አሜሪካ ያላችሁ
እስኪ እንያችሁ
የዙፋን ልፊያ ውቂያኖስ አቋርጣ ፥ አሜሪካ ደርሳለች።
መጽሐፍ ወደ አሜሪካ መላክ እጅግ አስቸጋሪ ነው። ፖስታ ቤት ውድ ገንዘብ ያስከፍላል። ከጥቂት ኮፒ በላይ መላክ ክልክል ነው። በእርግጥ እዚህ ሐገር የመጽሐፍ ስራ አደንዛዥ እፅ ማዘዋወርን ይመስል ተግዳሮት ይበዛበታል።
ቢሆንም ጥቂት ኮፒ ለአሜሪካ አንባቢ ተልኳል።
በአሜሪካ ያላችሁ ፥ የዙፋን ልፊያን ማንበብ የምትፈልጉ ልታናግሩኝ ትችላላችሁ።
የተላከው ሳያልቅ የራሳችሁን ኮፒ አስቀሩ።
መጽሐፉን የምትፈልጉ @Jtesfaab ላይ ፃፉልኝ
እስኪ እንያችሁ
የዙፋን ልፊያ ውቂያኖስ አቋርጣ ፥ አሜሪካ ደርሳለች።
መጽሐፍ ወደ አሜሪካ መላክ እጅግ አስቸጋሪ ነው። ፖስታ ቤት ውድ ገንዘብ ያስከፍላል። ከጥቂት ኮፒ በላይ መላክ ክልክል ነው። በእርግጥ እዚህ ሐገር የመጽሐፍ ስራ አደንዛዥ እፅ ማዘዋወርን ይመስል ተግዳሮት ይበዛበታል።
ቢሆንም ጥቂት ኮፒ ለአሜሪካ አንባቢ ተልኳል።
በአሜሪካ ያላችሁ ፥ የዙፋን ልፊያን ማንበብ የምትፈልጉ ልታናግሩኝ ትችላላችሁ።
የተላከው ሳያልቅ የራሳችሁን ኮፒ አስቀሩ።
መጽሐፉን የምትፈልጉ @Jtesfaab ላይ ፃፉልኝ
"ኢትዮጵያ ሞ ት የሚታጨድባት ማሳ ሆናለች"
ከምንይሉ ፖድካስትጋ ያደረግነውን ቆይታ ተከታተሉ። መጽሐፌን መሰረት አድርገን የተለያዩ ጉዳዮች ላይ አውግተናል
👇
https://youtu.be/5kkyV_iMWV8?si=XnHTVj2mN4dJ6QJv
ከምንይሉ ፖድካስትጋ ያደረግነውን ቆይታ ተከታተሉ። መጽሐፌን መሰረት አድርገን የተለያዩ ጉዳዮች ላይ አውግተናል
👇
https://youtu.be/5kkyV_iMWV8?si=XnHTVj2mN4dJ6QJv
YouTube
ኢትዮጵያ ሞት የሚታጨድባት ማሳ ሆናለች | የልደቱ አያሌው አድናቂ ነኝ፡-ደራሲ ተስፋኣብ ተሸመ- #ገፅ ፲፪ #MinyiluPodcast
ክራራዊ ሕይወትና የነገን ፍለጋ የሚሉ መፅሃፎችን ለአንባቢያ ያደረሰው ጋዜጠኛ እና ደራሲ ተስፋኣብ ተሾመ በቅርቡ የዙፋን ልፊያ የሚል ፖለቲካዊ ልቦለድ አሳትማል፡፡
ለአናሳ ቁጥር ማህበረሰቦች ግድ ይሠጠኛል የሚለው ደራሲው በዙፋን ልፊያ የልቦለድ መፅሐፉ በርካታ የማህበረሰብ ችግሮችን፤ የምሁራንን ዝምታ፤ የመሪዎችን አምባገነንነት፤ የጦርነትን አስከፊነት በምዕናብ አስቃኝቷል፡፡
#Minyilupodcas…
ለአናሳ ቁጥር ማህበረሰቦች ግድ ይሠጠኛል የሚለው ደራሲው በዙፋን ልፊያ የልቦለድ መፅሐፉ በርካታ የማህበረሰብ ችግሮችን፤ የምሁራንን ዝምታ፤ የመሪዎችን አምባገነንነት፤ የጦርነትን አስከፊነት በምዕናብ አስቃኝቷል፡፡
#Minyilupodcas…
ዘሪቱ ከብዙ ወንድጋ ተኝቻለሁ ብላለች?
ብዙ ሰው የዘሪቱን መጽሐፍ ያነበበ አይመስለኝም። ያነበበ ሰው መጽሐፉ ላይ በሌለ ሃሳብ አይዘምትባትም።
መጽሐፉን አንብቤዋለሁ።ዘሪቱ "ከብዙ ሰውጋ ተኝቻለሁ" አላለችም። አዎ አላለችም።
ዘሪቱ በ ዝ ሙ ት ሀጢያት ወድቃ እንደምታውቅ በግልፅ ፅፋለች። ሃጢያቷን የገለፀችው ስለ እግዚአብሔር ፀጋ ለማስረዳት ነው። "በሰው ፊት እንዳፃዲቅ በምቆጠርበት ፥ እኔም ራሴን እንደ ፃዲቅ በምቆጥርበት ወቅት ወደቅኹ" አለች።
ሰዎች በመውደቅ ጭምር ከራሳቸው እንደ አዲስ ይተዋወቃሉ። ከራስ መተዋወቅ ደካማ እና ሃጢያተኛ መሆንን መገንዘብ ነው። ሃጢያተኝነቱን የተረዳ የእግዚአብሔርን ምሕረት እና ፀጋ ይረዳል። ዘሪቱ መጽሐፍ ላይ ያለውም ይሄው ነው።
ይልቅ ዘሪቱ ስለ ውድቀቷ የፃፈችው ላይ መጠነኛ ቅሬታ አለኝ። ውድቀቷ የእግዚአብሔርን ፀጋ እንድታውቅ እንደረዳት ግልፅ ቢሆንም ጉዳዩ በተሻለ ጥልቀት መብራራት ነበረበት።
የህይወት ታሪክን ከማንበብ ጥቅሞች መካከል አንዱ ከሌላው የህይወት ጉዞ መማር ነው።
ደካሞች ነን። ከኛጋ ድካም የሚጋራን ሰው የህይወት መንገድ ማወቅ ይረዳናል። ዘሪቱ ስለ ውድቀቷ ስትፅፍ በተሻለ ጥልቀት ብትፅፍ ጥሩ ነበር።
ለውድቀቷ የዳረጓትን ገፊ ምክኒያቶች ፥ አስቻይ ሁኔታዎች ፥ ስነልቦናን ወዘተ ብትነግረን ሌሎቻችን ለምን እንደምንወድቅ እንድንገነዘብ ይረዳን ይሆናል።
ከችግሩ ነፃ ስትወጣም እንዴት ባለ መንገድ ነፃ እንደወጣች በተሻለ ጥልቀት ብታስረዳን ጥሩ ነበር።
ዘሪቱ በ ዝ ሙ ት የወደቀችባቸውን አጋጣሚዎች በግልፅ ፅፋለች። ነገር ግን ከብዙ ወንድ ጋ ተኝቻለሁ አላለችም። ይልቅ "ይሄ /መወደቋ/ የሁልጊዜ ተግባሬ ሳይሆን አልፎ አልፎ የሚፈትነኝ ድካሜ ነው" ብላለች።
Via ተስፋኣብ ተሾመ
@Tfanos
ብዙ ሰው የዘሪቱን መጽሐፍ ያነበበ አይመስለኝም። ያነበበ ሰው መጽሐፉ ላይ በሌለ ሃሳብ አይዘምትባትም።
መጽሐፉን አንብቤዋለሁ።ዘሪቱ "ከብዙ ሰውጋ ተኝቻለሁ" አላለችም። አዎ አላለችም።
ዘሪቱ በ ዝ ሙ ት ሀጢያት ወድቃ እንደምታውቅ በግልፅ ፅፋለች። ሃጢያቷን የገለፀችው ስለ እግዚአብሔር ፀጋ ለማስረዳት ነው። "በሰው ፊት እንዳፃዲቅ በምቆጠርበት ፥ እኔም ራሴን እንደ ፃዲቅ በምቆጥርበት ወቅት ወደቅኹ" አለች።
ሰዎች በመውደቅ ጭምር ከራሳቸው እንደ አዲስ ይተዋወቃሉ። ከራስ መተዋወቅ ደካማ እና ሃጢያተኛ መሆንን መገንዘብ ነው። ሃጢያተኝነቱን የተረዳ የእግዚአብሔርን ምሕረት እና ፀጋ ይረዳል። ዘሪቱ መጽሐፍ ላይ ያለውም ይሄው ነው።
ይልቅ ዘሪቱ ስለ ውድቀቷ የፃፈችው ላይ መጠነኛ ቅሬታ አለኝ። ውድቀቷ የእግዚአብሔርን ፀጋ እንድታውቅ እንደረዳት ግልፅ ቢሆንም ጉዳዩ በተሻለ ጥልቀት መብራራት ነበረበት።
የህይወት ታሪክን ከማንበብ ጥቅሞች መካከል አንዱ ከሌላው የህይወት ጉዞ መማር ነው።
ደካሞች ነን። ከኛጋ ድካም የሚጋራን ሰው የህይወት መንገድ ማወቅ ይረዳናል። ዘሪቱ ስለ ውድቀቷ ስትፅፍ በተሻለ ጥልቀት ብትፅፍ ጥሩ ነበር።
ለውድቀቷ የዳረጓትን ገፊ ምክኒያቶች ፥ አስቻይ ሁኔታዎች ፥ ስነልቦናን ወዘተ ብትነግረን ሌሎቻችን ለምን እንደምንወድቅ እንድንገነዘብ ይረዳን ይሆናል።
ከችግሩ ነፃ ስትወጣም እንዴት ባለ መንገድ ነፃ እንደወጣች በተሻለ ጥልቀት ብታስረዳን ጥሩ ነበር።
ዘሪቱ በ ዝ ሙ ት የወደቀችባቸውን አጋጣሚዎች በግልፅ ፅፋለች። ነገር ግን ከብዙ ወንድ ጋ ተኝቻለሁ አላለችም። ይልቅ "ይሄ /መወደቋ/ የሁልጊዜ ተግባሬ ሳይሆን አልፎ አልፎ የሚፈትነኝ ድካሜ ነው" ብላለች።
Via ተስፋኣብ ተሾመ
@Tfanos
❤4👍4
ፕሮቴስታንት ላይ የሚወረወር እያንዳንዱ የጥላቻ ቀስት እኔንም ይ ወ ጋ ኛ ል። ለፕሮቴስታንት የታቀደ ጥ ላ ቻ ወለድ ጦ ር ሳይወጋኝ አያልፍም። ለወገኖቼ የተወረወረ ድን ጋ ይ እኔን ማግኘቱ አይቀርም።
ወገኖቼን አትንኩ!
ቸርች መሄድ ካቆምኩ አመታት ተቆጥረዋል። በማውቀውና በማላውቀው ምክኒያት ህብረት ማድረግ አቁሜያለሁ። ከፀልይኩ ብዙ አመቴ ነው። አንዳንዴ የተማርኩትን ሀይማኖታዊ ትምህርት እጠረጥራለሁ። የእምነቴ መስመር ከወገኖቼ እምነት መስመር ከተለየ ቆየ። አንዳንዴ ከሀይማኖት ወገኖቼ የተበጠስኩ ያህል ይሰማኛል። ቢሆኑም ወገኖቼ ናቸው። ሲነኩ ያመኛል። በነገር ቀስት ሲ ወ ጉ ልቤ ይደማል። የሚወረወርባቸው ድ ን ጋ ይ እኔም ይሰብረኛል።
ወገኖቼን አትንኩ!
እኔ ዘንድ በጎ ፍሬ ካለ ዘሩን የዘራችው ያደግኩባት ቃለ ህይወት ቤተ ክርስቲያን ናት። ምናልባት አንዳች ጥሩ ነገር ካለኝ ያንን ጥሩ ነገር ያገኘሁት ከቸርች መጋቢዎቼ ነው። የፓስተር አበበ ፈረንጅ የደህንነት ትምህርት ፥ የፓስተር ሀብቴ አሰፋ የደቀ-መዝሙርነትና የአገልግሎት ትምህርት ፥ የመምህሬ ሙልዬ የልጅነት ትምህርት ፥ የወንጌላዊ በላይ ቦርኩ ምክሮች ናቸው የሰሩኝ። እኔን የሰራኝ የፕሮቴስታንት ትምህርት ነው።
ወገኖቼን አትንኩ!
ከትምህርት ጋር የተዋወቅኩት በቃለ-ህይወት በኩል ነው። ፊደል ያስቆጠሩኝ ፥ የሂሳብ ስሌቶችን ያስተማሩኝ ፥ ማንበብ ያለማመዱኝ የቸርች መምህራን ናቸው።
ወንጌላዊ ስምኦን ፥ መምህር አለማየሁ ፥ ወንጌላዊ ተሻገር... ወዘተ እንዴት ረሳቸዋለሁ?
ወገኖቼን አትንኩ!
ትዝታዬን ከፕሮቴስታንት መነጠል አልችልም። ያለ ፕሮቴስታንት ወገኖቼ ምንም ነኝ። ሰው ያደረጉኝ እነሱ ናቸው። ፍቅር አስተምረውኛል።
ልጅ ሆኜ የተረት መጻሕፍት አላነበብኩም። ይልቅ ለሕፃናት የተዘጋጀ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክን አነብ ነበር። ከፍ ስል ወንጌላዊ ተስፋዬ "የሰው ልብ" የሚል መጽሐፍ አስነበበኝ። ያኔ እድሜዬ 11 ነበር። ቀጥሎ ደግሞ ወንጌላዊ ወርቅነህ መንፈሳዊ መጽሔቶችን አስተዋወቀኝ።
ሴኩላር መጻሕፍት ያገኘሁት ዘግይቼ ነው። ከዛ በፊት አነባቸው የነበሩት መጻሕፍት የነበረው የነዶክተር መለሰ ወጉን መጻፍት ነበር። በእርግጥ አይገባኝም ነበር።
ወገኖቼን አትንኩ
ፕሮቴስታንት ማለት ትዝታዬ ነው። ማንም ትዝታዬ ላይ ሲዘባበት ደስ አይለኝም። ፕሮቴስታንት ከእውቀት ጋር መተዋወቂያ በር ሆኖኛል። ፕሮቴስታንት ስነልቦናዬን ቀርፆኛል። ፕሮቴስታንት ብዙ ነገሬ ነው።
ኪነ-ጥበብን የተዋወቅኩት በቸርች በኩል ነው። ድራማ መፃፍ ፥ መግጠም ፥ ልብወለድ መድረስን የተማርኩት በቸርች በኩል ነው።
ልጆች ሆነን ድ ን ጋ ይ ይወረወርብን ነበር። እንሰደብ ነበር። ዛሬም እንደትላንቱ ማድረግ የሚፈልጉ እንዳሉ አውቃለሁ። እነሱን "እንከባበር" ማለት ያስፈልጋል።
ወገኖቼን አትንኩ!
ግማሽ አካሌ ፥ ትዝታዬ ፥ ቤተሰቦቼ ፥ ገጠመኞቼ ሁሉ ከፕሮቴስታንት ጋር የተሳሰረ ነው። ስለዚህ ወገኖቼ ላይ የሚሰነዘር ጥ ላ ቻ ወለድ ቀስት ልቤን ያደማዋል።
ወገኖቼን አትንኩ! እነሱን ስትነኩ "እኔም ከእነሱ እንደ አንዱ ነኝ" ብዬ እመጣለሁ
@Tfanos
ወገኖቼን አትንኩ!
ቸርች መሄድ ካቆምኩ አመታት ተቆጥረዋል። በማውቀውና በማላውቀው ምክኒያት ህብረት ማድረግ አቁሜያለሁ። ከፀልይኩ ብዙ አመቴ ነው። አንዳንዴ የተማርኩትን ሀይማኖታዊ ትምህርት እጠረጥራለሁ። የእምነቴ መስመር ከወገኖቼ እምነት መስመር ከተለየ ቆየ። አንዳንዴ ከሀይማኖት ወገኖቼ የተበጠስኩ ያህል ይሰማኛል። ቢሆኑም ወገኖቼ ናቸው። ሲነኩ ያመኛል። በነገር ቀስት ሲ ወ ጉ ልቤ ይደማል። የሚወረወርባቸው ድ ን ጋ ይ እኔም ይሰብረኛል።
ወገኖቼን አትንኩ!
እኔ ዘንድ በጎ ፍሬ ካለ ዘሩን የዘራችው ያደግኩባት ቃለ ህይወት ቤተ ክርስቲያን ናት። ምናልባት አንዳች ጥሩ ነገር ካለኝ ያንን ጥሩ ነገር ያገኘሁት ከቸርች መጋቢዎቼ ነው። የፓስተር አበበ ፈረንጅ የደህንነት ትምህርት ፥ የፓስተር ሀብቴ አሰፋ የደቀ-መዝሙርነትና የአገልግሎት ትምህርት ፥ የመምህሬ ሙልዬ የልጅነት ትምህርት ፥ የወንጌላዊ በላይ ቦርኩ ምክሮች ናቸው የሰሩኝ። እኔን የሰራኝ የፕሮቴስታንት ትምህርት ነው።
ወገኖቼን አትንኩ!
ከትምህርት ጋር የተዋወቅኩት በቃለ-ህይወት በኩል ነው። ፊደል ያስቆጠሩኝ ፥ የሂሳብ ስሌቶችን ያስተማሩኝ ፥ ማንበብ ያለማመዱኝ የቸርች መምህራን ናቸው።
ወንጌላዊ ስምኦን ፥ መምህር አለማየሁ ፥ ወንጌላዊ ተሻገር... ወዘተ እንዴት ረሳቸዋለሁ?
ወገኖቼን አትንኩ!
ትዝታዬን ከፕሮቴስታንት መነጠል አልችልም። ያለ ፕሮቴስታንት ወገኖቼ ምንም ነኝ። ሰው ያደረጉኝ እነሱ ናቸው። ፍቅር አስተምረውኛል።
ልጅ ሆኜ የተረት መጻሕፍት አላነበብኩም። ይልቅ ለሕፃናት የተዘጋጀ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክን አነብ ነበር። ከፍ ስል ወንጌላዊ ተስፋዬ "የሰው ልብ" የሚል መጽሐፍ አስነበበኝ። ያኔ እድሜዬ 11 ነበር። ቀጥሎ ደግሞ ወንጌላዊ ወርቅነህ መንፈሳዊ መጽሔቶችን አስተዋወቀኝ።
ሴኩላር መጻሕፍት ያገኘሁት ዘግይቼ ነው። ከዛ በፊት አነባቸው የነበሩት መጻሕፍት የነበረው የነዶክተር መለሰ ወጉን መጻፍት ነበር። በእርግጥ አይገባኝም ነበር።
ወገኖቼን አትንኩ
ፕሮቴስታንት ማለት ትዝታዬ ነው። ማንም ትዝታዬ ላይ ሲዘባበት ደስ አይለኝም። ፕሮቴስታንት ከእውቀት ጋር መተዋወቂያ በር ሆኖኛል። ፕሮቴስታንት ስነልቦናዬን ቀርፆኛል። ፕሮቴስታንት ብዙ ነገሬ ነው።
ኪነ-ጥበብን የተዋወቅኩት በቸርች በኩል ነው። ድራማ መፃፍ ፥ መግጠም ፥ ልብወለድ መድረስን የተማርኩት በቸርች በኩል ነው።
ልጆች ሆነን ድ ን ጋ ይ ይወረወርብን ነበር። እንሰደብ ነበር። ዛሬም እንደትላንቱ ማድረግ የሚፈልጉ እንዳሉ አውቃለሁ። እነሱን "እንከባበር" ማለት ያስፈልጋል።
ወገኖቼን አትንኩ!
ግማሽ አካሌ ፥ ትዝታዬ ፥ ቤተሰቦቼ ፥ ገጠመኞቼ ሁሉ ከፕሮቴስታንት ጋር የተሳሰረ ነው። ስለዚህ ወገኖቼ ላይ የሚሰነዘር ጥ ላ ቻ ወለድ ቀስት ልቤን ያደማዋል።
ወገኖቼን አትንኩ! እነሱን ስትነኩ "እኔም ከእነሱ እንደ አንዱ ነኝ" ብዬ እመጣለሁ
@Tfanos
❤13👍2👎2
