Telegram Web Link
ይህ ማማረር ሳይሆን ትዝብት ነው...

በአገራችን ካሉ ግዙፍ የቴሌቭዥን ጣቢያዎች መካከል ከአንዱጋ ስለ የዙፋን ልፊያ የቃለመጠይቅ ቀጠሮ ነበረን። እንዳላረፍድ ስላስጠነቀቁኝ በጊዜ ከቤቴ ወጣሁ። የቀጠሮችን እለት "በጊዜ ተገኝልኝ" ብሎኝ ነበር አስተባባሪው።... በጊዜ ተገኝ ካለኝ ከ30 ደቂቃ በኋላ ቀጠሮ መሰረዙን ነገረኝ።
የሚጠበቅ ነው!

ሰሞኑን ስለዙፋን ልፊያ ልናወራ ከአንድ ሬዲዮ ጣቢያ ጋር ቀጠሮ ነበረን። እሱም ተሰረዘ። አልገረመኝም።

የኛ አገር ሚዲያ ባህሪ አስቸጋሪ ነው። ሎቢ ማድረግ ይፈልጋል። "መጽሐፍ ፅፌያለሁና እንግዳ አድርጉኝ" እንድትሏቸው ይፈልጋሉ። ራስን ማሻሻጥ ላይ ጎበዝ ያልሆነ ስለስራው አይወራለትም።

ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ ስለ ዙፋን ልፊያ ለማውራት ቀጠሮ ከሰጡኝ በኋላ ቀጠሯቸውን የሰረዙ የዩቲዩብ ፥ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ሚዲያዎች አሉ።... የጠበቅኩት ነው። ገና የመጽሐፉን ርዕስ ሲያዩ "ይሄ ነገር..." ያሉኝ ብዙ ናቸው። አልፈርድባቸውም።

ማማረር አልፈልግም። ግን ደግሞ የተጋነነ ፍርሃት ትክክል አይመስለኝም።

ለማንኛውም ከዚህ በኋላ የዙፋን ልፊያን ለማስተዋወቅ የተሻለው ቦታ ማህበራዊ ገፅ ይመስለኛል።

መጽሐፉን ያነበባችሁ ሰዎች ሪቪው ብትፅፉ ደስ ይለኛል።

አቅም ያላችሁ ደግሞ መጽሐፉን ለሰዎች በስጦታ ብትሰጡ ሸጋ ነው።

ለምሳሌ ወንድማችን ቢላል ከዚህ ለ35 ሰዎች ዮሴፍ ኢየሱስ ወርቅ ደግሞ ለ10 ሰዎች የዙፋን ልፊያን ስጦታ ሰጥተዋል።

መጽሐፉን አምስትም አስርም እየገዙ ስጦታ መስጠት እኔን ማበረታታት ነው። ደግሞ ማንበብ የሚፈልጉ እንዲያነቡት ማገዝ ነው።
👍6
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ቴዎድሮስ ፀጋዬ 🤝 የዙፋን ልፊያ

"ለሌሎችም አረአያ እንዲሆን ብዬ ነው የዙፋን ልፊያን የማነሳው"
👍2
‹‹... ‹ተደፈርኩኝ› ብዬ ለማዘን አቅም የለኝም፡፡ የመጣሁት ስለልጄ ወደፊት በመጨነቄ ነው››

‹‹ልጅሽን ምን አገኘው?››

‹‹የአራት ዓመት ልጅ አለኝ፡፡ ስለ እርሱ ተጨንቄ መ ሞ ቴ ነው፡፡ ጦርነቱ ሲጀምር ሕግ ጠፍቶ ስርዓት አልበኝነት ነገሠ››

አዛውንቱ የሚያውቁትን እውነት ደግመው እየሰሙ ነው፡፡ የእርስ በእርሰ ጦርነቱ ከጀመረ በኋላ የሐገሪቱ ሕግ ሕገ-ወጥነት እንደሆነ አስተውለዋል፡፡ የሐይማኖት አባቶች ጆሮ ሲነፈጉ፣ የእምነት ተቋማት አቅም ሲያጡ፣ የመብራት ከተማ አባቶች መደመጥ የማይችሉ ሲሆኑ፣ ሸንጎው መዘባበቻ ሲደረግ፣ ሥነ-ምግባር ለጉልበት ሲገብር፣ ሕግ ለአመፅ ሲሰግድ አይተዋል፡፡

‹‹ጉልበተኞች ባሌን አገቱት›› አለች ሕይወት

‹‹ጉልበተኞች ባሌን ካገቱተ በኋላ ማስለቀቂያ ገንዘብ ጠየቁኝ፡፡ የጠየቁኝን ያህል ገንዘብ ዘር ማንዘሮቼ ኖሯቸው አያውቅም፡፡ የማደርገው ግራ ቢገባኝ የልጄን አባት ለማስለቀቅ ለልመና ወጣሁ፡፡ የሆነብኝን እየተናገርኹ የመብራትን ሕዝብ ለመንኹ፡፡ህዝቡ አላሳፈረኝም ነበር፤ አጋቾቹ ግን አሳፈሩኝ፡፡ ገንዘቡን ከተቀበሉኝ በኋላ ባሌን ይለቁልኛል ብዬ ብጠብቅም እነርሱ ግን ‹ገንዘቡን የከፈልሽው የሰጠንሽን ቀነ ገደብ አሳልፈሽ ነው› ብለው ባሌን ገ ደ ሉ ት››

አዛውንቱ ‹የመብራታዊያን አባት› በመሆናቸው ሲደሰቱ ኖረዋል፡፡ ‹‹ፈጣሪ ስለወደደኝ መረጠኝ›› ይሉ ነበር፡፡ ከቅርብ ጊዜ በኋላ ግን ደስታቸው በምሬት ተተክቷል፡፡ ‹ምነው ባልተመረጥኩ› ማለት ጀምረዋል፡፡ የእርስ በእርስ ጦርነቱ ከጀመረ በኋላ በየዕለቱ ብዙ ሀዘን ይሰማሉ፡፡ ጫንቃቸው መቋቋም ከሚችለው የበለጠ የመከራ ታሪክ ያደምጣሉ፡፡

‹‹አባቴ ፈርቻለሁ›› አለች ሕይወት

‹‹እንደምሞት ታውቆኛል፡፡ ባሌ ከሞተ በኋላ ልጄን ለማሳደግ ብዙ ለፋሁ፡፡ እድሜ ለዐጦ ርነ ቱ ስራ ማግኘት በባዶ ሆድ ወደተራራ መሮጥ ሆነብኝ፡፡ ቢቸግረኝ ልመና ጀመርኩ፡፡ ጦ ር ነ ቱ ኩራቴን ወስዶብኛል፣ ክብሬን ቀምቶኛል፡፡ ልመናን ብቻ ሳይሆን ተገዶ መደፈርን በፀጋ መቀበል ቻልኩበት፡፡ ከአንድም ሦስቴ ተደፈርኩ፡፡ በህብረት ተፈራረቁብኝ፡፡ መደፈርን ይሄ ጦርነት ለሁሉም ሴቶች ያመጣው መርገም እንደሆነ ስላመንኩ ህመሜን ቻልኩት››

ህይወት እየተናገረች አዛውንቱ ወደ ውስጥ አለቀሱ፡፡

የጦርነት እሳት ከተለኮሰበት ቀን ጀምሮ የሴቶች ማሕጸን ጦር ሜዳ መሆኑ ያንገበግባቸዋል፡፡ ‹ሴት ስትጠቃ ሐገር ትጠቃለች› ይላሉ አዛውንቱ፡፡

‹ሴት የቤተሰብ ማገር ናት፡፡ የተጠቃች ሴት ለመንፈስ ህመም ተጋላጭ ትሆናለች፡፡ ሥነ-ልነቦናዋ ይታመማል፣ የአዕምሮ ጠባሳ ይፈጠርባታል፡፡ ሥነ-ልቦናዋ የተጎዳ ሴት ቤተሰብ ስትመሠርት ቤተሰብዋ ለህመም ተጋላጭ ይሆናል፣ የታመመ ቤተሰብ የታመመ ልጅ ይፈጥራል፣ መንፈሱ የታመመ ልጅ የሐገር ስጋት ነው› ይላሉ አዛውንቱ፡፡
‹የሰለጠነ ሕዝብ ለደካሞች ይሟገታል፡፡ ጉልበተኛ ወንድ ደካመዋን ሴት ሲያጠቃ ጠበቃ መሆን ማህበረሰባዊ ግዴታ ነው› ይላሉ አዛውንቱ፡፡

‹ጉልበተኞች ደካሞችን ሲያጠቁ ዝም ማለት ሐገር እንድትፈርስ መፍቀድ ነው፡፡ ወንድ ሴትን ሲያጠቃ ዝም የሚል ሰው ጉልበተኛው ደካማን እንዲያጠቃ ፈቅዷል፡፡ ይህ ማለት ሀብታም ድሃን እንዲበድል፣ በቁጥር ብዙ የሆነ ጥቂት የሆኑትን እንዲያጠቃ፣ ስልጣን ያለው ስልጣን አልባው ላይ እንዲሰለጥን መፍቀድ ነው፡፡ ጉልበተኛ ጉልበት የለሽን ሲያጠቃ ስርዓት አልበኝነት ይፈጠራል፡፡ ስርዓት አልበኝነት ደግሞ ሐገር ያፈርሳል› ይላሉ አዛውንቱ፡፡

‹አስገድዶ የሚደፍር ወንድ ማህበራዊ ግኑኝነት ላይ ጥቃትን ይፈፅማል፡፡ እርስ በእርስ እንዳንተማመን የሚያደርግ መርዝን ይረጫል፡፡ ማህበራዊ ግኑኝነትን ያላላዋል› ይላሉ አዛውንቱ

‹አስገድዶ ደፋሪ፣ ወንድነት ላይ ጭምር ጥቃት አድራሽ ነው፡፡ ደፋሪዎች ሌሎች ወንዶች እንደ አውሬ እንዲታዩ ያደርጋሉ፡፡ ወንዶች ጠባቂዎች ተደርገው መቆጠር ሲገባቸው እንደስጋት እንዲታሰቡ ሰበብ ይሆናሉ› ይላሉ አዛውንቱ፡፡

‹‹አባቴ›› አለች ሕይወት እንባዋን እየጠረገች

‹‹እያደመጥኩሽ ነው፤ ቀጥይ ልጄ››

‹‹በልመናው ብዙ አልቆየሁኝም፡፡ ሁሉም ህዝብ ለማኝ ሆኗል፡፡ ትላንት ለተቸገሩት ይረዱ የነበሩ ዛሬ እርዳታ ፈላጊ ሆነዋል፡፡ ቸርነትን ለማድረግ ይዘረጋ የነበር እጅ ለእርዳታ ፍለጋ ሲዘረጋ አየን፡፡ ለማኙ ሲበዛ ልጄን ለምኜ ማብላት ቸገረኝ፡፡ ያኔ ገላ ሽያጭ መፍትሄ መሰለኝ፡፡ ከልመና ወደ ሽርመጥና ገባሁ፡፡ … እድሜ ለጦርነቱ አቻዎቼ በመደዳ ሴተኛ አዳሪ እየሆኑ ነው፡፡ ስህተት እና ትክክሉ ድንበሩ ጠፍቶብናል፡፡ ለእኔና ቢጤዎቼ ትክክል ማለት ራስን በሕይወት ማቆየት ሆኗል››

አዛውንቱ ጦርነቱ የተጀመረበትን ቀን ረገሙ፡፡ በሐገሪቱ ምን እየተደረገ እንዳለ የማያውቁ ሚስኪኖች በጦርነቱ የተነሳ የተጫነባቸውን የመከራ ቀንበር አስበው ጦርነቱ የጀመረበትን ቀን ረገሙት፡፡

‹‹አባቴ ሰሞኑን የምሞት ይመስለኛል፡፡ የስኳር ህመም እያሰቃየኝ ነው፡፡ መድሀኒት የለኝም፡፡ መድሀኒት መግዣ አላጣሁም፤ ያጣሁት መድሀኒት ነው፡፡ ሁለቱ ተዋጊዎች በዙሪያችን መፋለም ከጀመሩ በኋላ ወደ ከተማችን መሠረታዊ ነገሮችን ማስገባት ከባድ ሆኖብን መክረሙን ያውቁታል፡፡በዚህ የተነሳ በከተማችን መድሀኒት ጠፍቷል፡፡ የምሞት እየመሰለኝ ስለልጄ ፈራሁኝ አባቴ››

አዛውንቱ እንባቸውን ለመገደብ ያደረጉት ጥረት ተሳክቶላቸው ቆይተው የነበረ ቢሆንም ተሸነፉ፣ ለእንባቸው ተረቱ፡፡ አንገታቸውን አቀርቅረው አለቀሱ፡፡

የለቅሷቸው ሰበብ ጉዳቷ ብቻ አልነበረም፡፡ በየዕለቱ ብዙ ሰቆቃ ያደምጣሉ፣ ችግር ሲያደምጡ ነግቶ ይመሻል...

ያስለቀሳቸው የሕይወት ስሜት ነው፡፡

በፊታቸው ሆና ብሶቷን የምትናገርው ምስኪን ሴት ገፅታ ላይ የተመለከቱት ስሜት አስነባቸው፡፡ ‹‹ሀዘኗ ከህመሟ አይነፃፀርም፡፡ ማዘን በሚገባት መጠን እንዳታዝን ያደረጋት መከራን መለማመዷ ነው›› ብለው ሲያስቡ አለቀሱ፡፡

‹‹መከራን እንደመልመድ ያለ መከራ ከወዴት ይገኛል?››

#የዙፋን_ልፊያ

መጽሐፉን ያላነበባችሁ አንብቡ፥ ያነበባችሁ ሃሳባችሁን አጋሩ።


@Tfanos
4
የአንባቢ አስተያየት

መጽሐፍህን አንብቤ ጨረስኩት። በስራ መደራረብ ምክንያት ለንባብ ጊዜ አላገኘሁም ነበርና፡ ትላንት ነው የጀመርኩት። ጀምሮ ለማቆም ይከብዳል። እያንዳንዱ ገፀ ባህሪ የሚወክለው ስብእና (ፖለቲካችን፥ ኋላ ቀር እምነታችን፥ የስነ አይምሮ በሽታ/ጠባሳ፥ ..) መማር ለሚፈልግ ብዙ ዕውቀት ይሰጣል።

በውስን ገፆች ብዙ subject ያካተተ ድንቅ መጽሐፍ ነው የጻፍከው፡ ጥልቅ አንባቢ መሆንክን ተረድቻለሁ ("አንተ ከተረዳኸኝማ ምኑን አንባቢ ሆንኩት" እንዳትለኝ አደራ 😊)።

ወቅታዊ ሁኔታ ስጋት ጥሎብን ለመናገር ምንፈራቸውን አሁናዊ እውነታዎችና የወደ ፊት ስጋቶች poetic በኾነ መንገድ ከትበህ voice of the voiceless ስለሆንከን ከልብ አመሰግናለሁ። የጻፍክበት ዓላማ ከግብ እንዲደርስ እመኛለሁ።

በርታ!

አስተያየቱን ያጋራን Henisha Henishom ነው።

#የዙፋን_ልፊያ

መጽሐፉን ያላነበባችሁ አንብቡ፥ ያነበባችሁ ሃሳባቾሁን አጋሩ
4🔥1
ለልደቱ አያሌው

ከአክብሮት ጋር

#የዙፋን_ልፊያ 🤝
"ወንድ ልጅ ከሃያዎቹ በኋላ ያለው ህይወት ከአትሌቲኮ ማድሪድ ጋር መጫወትን ይመስላል?"

... አትሌቲኮ ግብ ካስቆጠረ በኋላ ከነሱጋ መጋጠም...


@Tfanos
አትሌቲኮ ተከላካይ ቡድን ነው። አንዴ ግብ ቀድሞ ካስቆጠረ በኋላ ፈፅሞ ይከላከላል። አትሌቲኮ ላይ ግብ ማስቆጠር ከባዱ ስራ ነው
👏3
የአንባቢ አስተያየት

ትዝታን ማን ፈጠረዉ?

የተሰበረ ልብ ያላቸዉ ሰዎች በጥሩም ይሁን በመጥፎ ጊዜ ፥ ትዝታቸውን ማን ፈጠረው?

መጥፎ ትዝታ በሰዉ ልጅ ላይ አሳርፎ ከሚያልፍ ነገር መካከል ዋነኛው ጦርነት ነው። ጦርነት ብዙ ሊባልለት የሚገባ ቢሆንም ዝምታን መርጠናል። ስለ ጉዳዮ በምሬት የያነሱትም ይፈረጃሉ። እንደ ፓለቲካኛ እና የአንድ ወገን ደጋፊ ተድርገው ይቆጠራሉ።

የጦርነት አጀንዳ በፅንፈኝነት ሰበብ ተደባብሶ ያልፋል። አንዳንዴ ደግሞ "ጦርነት ዛሬ ነዉ ወይ የተጀመረዉ? ምነዉ አዲስ ሆነባችሁ?" አይነት የስላቅ ጥያቄ ይነሳል።
እይታችን ምንም ሆነ ምን ጦርነት disaster ነዉ።

የዙፋን ልፊያ የጦርነትን ጅራፍ በmass ሳይሆን በነጠላ ያስቃኛል። እያንዳንዳችን ልብ ላይ ያረፈዉን ጅራፍ ያስታዉሰናል።

የዙፋን ልፊያን ሳነብ ጦርነቶ እንዴት ሰባሪ እንደሆነ ተረድቻለሁ። መጽሐፉን እያነበብኩት ከ 2 ገፅ ማለፍ ያቅተኝ ነበር። ብዙ ጊዜ ሰዉነቴ ሲቆጣ ፥ ሲከፋኝ ፥ ግፋ ሲልም ጉሮሮዬ ላይ ማላቀዉ ነገር ሲመረኝ እና ሳለቅስ እራሴን አግኝቼዋለሁ።

ለእኔ ለአንዲት ድሃ ሴት ጦርነት የሚያመጣዉን ዉድመት ተስፋአብ ብዙ ቃላት ሳያባክን ገልፆልኛል። የጦርነትን ግፍ፣ የግብዝነትን ጥግ ማወቅ እና መጠንቀቅ ከፈለጋችሁ የዙፋን ልፊያን አንብቡት

አስተያየቷን ያጋራችን አርሴማ ረታ ናት

የዙፋን ልፊያን ያላነበባቾሁ አንብቡ ፥ ያነበባችሁ ሃሳባችሁን አካፍሉ

@Tfanos
3
ለአሜሪካ አንባቢዎች ፥

"የዙፋን ልፊያ" ን ማንበብ የምትፈልጉ ፥ በአሜሪካ የምትኖሩ ሰዎች ጥቂት ኮፒ ተልኳል። መጽሐፉን የምትፈልጉ ፃፉልኝ

@Jtesfaab
1
2025/10/22 10:11:18
Back to Top
HTML Embed Code: