TIKVAH-ETHIOPIA
ጥያቄያችን ካልተመለሰ ወደ ቤት አንገባም ያሉ ነዋሪዎች ! " መንግስት መጥቶ ጥያቄያችንን ካለመለሰልን ወደ ቤት ላለመመለስ ወስነን ሜዳ ላይ ተሰብስበናል " - ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ " ሰሚ እስክናገኝ ወደ ቤታችን አንመለስም ! " በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ የዶሬ ባፋኖ አከባቢ ነዋሪዎች " በአዲስ የመዋቅር ጥናት እና ልማታዊ ጉዳዮች ዙሪያ የወረዳዉ…
" ሸዉደዉናል 5ዐ ሰዉ መርጣችሁ ስጡን ብለዉ ካስነሱን በኋላ የተወከሉትን ስብሰባ ጠርተዉ አስፈራርተዋል " - ነዋሪዎች
➡️ " የኛ ጥያቄ የወረዳውን የተወሰኑ ቀበሌያት ወደ ሀዋሳ ከተማ ክፍለ ከተማነት ለማጠቃለል መወሰኑ ተገቢነት የለዉም የሚል ነው ! "
የሲዳማ ክልል ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ የዶሬ ባፋኖ አከባቢ ነዋሪዎች ለሀዋሳ ከተማ አስተዳደር አዲስ ተዋቀረ በተባለው የክፍለ ከተማ አደረጃጀት ከሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ 5 ቀበሌያትን ብቻ ነጥሎ መወሰዱን በመግለፅ ቅሬታ እንዳደረባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵየ ገልጸው ነበር።
ነዋሪዎቹ የተመረጡት ቀበሌያት ምርታማና የተሻለ የኢኮኖሚ አቅም ያላቸዉ በመሆኑ የወረዳዉን የመልማት አቅም ያዳክመዋል፤ ከዚህ ቀደም የተገባልንም ቃል ተግባራዊ አልተደረገም ሲሉ አደባባይ በመዉጣት " ጥያቄያችን እስኪመለስ ወደ ቤታችን አንመለስም " ማለታቸው አይዘነጋን።
" በዕለቱ ሕዝቡ ከሜዳ ላይ አልነሳ በማለቱ ምሽት ከ2 ሰዓት በኋላ የዞንና የወረዳ አመራሮች መጥተዉ 'ለነገ 50 ተወካዮችን መርጣችሁ ዉይይት እናድርግ' ብለዉ ሕዝቡ እንዲበተን ካደረጉ በኋላ በማግስቱ የተመረጡትን ተወካዮች ሰብስበዉ አስፈራርተዋቸው ስብሰባዉን ረግጠዉ ወጥተዋል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" አመራሮች ሸዉደዉናል 50 ሰዎችን መርጣችሁ ወክሉና እናንተ ወደ ቤት ተመለሱ እነሱ ነገ ከኛ ጋር ይወያዩ ብለው በሽማግሌዎች በኩል ሕዝቡ እንዲበተን ካደረጉ በኋላ በማግስቱ የተወከሉትን ሰዎች ' እናንተ ናችሁ ሕዝቡን የሚታሳምፁት ' ብለዉ በማስፈራራት ስብሰባዉን ጭምር ረግጠዉ ወጥተዋል " ሲሉ ገልፀዋል።
ዶሬ ባፋናና አከባቢዉ ያሉ ሌሎች ቀበሌዎች ከዚህ ቀደም በሀዋሳ ከተማ ስር ከመካለል ጋር ተያይዞ አንድ ላይ ዉሳኔው ያለ ልዩነት ተግባራዊ እንደሚደረግ እየተነገራቸዉ የቆየ ቢሆንም አሁን ላይ በወረዳው የተሻለ አቅም ያላቸው የተባሉ 5 ቀበሌያትን ብቻ ነጥሎ ' በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሀዋሳ ላንጋኖ ክፍለ ከተማ ' በሚል ሊደራጅ እንደሆነ መነገሩ ሕዝቡን ማስቆጣቱን ነዋሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረገዉ ሙከራ የወረዳዉ አስተዳዳሪ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሳይሳካ ቀርቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamliyHawassa
@tikvahethiopia
➡️ " የኛ ጥያቄ የወረዳውን የተወሰኑ ቀበሌያት ወደ ሀዋሳ ከተማ ክፍለ ከተማነት ለማጠቃለል መወሰኑ ተገቢነት የለዉም የሚል ነው ! "
የሲዳማ ክልል ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ የዶሬ ባፋኖ አከባቢ ነዋሪዎች ለሀዋሳ ከተማ አስተዳደር አዲስ ተዋቀረ በተባለው የክፍለ ከተማ አደረጃጀት ከሀዋሳ ዙሪያ ወረዳ 5 ቀበሌያትን ብቻ ነጥሎ መወሰዱን በመግለፅ ቅሬታ እንዳደረባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵየ ገልጸው ነበር።
ነዋሪዎቹ የተመረጡት ቀበሌያት ምርታማና የተሻለ የኢኮኖሚ አቅም ያላቸዉ በመሆኑ የወረዳዉን የመልማት አቅም ያዳክመዋል፤ ከዚህ ቀደም የተገባልንም ቃል ተግባራዊ አልተደረገም ሲሉ አደባባይ በመዉጣት " ጥያቄያችን እስኪመለስ ወደ ቤታችን አንመለስም " ማለታቸው አይዘነጋን።
" በዕለቱ ሕዝቡ ከሜዳ ላይ አልነሳ በማለቱ ምሽት ከ2 ሰዓት በኋላ የዞንና የወረዳ አመራሮች መጥተዉ 'ለነገ 50 ተወካዮችን መርጣችሁ ዉይይት እናድርግ' ብለዉ ሕዝቡ እንዲበተን ካደረጉ በኋላ በማግስቱ የተመረጡትን ተወካዮች ሰብስበዉ አስፈራርተዋቸው ስብሰባዉን ረግጠዉ ወጥተዋል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" አመራሮች ሸዉደዉናል 50 ሰዎችን መርጣችሁ ወክሉና እናንተ ወደ ቤት ተመለሱ እነሱ ነገ ከኛ ጋር ይወያዩ ብለው በሽማግሌዎች በኩል ሕዝቡ እንዲበተን ካደረጉ በኋላ በማግስቱ የተወከሉትን ሰዎች ' እናንተ ናችሁ ሕዝቡን የሚታሳምፁት ' ብለዉ በማስፈራራት ስብሰባዉን ጭምር ረግጠዉ ወጥተዋል " ሲሉ ገልፀዋል።
ዶሬ ባፋናና አከባቢዉ ያሉ ሌሎች ቀበሌዎች ከዚህ ቀደም በሀዋሳ ከተማ ስር ከመካለል ጋር ተያይዞ አንድ ላይ ዉሳኔው ያለ ልዩነት ተግባራዊ እንደሚደረግ እየተነገራቸዉ የቆየ ቢሆንም አሁን ላይ በወረዳው የተሻለ አቅም ያላቸው የተባሉ 5 ቀበሌያትን ብቻ ነጥሎ ' በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ሀዋሳ ላንጋኖ ክፍለ ከተማ ' በሚል ሊደራጅ እንደሆነ መነገሩ ሕዝቡን ማስቆጣቱን ነዋሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረገዉ ሙከራ የወረዳዉ አስተዳዳሪ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሳይሳካ ቀርቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamliyHawassa
@tikvahethiopia
❤298😢45🕊21😡16😭9🤔8💔7🥰5👏4😱3
#ATTENTION🚨
ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልገው መልዕክት !
በኢትዮጵያ በርካታ አካባቢዎች ለአብነትም አዋሽ ወንዝን ተከትሎ የሚኖሩ ከመካከለኛው የሀገሪቱ ክፍል ከኦሮሚያ ክልል ከደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ወረዳዎች ጀምሮ እስከ ታችኛው አዋሽ አካባቢዎች በተለይም ፦
- በአፋር ክልል በአዋሽ ወንዝ ዳር የሚገኙ ወረዳዎች፣
- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዳሰች ወረዳ ሆሞራቴ ከተማን ጨምሮ፣
- በጋምቤላ ክልል ጋምቤላ ከተማ እና ሌሎች በባሮ ወንዝ ተጋላጭ ሊሆኑ የሚችሉት ወረዳዎች፣
- በዋቤ ሸበሌ ወንዝ ሊጠቁ የሚችሉ የሶማሌ ክልል ወረዳዎች፣
- በአማራ ክልል በጣና ሀይቅ አቅራቢያ የሚገኙ አንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች በዚህ የክረምት ወቅት ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ እና የተጎጂ ይሆናሉ ተብሎ ተለይቷል፡፡
በተጨማሪም የክረምት ወቅት ዝናብ ተጠቃሚ የአገሪቱ አከባቢዎችና ከተሞች በሙሉ ከባድ ዝናብ በሚኖርበት ወቅት በየትኛዉም ጊዜ በቅፅበታዊ ጎርፍ አደጋ ሊጠቁ የሚችሉ ሲሆን በአንዳንድ አካባቢዎች ባልታሰቡ ክስተቶች እና ትናንሽ ወንዞች ምክንያት የጎርፍ አደጋ ሊከሰት ይችላል፡፡
የ2017 ክረምት ወቅት የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት እና ዓለም አቀፍ ትንበያዎች እንደሚያመለክቱት በእነዚህ ክልሎች እና ሌሎችም ከመደበኛ በላይ የሆነ ዝናብ የሚጠበቅ ነዉ፡፡
የጎርፍ አደጋ ስጋት ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎች የትኞቹ ናቸው ?
➡️ በተፋሰስና ወንዝ ዳርቻ (አዋሽ ፣ ዋቤ ሸበሌ፣ ተከዜ፣ ባሮ፣ ኦሞ፣ የከተሞች ወንዞች፣ ወ.ዘ.ተ….)፣
➡️ በግድቦች ማስተንፈሻ አካባቢዎች (ተንዳሆና ቀሰም፣ ግልገል ጊቤ ፣ ተከዜ፣ ገናሌ፣ ዳዋ ፣ ፊንጫ፣ ቆቃ ወ.ዘ.ተ...)፣
➡️ የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆነ አከባቢዎችና ከተሞች ሙሉ በሙሉ ከባድ ዝናብ በሚኖርበት ወቅት በየትኛዉም ጊዜ ቅፅበታዊ ጎርፍ ሊጠቁ ይችላሉ።
ማህበረሰቡ፣ የሚመለከታቸው ተቋማት እና የአስተዳደር መዋቅሮች አስፈላጊውን ጥንቃቄና በክትትል ላይ ተመሰረተ እርምጃዎች እንዲወስዱ የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አሳስቧል።
(ዝርዝር መረጀዎች ከላይ ተያይዟል)
⚠️ መልዕክቱን ለሌሎች ያጋሩ!
#EDRMC
#TikvahEthiopiaFamliyAA
@tikvahethiopia
ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልገው መልዕክት !
በኢትዮጵያ በርካታ አካባቢዎች ለአብነትም አዋሽ ወንዝን ተከትሎ የሚኖሩ ከመካከለኛው የሀገሪቱ ክፍል ከኦሮሚያ ክልል ከደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ወረዳዎች ጀምሮ እስከ ታችኛው አዋሽ አካባቢዎች በተለይም ፦
- በአፋር ክልል በአዋሽ ወንዝ ዳር የሚገኙ ወረዳዎች፣
- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዳሰች ወረዳ ሆሞራቴ ከተማን ጨምሮ፣
- በጋምቤላ ክልል ጋምቤላ ከተማ እና ሌሎች በባሮ ወንዝ ተጋላጭ ሊሆኑ የሚችሉት ወረዳዎች፣
- በዋቤ ሸበሌ ወንዝ ሊጠቁ የሚችሉ የሶማሌ ክልል ወረዳዎች፣
- በአማራ ክልል በጣና ሀይቅ አቅራቢያ የሚገኙ አንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች በዚህ የክረምት ወቅት ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ እና የተጎጂ ይሆናሉ ተብሎ ተለይቷል፡፡
በተጨማሪም የክረምት ወቅት ዝናብ ተጠቃሚ የአገሪቱ አከባቢዎችና ከተሞች በሙሉ ከባድ ዝናብ በሚኖርበት ወቅት በየትኛዉም ጊዜ በቅፅበታዊ ጎርፍ አደጋ ሊጠቁ የሚችሉ ሲሆን በአንዳንድ አካባቢዎች ባልታሰቡ ክስተቶች እና ትናንሽ ወንዞች ምክንያት የጎርፍ አደጋ ሊከሰት ይችላል፡፡
የ2017 ክረምት ወቅት የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት እና ዓለም አቀፍ ትንበያዎች እንደሚያመለክቱት በእነዚህ ክልሎች እና ሌሎችም ከመደበኛ በላይ የሆነ ዝናብ የሚጠበቅ ነዉ፡፡
የጎርፍ አደጋ ስጋት ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎች የትኞቹ ናቸው ?
➡️ በተፋሰስና ወንዝ ዳርቻ (አዋሽ ፣ ዋቤ ሸበሌ፣ ተከዜ፣ ባሮ፣ ኦሞ፣ የከተሞች ወንዞች፣ ወ.ዘ.ተ….)፣
➡️ በግድቦች ማስተንፈሻ አካባቢዎች (ተንዳሆና ቀሰም፣ ግልገል ጊቤ ፣ ተከዜ፣ ገናሌ፣ ዳዋ ፣ ፊንጫ፣ ቆቃ ወ.ዘ.ተ...)፣
➡️ የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆነ አከባቢዎችና ከተሞች ሙሉ በሙሉ ከባድ ዝናብ በሚኖርበት ወቅት በየትኛዉም ጊዜ ቅፅበታዊ ጎርፍ ሊጠቁ ይችላሉ።
ማህበረሰቡ፣ የሚመለከታቸው ተቋማት እና የአስተዳደር መዋቅሮች አስፈላጊውን ጥንቃቄና በክትትል ላይ ተመሰረተ እርምጃዎች እንዲወስዱ የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አሳስቧል።
(ዝርዝር መረጀዎች ከላይ ተያይዟል)
#EDRMC
#TikvahEthiopiaFamliyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤622🙏165🕊35😭18😢15🥰10👏8😡2🤔1😱1