Telegram Web Link
Addis Ababa University- Cisco Networking Academy,
@CiscoExams www.netacad.com www.cisco.com

Online Live class - Cybersecurity Training & Certification Preparation.

Registration Date: April 22 to June 07, 2024
Class start date: June 08, 2024.

Course Recognitions:- Trainees will receive 4 certificates of training completion; 4 digital badges that recognized and accepted in USA, Canada, and Europe, and you will get 32% discount for LPI Linux Essentials and 58% discount for CyberOps Associate Certification exam vouchers.

Mobile #: 0945-039478/ 0902-340070/ 0935-602563
Office : 011-1-260194

Follow our telegram channel: @CiscoExams
BK  C  O  M  P  U  T  E  R S

ማንኛውንም አይነት አዳዲስ ላፕቶፖች ዱባይ ዩዝድ ላፕቶፖች ዴስክ ቶፖችን ጨምሮ ከብዛትና ቅናሽ ጋር ያዘንላቹ መተናል።

ለቢሮዎች ፣ ለተማሪዎች፣ለግሪፊክስ ዲዛይን ባለሙያዎች ፣ ለጌመሮች እንዲሁም ለጨረታ የሚሆኑ በጥራት እና በ ብዛት  ከ1 አመት ዋስትና ጋር እኛ ያገኛሉ።

የላፕቶፕ አማራጮችን ለማየት የቴሌግራም ፔጃችንን Join ያድርጉ https://www.tg-me.com/BKComputers
Inbox @bkcomputer27

አድራሻ አዲስ አበባ መገናኛ ሲቲ ሞል ከ መሰረት ደፋር ህንፃ አጠገብ 1 ፎቅ ላይ እንገኛለን ፤ 0911448148. 0955413433
we make IT easy!
#WKU

" አንድ ተመራቂ ተማሪ እና አንድ  መምህር ጉዳት ካስተናገዱ በኋላ ሁኔታዉ በቁጥጥር ስር ውሏል " - የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አመራር

ከሰሞኑ በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አንድ ሽጉጥ የታጠቀ ወጣት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ተኩስ በመክፈቱ አንዲት ተመራቂ ወጣት እና አንድ መምህር ተጎድተዋል።

የግቢዉ ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት አስተያየት በወቅቱ የተፈጠረው የተኩስ ድምጽ እና ሁኔታ እጅግ ረብሿቸው ነበር።

ይሁንና " ታጥቆ ወደ ግቢው የገባው አካል በቁጥጥር ስር መዋሉና ሰላም መሆኑ " ተነግሯቸው ወደ ትምህርታቸው እንዲመለሱ መደረጉን አስረድተዋል።

ሁኔታውን በተመለከተ አስተያየታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የዩኒቨርሲቲው ኃላፊ " ጉዳዩ ድንገት በመፈጠሩ ለጥቂት ሰአታት ግርግር ቢፈጥርም በግቢዉ የጸጥታ ሀይል በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል " ብለዋል።

በወቅቱ " የመመረቂያ ጽሁፍን በዲስፕሊን ምክኒያት እንዳያቀርብ የተከለከለ የነርሲንግ ተማሪ  ሽጉጥ ታጥቆ በመምጣት ጉዳት አድርሷል " ሲሉ ገልጸዋል።

" የመመረቂያ ወረቀቷን ታቀርብ የነበረዉንና ጓደኛዬ የሚላትን ' እኔ ካላቀረብኩ አንችም አታቀርቢም ' በማለት ሽጉጥ ተኩሶ በማቁሰል በዛ የነበሩትን መምህራን አባሯል " ሲሉ አስረድቷል።

ከዚህ በኋላ ሰዎችን ባይጎዳም ደጋግሞ መተኮሱ በግቢው ውስጥ ችግር መፍጠሩን የሚገልጹት ሀላፊዉ ይህም ተማሪዎችን መረበሹን ገልጸዋል።

በዚህ ወቅት የተሰማዉን የተኩስ ድምጽ የሰማዉ የግቢዉ የጸጥታ ሀይል ወጣቱን በፍጥነት በመቆጣጠር ሁለቱን ተጎጅዎች ወደህክምና ሊወስዳቸዉ እንደቻለና ገልጸዋል።

በወቅቱ ከተከሰተዉ ችግር ለመሸሽ መምህራኑ ባደረጉት ጥረት አንዱ በመስኮት ሲዘል ከፍተኛ አደጋ እንደደረሰበትና የሁለት እግሮቹ አጥንቶች ተሰብረዉ ከፍተኛ የአጥንት ህክምና በማስፈለጉ የግቢዉ ማህበረሰብ ገንዘብ እያወጣለት መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለማወቅ ችሏል።

አንድ ጉዳዩን የምታውቅ ተማሪ ፤ " 1 ወር ከ15 ቀን ልጅ በፊት ደብድቧት ሆስፒታል ገብታ ፤  እሱም 2 ዓመት ተቀጥቶ ነበር። ከዛም በፊት መትቷት ያቃል። ባለፈው ደግሞ ዲፌንስ አቀርባለው ብሎ ሲከለከል ሽጉጥ ይዞ መተኮስ ጀመረ ልጅቷን ተኩሶ ስቷቷል ፤ ከዛ ይዞ ደብድቧታል። ጭንቅላቷ ተፈንክቷል። አንድ መምህርም ከፎቅ ዘሎ ተሰብሯል። አንድ ተማሪም ወድቃ ጭንቅላቷ ውስጥ ደም ፈሶ ሰርጀሪ ተሰርቶላታል " ብላለች።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የ18 ወራት የዱቲ ክፍያ አልተከፈለንም " - የዲላ ዙሪያ ወረዳ ጤና ባለሙያዎች " መሠረታዊ ችግሩ የበጀት ችግር ነው፤ የካሽ እጥረት ነው ያለው " - የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ በጌዴኦ ዞን ዲላ ዙሪያ ወረዳ በ6 ጤና ጣቢያዎች የሚገኙ ጤና ባለሙያዎች የ18 ወራት የዱቲ ክፍያ እንዳልተከፈላቸው፣ እንዲከፈላቸው ቢጠይቁም መፍትሄ እንዳላገኙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። ጤና ባለሙያዎቹ በሰጡት ቃል፣…
#Update

“ ክፍያው ሁሉንም የጤና ባለሙያ ያላማከለ ነው ” - የዲላ ዙሪያ ጤና ባለሙያዎች

“ በወቅቱ ሥራ ያላደሩ ልጆች ናቸው ያልተከፈላቸው ” - የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፤ ጌዴኦ ዞን ዲላ ዙሪያ ወረዳ የሚገኙ ጤና ባለሙያዎች የ18 ወራት የዱቲ ክፍያ እንዳልተከፈላቸው ቅሬታ አቅርበው የነበረ ሲሆን ፣ አሁን ደግሞ ክፍያው ቢጀመርም ሁሉንም ባለሙያዎች ያላማከለ መሆኑን ተናግረዋል።

ባለሙያዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ ክፍያው ሁሉንም የጤና ባለሙያ ያላማከለ ነው” ብለው፣ ክፍያውም የ5 ወራት ብቻ ከመሆኑም ባሻገር ለአንድ ጤና ጣቢያ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል።

ባሉ መረጃዎች ከ5 ወራቱ ለጤና ባለሙያዎቹ የ1 ወር ብቻ ፣ ለኃላፊዎች ለጪጩ ጤና ጣቢያ ባለሙያዎቾ ግን የ5 ወራት እንደተከፈላቸው አስረድተዋል።

“ መንግስት #ብሩን_በጅቶ ወጪ እስካደረገው ድረስ ለሁሉም ጤና ባለሙያዎች መብቱን በማስከበር ያቆሙበት ወራት ገንዘብ ሳይቀር ፦
- ለኡዶ፣
- ለስሶታ 
- ለወቸማ
- ለቱምትቻ ጤና ጣቢያዎች ገንዘቡ ይከፈል” ሲሉ ጠይቀዋል።

ለምን ለሁሉም አልተከፈለም ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቃቸው የጌድኦ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊው አቶ አንዱዓለም ማሞ ፥ “ በወቅቱ ሥራ ያላደሩ ልጆች ናቸው ያልተከፈላቸው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

“ ከ6ቱ ጤና ጣቢያዎች ባለሙያዎች የጪጩ ጤና ጣቢያ ሲያድሩ ነበር። የሌሎቹ ጋ ደግሞ ኃላፊዎች ሲያድሩ ነበር። ስለዚህ የእነርሱ #ባለማደራቸው በዛ ሴኬጁል ውስጥ አልገቡም ፤ እንጂ ሆን ተብሎ አይደለም” ነው ያሉት።

“ የበጀት ችግር ነበር በጋራ ሰርተን የተወሰነ ገንዘብ እንዲከፈላቸው ተደርጓል” ብለው፣ አሁን የተከፈለው ሙሉ የ2015 ዓ/ም የ5 ወራት እንደሆነ፣ የሰሩበት ቀሪው ወራትም በቀጣይ እንደሚከፈል አስረድተዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#ስፖርት : ሪያል ማድሪድ በአውሮፓ ሻሚዮንስ ሊግ ፍጻሜ ቦሪስያ ዶርትመንድን በማሸነፍ ሻምፒዮን ሆነ።

ቡድኑ እጅግ ጠንካራ ነው የሚባለውን የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን በተደጋጋሚ አሸንፏል።

ቡድኑ በታሪኩ ይህን ዋንጫ ሲያሸንፍ 15ኛ ጊዜ ነው።

ይህ የእግር ኳስ ፍልሚያ በሀገራችን ኢትዮጵያ በተለይ በወጣቶች ዘንድ እንዲሁም በመላው ዓለም በርካታ ሚሊኒዮን ተመልካች ያለው ሲሆን ምርጥ የሚባሉት የአውሮፓ ክለቦች የሚሳተፉበት ነው።

Via @tikvahethsport

@tikvahethiopia
Addis Ababa University- Cisco Networking Academy,
@CiscoExams www.netacad.com www.cisco.com

Online Live class - Cybersecurity Training & Certification Preparation.

Registration Date: April 22 to June 07, 2024
Class start date: June 08, 2024.

Course Recognitions:- Trainees will receive 4 certificates of training completion; 4 digital badges that recognized and accepted in USA, Canada, and Europe, and you will get 32% discount for LPI Linux Essentials and 58% discount for CyberOps Associate Certification exam vouchers.

Mobile #: 0945-039478/ 0902-340070/ 0935-602563
Office : 011-1-260194

Follow our telegram channel: @CiscoExams
#DStv

✈️ አውሮፓ እንሂድ

⚽️በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የአውሮፓ ዋንጫ ሊጀመር ነው! በጀርመን የሚደረጉትን ደማቅ ጨዋታዎችን በቀጥታ በዲኤስቲቪ ሱፐርስፖርት ይከታተሉ!

🏆የምትወዱዋቸውን የአውሮፓ ታላላቆችን ዋንጫ ፍልሚያ በወር 350 ብር!

የዲኤስቲቪ ዲኮደር በ1,999 ብር ከ1 ወር ነፃ ሜዳ ፓኬጅ ጋር ያገኛሉ።

የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን የMyDStv Telegram bot ሊንክ ይጫኑ!
👇
https://mydstv.onelink.me/vGln/eth2

#Euro2024 #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
“ እናቴን አድኑልኝ፣ የልቧ ሁለቱ ቱቦዎች በመጥበባቸው ደም እየመለሱ ነው ” - ልጅ

የእናቱ ሁለት የልብ ቱቦዎች ጠበው ወደ ሰውነት አካል ክፍላቸው መተላለፍ ያለበት ደም ወደ ኋላ እየተመለሰ በመሆኑ በአስቸኳይ መታከም እንዳለባቸው ሀኪም ማዘዙን የታማሚዋ ልጅ ገልጿል።

የታማሚ ወ/ሮ ትዕግስት ነብሮ ልጅ ናትናኤል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል፣ “ እናቴን አድኑልኝ፣ የልቧ ሁለቱ ቱቦዎች በመጥበባቸው ደም እየመለሱ ነው ” ይላል።

“ እኔ የአምስተኛ ዓመት አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ የዘንድሮ ተመራቂ ተማሪ ነኝ። እናቴን ለማሳከም 760,000 ብር ተጠይቀናል። የተገኘው 192,000 ብር ብቻ ነው ” ብሏል።

“ ልቧ ሲመታ ስለሚያማት እናቴ አሁን ምንም አይነት እንቅስቃሴ አታደርግም ” ያለው ተማሪ ናትናኤል፣ “ ኬዙ ቆየት ብሏል፤ ከአንድ ወር በፊት ግን በጣም አሟት ለ17 ቀናት ሆስፒታል ተኝታ ነበር ” ሲል ሁነቱን አስረድተዋል።

ለህክምና 760,000 ብር እንደሚያስፈልግ ከሆስፒታል የተጻፈ ማስረጃ ደብዳቤ አለ ? ተብሎ ለቀረበለት ጥያቄ፣ “ አዎ አለ ” ብሎ የላከ ሲሆን፣ ደብዳቤውም ከላይ ተያይዟል።

ተማሪ ናትናኤል ባስተላለፈው መልዕክት፣ “ከአቅም በላይ ስለሆነ ነው እንጂ እርዳታ አልጠቅም ነበር። ግን ካለው የኑሮ ውድነት አንጻር አቅም ጠፍቶ ነውና እርዳታ አድርጉልኝ” ሲል ተማጽኗል።

መርዳት ለምትፈልጉ 1000298948935 የNatnael Demelash አካውንት ቁጥር ነው። እንዲሁም 1000032440324 የTigst Nebro አካውንት መጠቀም ይቻላል።

መደወል ለምትፈልጉ 0993655876 ናትናኤል ደመላሽን ማግኘት ይቻላል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

በጀኔቭ የመኪና አስመጭና በቤቶች ኮርፖሬሽን መካከል የተፈጠረው ነገር ምንድን ነው ?

በአዲስ አበባ ቂርቆስ ክ/ከተማ ደንበል አደባባይ አካባቢ " ጄኔቭ የመኪና አስመጪና ሻጭ ድርጅት " የተከራየው ህንፃ የኪራይ ውሉ እንዲቋረጥ ሊደረግ በመሆኑ ያለውን ቅሬታ እያቀረበ ይገኛል።

የጀኔቭ ዋና እና ምክትል ማናጀሮች ቅሬታቸው ፦
- ህንፃው ለMixed አገልግሎት ሆኖ ሳለ ለሆቴል ማስፋፊያ ይሰጥ መባሉ፣
- እኛ እራሳችን ከፍተኛ ግብር ከፋይ ሆነን ለሌላ ለሆነ አካል ይሰጥ መባሉ፣
- ቤቱ ለልማት ይሰጥ ተብሎ የካቢኔ ውሳኔ ባለማግኘታቸው፣
- ለልማት ይሰጥ የተባለው በ2013 ዓ/ም ሆኖ ሳለ አሁን ውሉ ይቋረጥ መባሉ፣
- ቤቶች ኮርፖሬሽን ሊሟገት ሰገባው የኪራይ ውሉ እንዲቋረጥ የድጋፍ ደብዳቤ በመፃፉ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ራሱ ኮርፖሬሽኑ ቢያለማው እኛ መልቀቅ እንችላለን የመንግስት ቦታ ስለሆነ ግን ለምንድነው ለሶስተኛ ወገን ተላልፎ የሚሰጠው ? ያውም ሆቴል ሳይሆን ሆቴል ተብሎ ሲሉ ጠይቀዋል።

የቤቶች ኮርፖሬሽን የፃፈው የድጋፍ ደብዳቤ ላይ፥ ምክንያቶቹን በዝርዝር ካብራራ በኋላ፣ የተከራይ ውል እንዲቋረጥ ያዛል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጥ ኮርፖሬሽኑን ጠይቋል።

የኮርፖሬሽኑ ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ አማኑኤል አያሌው፣ “ የመጀመሪያ ስህተቱ ሰዎቹ ልክ እንደ ግል ይዞታ አድርገው እያቀረቡ ነው። ይዞታው የቤቶች ኮርፖሬሽን ነው። ቅሬታ አቅራቢዎቹ ደግሞ የንግድ ቤት ተከራይ ናቸው ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

“ ከተማ አስተዳደሩ ‘እዚያ አካባቢ የሆቴል ዲዛይን ነው’ አለ። እኛ ሆቴል አንገነባም። ስለዚህ እኛ ይዞታ አናስተላልፍም ለግለሰብ። እሳቸውም ለእኛ ቅሬታ ቢያቀርቡ መስጠት አንችልም ” ብለዋል።

አቶ አማኑኤል፣ “ ቅሬታ ካላቸው ለከተማ አስተዳደሩ ነው ማቅረብ ያለባቸው። ቦታው ለእኔ ይመደብ ብለው ማቅረብ ይችላሉ ” ነው ያሉት።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ፣ ቦታው ለልማት እንዲነሳ በካቢኔ ስለመወሰኑ እንደማያውቁ ላነሱት ቅሬታ በሰጡት ምላሽ አቶ አማኑኤል፣ “ የካቢኔ ውሳኔ ተለጥፏል ያውቃሉ። በ2013 ዓ/ም የተለጠፈ የካቢኔ ውሳኔ ነው ” ብለዋል። (ይህን የሚገልጽ ዶክመትም አሳይተዋል)

ለቲክቫህ የላኩት ሰነድም ህንፃው ለልማት እንዲነሳ በከተማ አስተዳደሩ በ2013 ዓ/ም መወሰኑን ያትታል።

እንዲሁም፣ ቦታው ለMixed አገልግሎት ሆኖ ሳለ ለምን ለሆቴል ማስፋፊያ ይሰጥ በመባሉ ጀኔቭ ላነሳው ቅሬታ፣ “ ይህ ሰው ተከራይ ነው። ይህን ያህል ቅሬታ ማንሳት የለበትም፣ ተቀባይነት የለውም ” ብሏል ኮርፖሬሽኑ።

“ ተከራይ ነው፤ በንግድ ህጉ መሠረት ይህ ሰው ሲዋዋል መንግስት ወይም ኮርፓሬሽኑ ቤቱን ለልማት  ሲፈልገው ውል ያቋርጣል ይላል ” ነው ያለው።

ተወሰነ የተባለው በ2013 ዓ/ም ሆኖ ሳለ ለምን አዘግይቶ አሁን መጠየቅ አስፈለገ ? ሲል ጀኔቭ ላነሳው ጥያቄ አቶ አማኑኤል፣ “ አብዛኛውን ውሳኔ አንቀበልም። መሬቱን ማቆየትና ማልማት ስለምንፈልግ ” ሲሉ መልሰዋል።

አክለው፣ “ ግን አሁን የአዲስ አበባ ከተማ መልሶ ማልማት ላይ ያለው ‘ ከመንግሥት እንቅፋት እየሆነናችሁ ነው ’ የሚል ቅሬታም እየመጣ ስለሆነ ማልማት በምንችለው መንገድ እኛ እናለማን። ባለሃብቱ ማልማት ባለበት ደግሞ ባለሃብቱ ” ነው ያሉት።

የጄኔቭ ማናጀር አቶ አብርሃም ለማ በበኩላቸው፣ “ ራሳቸው ተጠይቀው የሰጡት መልስ አለ። ‘ ራሱን ችሎ የሚገነባ ቦታ ስለሆነ ራሳችን እንገነባለን። ካልሆነ ደግሞ ተከራዩ ማልማት የሚችል ከሆነ ቅድሚያ እንሰጣለን’ ” የሚል ምላሽ ከከተማ ከንቲባ ለቀረበላቸው ጥያቄ እንደሰጡ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#Amhara

የኤፍራታ ግድም ወረዳ አስተዳዳሪ ተገደሉ።

በወረዳው የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች የወረዳውን አስተዳዳሪ አቶ አልብስ አደፍራሽን ትለንትና በምሽት በመግባት እንደገደሏቸው ተሰምቷል።

ወረዳው ባወጣው የሀዘን መግለጫው ፥ " አቶ አልብስ ለዓመታት በቀውስ ነጋዴዎች ለችግር ተጋልጦ የሴራ ፖለቲካ መሸቀጫ የተደረገውን የጀውሃና አካባቢው ማህበረሰብ ቀርቦ በማወያየት መተማመን ፈጥሮና አደራጅቶ ወደ ቀደመ አካባቢውና ኑሮው እንዲመለስ በማድረግ ላይ ነበሩ " ሲል ገልጿል።

አክሎ " የወደሙትን የጤናና ሌሎች ተቋማትንም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅርበት በመስራት መልሶ እያቋቋመ የነበረ ደከመኝን የማያውቅ፣ ለእውነት የቆመ ንፁህ የሕዝብ ልጅና አገልጋይ፤ እውነተኛ የአማራ ጀግና ነበር " ብሏል።

አቶ አልብስ አደፍራሽ ትላንትና ምሽት ቤታቸው በገቡ ታጣቂዎች ተገድለዋል።

@tikvahethiopia
#Tigray

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በትግራይ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በያዝነው ሳምንት አገልግሎት መስጠት የጀመረው በመቐለ ከተማና አከባቢዋ ነው።

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በትግራይ አገልግሎት መስጠት ስለመጀመሩ አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ በ2 ምዕራፎች 16 የትግራይ ከተሞች የ4G እንዲሁም የ5G የሞባይል ዳታ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየተሰራ ነው ብሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
" የሃይማኖት ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ ምን ይዟል ? በኢትዮጵያ አዲስ የተዘጋጀ " #የሃይማኖት_ጉዳዮች " ረቂቅ አዋጅ አለ። ይህ ረቂቅ አዋጅ በርካታ ጉዳዮችን ይዟል። አንዱ የአምልኮና የመቃብር ቦታን የተመለከተ ሲሆን ፥ ረቂቅ አዋጁ ለሃይማኖት ተቋማት የመሬት አቅርቦት በመሬት አጠቃቀምና የሊዝ ሕጎች መሠረት ይወሰናል ይላል። ለአምልኮ ወይም ለመቃብር ቦታ በተጠየቀበት አካባቢ ለሃይማኖት ተቋሙ ለተመሳሳይ…
#Update

" በሃይማኖት ጉዳዮች ረቂቅ አዋጅ " ላይ የመጨረሻ የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ተካሂዷል።

በመድረኩም የሃይማኖት ተቋማት ቅሬታ ማቅረባቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

ተቋማቱ ረቂቅ አዋጁ ከመፅደቁ በፊት የሁሉንም የሃይማኖት ተቋማት መብትና ክብር የሚጠብቅ መሆኑ ማረጋገጥ ይገባል ብለዋል።

በአብዛኛው ተከብሮ የቆየው የሃይማኖቶች ነፃነት ላይ ገደቦችን እንዳይጥል ሥጋት እንዳላቸው ገልጸዋል።

የቀረቡ ቅሬታዎች ምንድናቸው ?

1ኛ. ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ተወካዮች የተነሳው ቅሬት፦

በረቂቁ አዋጁ ላይ የአደባባይ በዓላትን በሚመለከት " የአደባባይ ኩነት " ተብሎ መቀመጡን በማንሳት ይህ ትክክለኛ ትርጉም አይደለም ብለዋል፡፡

ለዚህ በማሳያ " የአደባባይ ኩነት በተፈቀደው ቦታ ብቻ መደረግ አለበት " በሚል በረቂቁ ላይ የተቀመጠውን ነው።

ለአብነት #የጥምቀት_በዓል የአደባባይ ሃይማኖታዊ በዓል ቢሆንም ፤" ከተፈቀደለት አደባባይ ውጪ መንገዶች ላይ መካሄድ አይፈቀድም " የሚል ትርጓሜ እንዳይሰጠው #ያሠጋል ብለዋል፡፡ 

ሌላው " የሃይማኖት ተቋም የሚይዘው ስያሜ፣ ዓርማ ወይም ምልክት ቀድሞ ከተቋቋመ ተቋም ስም፣ ዓርማ ወይም ምልክት ጋር ተመሳሳይ መሆን የለበትም " በሚል ረቂቁ ላይ የተቀመጠው ነው።

ይህ ፤ " #በከፊልም ሆነ #ሙሉ_በሙሉ ተመሳሳይ መሆን የለበትም " በሚል ሊስተካከል እንደሚገባው ገልጸዋል።

ለዚህ ምክንያቱ " የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሚለውን ስያሜ የኢትዮጵያ የሚለውን ብቻ በማውጣትና የራሳቸውን በመተካት አገልግሎት ላይ ሲያውሉ የሚታዩ አካላትን ስለተመለከትን ነው " በማለት አስረድተዋል፡፡

2ኛ. የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ ቤትን በመወከል የተገኙ ተሳታፊዎች ያቀረቡት ቅሬት ፦

ሃይማኖታዊ ተግባራትን በሚከለክለው የረቂቅ አዋጁ ክፍል " በአውሮፕላን ማረፊያ ተርሚናሎች መፈጸም የተከለከለ ነው " በሚል የቀረበው ሊስተካከል ይገባል ብለዋል።

#ሶላት_የደረሰበት_ሙስሊም በአውሮፕላን ማረፊያ ተርሚናሎች እንዳይሰግድ መከልከል እንደማይቻል ገልጸዋል፡፡

" በከተሞች ውስጥ ለአምልኮና መቃብር የሚሰጥ ቦታ የከተማውን የዕድገትና የልማት ዕቅድ ወይም ማስተር ፕላን የማይቃረን መሆን አለበት " በሚለው ረቂቁ ላይ ይህ ወደ ተግባራዊነቱ ሲገባ አስቸጋሪ እንደሚሆን ገልጸዋል።

መጀመሪያ የተገነባ ቤተ እምነት " ከከተማው ማስተር ፕላን ጋር የሚቃረን ነው " በሚል እንዳይፈርስ ዋስትና የማይሰጥ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

በመንግሥት ተቋማት የሚሠሩ ሠራተኞች ሁሉ እምነት እንዳላቸው፣ ለአብነትም አንድ ሙስሊም በመንግሥት ተቋም ተቀጥሮ ሲሠራ ሶላቱን በሚሰግድበት ወቅት፣ በተቋሙ ውስጥ ሃይማኖታዊ ክንውን አድርጓል ሊባል መሆኑንና ረቂቁ ይህን እንዴት ማስታረቅ እንደሚችል ጥያቄ አስነስቷል፡፡

3ኛ. የወንጌል አማኞች ካውንስል ተወካዮች ቅሬታ ፦

ረቂቅ አዋጁ በወንጌላውያን ሃይማኖት ላይ ያነጣጠረ መሆኑን ገልጸዋል።

" በተለይ ሃይማኖታዊ አስተምህሮ የሚከለክሉ የረቂቁ ክፍሎች፣ ወንጌል መስበክ መሠረታዊ አስተምሯችን ለሆነው ለወንጌላውያን ተቀባይነት ሊኖረው የማይችል ነው " በማለት ተናግረዋል፡፡

ይህ ' መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም ' በሚል የተቀመጠውን መርህ የጣሰ እንዳይሆን ሥጋታቸውን ገልጸዋል፡፡ 

Credit ➡️ Reporter Newspaper

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ በሀገሪቱ ውስጥ ያለ ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም የፋይናንስ ኦዲት ሪፖርቱን ለሰላም ሚኒስቴር ማቅረብ እንደሚኖርበት ፤ ከውጭ አገር የሚመጣ የገንዘብ ዕርዳታ በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚኖርበት የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ መዘጋጀቱን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል። " የሃይማኖት ጉዳዮች አዋጅ " የተሰኘው ረቂቅ አዋጁ የሃይማኖት ተቋማቱ ተቀባይነት ያለው የሒሳብ አያያዝና የኦዲት ሥርዓት…
#Update

" በሃይማኖት ጉዳዮች ረቂቅ አዋጅ " ላይ የመጨረሻ የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ ላይ ረቂቁ ከባለፈው መጠነኛ #ማሻሻያዎች ተደርጎበት መቅረቡን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

ምንድናቸው ?

በመጀመሪያው ረቂቅ አዋጅ ያልነበረና የመንግሥትንና የክልሎችን ግዴታና ኃላፊነት በመዘርዘር የተቀመጠው ክፍል አንዱ ነው።

በዚህ ክፍል ላይ መንግሥት በሃይማኖት አስተምህሮና የውስጥ ጉዳይ #ጣልቃ_መግባት_እንደማይችል ተደንግጓል፡፡

በተጨማሪ ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም ከውጭ አገር የሚላክለትን የገንዘብ ዕርዳታ፣ ስጦታ ወይም ሌሎች የገንዘብ ድጋፎችን በሕግ ሥልጣን ለተሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚኖርበት ተደንግጎ የነበረው የረቂቅ አዋጁ ክፍል ከተሻሻለው ረቂቅ እንዲወጣ ተደርጓል፡፡

ነገር ግን ማንኛውም የሃይማኖት ተቋም ፦

° የሃይማኖት ተቋሙን ኦዲት ሪፖርት ለሰላም ሚኒስቴር እንዲያቀርብ፣

° የበጀት ዓመቱ በተጠናቀቀ #በ3_ወራት የፋይናንስ እንቅስቃሴውን በገለልተኛ ኦዲተር ማስመርመር እንደሚኖርበት የተቀመጠው የረቂቁ ክፍል በተሻሻለው ላይ #ተካቷል፡፡

ሌላኛው ተሻሽሎ የቀረበው የረቂቅ ክፍል #አለባበስን እና የተማሪዎች #አመጋገብን ጨምሮ በማንኛውም የትምህርት ተቋም ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚደረግ ሃይማኖታዊ ተግባር የመንግሥትና ሃይማኖት መለያየት መርህንና የሃይማኖት ነፃነትንም በጠበቀ መንገድ መከናወን አለበት የሚለው ነው፡፡

የሰላም ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች ምን አሉ ?

የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረኩ #የመጨረሻ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ከዚህ ቀደም #በመንግሥት እና #በሃይማኖት መካከል ያለው ልዩነት ምን ድረስ እንደሆነ ሳይታወቅ ቆይቷል ብለዋል።

አዋጁን ማዘጋጀትም ያስፈለገው ይህን ጉዳይ በግልጽ ለማስቀመጥ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

መንግሥት በሃይማኖት ተቋማት ነፃነት ውስጥ ጣልቃ የመግባት ፍላጎት እንደሌለው  ፤ ነገር ግን አብረው በሚሠሩባቸው ጉዳዮች በሕግ የተቀመጠ አሠራር ሊኖር እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

በመድረኩ ላይ የተነሱ ሐሳቦችን በግብዓትነት #ወስዶ ለሚመለከተው አካል የሚቀርበውን ረቂቅ አዋጅ እንደሚያዘጋጅ ተገልጿል፡፡

Credit - Reporter Newspaper

@tikvahethiopia
2024/06/03 01:46:05
Back to Top
HTML Embed Code: