Telegram Web Link
TIKVAH-ETHIOPIA
#አዲስአበባ #ሊዝ የመሬት ሊዝ ጨረታ አሸናፊዎች ዝርዝር ይፋ ሆኗል። • በአንድ ካሬ ሜትር አሸናፊ የሆነው ከፍተኛ ዋጋ 470 ሺህ ብር ሲሆን ዝቅተኛ 20 ሺህ 100 ብር ነው። የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማት እና አስተዳደር ቢሮ የ2ኛ ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ አሸናፊዎች ዝርዝር በአዲስ ልሳን ጋዜጣ ታትሞ ተሰራጭቷል። በጨረታው ዝቅተኛ ዋጋ የተመዘገበው በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ሲሆን ይህም…
Addis Lissan Ginbot 27-2016.pdf
7.2 MB
#AddisAbaba

የ2ኛ ዙር የመሬት ሊዝ ጨረታ #አሸናፊዎች ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።

በጋዜጣው ላይ በካሬ ሜትር የቀረበው ከፍተኛው ገንዘብ 478 ሺህ ብር ተብሎ ተገልጿል።

ከታች ዝርዝሩ ላይ ደግሞ ከፍተኛው 470 ሺህ ብር እንደሆነ ሰፍሯል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ትክክለኛው ስንት ነው ? 478 ሺህ ብር ወይስ 470 ሺህ ብር ? ሲል ጠይቋል።

ቢሮውም ትክክለኛው 470 ሺህ (በዝርዝሩ ላይ ያለው) እንደሆነ ገልጿል።

478 ሺህ የሚለው ስህተት እንደሆነ አመልክቷል።

#AddisLisan
#AddisAbabaLandDevelopmentandAdministrationBureau

@tikvahethiopia
#አቢሲንያ_ባንክ
የተለያዩ ተቋሟት የአገልግሎት ክፍያዎችን እንደዚሁም የአዲስ አበባ ትራፊክ ቅጣትዎን በባንካችን መክፈል እንደሚችሉ ያውቃሉ?
በአቅራቢያዎ የሚገኙ ቅርንጫፎቻችንን እና የቨርቹዋል ባንኪንግ ማዕከሎቻችንን ይጎብኙ እንዲሁም እጅዎ ላይ በሚገኙ የተለያዩ የዲጂታል መክፈያ ዘዴዎች በመጠቀም ይክፈሉ።
የተለያዪ ጠቃሚ ምክሮችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ።
https://www.tg-me.com/BoAEth

#banksinethiopia #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
#SamiTech

አዳዲስ ላፕቶፕች ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech

ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች ፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች ፣ ለጌመሮች  ወ.ዘ.ተ

አቅምን ካገናዘቡ እስከ ቅንጡ ላፕቶፖች ይህ ቀረ ሳይሉ የሚያገኙበትን ሱቃችንን ይጎብኙ።

የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ ባሉበት ሆነው ይዘዙን እናደርሳለን።

የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት ይሄን 👉 @samcomptech ተጭነው በቴሌግራምው ማየት ይችላሉ።

@sww2844 0928442662 / 0940141114

https://maps.app.goo.gl/H3PM1NrTcQ4SWkK17
 #Tigray

በአንድ ቀን ብቻ የ 7 ሰዎች ህይወት በትራፊክ አደጋ ሲቀጠፍ ከ20 በላይ ሰዎች የአከል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

ከሟቾቹ ሶስቱ የአንድ ቤተሰብ አባል ናቸው።

የትራፊክ አደጋው ያጋጠመው ግንቦት 28/2016 ዓ.ም በአንድ ቀን በሁለት የትግራይ አከባቢዎች ነው።

ከዓድዋ ከተማ ወደ ጥንታዊትዋ የይሓ የቱሪስት ማእከል በየዓመቱ የሚከበረውን የቤተክርስትያን ዝክር ለማክበር በግል መኪና ሲጓዙ የነበሩት የአንድ ቤተሰብ አባላት ላይ በተከሰተው የትራፊክ አደጋ አራቱ ለህልፈት ሲዳረጉ ፤ ከ10 በላይ ሰዎች ተጎድተዋል።

በዚያው በተመሳሳይ ቀን በሓውዜን ወረዳ ሙሽሮች የጫነ መኪና ከሞተር ሳይክል ጋር በመጋጨቱ የሶስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ከ10 በላይ ሰዎች ተጎድተዋል።

የአደጋዎቹ መነሻ በማይመች ቦታ ከሚፈቀደው በላይ መፈጥንና መጫን መሆኑ የትራፊክ ባለሙያዎች ገልጸዋል።

አሽከርካሪዎች ለራሳቸውና ለሰው ደህንነት ትኩረት ሰጥተው እንዲያሽከርክሩ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሬሜዲያል " በበዓል ቀናት ሆነ ማግስት የሚወጣ የፈተና ሰሌዳ አግባብነት የለውም " - የፌዴራል መጅሊስ የሬሜዲያል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ቅሬታ አስነስቷል። የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ እንደሚሰጥ ይጠበቃል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው የሪሚዲያል ተማሪዎች የፈተና መርግብር፤ ፈተናው ከሰኔ 3-10/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ያሳያል። የማኅበራዊ ሳይንስ…
" ፈተናው ወደ ሰኔ 11 ተዘዋውሯል " - ትምህርት ሚኒስቴር

በኢድ አል አድሃ አረፋ ቀን ሊሰጥ የነበረው ሀገር አቀፉ የሬሚዲያል ፈተና ወደ ሰኔ 11 ቀን ተዛወረ።

የትምህርት ሚኒስቴር ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ/ም ሊሰጥ የነበረው የሬሚዲያል ፈተና ወደ ሰኔ 11 ቀን 2016 ዓ.ም መዛወሩን ዛሬ አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ ፥ የሬሚዲያል ትምህርት የማጠቃለያ ፈተናን ከሰኔ 3 እስከ 10 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ለመስጠት የፈተና ፕሮግራም ተዘጋጅቶ እንደነበር አስታውሷል፡፡

ይሁን እንጂ ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም የዒድ አል-አድሃ አረፋ በዓል በመሆኑ በዕለቱ ይሰጥ የነበረው ፈተና ሰኔ 11 ቀን 2016 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን  አስታውቋል፡፡

የዘንድሮ የሬሜዲያል ፈተና ቀንን በተመለከተ ትላንትና የፌዴራል መጅሊስ ፤ " በበዓል ቀናት ሆነ ማግስት የሚወጣ የፈተና ሰሌዳ አግባብነት የለውም " ሲል መቃወሙ ይታወሳል።

የፌዴራል መጅሊሱ " የትኛውም የተማሪዎች የመፈተኛ የጊዜ ሰሌዳ የሙስሊሙን በዓላት ታሳቢ አድርገው መውጣት አለባቸው " ሲል ማሳሰቡ አይዘነጋም።

ከዚህም ቀደም ከበዓል ጋር በተያያዘ መሰል ሁኔታዎች ማጋጠማቸው ይታወቃል።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#Ethiopia

ለ2017 በጀት አመት 1 ትሪሊዮን የሚጠጋ በጀት ቀረበ።

ዛሬ የሚኒስትሮች ም/ቤት ስብሰባ ተቀምጦ ነበር።

በዚህም ስብሰባው ላይ የተለያዩ ውሳኔዎች አሳልፏል።

ከውሳኔዎቹ አንዱ ደግሞ የ2017 በጀት አመት የፌዴራል መንግስት ረቂቅ የበጀት አዋጅ ነው።

በዚህም ፦
➡️ ለፌዴራል መንግስት መደበኛ ወጪዎች ፣
➡️ ለካፒታል ወጪዎች ፣
➡️ ለክልሎች የሚሰጥ ድጋፍ፣
➡️ ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ድጋፍ
➡️ ተጠባባቂ ወጪን ጨምሮ ወደ #አንድ_ትሪሊየን የሚጠጋ በጀት ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡

ምክር ቤቱም በቀረበው የፌዴራል መንግስት የ2017 ረቂቅ በጀት አዋጅ ላይ ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

(ተጨማሪ መረጃ እና ሌሎች ውሳኔዎች ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#Amhara

በአማራ ክልል ፤ በሰሜን ጎንደር ዞን በአድርቃይ ወረዳ በተፈጸመ ጥቃት 15 የሚሆኑ ሰዎች መገደላቸውን እና በርካታ ቤቶች መቃጠላቸውን ነዋሪዎች እና የአካባቢው አስተዳደር አሳውቀዋል።

ይህ አካባቢ የትግራይ እና አማራ ክልሎች አዋሳኝ ነው።

ነዋሪዎች ምን አሉ ?

- ባለፈው ማክሰኞ ግንቦት 27 ከንጋቱ በ11፡00 ሰዓት አሊጣራ ቀበሌ አንካቶ በተባለ ጎጥ የቡድን መሳሪያ #ከትግራይ_በኩል በመጡ የታጠቁ ኃይሎች ከባድ ጥቃት ተከፍቶ ነበር።

- ጥቃቱ ከንጋቱ 11፡00 ጀምሮ እስከ ጠዋት 2፡30 ገደማ ነበር የዘለቀው።

- አንድ የአካባቢው ነዋሪ ፥ " #በአንድ_ቤት 5 ነበርን፣ ከአምስታችን እኔ ነኝ በአጋጣሚ የተረፍኩት፤ ሌሎቹ ሞቱ። አሰልፈው ነው የተኮሱብን።...እኔንም ሞቷል ብለው ነው ትተውኝ የሄዱት። በፈጣሪ ፈቃድ ነው የተረፍኩት ፤ ጀርባዬን በጥይት ተመትቼ ሆስፒታል ነው ያለሁት " ብለዋል።

- ሌላ ነዋሪ ፤ " በጥቃቱ 15 ሠዎች መገደላቸውን በዐይኔ ተመልክቻለሁ። ሁለት የ16 እና የ19 ዓመት የእህት ልጆቼም ተገድለዋል። " ሲሉ ተናግረዋል።

- ሌላኛው ነዋሪ ፥ " በእሳት እና በጥይት 3 ታዳጊዎችን ጨምሮ የበርካታ ሰዎች ሕይወት አልፏል። ህጻናትን ጨምሮ 15 ሠዎች መገደላቸውን አይቻለሁ " ብለዋል።

- የአካባቢው #የሚሊሻ አባል ፤ " ከጥቃት ፈጻሚዎች ጋር የተኩስ ልውውጥ ነበር። አብሮኝ የነበረው ታናሽ ወንድሜ በጥቃቱ ተገድሏል። ቦምብ ጉዳት አድርሷል፤ ጥይቱ፤ መሳሪያውም ብዙ ስለሆነ፤ ድሽቃ፣ ስናይፐር፣ ብሬን አላቸው። በእርቀት እየተኮሱ ነው ጉዳት ያደረሱት " ብለዋል።

-  ታጣቂዎቹ አካባቢውን ለቀው ሲወጡ 3 ሰዎችን ወስደዋል። 500 ከብቶችን ዘርፈወል። ቤቶችም ተቃጥለዋል።

ወረዳው ምን አለ ?

ዋና አስታዳዳሪ አቶ ሚሊዮን ታደሰ ጥቃቱን የፈጸሙት በዋልድባ ገዳም በኩል አድርገው የገቡ የትግራይ ኃይሎች ናቸው ብለዋል።

ቀብራቸው መፈጸሙን #ማረጋገጥ የቻሉት የስምንት ሰዎች መሆናቸውን ተናግረዋል።

ከ8ቱ ሟቾች መካከል 6ቱ #ንጹሃን_ነዋሪዎች እንደሆኑ 2ቱ የአካባቢው ሚሊሻ አባላት እንደነበሩ ገልጸዋል።

ጥቃተ የፈጸሙት የትግራይ ኃይሎች ስለመሆናቸው በምን እንዳወቁ ተጠይቀው ፥ ነዋሪዎች በሚናገሩት ቋንቋ እንደለይዋቸውና በተለያዩ ጊዜያትም ትንኮሳዎችን ይፈጽሙ እንደነበር ገልጸዋል።

" የትግራይ ታጣቂዎች ናቸው። ከእነሱ ውጪ የሚመጣብን ሌላ እንደሌለ ነው የተረዳነው " ብለዋል።

" ቡድኑን የሚመራውን ግለሰብ ጭምር እናውቃለን ፤ የህወሓት ታጣቂዎች ናቸው " ሲሉ ተናግረዋል።

ቦታው ይገባኛል የሚነሳባቸውን አካባቢዎችን ለመያዝ " ስልታዊ " መሆኑን ተንተርሶ ጥቃቱ ሳይፈጸም አልቀረም ብለዋል።

" የማንነት ጉዳይ ሚነሳባቸውን አካባቢዎች በቁጥጥራቸው ስር ለማድረግ የግድ የእኛን አካባቢ ማጥቃት አለባቸው። በ2013ም የተመለከትነው ይህን ነው። ስለዚህ ይህን አካባቢ የመቁረጥ፤ ቆርጦ መሀል ላይ ያለን የመንግሥትን መዋቅር የማጥቃት ፍላጎት አለ " ሲሉ ተናግረዋል።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምን ምላሽ ሰጠ ?

የትግራይ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ባልደረባ አቶ አማረ ኃይሌ ፤ የትግራይ ኃይሎች ጥቃት አልፈጸሙም ብለዋል።

" እስካሁን ድረስ ወደዚያ አካባቢ ያደረግነው ምንም እንቅስቃሴ የለም " ብለዋል።

" እኛ ያለንበት ቦታና አሁን እየተባለ ባለው ቦታ በጣም ሰፊ ርቀት ነው ያለው። በቀጥታ የሚዋሰን ቦታም አይደለም " በማለት ጥቃቱን እንዳላደረሱ ገልጸዋል።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር " ያሉ ችግሮችን ግጭት አልባ በሆነ መንገድ ለመፍታት ነው የሚያስበው ወደ ግጭት የመግባት ሁኔታ የለንም " ብለዋል።

Credit - BBC AMHARIC

@tikvahethiopia
እንኳን ለ2016 ዓ.ም የቤንች ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ በዓል "ቢስት ባር " በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን!

እስከ 25% በሚደርስ ቅናሽ ያቀረብናቸውን የበአል ልዩ ጥቅሎች በቴሌብር ሱፐርአፕ ከተጨማሪ 10% ስጦታ ጋር እንዲሁም በ*999# ይግዙ፤ ለሚወዷቸውም በስጦታ ያበርክቱ!

መልካም በዓል!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia
#ስራ #ደመወዝ

° " ያለስራና ደመወዝ በመቆየታችን ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቀናል " - የመንግስት ሰራተኞች

° " ጉዳዩን እናውቀዋለን እየተወያየንበት ነው ፥ በአጭር ቀናት መፍትሄ ይሰጣቸዋል " - የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለስልጣን

የደቡብ ክልል መበተኑን ተከትሎ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተመደቡ የ " ውሀ ስራዎች ኮንስትራክሽን ሰራተኞች " ከስራ እና ከደመወዝ ውጭ ሆነው ወራት እንደተቆጠሩ ገልጸዋል።

ሰራተኞቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ባቀረቡት ቅሬታ ፥ ክልሉ ከፈረሰ በኋላ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቢመደቡም እስካሁን ስራ አለመጀመራቸውን በዚህም ለችግር መጋለጣቸውን ተናግረዋል።

ከ2 ወር በፊት ዘግይቶ በተሰጣቸው ደብዳቤ ሆሳዕና ከተማ መመደባቸው እንደተነገራቸው ጠቁመዋል።

ቦታው ላይ ተገኝተው ሪፖርት በማድረግ ደመወዝ እና ጥቅማጥቅም እንደሚሰጣቸውም ተገልጾላቸው ነበር።

በዚህም ግማሽ ሰራተኞች እቃቸውን በገንዘብ እጥረት ሽጠው እንዲሁም ቀሪውን በሌለ ገንዘብ ትራንስፖርት ከፍለው ቦታው ቢደርሱም አንድም የሚያስተናግዳቸው ሆነ የሚቀበላቸዉ አካል ማጣታቸውን አስረድተዋል።

በመሆኑም ያለደሞዝና ስራ በተመደቡበት ከተማ ለ2 ወራት መቆየታቸው ህይወትን ከባድ እንዳደረገባቸዉ ገልጸዋል።

በገንዘብ እጦት የምግብ መግዣ እንኳ እንስከማጣት መድረሳቸውን ከዚህም በላይ በቤት ኪራይ ችግር አብዛኛዉ ሰራተኛ ጎዳና ለመውጣት ጫፍ መድረሱን ተናግረዋል።

" ሆሳዕና የሚገኘው አዲሱ ቢሮ ስንሄድ #ጸሀፊ_ብቻ ነው የምናገኘው " የሚሉት ሰራተኞቹ " የሚመለከተው አካል ሌላዉ ቢቀር ጥያቄያችን ሊያደምጥ ይገባል " ሲሉ ቅሬታቸው ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰራተኞቹን ጥያቄ ይዞ ያናገራቸዉ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አማካሪ እና ልዩ ረዳት የሆኑትን አቶ ንጉሴ አስረስ ፥ ጉዳዩን እንደሚያውቁት በመግለጽ ችግሩ በቅርብ እንደሚፈታ ተናግረዋል።

ከሰሞኑ ሰራተኞችን በአካል አግኝተዋቸው ለማነጋገር እቅድ እንዳላቸውም የገለጹት አቶ ዘሪሁን " ለሁለት መቶ አስር ሰራተኞች ደሞዝ መክፈል ለክልሉ ቀላል ነው " ብለዋል።

በቅርቡ ችግሩ ላይ የተወሰዱ እርምጃዎች እንዲሁም ሌሎችም ተጨማሪ ጥያቄዎች ካሉ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሊያነጋግራቸው እንደሚችል ቃል ገብተዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
#CentralEthiopiaRegion

@tikvahethiopia
#BahirDarUniversity

ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ለ2016 የሪሚዲያል ተማሪዎቹ ጥሪ ሊያደርግ ነው፡፡

ዩኒቨርሲቲው በፀጥታ እና በሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች በ2016 ዓ/ም አዲስ ለተመደቡለት የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች እስካሁን ድረስ ጥሪ ሳያደርግ ቆይቷል።

ረቡዕ ግንቦት 28 ቀን 2016 ዓ.ም ውይይት ያደረገው የዩኒቨርሲቲው ሴኔት፣ በሰኔ ወር መጨረሻ ለተማሪዎቹ ጥሪ እንዲደረግ መወሰኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተቋሙ ለማረጋገጥ ችሏል፡፡

በዚህም #ከሐምሌ_ወር አጋማሽ ጀምሮ ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን በዩኒቨርሲቲው በመገኘት መከታተል ይጀምራሉ ተብሏል፡፡

ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁም ፣ ትምህርት ሚኒስቴር #በልዩ_ሁኔታ ፈተና እንደሚያዘጋጅላቸው ለማወቅ ተችሏል።

የሬሜዲያል ተማሪዎቹ ያለትምህርት በመቀመጣቸው ከፍተኛ የሆነ ጫና እየደረሰባቸው በመሆኑ መፍትሄ እንዲፈለግላቸው ተደጋጋሚ ጥሪ ሲያቀርቡ እንድነበር አይዘነጋም።

More ➡️ @tikvahuniversity
#ግላመር

ግላመር የስነ-ውበት አካዳሚ አዳዲስ የከፈታቸውን ቅርንጫፎች እና ተማሪዎቹን አስመረቀ።

ግላመር የስነውበት አካዳሚ የቁጥር 5 ፣ 6 እና 7ተኛ ቅርንጫፎቹን መከፈት እንዲሁም በጥፍር እና አይላሽ ስራ ያስተማራቸውን ተማሪዎች መመረቅ ምክንያት በማድረግ ግንቦት 28/2016 ዓ.ም ምሽት በሸራተን አዲስ ሆቴል ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች እና ታዋቂ አርቲስቶች እንዲሁም የግላመር ቤተሰቦች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተመረቀ።

የግላመር ድርጅት መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ የሆኑት ወ/ሮ ህይወት ታደሰ በመድረኩም የመጡትን እንግዶች አመስግነው ለተመራቂ ተማሪዎች የእንኳን ደስ አላቹ መልእክት ያስተላለፋ ሲሆን ግላመር ከዚህ በሗላም በመላው ኢትዮጵያ ቅርንጫፎቹን በጥራት እንደሚያሰፋ ገልፀዋል።

የድርጅቱ ም/ት ስራ አስኪያጅ የዚህዓለም ታምራት ይህንን ፕሮግራም በማስመልከት ለወንድም ካሊድ ፋውንዴሽን ለ10 ተማሪዎች የነፃ የትምህርት እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ በስጦታነት አበርክቷል።

ግላመር የከተማችን ምርጥ እና ግዙፍ የስነ-ውበት ተቋም ነው።

https://www.instagram.com/glamournail_addis1?igsh=bnUyYnV5OWdjN3d1
#glamournail
#glamoureylash
#SamiTech

አዳዲስ ላፕቶፕች ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech

ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች ፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች ፣ ለጌመሮች  ወ.ዘ.ተ

አቅምን ካገናዘቡ እስከ ቅንጡ ላፕቶፖች ይህ ቀረ ሳይሉ የሚያገኙበትን ሱቃችንን ይጎብኙ።

የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ ባሉበት ሆነው ይዘዙን እናደርሳለን።

የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት ይሄን 👉 @samcomptech ተጭነው በቴሌግራምው ማየት ይችላሉ።

@sww2844 0928442662 / 0940141114

https://maps.app.goo.gl/H3PM1NrTcQ4SWkK17
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ፤ የመኖሪያ ቤት የአከራይ ተከራይ የውል ስምምነት ምዝገባ ዛሬ በሁሉም ክ/ ከተማ በሚገኙ ወረዳዎች ተጀመረ።

ማንኛውም የመኖሪያ ቤት አከራይና ተከራይ በምዝገባ ወቅት ማሟላት ያለባቸው ምንድነው ?

➡️ በህግ አግባብ የተዘጋጀ የመኖሪያ ቤት ውል ሰነድ

➡️ #የአከራይ እና #የተከራይ የነዋሪነት መታወቂያ ፣ የመስሪያ ቤት መታወቂያ ፣ መንጃ ፍቃድ ፣ ፓስፖርት ፣ የጠበቃ ፍቃድ ፣ የሰራተኞች ጡረታ መታወቂያ ፣ የዩኒቨርሲቲ / ኮሌጅ ተማሪ የሙያ ስራ ፍቃድ ኦርጅናል ኮፒ ፤

➡️ የመኖሪያ ቤት ውሉ የሚመዘገበው በወኪል ከሆነ ህጋዊ ውክልና የሁለት ምስክሮች የታደሰ መታወቂያ ኦርጅናል ኮፒ፤

➡️ አከራይ የመኖሪያ ቤቱን ለማከራየት የሚያስችል መብት እንዳለው የሚያሳይ ህጋዊ ሰነድ :-
- የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ
- ሰነድ አልባ ይዞታዎች መሆኑን ከሚመለከተው አካል ማስረጃ ወይም
- በፍርድ አፈፃፀም የተሸጠ ንብረት ሰነድ ወይም
- የተከራየው ቤት በውርስ የተገኘ ሆኖ ስም ዝውውር ካልተፈፀመ የወራሽነት ማረጋገጫ

#ኦርጅናል እና #ኮፒ ይዘው  መገኘት አለባቸው።

መረጃው የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ነው።

" የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1320/2016 " ምን ይዟል ? በዚህ ያንብቡ👇
https://www.tg-me.com/tikvahethiopia/88081

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#SouthEthiopiaRegion ➡️ " ... በረሀብ ከምንሞት መብታችን እየጠየቅን አደባባይ ላይ መሞት መርጠን ነው ወደ ርእሰ መስተዳድሩ ቢሮ የሄድነው " - የሶዶ ዙሪያ የመንግስት ሰራተኞች ➡️" ማንም መብቱን በነጻነት የመጠየቅ መብት አለው " - የደቡብ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃፊዉ አቶ ወገኔ ብዙነህ የ2 ወራት ደሞዛችን ይከፈለን ያሉ የወላይታ ዞን የመንግስት ሰራተኞች አደባባይ መውጣታቸዉን…
#ደመወዝ #ደቡብኢትዮጵያ

° " ...ድርጊቱ የደመወዝ ቅሸባ ነው ሊባል የሚችለው ፤ እንዲህ አይነት የደመወዝ አከፋፈል ሰምተንም አናውቅ " - ሰራተኞች

° " ከእኛ #የሚወርደው የበጀት ሀብት እኮ የመንግስት ሰራተኛ ደመወዝ ለመክፈል የሚያስችል ነው " - የክልል ፋይናንስ ቢሮ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ የመንግስት ሰራተኞች " የደመወዝ ይከፈለን " ጥያቄ በብርቱ ከተነሳባቸው አካባቢዎች አንዱና ዋነኛው የ #ወላይታ_ዞን እንደሆነ ይታወቃል።

ሰራተኞቹ ችግር ሲብስባቸው እና ታግሰው ሲመራቸው ሰልፍ  ጭምር በመውጣት ጥያቄ አቅርበዋል።

ለ3 ወራት ያለ ደመወዝ የቆዩት የመንግስት ሰራተኞች አሁን ላይ #የ40_በመቶ እና #የ50_በመቶ ክፍያ ብቻ እየተፈጸመላቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል #የፋይናንስ_ቢሮ ፤ " ደመወዝ ባለመክፈል የመንግሥት ሰራተኛውን እያስራቡ ይገኛሉ " ባላቸው የዞንና የወረዳ የስራ ሃላፊዎች ላይ ፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ #እርምጃ እንደሚወስድ አሳውቋል።

ቢሮው ለወረዳዎቹ በቂ በጀት ማስተላለፉን ገልጿል።

" ለሰራተኛው #ግማሽ_ደመወዝ በመክፍል ቀሪውን ለሌላ የወጭ ርዕስ ይጠቀሙበታል " ሲል ወቅሷል።

አሁን በተለያዩ ወረዳዎች እየተከፈለ ይገኛል የተባለው ደመወዝ በዞኑ መንግሥት ሰራተኞች ዘንድ አጥጋቢ ምላሽ ተደርጎ አልተወሰደም።

ሰራተኞቹ ለ ' ዶቼ ቨለ ሬድዮ ' በሰጡት ቃል ፤ " ምላሹ አጥጋቢ ያልሆነ ፣ የሰራተኛውን ስነ ልቦናም የጎዳ ነው " ብለውታል።

የመንግስት ሰራተኞቹ ፥ ደመወዛቸው ባልተለመደ ሁኔታ ተቆራርጦ እየተከፈላቸው እንደሚገኝ ተናግረው ፤ " የሰራተኞች ጥያቄው ተመልሷል ለማለት እንቸገራለን " ብለዋል።

በአብዛኞቹ ወረዳዎች ላይ አሁን እየተከፈለ የሚገኘው የደመወዛቸውን ከ40 እስከ 50 ፐርሰት ያህል መሆኑን ጠቅሰዋል።

ሰራተኞቹ ፦

ደሞዛችን እንደተፈለገ ተቆረጦ እየቀረ ነው፤

አከፋፈሉ የፋይናንስንም ሆኖ የመንግሥት ሰራተኛ አስተዳደር መመሪያን የሚጻረር ነው፤

ድርጊቱ #የደመወዝ_ቅሸባ እንጂ ሌላ ምንም ሊባል አይችልም ምክንያቱም እንዲህ አይነት የደመወዝ አከፋፈል በትኛውም ዓለም ሰምተን አናውቅም ብለዋል።

ሰሞኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፋይናንስ ቢሮ ዎላይታ ሶዶ ላይ የፋይናንስ ባለሙያዎች ሥልጠናዊ ውይይት አካሄዶ ነበር።

በመድረኩ የደሞዝ ጉዳይ በሰራተኞች ተነስቷል፡፡

የቢሮው ሃላፊ የሆኑት አቶ ተፈሪ አባተ ፥ ፋይናንስ ቢሮ ለወረዳዎች በቂ የበጀት ሀብት እያስተላለፈ እንደሚገኝ አሳውቀዋል።

ወላይታን ጨምሮ በክልሉ አንዳንድ ወረዳዎች ውቅጥ የፋይናንስ ቁጥጥር / ኦዲት / መደረጉን ጠቅሰዋል።

" ወደ ወረዳዎች ሚወርደው የበጀት ሀብት የመንግስት ሰራተኛ ደመወዝ ለመክፈል የሚያስችል ነው፡፡ ይሁን አንጂ አንዳንድ ወረዳዎች ከአሰራር ውጭ ደመወዝ #በፐርሰንት_እየከፈሉ ሰራተኛው እንዲራብ ፣ በክልሉ ላይም እንዲያማርር እያደረጉ ይገኛሉ " ብለዋል።

ክልሉ በቀጣይ በእነኝህ አካላት ላይ አስተዳደራዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እንደሚወስድ ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪ " #ለሽብረቃ የሚወጡ አላስፈላጊ ወጪዎችን ለመገደብ የሚያስችል የወጭ ቅነሳ መመሪያ ተግባራዊ ይደረጋል " ሲሉ የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊው ተናግረዋል።

Credit - #ዶቼቨለሬድዮ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ሲጀመር ‘የኮቴ’ ክፍያ አገር ውስጥ መጠየቅ አግባብ አይደለም " - ጣና የከባድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች ማኀበር የከባድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች ፣ ሞጆ መግቢያ ‘ #የኮቴ ’ በሚል ታጣቂዎች አስቁመው 2,000 ብር እያስከፈሏቸው መሆኑን እየገለጹ ይገኛሉ። ካሁን ቀደም ገንዘቡን ሲጠየቋቸው የነበረው አንዳንድ ጊዜ በቀን እንደነበር ፣ ከሰሞኑን ግን ቀንም ሌሊትም እየጠየቋቸው ከመሆኑም ባሻገር ድብደባና…
#Ethiopia

“... የፌደራል ፓሊስ በፓትሮል መንገድ ላይ ወጥቶ እንዲሰራ ሁሉ ተደርጓል ” - ትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር

የድንበር ተሻጋሪ የከባድ መኪና #አሽከርካሪዎች አገር ውስጥ ከገቡ በኋላ በታጠቁ ኃይሎች እስከ ግድያ የሚድረስ ጥቃት እንደሚፈጸምባቸው መግለጻቸውን በተደጋጋሚ መረጃ ተለዋውጠን ነበር።

አሽከርካሪዎቹ፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ እየሰጠ እንዳልሆነ በመውቀስ የጥቃት መጠኑ ይለያይ እንጂ እስከ ቅርብ ጊዜ እንደቀጠለ ገልጸዋል።

ከዚህ ባለፈ ሀገር ውስጥ ገብተው የ " ኮቴ " እየተባለ የሚከፍሉት ክፍያ እጅግ ለስራቸው ፈተና እንደሆነ አስረድተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም የከባድ ተሽከርካሪ አሽከርካሪዎች እየደረሰብን ነው ያሉትን ችግር ለመቅረፍ በተጨባጭ ምን እየተሰራ ነው ? ሲል የትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴርን ጠይቋል።

የተቋሙ ሚኒስትር ዴኤታ አማካሪ ዶ/ር ቶለሳ በሰጡት ምላሽ ፣ “ ኢትዮጵያ ውስጥ ከገቡ በኋላ ሞጆ ወይንም ደግሞ ማራገፊያ ቦታ እስከሚደርሱ ነበር አሁን በጣም ቁጥጥር እየተደረገ ነው ” ብለዋል።

“ ከሚኒስቴር መ/ቤታችንም ሌላም አካል Direction ተሰጥቶ፣ እንዲያውም #የፌደራል_ፓሊስ በፓትሮል መንገድ ላይ ወጥቶ እንዲሰራ ሁሉ ተደርጓል ” ነው ያሉት።

“ ስለዚህ እኛ እንደዚህ አይነት #እሮሮ ይደርስባቸዋል የሚል መረጃ የለንም ” ያሉት ዶክተር ቶተሳ፣ “ አዲስ የመጣ ነገር የለም። #እየተሻሻለ_መጣ_እንጂ ” ሲሉ ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፣ አሽከርካሪዎቹ አገር ውስጥ ከገቡ በኋላ “ በተለይ ኦሮሚያ ክልል” የ “ #ኮቴ ” እየተባሉ 2,000 እንደሚከፍሉና ከዚህም አለፍ ሲል ድብደባ ጭምር እየደረሰባቸው መሆኑን እየገለጹ ነው። እናንተ ደግሞ ‘ ችግሩ እየቀነሰ ነው ’ እያላችሁ ነው። ለዚህ ቅሬታ ምላሽዎ ምንድን ነው ? የሚል ጥያቄ አቅርቧል።

ዶ/ር ቶለሳ “ አዎ ይኼኛውን እኛም ከጭነት ተሽከርካሪ ተወካዮች ጋር ስብሰባ አካሂደን ነበር። በዚህም ወቅት ክፍያ እንደሚያስከፍሉ ሰምተናል ” ብለዋል።

ችግሩን ለመቅረፍ ከከተማው አስተዳደር ጋር ውይይት እንደሚደረግ ገልጸዋል። “ #ድብደባ ለሚባለውን ግን መረጃ የለንም። ካለ እንሄድበታለን ” ብለዋል።

“ ከኦሮሚያ ክልል መንግስትም ጋር አውርተን መፍትሄ የምንሰጥ ይሆናል ” ሲሉም አክለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#Amhara

በአማራ ክልል ዓመቱን ሙሉ ጭራሽ ምንም ያልተማሩ ተማሪዎች እንዳሉ ተሰምቷል።

በዚህም ምክንያት ምንም አይነት የ6ኛ፣ የ8ኛ እና የ12 ክፍል ፈተና የማያስትፈትኑ ዞኖች እንዳሉ ታውቋል።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ በሰጠው መግለጫ ፥ ከዓመቱ መጀመሪያ ጀምሮ ምንም መቆራረጥ ሳይኖር እየተማሩ አሁን ላይ ትምህርታቸውን እየጨረሱ ያሉ ተማሪዎች አሉ ብሏል።

መሃል ላይ እንዲጀምሩ የተደረጉና የይዘት ክለሳ ተደርጎ እክሰ ነሃሴ ወር ተምረው እንዲያጠናቅቁ የሚደረጉም አሉ ፤ እነሱ አሁን ትምህርት ላይ ናቸው ሲል ገልጿል።

ዓመቱን ሙሉ በሙሉ ደግሞ ጭራሽ ምንም ያልተማሩ ተማሪዎች እንዳሉ ቢሮው አሳውቋል።

ይህ በአብዛኛው በጎጃም ቀጠና እንደሆነ ተጠቁሟል።

ሰሜን ጎጃም እና ምዕራብ ጎጃም ዞኖች ምንም አይነት ተማሪ / አንድም እንኳን ተማሪ የ6ኛ ፣ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ፈተና #እንደማያስፈትኑ ገልጿል።

ምስራቅ ጎጃም ግን ትንሽ ተማሪ አለው ተብሏል።

የትምህርት ቢሮው አሁን ላይ እየተማሩ ያሉ ግን ፈተና የማይፈተኑትን በቀጣይ በሁለተኛው ዙር እንዲፈተኑ ለማድረግ መታቀዱን አመልክቷል።

ምንም ያልተማሩ ተማሪዎችን በሚመለከት ያለ አንዳች ጥፋታቸው ከእድሜያቸው ላይ አንድ አመት መቀነሱ አገባብነት ስለሌለው የተጎዳ ስነልቦናቸውን ለመጠገን ሚያግዝ ስልጠና ይዘጋጃል ብሏል።

የይዘት ክለሳ ተደርጎም ቢሆን ሲማሩ ከነበሩ ተማሪዎች ወደኃላ እንዳይቀሩ ለማድረግ ጥረት ይደረጋል ሲል ገልጿል።

በአማራ ክልል የ8ኛና 6ኛ ክፍል ፈተና ከሰኔ 4/2016 ዓ.ም ጀምሮ የሚሰጥ ሲሆን ፦

184,393 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ሰኔ 4 እና 5 ቀን 2016 ዓ.ም

170,470 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ሰኔ 13 እና 14 ቀን 2016 ዓ.ም ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሏል።

በአማራ ክልል በአጠቃላይ (በሁሉም የትምህርት ደረጃ) በዚህ ዓመት መመዝገብ የነበረባቸው 6.2 ሚሊዮን ተማሪዎች ውስጥ የተመዘገቡት 4 ሚሊዮን ናቸው።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
2024/06/09 01:25:21
Back to Top
HTML Embed Code: