Telegram Web Link
TIKVAH-ETHIOPIA
" በነዳጅ ላይ የሚጨመር ዋጋ የለም " - ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ፤ ነዳጅ እያለ ዋጋ ይጨምራል በሚል እሳቤ ' የለም ' በሚሉ ማደያዎች ላይ  እርምጃ እንደሚወሰድ ገለጹ። " አንዳንድ የነዳጅ ማደያዎች ' ነዳጅ ይጨምራል ' በሚል አገልግሎት አቁመዋል። ነዳጅ ላይ የሚጨመር ዋጋ የለም " ሲሉ ለኤፍ ኤም ሲ ተናግረዋል። መንግስት ከግንቦት ወር ጀምሮ…
" የነዳጅ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል " - ሚኒስቴሩ

የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ።

የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከዛሬ ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሰኔ ወር ሲሸጥ በነበረበት የመሽጫ ዋጋ እንዲቀጥል በመንግሥት መወሰኑን አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ የነዳጅ ማደያዎች እና ኩባንያዎች በነዳጅ ውጤቶች ግብይት አዋጁና በአሠራር መመሪያው መሠረት ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርጉ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" በእጀባ ተማሪዎችን የጫኑ 6 የሚጠጉ የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶች ደርሰው በሰላም ተመልሰዋል " - ሹፌሮች

ከሰኔ 16/2017 ዓ/ም በኃላ ተዘግቶ የሰነበተው የጎንደር መተማ መንገድ ዛሬ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን የጫኑ ተሽከርካሪዎች በመከላከያ ሰራዊት ፤ በከባድ ጥበቃ ታጅበው ደርሰው እንደተመለሱ ሹፌሮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለፁ።

ጥቃቱ በደረሰበት ወቅት በቦታው የነበረው አሽከርካሪ ከጥቃቱ በኃላ መንገዱ ተዘግቶ የቆየ ቢሆንም ዛሬ ሰኔ 21/2017 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ከጎንደር መተማ ከመተማ ወደ ጎንደር ማመላለስ እንደቻሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

ሌላው ለደህንነቱ በመስጋት ስሙን እንዳንጠቅስ የጠየቀን አሽከርካሪ " እጀባው የተካሄደው በሀገር መከላከያ ሰራዊት ሲሆን ብዛት ባላቸው እንደ ስናይፕርና መትረየስ የመሳሰሉ የቡድን መሳሪያዎችን በጫኑ ተሽከርካሪዎች ነው " ብለዋል።

ይህው አሽከርካሪ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደተናገረው  " እኔን ጨምሮ ሌሎች ሹፌሮች በዚህ መስመር አንሄድም ብለን ብናምጽም የጎንደር ከተማ መናህሪያ  ስምሪት ክፍል በግዳጅ እንድንሄድ ስለታዘዝን ለመሄድ ተገደናል " ብሏል።

በእጀባ ተማሪዎችን የጫኑ 6 የሚጠጉ የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶች ደርሰው በሰላም መመለሳቸውን አሽከርካሪዎቹ አክለው ገልፀዋል።

በዚሁ መንገድ ሰኔ 16/2017 ዓ/ም እና 18 2017 ዓ/ም በታጣቂዎች በተፈፀመ ጥቃት 16 አሽከርካሪዎች ፣ የመንግስት የፀጥታ ሀይሎችና ንፁሃን መገደላቸውን የዞኑን አስተዳደርና የአይን እማኞችን ጠቅሰን መረጃ ማካፈላችን ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ባሕር ዳር
#TikvahEthiopiaFamilyBahirdar

@tikvahethiopia
🕊#Peace

" ለችግሮቻችን መፍትሄ ከጠመንጃ ይልቅ የጠረጴዛ ውይይት እናስቀድም "  - የሰላም ሚኒስቴር ሚንስትር 

➡️ " በአሁኑ ሰዓት ትልቅ የህልውና አደጋ ለተጋረጠበት የትግራይ ህዝብ ስለ ዴሞክራሲና ልማት ማውራት ቅንጦት ነው " - የጠቅላይ ሚንስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚንስትር 


በአዲስ አበባ ከተማ " ሰላም ፣ ዲሞክራሲ እና ልማት በትግራይ እድሎችና ፈተናዎች " በሚል ርእስ የውይይት መድረክ ተካሂዶ ነበር።

የውይይት መድረኩ CENTRE FOR RESPONSIBLE AND PEACEFUL POLITICS (CRPP) የተባለ ተቋም ከአዲስ አበባ ዪኒሸርስቲ በመተባበር ነው ያዘጋጁት።

የውይይት መድረኩ ላይ ተገኝተው መልእክት ያስተላለፉት የሰላም ሚንስቴር ሚንስትር አቶ መሐመድ እድሪስ " ከመነጋገር እናተርፋለን " ብለዋል።

" ሃሳብ ነው ሃገርን የሚገነባው ስለሆነም ለሃሳብ ክብርና ልዕልና እንስጥ ፤ ጠመንጃንና ጦርነትን እንጠየፍ የትግራይ የፓለቲካ ምህዳር ለወጣቶች እድልና ቅድሚያ ይስጥ " ሲሉ ተናግረዋል።

" ' አንዋጋም ይበቃል ' ማለት ታላቅ ድፍረት ይጠይቃል ከተቻለ ግን ውጤቱ እጅግ አመርቂና ፍሬውም ጣፋጭ ነው። ስለሆነም እርስ በርስ መዋጋት ይብቃ ፤ ሳንገዳደል አሸናፊ የምንሆንበት ሰላማዊ መንገድ እናስቀድም የመገዳደል የመተላለቅ ታሪክ ልንዘጋው ይገባል " ሲሉ ተደምጠዋል።

የጠቅላይ ሚንስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚንስትር አቶ ጌታቸው ረዳ፥ " የትግራይ ህዝብ አሁንም ከህልውና አደጋ አልወጣም " ብለዋል።

" ችግሮቻችን በውጭ ምክንያቶች እያሳሰበን ከመኖር ውስጣችን በደምብ በመፈተሽ የተወሳሰቡ ችግሮቻችን መፍታት እንችላለን " ሲሉ ገልጸዋል።

" ትግራይ ጥቂት አመራሮች ማረምና ማንሳት አቅተዋት በከባድ ፈተና ተዘፍቃ ትገኛለች ፤ ይህንን ከባድ ፈተና ለመወጣትና ለማለፍ ወጣቶችን ወደ መሪነት ማምጣት ይጠበቅበታል " ብለዋል።

" በአሁኑ ሰዓት ትልቅ የህልው አደጋ ለተጋረጠበት የትግራይ ህዝብ ስለ ዴሞክራሲና ልማት ማውራት ቅንጦት ነው " በማለት አክለዋል።

ለአንድ ቀን በተካሄደው የውይይት መድረክ " ሰላምና ደህንነት ፣ ዲሞክራሲ ግንባታ ፈተና እና እድል " የሚሉና ሌሎች የመወያያ ፅሁፎች ቀርበዋል።

በመድረኩ ከትግራይ የተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ፣ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ፣ ስቪክ ማህበራት እንዲሁም በአዲስ አበባ የሚኖሩ ታዋቂ ሙሁራንን ፓለቲከኞች ተገኝተው ነበር።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyMK

@tikvahethiopia            
#Medrek

አቶ ዓምዶም ገብረስላሴ የመድረክ ሊቀመንበር ሆኑ።

ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ምክትል ሊቀመንበርና የውጭ ጉዳይ ኃላፊ ሆነዋል።

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) " ታሪካዊ " ሲል የጠራውን ጠቅላላ ጉባዔውን አካሂዶ አዲስ አመራር መምረጡን ይፋ አደረገ።

" በሀገሪቱ ብቸኛው ቀዳሚ የብሔር ብሔረሰቦች የፖለቲካ ጥምረት " እንደሆነ የገለጸው መድረክ 17ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን በተሳካ ሁኔታ በማካሄድ የውስጥ መነቃቃቱን የሚያበስር ወሳኝ እርምጃ እንደወሰደ ገልጿል።

በግንባሩ ጽ/ቤት የተካሄደው ጉባዔ፣ አዲስ አመራር በመምረጥና እውነተኛ ዴሞክራሲያዊትና ሰላማዊ #ኢትዮጵያን 🇪🇹 ለመገንባት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ አቅጣጫ በማስቀመጥ መጠናቀቁን አሳውቋል።

አዲስ የተመረጠው አመራር፣ ወጣት አመራሮችን ከተመክሮና ልምድ ካካበቱ አንጋፋ ፖለቲከኞች ጋር በስትራቴጂካዊ ቅንጅት ያካተተ እንደሆነና ይህም መድረክ የኢትዮጵያን ውስብስብ ፖለቲካዊ ተግዳሮቶች በብቃት እንዲወጣ እንደሚያስችለው አመልክቷል።

አዲሱ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሆነው እነማን ተመረጡ ?

1. አቶ ዓምዶም ገብረስላሴ ፦ የመድረክ ሊቀመንበር
2. አቶ ሱልጣን ቃሲም፦ ምክትል ሊቀመንበርና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ
3. ወ/ሮ መርየም ሓሰን ፦ ምክትል ሊቀመንበርና የፋይናንስ ጉዳይ ኃላፊ
4. አቶ ሙላቱ ገመቹ፦ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበርና የህዝብ ድርጅት ጉዳይ ኃላፊ
5. ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ፦ ምክትል ሊቀመንበርና የውጭ ጉዳይ ኃላፊ
6. አቶ ለገሰ ለንቃሞ፦ የመድረክ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ
7. አቶ ደስታ ዲንቃ፦ የመድረክ ምክትል ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ተመርጠዋል።

መድረክ ፦
- ዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ሉዓላዊነት (ዓረና)፣
- የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ)፣
- የሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን) እና የዓፋር ህዝብ ፍትህና ዲሞክራሲ ፓርቲን በአባልነት አቅፏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው የደረሰው ከመድረክ ህዝብ ግንኙነት ክፍል ነው።

(NB. ከላይ የተያያዘው የመድረክ መግለጫ ነው)

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

ፎቶ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#EthiopianAirlines🇪🇹

" አውሮፕላኑ ያለምንም ችግር በሰላም አርፏል። ካረፈ በኋላ ስምንት ተጓዦች የህመም ስሜት ተሰምቷቸው ወዲያውኑ በህክምና ባለሙያዎች ክትትል ተደርጎላቸዋል " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ

ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነ አውሮፕላን ህንድ ውስጥ በድንገት ለማረፍ መገደዱና በተሳፋሪዎች ህመም ማጋጠሙን " ዘፋይናንሻል ኤክስፕረስ " የተሰኘው የውጪ ሚዲያ ዘግቧል።

ቦይንግ 787 ድሪምላይነር አውሮፕላኑ በሙምባይ ባጋጠመው ችግር " ሰባት ሰዎች መታመማቸው"ን የጠቀሰው ዘገባው፣ ከሰባቱ ሰዎች መካከል "አንዱ በጠና ታሞ ሆስፒታል ገብቷል" ብሏል።

የበረራ ቁጥር ET640 አውሮፕላኑ ክስተቱ ያጋጠመው 33 ሺህ ጫማ ብሎ መጓዝ እንደጀመረ መሆኑ ተመልክቷል። በዚህም " አውሮፕላኑ በድንገት ለማረፍ የተገደደው በአካባቢው በተከሰተው የአየር ፀባይ ነው " ተብሏል።  

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በበኩሉ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ለጉዳዩ ማብራሪያ የጠየቀ ሲሆን፣ የአየር መንገድ የሕዝብ ግንኙነት ሐና አጥናፉ በሰጡን ቃል፣ " አውሮፕላኑ ወደ ሙምባይ እየበረረ በነበረበት ወቅት የበረራ አባላቱ በካቢን ውስጥ የነበረው ግፊት ቀንሶ አጎኝተውታል " ብለዋል።

" በበረራ ወቅት የበረራ አባላት ባረጋገጡት መረጃ መሰረት ፓይለቱ ደህንነቱ ወደ ተጠበቀ/ለፕሌኑ በሚመች (ከፍታ ቦታ ላይ) በመሄድ አርፏል " ያሉት ሐና፣ " የአደጋ ጊዜ የኦክስጅን ማስኮችን በአግባቡ ተጠቅሟል " ሲሉ ገልጸዋል።

" አውሮፕላኑ ያለምንም ችግር በሰላም አርፏል " በማለት ገልፀው፣ " ካረፈ በኋላ ስምንት ተጓዦች የህመም ስሜት ተሰምቷቸው ወዲያውኑ በህክምና ባለሙያዎች ክትትል ተደርጎላቸዋል" ሲሉም ሁነቱን አስረድተዋል።

" ሰባቱ በዚያው በአየር መንገዱ ህክምና አግኝተዋል። አንዱ ተጎጂ ለተጨማሪ ህክምና ወደ ሆስፒታል ተወስዷል። ነገር ግን ክትትል ከተደረገለት በኋላ ከሆስፒታል ወጥቷል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

የአውፕላኑ አብራሪ ሁኔታው ሳይባባስ ፕሮፌሽናል በሆነ መንገድ መቆጣጠሩን ለመረዳት ተችሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#FaydaforEthiopia

ያስተውሉ!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዚህ ቀደም ባወጣው መመሪያ መሰረት ከታህሳስ 23፣ 2017 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በሚገኙ በሁሉም ባንኮች አዲስ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እንደ መጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ ተግባራዊ ተደርጎ እየተተገበረ መሆኑ ይታወሳል።

በተመሳሳይ ከሰኔ 24 ፣ 2017 (July 1, 2025) ጀምሮ በተጠቀሱት ክልል ከተሞች ማለትም ፦
- ባሕር ዳር
- ጎንደር
- ሐዋሳ
- ድሬዳዋ
- ደሴ
- ደብረ ብርሃን
- ሀረር
- አርባ ምንጭ
- ኮምቦልቻ
- ሸገር
- ወላይታ ሶዶ
- ጅግጅጋ
- አዳማ
- ሻሸመኔ
- መቐለ
- አክሱም
- ቢሾፍቱ
- ባቱ
- ወራቤ
- ቡታጅራ
- ጅማ
- አምቦ
- አዲግራት
- ሆሳዕና
- ወልቂጤ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ (የፋይዳ ቁጥር) ይዞ መቅረብ እንደ መጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ ተግባራዊ የሚደረግ ይሆናል።

#ፋይዳለኢትዮጵያ #Fayda #FaydaforEthiopia
#SafaricomEthiopia

🌐 ቅመም ማይፋይ በአዲስ ዋጋ መጥቷል 🙌

💨 እስከ 7 ሰዓት የሚቆይ የባትሪ አቅም ያለውና አዳዲስ የቴክኖሎጂ ትሩፋቶችን ይዞ በአንዴ እስከ 8 ሰው ድረስ የሚያስጠቅመውን ልዩ ቅመም MIFIን ገዝተን ፈጣን 4G ኢንተርኔት እንጠቀም!

🍰  ለ30 ቀን ከሚቆይ ነጻ 30ጊባ ዳታ ጉርሻ ጋር 😊

ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት
" 2.45 ሚሊዮን ህዝብ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ይፈልጋል " - የክልሉ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን

ከሁለት አመቱ ደም አፋሳሽ ጦርነት ባላገገመው የትግራይ ክልል ውስጥ፣ 2 ሚሊዮን 450 ሺህ ህዝብ አስቸኳይ የነፍስ አድን እርዳታ እንደሚፈልግ ተገለፀ፡፡

የእርዳታ ፈላጊው ብዛት የታወቀው በጥቅምትና ታህሳስ ወራት የ2016/2017 የምርት ዘመን ላይ በተደረገ ጥናት መሰረት መሆኑን፣ የክልሉ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ሐላፊ ዶ/ር ገብረህይወት ገ/እግዚአብሔር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡

ጥናቱ የሚመለከታቸው የሀገር ውስጥና አለምአቀፍ የእርዳታ ተቋማት የተሳተፉበት፣ በሁሉም ባለድርሻ አካላት የተገመገመና ሁሉም ተቋማት የተስማሙበት እንደሆነም ተናግረዋል፡፡

ጥናቱ ፦
- በእርሻ፣
- በትምህርት፣
- በጤና፣
- በመጠጥ ውሀ፣
- በምግብ አቅርቦት፣
- በሴቶችና ወጣቶች ተጠቃሚነት ያሉትንም ክፍተቶች የዳሰሰ መሆኑንም አመልክተዋል፡፡

ከተጠቀሰው 2 ነጥብ 45 ሚሊዮን የእርዳታ ፈላጊ ውስጥ አንድ ሚሊዮኑ በመጠለያ ጣቢያዎች የሚኖር ተፈናቃይ ሲሆን፣ 1 ነጥብ 45 ሚሊዮኑ ደግሞ የዘላቂ ማቋቋሚያ ሳይደረግለት ወደ ፈረሰ ቤቱ የተመለሰ ህዝብ መሆኑን ሐላፊው አመልክተዋል፡፡

የአሜሪካው አለምአቀፍ የተራድኦ ድርጅት/ዩኤስኤይድ የእርዳታ አቅርቦት ከአራት ወራት በፊት በፕረዝደንት ትረምፕ ትእዛዝ በመቋረጡ፣ በትግራይ ያለው የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት አደጋ ላይ ወድቋል ያሉት ዶ/ር ገብረህይወት፣ “ የትግራይ ህዝብ በአሁኑ ወቅት የጥይት ድምፅ በሌለበት ጦርነት ውስጥ ነው የሚገኘው ” ሲሉም የሰብአዊ ቀውሱን አስከፊነት ገልፀዋል፡፡

ከአንድ ሚሊዮን በላይ ተፈናቃዮች ወደ ቀዬያቸው አልተመለሱም፣ በስቃይ ውስጥ መኖር ከጀመሩ አምስተኛ አመታቸውን ይዘዋል ያሉት ሐላፊው፣ ወደ ቀዬያቸው ቢመለሱ ኖሮ፣ በመሬታቸው ላይ ሰርተው ራሳቸውን ማስተዳደር በቻሉ ነበር በማለት ገልፀዋል፡፡

ተፈናቃዮቹን ወደ ቀዬያቸው በመመለስ ዘላቂ መፍትሔ እስኪሰጣቸው ድረስ ግን፣ አለምአቀፉ ማህበረሰብና የረድኤት ድርጅቶች የትግራይን የሰብአዊ እርዳታ ጉዳይ እንደገና ካላዩትና የፍላጎቱን መጠን ዳግም ካልከለሱ፣ እስካሁን በእርዳታ ያቆዩትን ማህበረሰብ ከዚህ በኋላ ለእልቂት መዳረግ ነው የሚሆነው ሲሉም ስጋታቸውን ተናግረዋል፡፡  

ዶ/ር ገብረህይወት ገብረእግዚአብሔር በዝርዝር ምን አሉ ?

" ቀደም ሲል በዩኤስኤይድ ሲሰጥ የነበረው እርዳታ በቂ ባይሆንም፣ የተሻለ የቀለብና የመድሐኒት አቅርቦት ነበር፡፡ በተወሰነ መልኩ የኑሮ ማሻሻያ ስራዎችም ሲከናወኑ ነበር፡፡ አሁን ግን ይህ አርዳታ ቀንሶዋል፡፡

ለምሳሌ የአለም ምግብ ፕሮግራም ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ እርዳታ ማቅረብ ሊያቆም እንደሚችል ገልፆዋል፡፡ ለዚህ ያቀረበው ምክንያት ደግሞ በፕረዝደንት ትራምፕ የዩኤስኤይድ እርዳታ ማቋረጥን ተከትሎ የእርዳታ አቅርቦት በመቀነሱ እህል የለኝም የሚል ነው፡፡

የአለም ምግብ ፕሮግራም በ 30 የትግራይ ወረዳዎች በምግብና በጥሬ ገንዘብ እስከ 8 መቶ ሺህ ህዝብ ሲረዳ ነበር፡፡ የሰሜን ምዕራብ ትግራይ 15 ወረዳዎች፣ የመቐለ 7 ክፍለ ከተሞች፣ በደቡብ ትግራይ 6 ወረዳዎች በዚህ ተቋም ነበር የሚታገዙት፡፡ ይህ የረድኤት ድርጅት ከዚህ ስራ ወጣ ማለት፣ እስከ 8 መቶ ሺህ የሚሆን ህዝብ ለሞት፣ ለችግርና ለበሽታ ይጋለጣል ማለት ነው፡፡ ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ እነዚህ 30 ወረዳዎች ምንም አይነት ድጋፍና እገዛ አያገኙም ማለት ነው፡፡

የአለም ምግብ ፕሮግራም 80 በመቶ እርዳታ ከዩኤስኤይድ ነበር የሚገኘው፡፡ ሌላኛው የረድኤት ድርጅትም ሲሰጠው የነበረው እርዳታ በሙሉ በሚባል መልኩ ከዚሁ ከዩኤስኤይድ ነበር የሚያመጣው፡፡ ይህ እርዳታ ያለምንም ማስጠንቀቂያ በመቋረጡ በትግራይ ትልቅ ችግር አስከትሏል፡፡ የዩኤስኤይድ እርዳታ መቋረጥ የፈጠረው ክፍተት በሌሎች ድርጅቶች የሚሸፈን አይደለም፡፡

ይህ ውሳኔ እንደገና ካልታየና ካልተሻሻለ፣ በትግራይ ክልል ያለውን ችግር በቀላሉ መቅረፍ የሚቻል አይደለም፡፡ አሁን እየታየ ያለው ሰብአዊ ቀውስ በአብዛኛው የዩኤስኤይድ እርዳታ በመቋረጡ የመጣ ነው፡፡ በአጠቃላይ ያ እርምጃ በትግራይ የሰብአዊ እርዳታ ስርዓቱን ነው ያናጋው፡፡ በህዝቡ እርዳታ አቅርቦት ላይ የፈጠረው ተፅዕኖ ግዙፍ ነው፡፡

አሁን ለአለምአቀፉ ማህበረሰብ ውትወታ የማናደርግና ጠንካራ ጥሪ የማናቀርብ ከሆነ፣ ችግር ላይ የሚወድቅ ህዝብ ነው ያለን፡፡ የትግራይ ህዝብ በረሀብ ሳይረግፍና፣ ለከፋ ማህበራዊ ቀውስ ከመጋለጡ በፊት ልንደርስለት ይገባል፡፡ አለምአቀፉ ማህበረሰብ ይህንን ሊገነዘብና ድጋፉን ሊቀጥልበት ይገባል፡፡ "

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
" የህክምና ስርዓቱ እንዲሻሻል የታገለ፣ ዓይንና እውቀት የገለጠ፣ ለጤና ባለሙያው ህይወት መሻሻል የሚለፋው ዶ/ር ዳንኤል መታሰሩ የሚያሳዝንና በመላው ባለሙያ ላይ የተቃጣ እርምጃ ነው " - የህክምና ተማሪዎች

የባሕር ዳር ፈለገ ግዮን ሆስፒታል የማህጸን እና ፅንስ ስፔሻሊቲ የመጨረሻ አመት ተማሪ ዶ/ር ዳንኤል ፈንታነህ የመብት ጥያቄ በማንሳት ጤና ባለሙያዎች እያደረጉት ባለው እንቅስቃሴ ሳቢያ እንደታሰሩና፣ እንዲፈቱ የህክምና ተማሪዎችና የጤና ባለሙያዎች ጠየቁ።

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ህክምና ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ " መምህራችንን ፣ ሀኪማችንን፣ በዚህ የመብት ጥያቄ ምክንያት 'አስተባብራችኋል፣ ሕዝብ አሳምጻችኋል፣ መንግስትን በኃይል ለመናድ ከሚሰሩ አካላት ጋር ተመሳጥራችኋል' በሚሉ የበሬ ወለደ ክስ በግፍ የታሰሩ እንቁ የጤና ባለሙያዎች እንዲፈቱ እንጠይቃለን " ብለዋል።

" የህክምና ስርዓቱ እንዲሻሻል የታገለ፣ ዓይንና እውቀት የገለጠ፣ ለጤና ባለሙያው ህይወት መሻሻል የሚለፋው ዶ/ር ዳንኤል መታሰሩ በጣም የሚያሳዝንና በመላው የጤና ባለሙያ ላይ የተቃጣ እርምጃ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" በእውኑ መብትን በሰላማዊ መንገድ መጠየቅ ወንጀል ነውን ? የጤና ሥርዓቱ ይሻሻል፣ የጤና ባለሙያዎች የልፋታቸውን ዋጋ ያግኙ ብሎ መጠየቅ ጥፋት ነውን ? " ሲሉም ጠይቀዋል።

ዶ/ር ዳንኤል ከዘጠኝ ዓመታት በፊት ጀምሮ አበርክቶ የተገበሩ፣ ለሥራ አጦች በጋራ ክሊኒክ መክፈት የሚያስችልን መፅሐፍ በማዘጋጀት ግንዛቤ ያስጨበጡ፣ ባለሞያዎች ከህክምና ውጭ ያላቸውን ተሰጥኦ እንዲጠቀሙ በማሰብ " MAC Ethiopia " የተሰኘ ማህበር ካቋቋሙት አካላት መካከል ዋነኛው እንደነበሩም አብራርተዋል።

" ዶ/ር ዳንኤል በድንገት ጋውን የለበሰ ሃኪም አይደለም። ለመጀመርያ ጊዜ በህክምና ተማሪዎች የተዘጋጀ 'ደቦል' የተባለ የቀዶ ህክምና መፅሐፍ በግንባር ቀደምነት ያዘጋጀ፣ በተከታታይ Edition በማውጣት ያለምንም ክፍያ ሙሉ የኢትዮጵያን ተማሪዎች ያገዘ ድንቅ የሜዲካል ሰው ነው " ብለዋል።

ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ቃላቸውን የሰጡ ጤና ባለሙያዎች በበኩላቸው፣ " ተይዞ የታሰረው ረቡዕ 7 ሰዓት ተኩል ነው። የተያዘውም በደኅንነቶች ነው። ባለሙያዎች ወደ ሥራ ይመለሱ ተብሎ በተግባባነው መሠረት ወደ ሥራ ተመልሶ ግን (በእርግጥ ሆስፒታል ላይ ሳይሆን) ቤተሰብ ጋር በነበረበት ነው የወሰዱት " ሲሉ ተናግረዋል።

" አርብ ፍርድ ቤት ቀርቦ ነበር፤ ' ጤና ባለሙያዎችን በማስተባበር፣ አድማ በማስመታት፣ አመጽን በመቀስቀስ ' የሚል ክስ ቀርቦበታል " ብለዋል።

" ይህ እሱን የማይወክል ነበር ዶ/ር ዳንኤል እንደማንኛውም ባለሙያ ጥያቄ ጠይቋል፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ከ320 ሺሕ በላይ እንዳሉ ይታመናል። ከእነዚህ አንዱ ነው " ሲሉ አስረድተዋን።

" ከሱም ውጪ እየታሰሩ ያሉ ባለሙያዎች አሉ። ምንም አላጠፋንም ጠቅላይ ሚኒስትሩም 'ጥያቄያችሁ የዳቦ ጥያቄ ነው፤ በቅደም ተከተል እንመልስላችኋለን' ብለዋል፤ ያንን እየጠበቅን ባለንበት ፊገር ባለሙያዎችን ማሰር ተገቢ አይደለም። በሚቀጥለው ሳምንት የማይፈቱ ከሆነ ባለሙያው አሁንም መብቱን ለመጠየቅ ይገደዳል " ነው ያሉት።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
2025/07/01 08:26:56
Back to Top
HTML Embed Code: