Telegram Web Link
የትምህርት ቤት ክፍያዎን በቀላሉ በፀሐይ ባንክ በኩል ይክፈሉ!

እጅግ ዘመናዊ የሆነው የፀሐይ ኢ-ስኩል ሲስተም የሚሰጣቸው ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች ተጠቃሚ ይሁኑ!

ወቅቱ ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ምዝገባ የሚያደርጉበት ነው፡፡ ፀሐይ ባንክ የትምህርት ቤቶችን ምዝገባ እና ሌሎች ሥራዎችን የሚያቀላጥፍ ምርጥ መላ ይዞ መጥቷል፡፡

አሁኑኑ አቅራቢያዎ ወደሚገኝ የፀሐይ ባንክ ቅርንጫፍ በመሔድ የፀሐይ ኢ-ስኩል ሲስተም ተጠቃሚ ይሁኑ!

ሥራዎትን ያቀላጥፉ! ከባንካችን ጋር በመስራት የሚያገኙትን ጥቅም ያሳድጉ!

ፀሐይ ባንክ
ለሁሉ!


Telegram: https://www.tg-me.com/tsehaybanksc
128🤔6🙏5🥰2😢1
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#መቃ

ሰሞኑን " መቃ " ላይ ታጣቂዎች በሹፌሮች  ንፁሃን ዜጎችና የጸጥታ ኃይሎች ላይ አሰቃቂ ነው የተባለ ግድያ መፈጸማቸው ይታወሳል።

ከዛ በኋላ ምን ተፈጠረ ?

- ከታጣቂዎቹ ግድያ በኋላ በመንግሥት ጸጥታ ኃይል በተወሰደ እርምጃ ከ17 በላይ የአካባቢው አርሶ አደሮች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።

- በጫካ የሚገኘው የቅማንት ሀይል ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ " በእጀባ ላይ የነበሩ ሹፌሮች፤ ተሳፋሪዎችን እና የመንግስት ጸጥታ ኃይል ላይ ጥቃት ያደረሱት በውንብድና ተግባር የተሰማሩ ሽፍቶች ናቸው " ብሏል። " ሰኔ 16/2017 ዓ.ም የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ የመንግስት ታጣቂዎች በአካባቢው ያሉ በመጀመሪያው በሁለተኛው ቀናቶች ወደ ከ17 በላይ ንፁሃን የአካባቢው ተወላጅ አርሶ አደሮችን ገድለዋል " ሲል ከሷል።

- የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ለጥቃቱ " ፅንፈኛው ቅማንት " ሲል የጠራውን ታጣቂ ኃይል ተጠያቂ ማድረጉ ይታወሳል።

- የብሄረሰቡ ተወላጅ የሆኑና በአካባቢው የሚኖሩ ስሜ አይጠቀስ ያሉ ግለሰብ " ጥቃቱን ተከትሎ የመንግስት ታጣቂዎች በወሰዱት እርምጃ ከ17 በላይ የአካባቢው ተወላጅ አርሶ አደሮች ተገድለዋል። ከተገደሉት መካከል ወንድሜ ይገኝበታል " ብለዋል።

- አንድ ሌላ ነዋሪ " የመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ታጣቂው የወሰደባቸውን የቡድን መሳሪያ ለማስመለስ ወደ መቃ ከተማ ተኩሰዋል፤ በርካታ ንፁሃን ተገድለዋል ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ የተገደሉትን ጨምሮ ከ17 በላይ ንፁሃን አርሶ አደሮች ተገለዋል " ሲሉ ተናግረዋል።

- በአሁኑ ሰዓት ቆስሎ ሆስፒታል የሚገኝ የዐይን እማኝ " ግጭቱ ከ10:30-11:00 ነበር የተካሄደው ታጣቂዎች አሽክርካሪዎችንና ተሳፋሪዎችን ተዟዙረው ገድለው ከጨረሱ በኃላ ተመልሰው ጫካ እስኪሄዱ ድረስ ከሞቱት ሰዎች ኪስ ግንዘብና ሞባይል እያወጡ ሲወስዱ በሞተ ሰው አስከሬን ተከልየ አይቻለሁ " ሲል ገልጿል። " ታጣቂዎቹ ወደ ጫካ ከሄዱ በኃላ መከላከያ መጥቶ አካባቢውን እስኪቆጣጠር እስከ ምሽቱ 2:30 ድረስ አስከሬን ሊያነሳ የመጣ ወጣት አላየሁም " ብሏል። የቆሰሉትን ሆነ የሞቱትን ሰዎች የመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ናቸው ከወደቁበት ያነሱት።

(ተጨማሪ ዝርዝሩ ከላይ ያንብቡ)

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ባሕር ዳር
#TikvahEthiopiaFamilyBahirdar

@tikvahethiopia
563😭153😡23🕊19🙏8😢7🤔5🥰4
TIKVAH-ETHIOPIA
" በፔይሮል የሚያገኘውን ብቻ በማሳደድ ሀገር ማሳደግ አይቻልም ! " የገንዘብ ሚኒስቴር ከሠራተኛ የሚቀነስ ግብርን ጨምሮ ሌሎች የገቢ ጉዳዮችን የሚመለከተውን የገቢ ግብር አዋጅ ለማሻሻል ባስደረገው ጥናት በየወሩ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ከግብር ነፃ የሚሆነው የትኛው የደሞዝ መጠን ላይ ነው ለሚለው ሦስት አማራጮችን አቅርቧል። እነዚህም 1,200፣ 1,600፣ ወይስ 2,000 ብር ከሚከፈላቸው ላይ ይሁን…
#Ethiopia🇪🇹

የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ እንደሚሻሻል ተገልጿል።

ዛሬ 48ኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ተካሂዶ የአዋጁ መሻሻል ላይ ውሳኔ አሳልፏል።

ምክር ቤቱ " ቀደም ሲል ሲሰራበት የነበረው የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ አሁን ከምንገኝበት ሀገራዊ እና አለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ አንጻር ሲታይ በርካታ ክፍተቶች ያሉበት ነው " ብሏል።

" የአዋጁን ድንጋጌዎች በማሻሻል የታክስ ስርአቱ መሠረታዊ የታክስ መርሆዎችን ለማሳካት በሚያስችል መልኩ እንዲቀረጽ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ የማሻሻያ አዋጁ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል " ሲል ገልጿል።

ምክር ቤቱ በማሻሻያ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ በሙሉ ድምጽ አጽድቆ ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ መወሰኑን አሳውቋል።

ከሳምንታት በፊት የገንዘብ ሚኒስቴር ከሠራተኛ የሚቀነስ ግብርን ጨምሮ ሌሎች የገቢ ጉዳዮችን የሚመለከተውን የገቢ ግብር አዋጅ ለማሻሻል ባስደረገው ጥናት በየወሩ ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ከግብር ነፃ የሚሆነው የትኛው የደሞዝ መጠን ላይ ነው ለሚለው ሦስት አማራጮችን አቅርቦ እንደነበር ፤ እነዚህም 1,200፣ 1,600፣ ወይስ 2,000 ብር ከሚከፈላቸው ላይ ይሁን የሚል እንደነበር መዘገቡ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማሕበራት ኮንፌደሬሽን በበኩሉ ዝቅተኛው ከግብር ነፃ መሆን ያለበት የደሞዝ መጠን 8,300 ብር ነው መሆን ያለበት በሚል ሲከራከር እንደነበር አይዘነጋም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
566😭85😡54🙏24😢9🥰5🤔3🕊1
" ሃይል እያቋረጥን ስራ ስንሰራ የነበረ በመሆኑ በምንፈልገው ደረጃ የሃይል መቆራረጡን እንዳንቀንስ የራሱን አስተዋጽኦ አድርጓል "- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

የኢትዮጵያ አሌክትሪክ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ሦስት ወራት ለክረምት ዝግጅት ሲያከናውን የቆያቸውን ስራዎች በሚመለከት በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥቷል።

አገልግሎቱ በከተማዋ ለሚያጋጥም የሃይል መቆራረጥ ምክንያት ናቸው ብሎ የለያቸውን የመስመሮች ከዛፍ ጋር የሚፈጥሩት ንክኪ እና የረገቡ መስመሮች ላይ የተለያዩ ስራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን አሳውቋል።

ተቋሙ ባለፉት ሦስት ወራት ብቻም ከ 25 ሺ በላይ ለሃይል መቆራረጥ ምክንያት የሆኑ አነስተኛ እና ከፍተኛ ግኝቶች አግኝተናል ነው ያለው።

ለሃይል መቆራረጥ ምክንያት ናቸው ካላቸው ግኝቶች ውስጥም ተቋሙ መፍታት የቻለው 56 በመቶዎቹን ብቻ ነው።

የአገልግሎቱ የኔትወርክ ኢንፍራስትራክቸር እና ኮርፖሬሽን ኤክሰለንስ ዳይሬክተር አቶ ፈሪድ አብዱሰላም ምን አሉ ?

" በስታንዳርዱ መሰረት ሽቦዎች እርስ በእርስ ሊኖራቸው የሚገባው ርቀት ከ 40-60 CM ፣ ከግራ እና ከቀኝ ካሉ ህንጻዎች እና ዛፎች 3 ሜትር እንዲሁም ከመሬት ያለው ከፍታ 5.5 ሜትር ከፍ ማለት የሚጠበቅባቸው ቢሆንም ይህ ሳይሆን በመቅረቱ ብልሽት እና አልፎ አልፎም አደጋ እያጋጠመ ነው።

ባለፉት ሦስት ወራት ብቻም ከ 25 ሺ 973 በላይ ለሃይል መቆራረጥ ምክንያት የሆኑ አነስተኛ እና ከፍተኛ ግኝቶች አግኝተናል።

ከተገኘው ግኝት አብዛኛው ወይም 30 በመቶ የሚሆነው የ ሃይል መቆራረጥ ምክንያት ዛፎች ናቸው።

በመዲናዋ 7,277 የሚሆኑ መስመር ውስጥ የገቡ እና ከ ኤሌክትሪክ መስመር 3 ሜትር መራቅ ያለባቸው ዛፎች የተገኙ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 5 ሺ 585 የሚሆኑትን የማጽዳት ስራ ተሰርቷል።

ያረጁ እና መቀየር የሚያስፈልጋቸው የኤሌክትሪክ ገመድ ተሸካሚ ፖሎች ቁጥር ከ 6 ሺ 367 በላይ ናቸው እዚህም ላይ ስራዎች ተሰርተዋል ይህም ለ ሃይል መቆራረጥ 25 በመቶ ምክንያት ነው።

በተጨማሪም 2 ሺ 425 ከግንባታዎችና እርስ በእርስ የተቀራረቡ መሥመሮች፣ 6 ሺ 298 የረገቡ እና የተለያዩ የመስመር ችግር ያለባቸው ሆነው ተገኝተዋል።

ከ 25 ሺ ግኝቶች ውስጥ 56 በመቶ የሚሆነውን ችግር ፈተናል።

በከተማዋ 10 ሺ 498 ትራንስፎርመሮች ላይ በተደረገ ምርምራ መጠነኛ ችግርች አግኝተንባቸዋል ለዚህም መፍትሄ በመስጠት ላይ እንገኛለን።

ሃይል እያቋረጥን ስራ ስንሰራ የነበረ በመሆኑ በምንፈልገው ደረጃ የሃይል መቆራረጡን እንዳንቀንስ የራሱን አስተዋጽኦ አድርጓል።

የሃይል መቆራረጥ መንስኤዎች ለስራ በሚል የሚቋረጡ ፣በብልሽት እና በሃይል አቅራቢው በኩል የሚያጋጥሙ ችግሮች ተጨማሪ ምክንያት ናቸው " ብለዋል።

ተቋሙ 20 ሚሊየን ብር በመመደብ ከነገ ጀምሮ 100 ሺ ችግኞችን ለመትከል ማቀዱን በጋዜጣዊ መግለጫው ወቅት ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
506😡70😭22👏20🤔8🙏7🕊5😱4🥰2😢1
#Ethiopia🇪🇹

የ1 ቢሊየን ዶላር የፋይናንስ ስምምነት በኢትዮጵያ እና ዓለም ባንክ መካከል ተፈርሟል።

የገንዘብ ሚኒስቴር ይህ የድጋፍ ስምምነት የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አካታች የኢኮኖሚ እድገትን ለማገዝ ይውላል ብሏል።

ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ እና የዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ማሪያም ሳሊም ነው የተፈራረሙት።

Via Ministry of Finance

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
😡676325😭73😱26👏24🤔23🕊16🙏5
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia 🇪🇹 #GERD 🇪🇹 " መስከረም ላይ ዝናብ ጋብ ሲል ህዳሴን እናስመርቃለን !!! " የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በሚመለከት ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምን አሉ ? " ህዳሴ አልቋል። ህዳሴን እናስመርቃለን። ህዳሴ ከመመረቁ በፊት ' ብንረብሽ ' ብለው የሚያስቡ ሰዎች አሉ ፤ እናስመርቃለን። ህዳሴን እንዳይመረቅ ለማድረግ የሚያስችል ነገር አሁን የለም። የሚመረቀውም አሁን ነው…
#GERD🇪🇹💪

የግብፅ ምሁራን፣ ባለስልጣናትና ሚዲያዎች የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ስራ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ስለ ግድቡ ተነግረው የማያልቁ እጅግ በርካታ መጥፎና አሉታዊ ነገሮችን ሲያስወሩ ቆይተዋል።

ይኸው አሁንም በዚሁ እኩይ በሆነው ድርጊታቸው ቀጥለዋል።

በየጊዜው አዳዲስ ሀሰተኛ ወሬዎችን እየፈበረኩ ያሰራጫሉ።

በቅርቡ ከግድቡ ብዙ ኪሎሜትር ርቀት ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ እያለ የግብፅ ሰዎችና ሚዲያዎቻቸው " ግድቡ በመሬት መንቀጥቀጡ ከፍተኛ ችግር ውስጥ ገብቷል ፤ የከፋ አደጋ ሊደርስበት ነው ፤ የመሬት መንቀጥቀጡ ግድቡን ያፈርሰው ነው ፤ ሊያወድመው ነው " የሚሉ ፍጹም የፈጠራ ወሬዎችን ለዓለም ህዝብ ሲያሰራጩ ከርመዋል።

ግን አንዳችም የተፈጠረ ነገር የለም ፤ በብዙ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥም ቆመ።

አሁን ደግሞ " የግድቡ ተርባይን ተበላሽቷል ፤ ሱዳን ካርቱም በግድቡ ምክንያት በጎርፍ ልትጥለቀለቅ ነው " የሚል የፈጠራ ወሬ ይዘው መጥተዋል።

ይህንን ወሬያቸውንም በሚዲያ እያሰራጩት ይገኛሉ።

ሀገሪቱ ግብፅ የግድቡ ስራ ገና ከመጀመሩ አንስቶ እንዲስተጓጎል ፣ እንዲደናቀፍ ያልፈነቀለችው ድንጋይ ፤ ያሞከረችው ሙከራ፣ ያልጠናችበት ደጅ አልነበረም። ያም ሆኖ ግን ምንም አልተሳካላትም።

የኢትዮጵያውያን የህይወት ፣ የደም እና የላብ ዋጋ የተከፈለበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ወደ መጠናቀቁ ደርሶ በመጪው መስከረም ወር 2018 ይመረቃል ተብሎ ይጠበቃል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
1.92K👏159🕊59😡55😭25🤔13💔10🥰9😱6
#ሂጅራባንክ

ሂጅራ ባንክ በ2024/25 የበጀት አመት ከ1.8 ቢሊዮን ብር በላይ ጠቅላላ ገቢ አስመዘገበ።

ሂጅራ ባንክ ሦስተኛ ዓመት የእድገት ስትራቴጂ (Growth Strategy) በመተግበር ላይ የሚገኝ ሲሆን 2024/25 በጀት ዓመት "ስኬታማ ውጤት በማግኘት አዲስ ምዕራፍ የከፈተበት" ነው ሲል ገልጿል።

ባንኩ በበጀት ዓመቱ ከ1.8 ቢሊዮን ብር በላይ ጠቅላላ ገቢ (Total Income) ማስመዝገቡን ሲገልጽ፥ ከባለፈው ዓመት ጠቅላላ ገቢ ጋር ሲነጻጸር የ 148.85% በመቶ እድገት አሳይቷል።

ከ840 ሚሊየን ብር በላይ ትርፍ ማግኘቱን የገለጸው ሂጅራ ባንክ ይህም ውጤት ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር 740% ጭማሪ ማስመዝገቡንና በዚሁ መሰረትም የባንኩ ጠቅላላ ROE 40% መድረስ መቻሉን ገልጿል።

የባንኩ ጠቅላላ ሀብትም በከፍተኛ ደረጃ በማደግ በ2024/25 የበጀት አመት ከ15 ቢሊዮን ብር አልፏል፤ ይህም ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር 95.37% ጭማሪ አሳይቷል።

እንዲሁም የተቀማጭ ገንዘብ መጠን ወደ 12 ቢሊዮን ብር በማሳደግ 91.4%በመቶ ስኬታማ የእድገት ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ገልጿል።

ሂጅራ ባንክ በበጀት ዓመቱ 40 ሚሊዮን ዶላር ማግኘቱን ሲገልጽ፥ ይህም ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር 304.5% በመቶ ጭማሪ ማስመዝገብ ችሏል።

ባንኩ የማክሮ ኢኮኖሚ ነባራዊ ሁኔታዎችን ተቋቁሞ ተደራሽነቱን በማስፋት 135 ቅርንጫፎችን መክፈቱን የገለጸ ሲሆን በ2024/25 የበጀት አመት 35 አዳዲስ ቅርንጫፎችን ለአገልግሎት ክፍት ማድረጉን አስታውቋል።

የደንበኞችን ብዛት በተመለከተ አዳዲስ ደንበኞችን በማፍራት ጠቅላላ የደንበኞቹን ቁጥር ወደ 931,148 ሲያሳድግ፥ ይህም ካለፈው ዓመት የደንበኞች ብዛት አንጻር 69.4%በመቶ የደንበኞች ጭማሪን ማሳየት ችሏል ብሏል።

ከዲጂታል አገልግሎቶች ጋር በተያያዘ የኦምኒ ፕላስ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ተጠቃሚዎች ከ350 ሺህ በላይ መሆናቸውንና ይህም ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር 141.86% እድገት ማሳየቱን ነው የገለጸው።

ባለፉት 6 ወራት ብቻ የሀላል ፔይ ዋሌት ተጠቃሚዎች ከ811 ሺህ በላይ የደረሱ ሲሆን ባንኩ ከመሰረታዊ የባንክ አገልግሎቶች በተጨማሪ ያለ ማስያዣ የፋይናንስ አገልግሎት መጠቀም የሚያስችል ኢ-ሙራበሃ የፋይናንስ አገልግሎትን በዋሌት በማስጀመር ስኬታማ ዓመት ማሳለፉን አስታውቋል።

ከ20.9 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ በዲጂታል በኩል ተንቀሳቅሷል ያለው ባንኩ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር 198.60% ዕድገት ማስመዝገቡን አስታውቋል።

አጠቃላይ ከተደረገው የገንዘብ ዝውውር 34.52% በዲጂታል መንገድ ሲሆን ይህም ካለፈው አመት ጋር ሲነጻጸር 10.68% እድገት አሳይቷል።

ሂጅራ ባንክ በ2024/25 የበጀት ዓመት የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት ለማስቀደም በርካታ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል፤ ከእነዚህም ውስጥ ማህበረሰቡን ከባንክ ተጠቃሚነት ወደ ባንክ ባለቤትነት ለማሸጋገር ሰፊ የአክሲዮን ሽያጭ ማከናወኑ ተጠቅሷል።

እንዲሁም "ሀላል ፋይናንሺያል ሊትረሲ ፕሮግራም" በሚል ስያሜ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን ስለ ሀላል ፋይናንስ በማስተማርና ግንዛቤ በማስጨበጥ ላይ ሰፊ ስራዎችን ሲሰራ ቆይቷል።

ባንኩ ስራ ፈጣሪዎችን እና ታታሪ ወጣቶችን ለማበረታታት በማሰብ "ሲራራ አዋርድ" የተሰኘ የውድድር መድረክ በማዘጋጀት እና ማህበራዊ ኃላፊነቱን ከመወጣት አኳያ፣ ለተለያዩ የበጎ አድራጎት ተቋማት እና ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ ሲያደርግም ቆይቷል።

ባንኩ፥ "ይህ ስኬታማ ውጤት የሂጅራ ባንክን ስትራቴጂክ አቅጣጫ፣ የደንበኞቻችን፣ የባለአክሲዮኖቻችን፣ የቦርድ ዳይሬክተሮቻችን፣ የሸሪዓ አማካሪዎቻችን፣ የማኔጅመንት አባላት እና የሰራተኞቻችን ዉጤት ነው።" ሲል ነው የገለጸው።

ካለፉት አመታት ካስመዘገበው ውጤት እጅጉን የጎላ ነው ሲል በገለጸው በዚህ ስኬት "በሀገሪቱ ከወለድ ነጻ ባንኪንግ ዘርፍ ያለውን ሰፊ ​​እምቅ አቅም እና ዘላቂነት ዳግም ያረጋገጥንበት ዓመት ነው" ሲል አስታውቋል።

#HijraBank

https://www.tg-me.com/HijraBank
1.34K👏77🤔53😡38🙏24🥰8🕊8💔8😢6😱2😭2
ዋሪት ፈርኒቸር

የፋይበር ትራሶች የመተንፈስ አቅም እና የአከርካሪ አጥንት ማስተካከልን
እና ማንኮራፋትን የመቀነስ አቅም አላቸው::
እንግዲያውስ በአንድ ቦታ  ምቾት፣ ጤና እና ምርታማ ወደሚሆኑበት
ወደ ማሳያ ክፍሎቻችን በመምጣት ይጎብኙን !
* 22 - ዋሪት ህንፃ
* ጉርድ ሾላ - ሴንቸሪ ሞል
* ለቡ - ቫርኔሮ ፊት ለፊት
* አዳማ - ሶረቲ ሞል 
* ቡልቡላ- ልዑል ህንፃ ፊት ለፊት 
*ወሎ ሰፈር- Ethiolife life real estate
        ዋሪት ፈርኒቸር
        ትክክለኛ ምርጫ!
   ለተጨማሪ መረጃ:  0911210706 / 07
https://web.facebook.com/WARYTZE
https://www.instagram.com/warytfurniture
https://www.tg-me.com/warytfurniture
https://www.tiktok.com/@warytzefurniture
157👏9🕊7🙏3😡1
🔵🛜 የDSTV ተወዳጅ ቻናሎች ከፋይበር ኢንተርኔት ጋር ያግኙ!!

በስማርት ቲቪዎ የዲ.ኤስ.ቲቪ ስትሪም መተግበሪያ በመረጡት ጥቅልና የዳታ ፍጥነት DSTVን በቤትዎ ፋይበር ያጣጥሙ።

🎬 #ጎጆ_ጥቅል ከ70 በላይ ተወዳጅ ቻናሎችን በወር ከ929 ብር ጀምሮ!

💁♂️ እስከ 26.5% በሚደርስ ቅናሽ የቀረቡትን የፋይበር ብሮድባንድ እና የዲ.ኤስ.ቲቪ ጥቅሎች ይግዙ፤ በአማራጭ ይዝናኑ።

ℹ️ ስማርት ላልሆኑ ቲቪዎች STB (Set-Top Box) ለማግኘትና አገልግሎቱን ለመጠቀም የአገልግሎት ማዕከሎቻችንን ይጎብኙ!

👉 እንዴት መጠቀም እንደሚችሉ ይመልከቱ: https://youtu.be/5u0r_t7_WGA


#DSTV
#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
115😡10🙏5🥰3😱1
“ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአየር ትራንስፓርት ትኬት ከኔ ብቻ ካልገዛችሁ በማለቱ የጉዞ መስተጓጎል እየፈጠረነብን ነው” - የውጪ ሀገር ሥራ ስምሪት ኤጀንሲዎች

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በቅርቡ በጀመረው አሰራር መሠረት በሕጋዊ መንገድ ወደ ውጩ ሀገር ለሥራ ለሚሄዱ ተጓዦች በግዴታ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የጉዞ ትኬት ካልገዛችሁ ለጉዞ የሚያስፈልጋቸው የማለፊያ ኪው አር ኮድ እንደማይሰጣቸውና ጉዟቸውን እንደማያጸድቅ መወሰኑን በውጪ ሀገር የሥሪ ስምራት የተሰማሩ ኤጀንሲዎች ተቃወሙ።

"የአየር ትራንስፓርት ትኬት ከኔ ብቻ ካልገዛችሁ በማለቱ የህጋዊ የጉዞ መስተጓጎል እየፈጠረብን ነው"  ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፣ "ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሰሞኑን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ካዘጋጀው አወዛጋቢ ረቂቅ አዋጅ ጎን ለጎን ሰሞኑን ህጋዊ ኤጀንሲዎችን በተለያየ መንገድ ለምን ማዋከብና አሰራሮችን መለዋወጥ እንዳስፈለገው ግራ አጋብቶናል" ብለዋል።

የውሳኔውን ጉዳት ሲያስረዱም፣ "ከዚህ በፊት ስንገዛበት ከነበረው ትኬት ዋጋ እስከ 25 ሺሕ ብር ጭማሪ በሲስተሙ አለ፤ በቃ መቁረጥ የምትችለው በዛ ብቻ ነው" ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

“ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከተቋቋመለት ዋነኛ አላማ አንፃር ወደ ውጪ የጉዞ ትኬት ሽያጭ ውስጥ ከመግባቱ በተጨማሪ ዜጎች በፈለጉት ህጋዊ ቦታ ትኬት ገዝተው የመጓዝ መብታቸውን የሚገድብና የነጻ ገበያ መርህን በግልጽ የሚጣረስ ነው" ሲሉም ተቃውመዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ?

“ዋጋው እጅግ በጣም ንሮብናል፤ መናሩ ብቻ አይደለም፤ ከዚህ በፊት ትኬት ስንቆርጥ ብር ስለማናገኝ ከትኬት ኦፊሶች በብድር ነበር የምንቆርጠው፡፡ አሁን ግን ዋጋውም ጨምሮ ካሽ ብቻ ነው የምንቆርጠው፤ ይሄ ራሱ ሌላ የራስ ምታት ነው ለኛ፡፡

ገና ገንዘብ ባልተቀበልነው ሰው ላይ ነው እንድንከፍል እያስገደዱን ያሉት፡፡ ከትላንት ወዲያ የጸደቀ አዋጅ አለ፤ ግን ይሄን ነገር አዲሱ አዋጅም የድሮውም አያውቀውም ሙሉ ለሙሉ ከሕግ ውጪ ነው፡፡ በሕግ ያልተሰጠው ሥራ ውስጥ መግባቱ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከተቋቋመበት ዓላማ ውጭ ርቆ ሲሄድ ዋና ሥራውን መዘንጋት ይጀመራል፡፡

በአዋጅ የተሰጠውን የሠራተኞችን መብት የሚከታተል ሌቨር አታች ያልመደበ መስሪያ ቤት ነው ትኬት ካልቆረጥኩ ብሎ እየተሟሟተ ያለው፡፡ በሌላ በኩል ቢያንስ ተጨማሪ 60 ዶላር ትከፍላላችሁ እየተባልን ነው፡፡ ለማን ነው የምንከፍለው? ሲሉ ጠይቀዋል።

ታዲያ መፍትሄ ምንድን ነው ትላላችሁ? 

“ባጭሩ ሲስተም ላይ ትኬት መቁረጥ የሚለው ነገር አስገዳጅ መሆኑ መቆም አለበት፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መሠረታዊ የሆነ ሥራ ሰርቶ ጨርሷል ብለን አናምንም፡፡ መሆን ካለበት የራሱን መሠረታዊ ሥራ ይስራ፡፡ ግን ትኬት እኔ ጋር መቆረጥ አለበት ካለ ኦፕሽናል ነው መሆን ያለበት፡፡ ኦፕሽናሊ ያስቀምጠው አወዳድረን ጥሩ ነገር ካገኘን እንሄዳለን፡፡ 

ግዴታ ግን ትኬት ካልቆረጣችሁ የሠራተኞች መውጫ ኪው አር አልሰጣችሁም ማለት ከጀመረ በጣም አሳሳቢ ነው፡፡ መንግስት አስተዳዳር ነው እንጅ ንግድ ውስጥ አይገባም። ግን መስራት አለበት፤ ትኬት ቆረጣ መግባት አለበት ካሉ ኦፕሽናል በሆነ መልኩ ነው እንጅ ግዴታ በመስሪያ ቤቱ ካቆረጣችሁ መውጫ አንስጥም የሚሉ ከሆነ በጣም አደገኛ ነው” ብለዋል።

(ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ምላሽ የሚጠይቅ ይሆናል)

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
599😡103😭25🕊14🤔12🥰6👏3😢3🙏2
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia🇪🇹 የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ እንደሚሻሻል ተገልጿል። ዛሬ 48ኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ተካሂዶ የአዋጁ መሻሻል ላይ ውሳኔ አሳልፏል። ምክር ቤቱ " ቀደም ሲል ሲሰራበት የነበረው የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅ አሁን ከምንገኝበት ሀገራዊ እና አለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ አንጻር ሲታይ በርካታ ክፍተቶች ያሉበት ነው " ብሏል። " የአዋጁን ድንጋጌዎች በማሻሻል የታክስ ስርአቱ…
#Ethiopia🇪🇹

" አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም ! " - የምክር ቤት አባል

በገቢ ግብር ማሻሽያ አዋጅ ላይ ዝቅተኛ  የግብር ከፋይ መነሻ ደመወዝ 5,000 ብር እንዲሆን በምክር ቤት ተጠየቀ፡፡

ይህ ጥያቄ የተጠየቀው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ዛሬ  ከሰዓት በጠራው ልዩ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው፡፡

አሁን በስራ ላይ ያለው የገቢ ግብር አዋጅ ከዘመኑ የኢኮኖሚ ሁኔታ አብሮ እንደማይሄድ እና ከዲጂታል ኢኮኖሚ ጋር እንደማይጣጣም በአዋጁ ላይ በቀረበው አጭር ማብራርያ ተመላክቷል፡፡

የማሻሽያ አዋጁን በተመለከተ ሃሳብ የሰጡት የምክርቤት አባሉ አቶ ባርጠማ ፍቃዱ ምን አሉ ?

- በአዋጁ አንቅጽ 11 ላይ የቀድሞው ተሰርዞ አዲስ ሃሳብ ገብቷል። ከዚህ በፊት ተቀጣሪ ከደሞዘ የሚከፍለው ግብር ከ600 ብር በላይ ጀምሮ ነው። ተሻሽሎ በቀረበው አዋጅ ግን ከ600 ብር ወደ 2,000 ብር አድጓል።

- በመሰረቱ 2 ሺ ብር አሁን በአገራችን የሚቀጠር ሰው የለም።

- ከዚህ ቀደም በመንግስት ተቋም ጽዳት ፣የጉልበት ስራ እና የመሳሰሉ ስራዎች ነበሩ ከ600 ብር እስከ 1,000 ብር ደሞዝ አሁን ባለው ሁኔታ ከ4,500 ብር በላይ ነው ቅጥር ያለው።

- አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም።

- ቢያንስ እንኳን ዝቅተኛ ተቀጣሪው ከግብር ነጻ ቢሆን ጥሩ ነው።

- ግብር ከፋይዉም ከ5,000 በላይ ያለው ስራተኛ ቢሆን።

- የ35 በመቶ ግብር እንዲከፍል የተቀመጠው ከ14ሺ 100 በላይ ነው። ይህም ከወቅቱ ገበያ አንጻር ሲታይ ምንም ነው፤ በዚህ ላይ 35 በመቶ ግብር ሲቆረጥበት ደግሞ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ ወደ 20 ሺ በላይ ከፍ ቢል።

- በስራ ላይ ባለው አዋጅ #መነሻ_ግብር 10 በመቶ ነው። ተሻሽሎ በቀረበው ረቂቅ አዋጁ ግን 15 በመቶ ብሎ ነው የሚጀምረው ይህም ወደ ቀድሞው ወደ 10 በመቶ ቢመለስ ሲሉ ጥሩ ነው።

የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን በስራ ላይ ባለው አዋጅ ላይ ያለው ከፍተኛ ግብር የሚከፈልበት ደሞዝ በተሸሻለው አዋጅ የዝቅተኛ ግብር መነሻ እንዲሆን መጠየቁ ይታወሳል።

ኮንፌደሬሽኑ የሰራተኛውን ኑሮ ያገናዘበ የገቢ ግብር ማሻሽያ እንዲደረግም ጠይቆ ነበር፡፡

ዝቅተኛ ገቢ ያለው የህበረተሰብ ክፍል ፦
- የሚያርፍበትን የግብር ጫና መቀነስ፤
- የግብር መሰረትን ማስፋት፤
- የግብር ስርአቱ ላይ የሚታዩ የፍትሃዊነት ችግሮችን መቅረፍ፤
- የአነስተኛ የንግድ እንቅስቃሴዎች የግብር አከፋፈል ስርአት ቀላል እንዲሆን ማድረግ፤
- ከአዋጁ አላማዎች ውስጥ ጥቂቶቹ ናቸው ተብሏል፡፡

ም/ቤቱ እነዚህን እና ሌሎች ከአባላት የተነሱ ሃሳቦች ታክለውበት ረቂቅ አዋጁ ለፕላን በጀት እና ፋይናንስ ጉዳይዎች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምጽ መርቶታል፡፡

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።

#ShegerFM

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
1.79K👏239🙏63😡60😢41🕊23😭20🤔19😱18🥰6
2025/07/08 15:41:36
Back to Top
HTML Embed Code: