አትሌቲኮ ተከላካይ ቡድን ነው። አንዴ ግብ ቀድሞ ካስቆጠረ በኋላ ፈፅሞ ይከላከላል። አትሌቲኮ ላይ ግብ ማስቆጠር ከባዱ ስራ ነው
👏4
የአንባቢ አስተያየት
ትዝታን ማን ፈጠረዉ?
የተሰበረ ልብ ያላቸዉ ሰዎች በጥሩም ይሁን በመጥፎ ጊዜ ፥ ትዝታቸውን ማን ፈጠረው?
መጥፎ ትዝታ በሰዉ ልጅ ላይ አሳርፎ ከሚያልፍ ነገር መካከል ዋነኛው ጦርነት ነው። ጦርነት ብዙ ሊባልለት የሚገባ ቢሆንም ዝምታን መርጠናል። ስለ ጉዳዮ በምሬት የያነሱትም ይፈረጃሉ። እንደ ፓለቲካኛ እና የአንድ ወገን ደጋፊ ተድርገው ይቆጠራሉ።
የጦርነት አጀንዳ በፅንፈኝነት ሰበብ ተደባብሶ ያልፋል። አንዳንዴ ደግሞ "ጦርነት ዛሬ ነዉ ወይ የተጀመረዉ? ምነዉ አዲስ ሆነባችሁ?" አይነት የስላቅ ጥያቄ ይነሳል።
እይታችን ምንም ሆነ ምን ጦርነት disaster ነዉ።
የዙፋን ልፊያ የጦርነትን ጅራፍ በmass ሳይሆን በነጠላ ያስቃኛል። እያንዳንዳችን ልብ ላይ ያረፈዉን ጅራፍ ያስታዉሰናል።
የዙፋን ልፊያን ሳነብ ጦርነቶ እንዴት ሰባሪ እንደሆነ ተረድቻለሁ። መጽሐፉን እያነበብኩት ከ 2 ገፅ ማለፍ ያቅተኝ ነበር። ብዙ ጊዜ ሰዉነቴ ሲቆጣ ፥ ሲከፋኝ ፥ ግፋ ሲልም ጉሮሮዬ ላይ ማላቀዉ ነገር ሲመረኝ እና ሳለቅስ እራሴን አግኝቼዋለሁ።
ለእኔ ለአንዲት ድሃ ሴት ጦርነት የሚያመጣዉን ዉድመት ተስፋአብ ብዙ ቃላት ሳያባክን ገልፆልኛል። የጦርነትን ግፍ፣ የግብዝነትን ጥግ ማወቅ እና መጠንቀቅ ከፈለጋችሁ የዙፋን ልፊያን አንብቡት
አስተያየቷን ያጋራችን አርሴማ ረታ ናት
የዙፋን ልፊያን ያላነበባቾሁ አንብቡ ፥ ያነበባችሁ ሃሳባችሁን አካፍሉ
@Tfanos
ትዝታን ማን ፈጠረዉ?
የተሰበረ ልብ ያላቸዉ ሰዎች በጥሩም ይሁን በመጥፎ ጊዜ ፥ ትዝታቸውን ማን ፈጠረው?
መጥፎ ትዝታ በሰዉ ልጅ ላይ አሳርፎ ከሚያልፍ ነገር መካከል ዋነኛው ጦርነት ነው። ጦርነት ብዙ ሊባልለት የሚገባ ቢሆንም ዝምታን መርጠናል። ስለ ጉዳዮ በምሬት የያነሱትም ይፈረጃሉ። እንደ ፓለቲካኛ እና የአንድ ወገን ደጋፊ ተድርገው ይቆጠራሉ።
የጦርነት አጀንዳ በፅንፈኝነት ሰበብ ተደባብሶ ያልፋል። አንዳንዴ ደግሞ "ጦርነት ዛሬ ነዉ ወይ የተጀመረዉ? ምነዉ አዲስ ሆነባችሁ?" አይነት የስላቅ ጥያቄ ይነሳል።
እይታችን ምንም ሆነ ምን ጦርነት disaster ነዉ።
የዙፋን ልፊያ የጦርነትን ጅራፍ በmass ሳይሆን በነጠላ ያስቃኛል። እያንዳንዳችን ልብ ላይ ያረፈዉን ጅራፍ ያስታዉሰናል።
የዙፋን ልፊያን ሳነብ ጦርነቶ እንዴት ሰባሪ እንደሆነ ተረድቻለሁ። መጽሐፉን እያነበብኩት ከ 2 ገፅ ማለፍ ያቅተኝ ነበር። ብዙ ጊዜ ሰዉነቴ ሲቆጣ ፥ ሲከፋኝ ፥ ግፋ ሲልም ጉሮሮዬ ላይ ማላቀዉ ነገር ሲመረኝ እና ሳለቅስ እራሴን አግኝቼዋለሁ።
ለእኔ ለአንዲት ድሃ ሴት ጦርነት የሚያመጣዉን ዉድመት ተስፋአብ ብዙ ቃላት ሳያባክን ገልፆልኛል። የጦርነትን ግፍ፣ የግብዝነትን ጥግ ማወቅ እና መጠንቀቅ ከፈለጋችሁ የዙፋን ልፊያን አንብቡት
አስተያየቷን ያጋራችን አርሴማ ረታ ናት
የዙፋን ልፊያን ያላነበባቾሁ አንብቡ ፥ ያነበባችሁ ሃሳባችሁን አካፍሉ
@Tfanos
❤3
❤2
አሜሪካ ያላችሁ
እስኪ እንያችሁ
የዙፋን ልፊያ ውቂያኖስ አቋርጣ ፥ አሜሪካ ደርሳለች።
መጽሐፍ ወደ አሜሪካ መላክ እጅግ አስቸጋሪ ነው። ፖስታ ቤት ውድ ገንዘብ ያስከፍላል። ከጥቂት ኮፒ በላይ መላክ ክልክል ነው። በእርግጥ እዚህ ሐገር የመጽሐፍ ስራ አደንዛዥ እፅ ማዘዋወርን ይመስል ተግዳሮት ይበዛበታል።
ቢሆንም ጥቂት ኮፒ ለአሜሪካ አንባቢ ተልኳል።
በአሜሪካ ያላችሁ ፥ የዙፋን ልፊያን ማንበብ የምትፈልጉ ልታናግሩኝ ትችላላችሁ።
የተላከው ሳያልቅ የራሳችሁን ኮፒ አስቀሩ።
መጽሐፉን የምትፈልጉ @Jtesfaab ላይ ፃፉልኝ
እስኪ እንያችሁ
የዙፋን ልፊያ ውቂያኖስ አቋርጣ ፥ አሜሪካ ደርሳለች።
መጽሐፍ ወደ አሜሪካ መላክ እጅግ አስቸጋሪ ነው። ፖስታ ቤት ውድ ገንዘብ ያስከፍላል። ከጥቂት ኮፒ በላይ መላክ ክልክል ነው። በእርግጥ እዚህ ሐገር የመጽሐፍ ስራ አደንዛዥ እፅ ማዘዋወርን ይመስል ተግዳሮት ይበዛበታል።
ቢሆንም ጥቂት ኮፒ ለአሜሪካ አንባቢ ተልኳል።
በአሜሪካ ያላችሁ ፥ የዙፋን ልፊያን ማንበብ የምትፈልጉ ልታናግሩኝ ትችላላችሁ።
የተላከው ሳያልቅ የራሳችሁን ኮፒ አስቀሩ።
መጽሐፉን የምትፈልጉ @Jtesfaab ላይ ፃፉልኝ
"ኢትዮጵያ ሞ ት የሚታጨድባት ማሳ ሆናለች"
ከምንይሉ ፖድካስትጋ ያደረግነውን ቆይታ ተከታተሉ። መጽሐፌን መሰረት አድርገን የተለያዩ ጉዳዮች ላይ አውግተናል
👇
https://youtu.be/5kkyV_iMWV8?si=XnHTVj2mN4dJ6QJv
ከምንይሉ ፖድካስትጋ ያደረግነውን ቆይታ ተከታተሉ። መጽሐፌን መሰረት አድርገን የተለያዩ ጉዳዮች ላይ አውግተናል
👇
https://youtu.be/5kkyV_iMWV8?si=XnHTVj2mN4dJ6QJv
YouTube
ኢትዮጵያ ሞት የሚታጨድባት ማሳ ሆናለች | የልደቱ አያሌው አድናቂ ነኝ፡-ደራሲ ተስፋኣብ ተሸመ- #ገፅ ፲፪ #MinyiluPodcast
ክራራዊ ሕይወትና የነገን ፍለጋ የሚሉ መፅሃፎችን ለአንባቢያ ያደረሰው ጋዜጠኛ እና ደራሲ ተስፋኣብ ተሾመ በቅርቡ የዙፋን ልፊያ የሚል ፖለቲካዊ ልቦለድ አሳትማል፡፡
ለአናሳ ቁጥር ማህበረሰቦች ግድ ይሠጠኛል የሚለው ደራሲው በዙፋን ልፊያ የልቦለድ መፅሐፉ በርካታ የማህበረሰብ ችግሮችን፤ የምሁራንን ዝምታ፤ የመሪዎችን አምባገነንነት፤ የጦርነትን አስከፊነት በምዕናብ አስቃኝቷል፡፡
#Minyilupodcas…
ለአናሳ ቁጥር ማህበረሰቦች ግድ ይሠጠኛል የሚለው ደራሲው በዙፋን ልፊያ የልቦለድ መፅሐፉ በርካታ የማህበረሰብ ችግሮችን፤ የምሁራንን ዝምታ፤ የመሪዎችን አምባገነንነት፤ የጦርነትን አስከፊነት በምዕናብ አስቃኝቷል፡፡
#Minyilupodcas…
ዘሪቱ ከብዙ ወንድጋ ተኝቻለሁ ብላለች?
ብዙ ሰው የዘሪቱን መጽሐፍ ያነበበ አይመስለኝም። ያነበበ ሰው መጽሐፉ ላይ በሌለ ሃሳብ አይዘምትባትም።
መጽሐፉን አንብቤዋለሁ።ዘሪቱ "ከብዙ ሰውጋ ተኝቻለሁ" አላለችም። አዎ አላለችም።
ዘሪቱ በ ዝ ሙ ት ሀጢያት ወድቃ እንደምታውቅ በግልፅ ፅፋለች። ሃጢያቷን የገለፀችው ስለ እግዚአብሔር ፀጋ ለማስረዳት ነው። "በሰው ፊት እንዳፃዲቅ በምቆጠርበት ፥ እኔም ራሴን እንደ ፃዲቅ በምቆጥርበት ወቅት ወደቅኹ" አለች።
ሰዎች በመውደቅ ጭምር ከራሳቸው እንደ አዲስ ይተዋወቃሉ። ከራስ መተዋወቅ ደካማ እና ሃጢያተኛ መሆንን መገንዘብ ነው። ሃጢያተኝነቱን የተረዳ የእግዚአብሔርን ምሕረት እና ፀጋ ይረዳል። ዘሪቱ መጽሐፍ ላይ ያለውም ይሄው ነው።
ይልቅ ዘሪቱ ስለ ውድቀቷ የፃፈችው ላይ መጠነኛ ቅሬታ አለኝ። ውድቀቷ የእግዚአብሔርን ፀጋ እንድታውቅ እንደረዳት ግልፅ ቢሆንም ጉዳዩ በተሻለ ጥልቀት መብራራት ነበረበት።
የህይወት ታሪክን ከማንበብ ጥቅሞች መካከል አንዱ ከሌላው የህይወት ጉዞ መማር ነው።
ደካሞች ነን። ከኛጋ ድካም የሚጋራን ሰው የህይወት መንገድ ማወቅ ይረዳናል። ዘሪቱ ስለ ውድቀቷ ስትፅፍ በተሻለ ጥልቀት ብትፅፍ ጥሩ ነበር።
ለውድቀቷ የዳረጓትን ገፊ ምክኒያቶች ፥ አስቻይ ሁኔታዎች ፥ ስነልቦናን ወዘተ ብትነግረን ሌሎቻችን ለምን እንደምንወድቅ እንድንገነዘብ ይረዳን ይሆናል።
ከችግሩ ነፃ ስትወጣም እንዴት ባለ መንገድ ነፃ እንደወጣች በተሻለ ጥልቀት ብታስረዳን ጥሩ ነበር።
ዘሪቱ በ ዝ ሙ ት የወደቀችባቸውን አጋጣሚዎች በግልፅ ፅፋለች። ነገር ግን ከብዙ ወንድ ጋ ተኝቻለሁ አላለችም። ይልቅ "ይሄ /መወደቋ/ የሁልጊዜ ተግባሬ ሳይሆን አልፎ አልፎ የሚፈትነኝ ድካሜ ነው" ብላለች።
Via ተስፋኣብ ተሾመ
@Tfanos
ብዙ ሰው የዘሪቱን መጽሐፍ ያነበበ አይመስለኝም። ያነበበ ሰው መጽሐፉ ላይ በሌለ ሃሳብ አይዘምትባትም።
መጽሐፉን አንብቤዋለሁ።ዘሪቱ "ከብዙ ሰውጋ ተኝቻለሁ" አላለችም። አዎ አላለችም።
ዘሪቱ በ ዝ ሙ ት ሀጢያት ወድቃ እንደምታውቅ በግልፅ ፅፋለች። ሃጢያቷን የገለፀችው ስለ እግዚአብሔር ፀጋ ለማስረዳት ነው። "በሰው ፊት እንዳፃዲቅ በምቆጠርበት ፥ እኔም ራሴን እንደ ፃዲቅ በምቆጥርበት ወቅት ወደቅኹ" አለች።
ሰዎች በመውደቅ ጭምር ከራሳቸው እንደ አዲስ ይተዋወቃሉ። ከራስ መተዋወቅ ደካማ እና ሃጢያተኛ መሆንን መገንዘብ ነው። ሃጢያተኝነቱን የተረዳ የእግዚአብሔርን ምሕረት እና ፀጋ ይረዳል። ዘሪቱ መጽሐፍ ላይ ያለውም ይሄው ነው።
ይልቅ ዘሪቱ ስለ ውድቀቷ የፃፈችው ላይ መጠነኛ ቅሬታ አለኝ። ውድቀቷ የእግዚአብሔርን ፀጋ እንድታውቅ እንደረዳት ግልፅ ቢሆንም ጉዳዩ በተሻለ ጥልቀት መብራራት ነበረበት።
የህይወት ታሪክን ከማንበብ ጥቅሞች መካከል አንዱ ከሌላው የህይወት ጉዞ መማር ነው።
ደካሞች ነን። ከኛጋ ድካም የሚጋራን ሰው የህይወት መንገድ ማወቅ ይረዳናል። ዘሪቱ ስለ ውድቀቷ ስትፅፍ በተሻለ ጥልቀት ብትፅፍ ጥሩ ነበር።
ለውድቀቷ የዳረጓትን ገፊ ምክኒያቶች ፥ አስቻይ ሁኔታዎች ፥ ስነልቦናን ወዘተ ብትነግረን ሌሎቻችን ለምን እንደምንወድቅ እንድንገነዘብ ይረዳን ይሆናል።
ከችግሩ ነፃ ስትወጣም እንዴት ባለ መንገድ ነፃ እንደወጣች በተሻለ ጥልቀት ብታስረዳን ጥሩ ነበር።
ዘሪቱ በ ዝ ሙ ት የወደቀችባቸውን አጋጣሚዎች በግልፅ ፅፋለች። ነገር ግን ከብዙ ወንድ ጋ ተኝቻለሁ አላለችም። ይልቅ "ይሄ /መወደቋ/ የሁልጊዜ ተግባሬ ሳይሆን አልፎ አልፎ የሚፈትነኝ ድካሜ ነው" ብላለች።
Via ተስፋኣብ ተሾመ
@Tfanos
❤4👍4
ፕሮቴስታንት ላይ የሚወረወር እያንዳንዱ የጥላቻ ቀስት እኔንም ይ ወ ጋ ኛ ል። ለፕሮቴስታንት የታቀደ ጥ ላ ቻ ወለድ ጦ ር ሳይወጋኝ አያልፍም። ለወገኖቼ የተወረወረ ድን ጋ ይ እኔን ማግኘቱ አይቀርም።
ወገኖቼን አትንኩ!
ቸርች መሄድ ካቆምኩ አመታት ተቆጥረዋል። በማውቀውና በማላውቀው ምክኒያት ህብረት ማድረግ አቁሜያለሁ። ከፀልይኩ ብዙ አመቴ ነው። አንዳንዴ የተማርኩትን ሀይማኖታዊ ትምህርት እጠረጥራለሁ። የእምነቴ መስመር ከወገኖቼ እምነት መስመር ከተለየ ቆየ። አንዳንዴ ከሀይማኖት ወገኖቼ የተበጠስኩ ያህል ይሰማኛል። ቢሆኑም ወገኖቼ ናቸው። ሲነኩ ያመኛል። በነገር ቀስት ሲ ወ ጉ ልቤ ይደማል። የሚወረወርባቸው ድ ን ጋ ይ እኔም ይሰብረኛል።
ወገኖቼን አትንኩ!
እኔ ዘንድ በጎ ፍሬ ካለ ዘሩን የዘራችው ያደግኩባት ቃለ ህይወት ቤተ ክርስቲያን ናት። ምናልባት አንዳች ጥሩ ነገር ካለኝ ያንን ጥሩ ነገር ያገኘሁት ከቸርች መጋቢዎቼ ነው። የፓስተር አበበ ፈረንጅ የደህንነት ትምህርት ፥ የፓስተር ሀብቴ አሰፋ የደቀ-መዝሙርነትና የአገልግሎት ትምህርት ፥ የመምህሬ ሙልዬ የልጅነት ትምህርት ፥ የወንጌላዊ በላይ ቦርኩ ምክሮች ናቸው የሰሩኝ። እኔን የሰራኝ የፕሮቴስታንት ትምህርት ነው።
ወገኖቼን አትንኩ!
ከትምህርት ጋር የተዋወቅኩት በቃለ-ህይወት በኩል ነው። ፊደል ያስቆጠሩኝ ፥ የሂሳብ ስሌቶችን ያስተማሩኝ ፥ ማንበብ ያለማመዱኝ የቸርች መምህራን ናቸው።
ወንጌላዊ ስምኦን ፥ መምህር አለማየሁ ፥ ወንጌላዊ ተሻገር... ወዘተ እንዴት ረሳቸዋለሁ?
ወገኖቼን አትንኩ!
ትዝታዬን ከፕሮቴስታንት መነጠል አልችልም። ያለ ፕሮቴስታንት ወገኖቼ ምንም ነኝ። ሰው ያደረጉኝ እነሱ ናቸው። ፍቅር አስተምረውኛል።
ልጅ ሆኜ የተረት መጻሕፍት አላነበብኩም። ይልቅ ለሕፃናት የተዘጋጀ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክን አነብ ነበር። ከፍ ስል ወንጌላዊ ተስፋዬ "የሰው ልብ" የሚል መጽሐፍ አስነበበኝ። ያኔ እድሜዬ 11 ነበር። ቀጥሎ ደግሞ ወንጌላዊ ወርቅነህ መንፈሳዊ መጽሔቶችን አስተዋወቀኝ።
ሴኩላር መጻሕፍት ያገኘሁት ዘግይቼ ነው። ከዛ በፊት አነባቸው የነበሩት መጻሕፍት የነበረው የነዶክተር መለሰ ወጉን መጻፍት ነበር። በእርግጥ አይገባኝም ነበር።
ወገኖቼን አትንኩ
ፕሮቴስታንት ማለት ትዝታዬ ነው። ማንም ትዝታዬ ላይ ሲዘባበት ደስ አይለኝም። ፕሮቴስታንት ከእውቀት ጋር መተዋወቂያ በር ሆኖኛል። ፕሮቴስታንት ስነልቦናዬን ቀርፆኛል። ፕሮቴስታንት ብዙ ነገሬ ነው።
ኪነ-ጥበብን የተዋወቅኩት በቸርች በኩል ነው። ድራማ መፃፍ ፥ መግጠም ፥ ልብወለድ መድረስን የተማርኩት በቸርች በኩል ነው።
ልጆች ሆነን ድ ን ጋ ይ ይወረወርብን ነበር። እንሰደብ ነበር። ዛሬም እንደትላንቱ ማድረግ የሚፈልጉ እንዳሉ አውቃለሁ። እነሱን "እንከባበር" ማለት ያስፈልጋል።
ወገኖቼን አትንኩ!
ግማሽ አካሌ ፥ ትዝታዬ ፥ ቤተሰቦቼ ፥ ገጠመኞቼ ሁሉ ከፕሮቴስታንት ጋር የተሳሰረ ነው። ስለዚህ ወገኖቼ ላይ የሚሰነዘር ጥ ላ ቻ ወለድ ቀስት ልቤን ያደማዋል።
ወገኖቼን አትንኩ! እነሱን ስትነኩ "እኔም ከእነሱ እንደ አንዱ ነኝ" ብዬ እመጣለሁ
@Tfanos
ወገኖቼን አትንኩ!
ቸርች መሄድ ካቆምኩ አመታት ተቆጥረዋል። በማውቀውና በማላውቀው ምክኒያት ህብረት ማድረግ አቁሜያለሁ። ከፀልይኩ ብዙ አመቴ ነው። አንዳንዴ የተማርኩትን ሀይማኖታዊ ትምህርት እጠረጥራለሁ። የእምነቴ መስመር ከወገኖቼ እምነት መስመር ከተለየ ቆየ። አንዳንዴ ከሀይማኖት ወገኖቼ የተበጠስኩ ያህል ይሰማኛል። ቢሆኑም ወገኖቼ ናቸው። ሲነኩ ያመኛል። በነገር ቀስት ሲ ወ ጉ ልቤ ይደማል። የሚወረወርባቸው ድ ን ጋ ይ እኔም ይሰብረኛል።
ወገኖቼን አትንኩ!
እኔ ዘንድ በጎ ፍሬ ካለ ዘሩን የዘራችው ያደግኩባት ቃለ ህይወት ቤተ ክርስቲያን ናት። ምናልባት አንዳች ጥሩ ነገር ካለኝ ያንን ጥሩ ነገር ያገኘሁት ከቸርች መጋቢዎቼ ነው። የፓስተር አበበ ፈረንጅ የደህንነት ትምህርት ፥ የፓስተር ሀብቴ አሰፋ የደቀ-መዝሙርነትና የአገልግሎት ትምህርት ፥ የመምህሬ ሙልዬ የልጅነት ትምህርት ፥ የወንጌላዊ በላይ ቦርኩ ምክሮች ናቸው የሰሩኝ። እኔን የሰራኝ የፕሮቴስታንት ትምህርት ነው።
ወገኖቼን አትንኩ!
ከትምህርት ጋር የተዋወቅኩት በቃለ-ህይወት በኩል ነው። ፊደል ያስቆጠሩኝ ፥ የሂሳብ ስሌቶችን ያስተማሩኝ ፥ ማንበብ ያለማመዱኝ የቸርች መምህራን ናቸው።
ወንጌላዊ ስምኦን ፥ መምህር አለማየሁ ፥ ወንጌላዊ ተሻገር... ወዘተ እንዴት ረሳቸዋለሁ?
ወገኖቼን አትንኩ!
ትዝታዬን ከፕሮቴስታንት መነጠል አልችልም። ያለ ፕሮቴስታንት ወገኖቼ ምንም ነኝ። ሰው ያደረጉኝ እነሱ ናቸው። ፍቅር አስተምረውኛል።
ልጅ ሆኜ የተረት መጻሕፍት አላነበብኩም። ይልቅ ለሕፃናት የተዘጋጀ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክን አነብ ነበር። ከፍ ስል ወንጌላዊ ተስፋዬ "የሰው ልብ" የሚል መጽሐፍ አስነበበኝ። ያኔ እድሜዬ 11 ነበር። ቀጥሎ ደግሞ ወንጌላዊ ወርቅነህ መንፈሳዊ መጽሔቶችን አስተዋወቀኝ።
ሴኩላር መጻሕፍት ያገኘሁት ዘግይቼ ነው። ከዛ በፊት አነባቸው የነበሩት መጻሕፍት የነበረው የነዶክተር መለሰ ወጉን መጻፍት ነበር። በእርግጥ አይገባኝም ነበር።
ወገኖቼን አትንኩ
ፕሮቴስታንት ማለት ትዝታዬ ነው። ማንም ትዝታዬ ላይ ሲዘባበት ደስ አይለኝም። ፕሮቴስታንት ከእውቀት ጋር መተዋወቂያ በር ሆኖኛል። ፕሮቴስታንት ስነልቦናዬን ቀርፆኛል። ፕሮቴስታንት ብዙ ነገሬ ነው።
ኪነ-ጥበብን የተዋወቅኩት በቸርች በኩል ነው። ድራማ መፃፍ ፥ መግጠም ፥ ልብወለድ መድረስን የተማርኩት በቸርች በኩል ነው።
ልጆች ሆነን ድ ን ጋ ይ ይወረወርብን ነበር። እንሰደብ ነበር። ዛሬም እንደትላንቱ ማድረግ የሚፈልጉ እንዳሉ አውቃለሁ። እነሱን "እንከባበር" ማለት ያስፈልጋል።
ወገኖቼን አትንኩ!
ግማሽ አካሌ ፥ ትዝታዬ ፥ ቤተሰቦቼ ፥ ገጠመኞቼ ሁሉ ከፕሮቴስታንት ጋር የተሳሰረ ነው። ስለዚህ ወገኖቼ ላይ የሚሰነዘር ጥ ላ ቻ ወለድ ቀስት ልቤን ያደማዋል።
ወገኖቼን አትንኩ! እነሱን ስትነኩ "እኔም ከእነሱ እንደ አንዱ ነኝ" ብዬ እመጣለሁ
@Tfanos
❤13👍2👎2
ያየሰው ሽመልስ ፥ ስለ ዙፋን ልፊያ መጽሐፍ!
የዙፋን ልፊያን አነበብኩ
መፅሀፍ ቅዱሳዊው አፃፃፍ ድንቅ ነው። በመጀመሪያዎቹ ገፆች ላይ የጀመርከው አፃፃፍ መፅሀፈ መክብብን የማነብ እስኪመስለኝ ሰቅዞኝ ነበር።
(እስከመጨረሻው ብታዘልቀው ያ አፃፃፍ መፅሐፍ ቅዱስ ሊትሬቸሩ ሃያል እንደሆነ የምትመሰክር ተጨማሪ ሰው ያደርግህ ነበር። የበዓሉ ግርማ ፀጋዬ ሃይለማርያም ''መፅሐፍ ቅዱስን የምወደው በሊትሬቸሩ ነው" ይላት ነበር ለሮማን። አለማየሁ ገላጋይ አንዱን መፅሀፍ ሙሉውን የፃፈው እንደ መሀልየ መሀልየ ዘሰለሞን ነው።( የተጠላው እንዳልተጠለን መሰለኝ)። የዙፋን ልፊያ በዚያ ቅርፅ መቅረብ ጀምራ ከጥቂት ገፆች በኋላ እየረሳችው ትሄዳለች)
በውነቱ ቅርፁ ድንቅ ነው። የታሪክ አቀራረቡና አመራረጡ አስገራሚ ነው። የመረጣቸው ሰዎችና እንስሳት ይደንቃሉ። (በመጽሐፉ የተጠቀሰውን ው ሻ ው ን "መቻል" የመሰለ አስር ታማኝ ሰው ብናገኝ አገራችን ኮሽ የሚል ነገር የሚሰማባት አይመስለኝም። ችግሩ ጡቱ ነው። የሕይወት ጡ ት። ያጋድለናል)!
መብራት የምትባል በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ የምትኖር ከተማ፣ "አልፈርስም" የሚል ተረት አላትና አልፈርስም ስትል ኖራ ትንኮታኮት ዘንድ ድ ን ቁር ና ሚናው ትልቅ ሆኗል። ሰላም ጠልነት፣ነግበኔ አለማለት አገርን ያፈርሳል። የሚተዋወቁ ሹሞች፣ የማይተዋወቀውን ሰው ፀባቸውን የማያውቀውን ወገን አጫረሱት። አንዱ ሕዝብ ወደ ሌላው ሕዝቡ እንዳይሄድ አደረጉት። የሴቶችን ገላ ጦርሜዳ አደረጉት! ያላደረጉት የለም!
poor them!
"እንዲህ ያለ ነገር በኢትዮጵያ ውስጥ ለመፃፍ ማሰብህ አስገርሞኛል" ማለት አለብኝ። ስለ ሰላም አስፈላጊነት ፣ ስለ ጦርነት ጎጂነት መፃፍና መናገር ሲያሰቅልና ሲያስወነጅል ያየን ትውልዶች ነን። ሰላም ይሻላል ብሎ መናገር ሰዎችን ለስደትና ለሞት የዳረገ ፖሊሲ መሆኑን ያየን ምስክሮች ነን።
ጀነራልና ፕሬዚዳንት ተጣሉ ተብሎ የሚጎዳውን የሚጨፈለቀውን የሳር ዓይነትና ብዛት በየገፁ ላይ መተረክ? ተቻለ እንዴ?
የመብራት ከተማ ሰዎች መብራታቸውን ሲያወድሙ፣ አገራቸውን ሲያፈርሱ ጠቆም ማድረግ ተቻለ እንዴ?
አንተ ግን ቻልክበት
መፍትሄው ግን ይሄው ነው። ሰው የሚሞትበትን ፣ አገር የሚወድምበትን ጦርነት "war is always unjust" እያልን መፃፍ፥ መናገር፤ ለዚህም ሲባል የሚመጣውን ቀራኒዮ መቀበል! ቢያንስ ትራስህ በወቀሳ ሲነዘንዝህ አታድርም! እንደ መ ን ጋ ው፣እንደ ጀኔራሉ፣ እንደ ፕሬዚዳንቱ አለመሆን... በእጄ ደ ም አለ ብሎ አለመሳቀቅ...ሰው ለሚሞትበት ነገር አንድ ግራም ጉልበት አለማዋጣት...የሕይወት ስንቅና መርህ መሆን አለበት!
በተቀረ
ጦርነት ነጋዴዎች አሉት፤ ሀብት የሚዝቁ አንድ ሰው በሞተ ቁጥር አስር ሺህ ዶላር የሚዝቁ፣ አንድ ጥይት በተተኮሰ ፍጥነት ሀብታቸው የሚተኮስ...! የዙፋን ልፊያ ላይ ተረስተዋል።
እንደገና በተቀረ...
ስለ እስር፣ ስለ መታሰር፣ በዘር መርጦ በመልክ አይቶ ስለማጎር የመብራት ከተማ ሰዎች አይመለከታቸውም?
ብርትት በልልኝ! ደጋግመህ ይሄን ጉዳይ ብትፅፈው የግራ እጅ ጣት የማይሞላ አሀዝ ካላቸው የትውልዳችን የሰላም ሰባኪያን ውስጥ መሆንህ ነው።
ስለተሰጠኝ privilege አመስጋኝ ነኝ።
በዘመናችን ውድ ምርቃት ልሰናበትህ!
ውለህ ግባ!
@Tfanos
የዙፋን ልፊያን አነበብኩ
መፅሀፍ ቅዱሳዊው አፃፃፍ ድንቅ ነው። በመጀመሪያዎቹ ገፆች ላይ የጀመርከው አፃፃፍ መፅሀፈ መክብብን የማነብ እስኪመስለኝ ሰቅዞኝ ነበር።
(እስከመጨረሻው ብታዘልቀው ያ አፃፃፍ መፅሐፍ ቅዱስ ሊትሬቸሩ ሃያል እንደሆነ የምትመሰክር ተጨማሪ ሰው ያደርግህ ነበር። የበዓሉ ግርማ ፀጋዬ ሃይለማርያም ''መፅሐፍ ቅዱስን የምወደው በሊትሬቸሩ ነው" ይላት ነበር ለሮማን። አለማየሁ ገላጋይ አንዱን መፅሀፍ ሙሉውን የፃፈው እንደ መሀልየ መሀልየ ዘሰለሞን ነው።( የተጠላው እንዳልተጠለን መሰለኝ)። የዙፋን ልፊያ በዚያ ቅርፅ መቅረብ ጀምራ ከጥቂት ገፆች በኋላ እየረሳችው ትሄዳለች)
በውነቱ ቅርፁ ድንቅ ነው። የታሪክ አቀራረቡና አመራረጡ አስገራሚ ነው። የመረጣቸው ሰዎችና እንስሳት ይደንቃሉ። (በመጽሐፉ የተጠቀሰውን ው ሻ ው ን "መቻል" የመሰለ አስር ታማኝ ሰው ብናገኝ አገራችን ኮሽ የሚል ነገር የሚሰማባት አይመስለኝም። ችግሩ ጡቱ ነው። የሕይወት ጡ ት። ያጋድለናል)!
መብራት የምትባል በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ የምትኖር ከተማ፣ "አልፈርስም" የሚል ተረት አላትና አልፈርስም ስትል ኖራ ትንኮታኮት ዘንድ ድ ን ቁር ና ሚናው ትልቅ ሆኗል። ሰላም ጠልነት፣ነግበኔ አለማለት አገርን ያፈርሳል። የሚተዋወቁ ሹሞች፣ የማይተዋወቀውን ሰው ፀባቸውን የማያውቀውን ወገን አጫረሱት። አንዱ ሕዝብ ወደ ሌላው ሕዝቡ እንዳይሄድ አደረጉት። የሴቶችን ገላ ጦርሜዳ አደረጉት! ያላደረጉት የለም!
poor them!
"እንዲህ ያለ ነገር በኢትዮጵያ ውስጥ ለመፃፍ ማሰብህ አስገርሞኛል" ማለት አለብኝ። ስለ ሰላም አስፈላጊነት ፣ ስለ ጦርነት ጎጂነት መፃፍና መናገር ሲያሰቅልና ሲያስወነጅል ያየን ትውልዶች ነን። ሰላም ይሻላል ብሎ መናገር ሰዎችን ለስደትና ለሞት የዳረገ ፖሊሲ መሆኑን ያየን ምስክሮች ነን።
ጀነራልና ፕሬዚዳንት ተጣሉ ተብሎ የሚጎዳውን የሚጨፈለቀውን የሳር ዓይነትና ብዛት በየገፁ ላይ መተረክ? ተቻለ እንዴ?
የመብራት ከተማ ሰዎች መብራታቸውን ሲያወድሙ፣ አገራቸውን ሲያፈርሱ ጠቆም ማድረግ ተቻለ እንዴ?
አንተ ግን ቻልክበት
መፍትሄው ግን ይሄው ነው። ሰው የሚሞትበትን ፣ አገር የሚወድምበትን ጦርነት "war is always unjust" እያልን መፃፍ፥ መናገር፤ ለዚህም ሲባል የሚመጣውን ቀራኒዮ መቀበል! ቢያንስ ትራስህ በወቀሳ ሲነዘንዝህ አታድርም! እንደ መ ን ጋ ው፣እንደ ጀኔራሉ፣ እንደ ፕሬዚዳንቱ አለመሆን... በእጄ ደ ም አለ ብሎ አለመሳቀቅ...ሰው ለሚሞትበት ነገር አንድ ግራም ጉልበት አለማዋጣት...የሕይወት ስንቅና መርህ መሆን አለበት!
በተቀረ
ጦርነት ነጋዴዎች አሉት፤ ሀብት የሚዝቁ አንድ ሰው በሞተ ቁጥር አስር ሺህ ዶላር የሚዝቁ፣ አንድ ጥይት በተተኮሰ ፍጥነት ሀብታቸው የሚተኮስ...! የዙፋን ልፊያ ላይ ተረስተዋል።
እንደገና በተቀረ...
ስለ እስር፣ ስለ መታሰር፣ በዘር መርጦ በመልክ አይቶ ስለማጎር የመብራት ከተማ ሰዎች አይመለከታቸውም?
ብርትት በልልኝ! ደጋግመህ ይሄን ጉዳይ ብትፅፈው የግራ እጅ ጣት የማይሞላ አሀዝ ካላቸው የትውልዳችን የሰላም ሰባኪያን ውስጥ መሆንህ ነው።
ስለተሰጠኝ privilege አመስጋኝ ነኝ።
በዘመናችን ውድ ምርቃት ልሰናበትህ!
ውለህ ግባ!
@Tfanos
👏4👍2❤1
