ካርዶች መቀበል እንደሚችል የተገለጸ ሲሆን በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ኮሚሽን ዕውቅና እንደተሰጠው ይፋ በማድረጊያ ስነ ስርአቱ ላይ ተገልጿል።
ይህ ሲስተም የሂሳብ ምዝገባ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን ነጋዴዎች የሚያንቀሳቅሱትን ሃብት ለማስተዳደር እና ማንኛውንም የክፍያ መረጃዎች በአንድ ያካተተ ደረሰኝ ለማግኘት ያስችላል ነው የተባለው፡፡
አገልግሎቱን ለማቅረብ ኢትዮ ቴሌኮም የቴሌክላውድ (TeleCloud) መሠረተ ልማት በማቅረብ የተሳተፈ ሲሆን ለዚህ አገልግሎት የሚውለውን ማሽን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት በማመቻቸት ዳሽን ባንክ አስተዋጽኦ ማድረጉን ተነግሯል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤662👏46😡44🕊35😭17🤔11🙏11🥰7😱6😢5
TIKVAH-ETHIOPIA
" የግፍ አገዳደል ነው የተፈጸመው ፤ የሟቹን ወንድም ቤትም ታጣቂዎቹ አቃጥለውታል ፤ የአካባቢው ነዋሪም ወደ አጎራባች ቦታዎች ተፈናቅሏል " - የሟች የቅርብ ሰው በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን ሮቤ ወረዳ የገደብሳ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይና የሰባት ልጆች አባት ካህን በአሰቃቂ ሁኔታ በ "ሸኔ" በታጣቂዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ። ግድያው አሰቃቂ…
" አንድ ካህንና ወንድሙ፤ ሁለት ሰዎች ናቸው ታግተው የተወሰዱት። አንድ አባት እስከ ልጃቸው ተገድለዋል " - የወረዳው ቤተ ክህነት
በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ጀጁ ወረዳ ሶኮራ ቀበሌ የ"ሸኔ" ታጣቂ ቡድን በአንድ ቤተሰብ አባላት የግድያ እና እገታ ጥቃት መፈጸሙን የወረዳው ቤተ ክህነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ቤተ ክህነቱ የሆነውን ሲያስረዳ፣ " ሁለት ሰዎች ተገድለዋል፤ ትላንት 3 ሰዓት ከሩብ ላይ ነው ጥቃቱ የተፈጸመው ዛሬ የሟች አባትና ልጅ ቀብር ተፈጽሟል። ካህንና ምዕመን ወንድማማቾች ታግተው ተወስደዋል፤ የተወሰዱትም የሟች ወንድም ናቸው " ሲል ተናግሯል።
" አንድ ካህንና ወንድሙ፤ ሁለት ናቸው ታግተው የተወሰዱት። አንድ አባት እስከ ልጃቸው ተገድለዋል " ብሎ፣ ታጋች ካህን የሰኮራ ኪዳነ ምህረት አገልጋይ መሆናቸውን ገልጿል።
ቤተ ክህነቱ፣ " ህዝቡ ሁሌም በልቅሶ ነው፤ ሁሌ መገደል ነው ማን ይደርስለታል " ሲልም በአካባቢው በተደጋጋሚ የሚፈጸምን ጥቃት አስከፊነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድቷል።
" ታጣቂ ቡድኑ 3 ሰዓት ይመጣል፤ ምሽት 11 ሰዓት ይመለሳል፤ በሌሊትም የፈለገውን ይፈጸሰማል" ብሎ " መንግስት የህዝቡ ድምጽ እንዲሰማና ህዝቡን እንዲጠብቅ አሳስቧል።
" መንግስት ቢደርስ ጥሩ ነው በወረዳው ከ2014 ዓ/ም ጀሞሮ ያለማቋረጥ ነው ግድያ እየተፈጸመ ያለው። ህዝቡ እየተፈናቀለ ነው፤ ተፈናቅሎም የሚገባበት የለም። ይህ የሆነው መንግስት ሃይ ባለማለቱ ነው " ሲልም ወቅሷል።
እናት ፓርቲ ባወጣው መግለጫ፣ በበዞኑ ሶኮራ ቀበሌ ሐምሌ 4/2017 ዓ/ም አባትና ልጅ በአሰቃቂ ሁኔታ እንደተገደሉ ገልጾ፣ " የሟች ወንድሞችና የአጥቢያው አገልጋይ ካህን ቄስ አድማሱ ጌታነህና ወገኔ ጌታነህ ታፍነው የተወሰዱ ሲሆን፣ የደረሱበት አልታወቀም " ሲል አስታውቋል።
" ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ብሎ የሚጠራው ኃይል በዞኑ በሁሉም አካባቢ በሚባል ደረጃ እየተንቀሳቀሰ ከፍተኛ ሰቆቃ የሚፈጽም ሲሆን፣ ከፌዴራሉም ሆነ ከክልሉ መንግሥት በኩል ነገሩን ከማድበስበስ ያለፈ እስካሁን ይህ ነው የሚባል እርምጃ ሲወስዱ አልታየም። ይህም ለሌላ ጥርጣሬ የሚጋብዝ ነው " ብሏል።
" ፓርቲያችን ግድያውን በጽኑ ያወግዛል፤ ታፍነው የተወሰዱ ካህንና ወንድማቸው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቀቁ ይጠይቃል " ሲል ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ጀጁ ወረዳ ሶኮራ ቀበሌ የ"ሸኔ" ታጣቂ ቡድን በአንድ ቤተሰብ አባላት የግድያ እና እገታ ጥቃት መፈጸሙን የወረዳው ቤተ ክህነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ቤተ ክህነቱ የሆነውን ሲያስረዳ፣ " ሁለት ሰዎች ተገድለዋል፤ ትላንት 3 ሰዓት ከሩብ ላይ ነው ጥቃቱ የተፈጸመው ዛሬ የሟች አባትና ልጅ ቀብር ተፈጽሟል። ካህንና ምዕመን ወንድማማቾች ታግተው ተወስደዋል፤ የተወሰዱትም የሟች ወንድም ናቸው " ሲል ተናግሯል።
" አንድ ካህንና ወንድሙ፤ ሁለት ናቸው ታግተው የተወሰዱት። አንድ አባት እስከ ልጃቸው ተገድለዋል " ብሎ፣ ታጋች ካህን የሰኮራ ኪዳነ ምህረት አገልጋይ መሆናቸውን ገልጿል።
ቤተ ክህነቱ፣ " ህዝቡ ሁሌም በልቅሶ ነው፤ ሁሌ መገደል ነው ማን ይደርስለታል " ሲልም በአካባቢው በተደጋጋሚ የሚፈጸምን ጥቃት አስከፊነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድቷል።
" ታጣቂ ቡድኑ 3 ሰዓት ይመጣል፤ ምሽት 11 ሰዓት ይመለሳል፤ በሌሊትም የፈለገውን ይፈጸሰማል" ብሎ " መንግስት የህዝቡ ድምጽ እንዲሰማና ህዝቡን እንዲጠብቅ አሳስቧል።
" መንግስት ቢደርስ ጥሩ ነው በወረዳው ከ2014 ዓ/ም ጀሞሮ ያለማቋረጥ ነው ግድያ እየተፈጸመ ያለው። ህዝቡ እየተፈናቀለ ነው፤ ተፈናቅሎም የሚገባበት የለም። ይህ የሆነው መንግስት ሃይ ባለማለቱ ነው " ሲልም ወቅሷል።
እናት ፓርቲ ባወጣው መግለጫ፣ በበዞኑ ሶኮራ ቀበሌ ሐምሌ 4/2017 ዓ/ም አባትና ልጅ በአሰቃቂ ሁኔታ እንደተገደሉ ገልጾ፣ " የሟች ወንድሞችና የአጥቢያው አገልጋይ ካህን ቄስ አድማሱ ጌታነህና ወገኔ ጌታነህ ታፍነው የተወሰዱ ሲሆን፣ የደረሱበት አልታወቀም " ሲል አስታውቋል።
" ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ብሎ የሚጠራው ኃይል በዞኑ በሁሉም አካባቢ በሚባል ደረጃ እየተንቀሳቀሰ ከፍተኛ ሰቆቃ የሚፈጽም ሲሆን፣ ከፌዴራሉም ሆነ ከክልሉ መንግሥት በኩል ነገሩን ከማድበስበስ ያለፈ እስካሁን ይህ ነው የሚባል እርምጃ ሲወስዱ አልታየም። ይህም ለሌላ ጥርጣሬ የሚጋብዝ ነው " ብሏል።
" ፓርቲያችን ግድያውን በጽኑ ያወግዛል፤ ታፍነው የተወሰዱ ካህንና ወንድማቸው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቀቁ ይጠይቃል " ሲል ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
😡506❤297😭195🕊20😢19🙏10💔10👏6🥰1🤔1