Telegram Web Link
TIKVAH-ETHIOPIA
2023.pdf
#ETHIOPIA

' አልያንስ 2015 ' የተባለው 8 የአዉሮጳ የልማት ድርጅቶች ያቀፉት ተቋም ሀገራት ያሉበትን የረሃብ አደጋ ደረጃ የሚያመላክተውን የዓለም አቀፍ የረሃብ ኢንዴክስ (Global Hunger Index) ይፋ አድርጓል።

በዚህ የረሃብ መለኪያ ሪፖርት ከ125 ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ ከመጨረሻዎቹ 101ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።

የሰቆጣ ቃልኪዳን የፕሮግራም አስተባባሪ ዶክተር ሲሳይ ሲናሞ ምን አሉ ?

- ሪፖርቱ ሲዘጋጅ ሀገራት ካሉበት ደረጃ አንጻር የተለያየ ደረጃ ይሰጣቸዋል።
- የረሃብ ደረጃው ባለፉት 20 ዓመታት በተሰሩት ስራዎች ከ53 በመቶ ወደ 26.1 በመቶ ዝቅ ብሏል። በጣም alarming ከነበረበት ወደ serious ደረጃ ነው የወረደው።
- አሁንም ብዙ ስራ ይቀራል።
- በሀገራችን ያለው የምግብ እና የስርዓተ ምግብ ሁኔታ ብዙ መሰራት አለበት።
- ሪፖርቱ በየዓመት ነው የሚወጣው። በቀጣይ ወጣቶችን ማዕከል ባደረጉ ስራዎች ትኩረት በማድረግ ለመስራት ያለው ሁኔታ ለማሻሻል ይረዳል።
- በአፍሪካ ያለው ከፍተኛ የወጣት ቁጥር በግብርናው ዘርፍ አሰማርቶ መጠቀም አለመቻል አፍሪካ በምግብ ራሷን እንዳትችል አድርጓል።
- ኢትዮጵያ ውስጥ 70 በመቶ የስራ እድል የሚመነጨው ከግብርና ሆኖ እያለ ያላደገው የግብርና ዘርፍ የሚፈለገውን ያህል የስራ እድል እንዳይፈጠር እንቅፋት ሆኗል።

እንደ ዓለም አቀፉ ሪፖርት በኢትዮጵያ እና በዓለም ዙሪያ ለታየው በምግብ እራስን ያለመቻል ችግር ፦
የአየር ንብረት ለውጥ
በየቦታው የሚደረጉት #ጦርነቶች
የኢኮኖሚ መላሸቅ
የኮሮና ወረርሽኝ ዋነኞቹ ናቸው።

በከፍተኛ የምግብ እጥረት እና በረሃብ አደጋ ውስጥ ላሉ ሀገራት መፍትሄ ተብሎ የተቀመጠው መንግሥታት ፦

° ትልቅ አቅም ያላቸው ወጣቶችን ወደ ስራ ገብተው ውጤት እንዲያመጡ ቦታ መስጠት፤

° ብድር ማመቻቸት፤

° ለስራ የሚሆኑ የተለያዩ ስልጠናዎች ማመቻቸት ይኖርባቸዋል  የሚሉት ይገኙበታል።

በግብርናው ዘርፍ ለመዘናት የቆየው በበሬ ማረስ ተግባር ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም በማዘመን በመጠንም በአይነትም ከፍ ያለ ምርት ማምረት ካልተቻለ ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት አሳስቢ ደረጃ ወደ መጨረሻው አስከፊ ደረጃ ልትደርስ ትችላለች ሲል ሪፖርቱ አስጠንቅቋል።

⚠️ ኢትዮጵያ በ2022 ሪፖርት ላይ 27.6 በመቶ በማስመዝገብ ከ121 ሀገራት 104ኛ ደረጃ ላይ ነበረች።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የዚህ መረጃ ምንጮች ፦ ሸገር ኤፍ ኤም ፣  የAlliance 2015 እና የGlobal Hunger Index ድረገጽ መሆናቸውን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
“ ልጅ ያለው የልጅን ነገር ያውቀዋል። ቶሎ ካልታከመች ክፍተቱ እየጨመረ ነገሮች ሁሉ ይከብዳሉ ” - የ9 ዓመቷ ታዳጊ እናት ልጃቸው ለየልብ ህመም የታመመችባቸው እናት ደጋግ ኢትዮጵያውያን እንዲያግዟቸው ተማጽኑ። ወ/ሮ መባ አላምረው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ሊያ የ3ኛ ክፍል ተማሪ 2ኛ ልጄ ናት። #ልቧ 15 ሚሊ ሜትር #ክፍተት አለው ” ብለዋል። የልብ ስፔሻሊቲ ዶክተርም፣ “ ‘ችግሩ ክፍተት…
#ተመስግናችኃል🙏

ከሳምንታት በፊት ' የልብ ክፍተት ' ችግር ስላለባት እና በአስቸኳይ መታከም ስላለባት የ9 ዓመቷ ብላቴና ሊያ የእገዛ መልዕክት ወደናተ ደርሶ ነበር።

በወቅቱም እናቷ ወ/ሮ መባ አላምረው ለህክምና 700 ሺ ብር መጠየቁን በመግለጽ አቅም ያለው ኢትዮጵያዊ ወገን ልጃቸውን ለመታደግ ትብብር እንዲያደርግላቸው ተማጽነው ነበር።

አሁን ላይ ጉዳዩ ከምን ደረሰ ? ስንል ጠይቀናል።

እናት ወ/ሮ መባ አላምረው ትላንትና ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ “ እናንተ ልበ ቀናዎች ባደረጋችሁት ድጋፍ ጭምር የልጄ ሰርጀሪ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል ” ሲል መልካም ዜና አሰምተዋል።

ወ/ሮ መባ በሰጡት ቃል ፦

“ አሁን በጥሩ ጤንነት ላይ ትገኛለች። ከ4 ቀናት ቆይታ በኋላ፣ እሁድ ግንቦት 18 ቀን 2016 ዓ/ም ወደ ቤቷ ገብታለች። ሰርጀሪዋ በጣም ውጤታማ እንደሆነ ዶክተሯ ነግሮኛል።

እናተን እንድገናኝ የረዳኝን ሀይሌ ከፍያለው ከፈረንሳይ እንዲሁም ዶክተር ፈቀደ አግዋር ፈጣሪ እድሜ ያድልልኝ።

#መላው_ኢትዮጵያውያን ፣ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት ማመን በማልችለው ፍቅር እና በፈጣን ምላሽ በአጭር ቀን ውስጥ ልጄ ህክምና እንድታገኝ አግዛችሁኛል። 

ቤተሰቦቼ ፣ ወዳጆቼ በሙሉ እርዳታችሁ ለዚህ ቀን ለማመስገን አድርሶኛል።

አሁንም ፀሎታችሁ አይለየኝ። አመሰግናለሁ ! ” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
(ኢትዮ ቴሌኮም)

እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን!

ቴሌብር በዲጂታል ሥነ-ምህዳሩ ላይ በነበረው የላቀ አበርክቶ የስትራይድ አዋርድ 2024 ኢኮሲስተም ሻምፒዮን  (Stride Award 2024 Ecosystem Champion) ተሸላሚ ሆነ!

የሽልማት መርሃግብሩን ያዘጋጀው የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሲሆን ኩባንያችን የዲጂታል ኢትዮጵያን ከመገንባት አንጻር በተለይም ለሀገራችን የዲጂታል ፋይናንስ መነቃቃት ላበረከተው የላቀ አስተዋጽዖ እውቅናው መበርከቱ ተገልጿል፡፡

ለዚህ ሽልማት ላበቃችሁን ለመላው የኩባንያችን ቤተሰቦች፣ ደንበኞቻችን፣ ባለድርሻ አካላት እና አጋሮቻችን ከልብ እናመሰግናለን!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #SmartAfrica #GSMA #ITU
#ሞደርን_ሾፒንግ_ሴንተር
 
ሞደርን ሾፒንግ እጅግ ዘመናዊ እና ጥራት ያላቸዉ አንዲሁም ኑሮን የሚያቀሉ  የቤት ዉስጥና የኪችን እቃዎች የሚሸጡበት ገበያ ነዉ።

የሁሉንም እቃዎች ዋጋ እና ሌሎች ተጨማሪ እቃዎችን ለማየት የቴሌግራም ቻናላችን ቤተሰብ ይሁኑ። ቴልግራም 👉 www.tg-me.com/modernshoppingcenter

አድራሻ ፦ ቁጥር 1=ጉርድ ሾላ ሆሊ ሲቲ ሴንተር M06
ቁጥር 2= ጀሞ መስተዋት ፋብሪካ ፊትለፊት ራሐ ሞል ግራዉንድ ፍሎር

አዲስ አበባ ዉስጥ ያሉበት ድረስ በፈጣን ሞተረኞቻችን እንልክልዎታለን። ለክፍለሀገር ደንበኞቻችን ባሉበት ሐገር በመናሐሪያ እንልካለን።
#ሪፖርት

በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች በግጭት ዐውድ ውስጥና ውጭ የሚፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች አሳሳቢነትና ሥጋቶችን በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ሪፖርት አውጥቷል።

በሪፖርቱ ፦

- ከሕግ ውጭ ግድያ (በድሮን ጨምሮ) ፣ የሲቪል ሰዎች ሞት፣ የአካል ጉዳት፣ የንብረት ውድመትና ዘረፋ፤
- የዘፈቀደ፣ ሕገወጥ፣ የጅምላና የተራዘመ እስራትና የተፋጠነ ፍትሕ እጦት፤
- እገታ
- አስገድዶ መሰወር እና ያሉበት ቦታ ሳይታወቅ አስሮ ማቆየት
- የሀገር ውስጥ መፈናቀል ... ተዳሰዋል።

° በጸጥታ መደፍረስ፣
° ከመንግሥት አካላት ተገቢውን ምላሽና ትብብር በወቅቱ ባለማግኘት
° በሌሎች ምክንያቶች ምርመራቸውና ክትትላቸው የዘገዩና የተጓተቱ በርካታ ጉዳዮችን መኖራቸው ተገልጿል።

እነዚህን ጉዳዮች በመርመርና ክትትል በማድረግ በተገቢው ጊዜ ይፋ የሚያደርግ ይሆናል ተብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከኮሚሽኑ የተላከለትን ዝርዝር ሪፖርት ከላይ አያይዟል፤ በጥሞና ያንብቡት።

ኢሰመኮ በግጭት ዐውድ ውስጥ እና ከዐውድ ውጭ የሚፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችንና ሥጋቶችን በአስቸኳይ ማቆም ይገባል ብሏል።

የአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎችን ጨምሮ ሁሉንም የትጥቅ ግጭቶች በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሰላምና የሰብአዊ መብቶች መከበርን ማረጋገጥ እንደሚገባም አስገንዝቧል።

#EHRC
#Ethiopia #TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Amhara

ኢሰመኮ፦

- ከየካቲት 15 እስከ 28 ቀን 2016 ዓ/ም በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ደጋ ዳሞት ወረዳ (ዝቋላ ወገም፣ ፈረስ ቤት01፣ ገሳግስና ጉድባ ሰቀላ ቀበሌዎች) እና ሰከላ (አጉት፣ ጉንድልና አምቢሲ ቀበሌዎች እና ግሼ ዓባይ ከተማ) በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎችና በታጣቂዎች መካከል የተካሄዱ የትጥቅ ግጭቶችን ተከትሎ በሲቪል ሰዎች ላይ ሞት፣ አካል ጉዳትና የንብረት ውድመት ደርሷል።

- የካቲት 20/2016 በሰሜን ጎጃም ዞን ሜጫ ወረዳ ብራቃት ቀበሌ በሚገኘው የጋፊት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የአብነት ተማሪዎች የዕለቱን ትምህርትና ጉባኤ ከምሽቱ 5፡00 ሰዓት አካባቢ አጠናቀው ወደ ማደሪያ ጎጇቸው ከገቡ በኋላ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች አባላት ከሌሊቱ 6፡30 ሰዓት ገደማ ላይ ወደ ቦታው ደርሰው ተማሪዎችን “ #ውጡ ” እያሉ ተኩስ በመክፈት ቀድመው በወጡ #በ11_ተማሪዎች ላይ ግድያ እንደፈጸሙ፤ ሌሎች 8 ተማሪዎችንም ደግሞ በቁጥጥር ሥር አውለው ካሳደሩ በኋላ በማግስቱ ምንም ጥፋት የለባችሁም ብለው እንደለቀቋቸው ኢሰመኮ ለመረዳት ችሏል። በወቅቱ በአቅራቢያው የሚንቀሳቀስ የታጠቀ ኃይል እንዳልነበር ምስክሮች አስረድተዋል።

- መጋቢት 2 ቀን 2016 ዓ/ም በኦሮሞ ብሔረሰብ ልዩ ዞን የተነሱ ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች በሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር #በኤፍራታና_ግድም እና #ቀወት ወረዳዎች በሚገኙ የተወሰኑ ቀበሌዎች ላይ በፈጸሙት ጥቃት በሲቪል ሰዎች ላይ ግድያ መፈጸሙን፣ የአካል ጉዳት መድረሱን፣ ንብረት መውደሙን፣ መኖሪያ ቤቶች መቃጠላቸውን እና የቀንድ ከብቶችና ባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎች መዘረፋቸውን ኢሰመኮ ተረድቷል።

- መጋቢት 6 ቀን 2016 በአማራ ክልል፣ በባሕር ዳር ከተማ ዘንዘልማ አካባቢ አቶ ብርሃኑ ሽባባው አካል ፣ አቶ በላይ አካል እና አቶ ተሾመ ይበልጣል የተባሉ ነዋሪዎች አንዱ በሚሠራበት ሱቅ እና ሁለቱ በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ " ኑ ለጥያቄ ትፈለጋላችሁ " በሚል በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር ከዋሉ በኋላ መጋቢት 7 ቀን 2016 በባሕር ዳር ቀበሌ 14 በተለምዶ ጉዶ ባሕር አካባቢ #የፊጥኝ_እንደታሰሩ በጥይት ተገድለው ተገኝተዋል።

- በባሕር ዳር ዳግማዊ ምኒልክ ክ/ከተማ ጋጃ መስክ ተብሎ በሚጠራ ስፍራ መጋቢት 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት አካባቢ ማንነታቸው ባልታወቁ አካላት በተፈጸመ ጥቃት ሶላት ስግደት አከናውነው ወደ ቤታቸው እየተመለሱ የነበሩ የእስልምና ተከታይ 5 ሰዎች (4ቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ) ተገድለዋል።

- ሚያዝያ 7/2016 ከጧቱ 3፡00 ሰዓት ላይ በደቡብ ጎንደር ዞን እስቴ ወረዳ አጎና ቀበሌ ላይ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ከእስቴ ወረዳ ወደ ላይ ጋይንት ወረዳ በመጓዝ ላይ እያሉ በአካባቢው ላይ በሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ኃይሎች (#ፋኖ ) ድንገተኛ የደፈጣ ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎ ታጣቂዎቹ አካባቢውን ጥለው እንደሸሹ #የመንግሥት_የጸጥታ_ኃይሎች ወደ ቦታው በመግባት 7 (1 ሴትና 6 ወንዶች) ሲቪል ሰዎች ላይ ከሕግ ውጪ ግድያ ፈጽመዋል። ከ15 በላይ የሚሆኑ የቆርቆሮ ክዳን ያላቸው መኖሪያ ቤቶች እና 3 የገለባ ቤቶችና ንብረት መቃጠላቸውን እንዲሁም ከ100 በላይ የሚሆኑ የቀበሌው ነዋሪዎች ወደ ሌላ አካባቢ የተፈናቀሉ መሆኑን የቀበሌው ነዋሪዎች እና ተጎጂዎች ገልጸዋል።

- ግንቦት 4/2016 ዓ/ም ከቀኑ ከ7፡00 ሰዓት አካባቢ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቀወት ወረዳ ተሬ ቀበሌ ውስጥ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት በጉሎ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ግቢ ውስጥ 2 ሲቪል ሰዎች ሲገደሉ አንድ ሴት መምህርትን ጨምሮ ሌሎች 9 ሲቪል ሰዎች የቆሰሉ መሆኑን ኢሰመኮ ተረድቷል።

#Amhara #EHRC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Amhara ኢሰመኮ፦ - ከየካቲት 15 እስከ 28 ቀን 2016 ዓ/ም በምዕራብ ጎጃም ዞን፣ ደጋ ዳሞት ወረዳ (ዝቋላ ወገም፣ ፈረስ ቤት01፣ ገሳግስና ጉድባ ሰቀላ ቀበሌዎች) እና ሰከላ (አጉት፣ ጉንድልና አምቢሲ ቀበሌዎች እና ግሼ ዓባይ ከተማ) በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎችና በታጣቂዎች መካከል የተካሄዱ የትጥቅ ግጭቶችን ተከትሎ በሲቪል ሰዎች ላይ ሞት፣ አካል ጉዳትና የንብረት ውድመት ደርሷል። - የካቲት 20/2016…
#Oromia

ኢሰመኮ ፦

- ታኀሣሥ 15 ቀን 2016 ዓ.ም. በግምት ከጠዋቱ 1፡30 ሰዓት አካባቢ በኦሮሚያ ክልል በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ጉዱሩ ወረዳ ውስጥ በተፈጸመ #የድሮን_ጥቃት
° በየነ ጢቂ፣
° ጉደታ ፊጤ፣
° ሀብታሙ ንጋቱ፣
° ታዴ መንገሻ፣
° ዳመና ሊካሳ፣
° ዱጋሳ ዋኬኔ፣
° ሕፃን አብዲ ጥላሁን
° ሕፃን ኦብሳ ተሬሳ የተባሉ 8 ሰዎች ተገድለዋል።

በተጨማሪም፦
• ስንታየሁ ታከለ፣
• ሽቶ እምሩ፣
• ተሜ ኑጉሴ
• አለሚ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል። በአካባቢው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (በተለምዶ “ #ኦነግ_ሸኔ ”) በሰፊው ይንቀሳቀስ የነበረ መሆኑን እና የሀገር መከላከያ ሰራዊት በአካባቢው በሚደረጉ ውጊያዎች አልፎ አልፎ #በድሮን_ይጠቀም የነበረ መሆኑን ኢሰመኮ ያነጋገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።

- ጥር 9/2016 ዓ/ም በሰሜን ሸዋ ዞን ፤ ደራ ወረዳ የሀገር መከላከያ ሰራዊት #ለሌላ_ግዳጅ አካባቢውን ለቅቆ ይወጣል። ይህን ተከትሎም የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (ኦነግ ሸኔ) ታጣቂዎች በማግስቱ አካባቢውን ከተቆጣጠሩ በኋላ “ ለመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ምግብ ስታቀርቡ ነበር ” በማለት 01 ቀበሌ የሚገኘው ሳላይሽ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ጥበቃ የነበሩት አቶ ስዩም ካሴን #በጥይት_በመምታት ገድሏል። አቶ ከበደ ዓለማየሁ የተባሉ ነዋሪን ከመኖሪያ ቤታቸው አስወጥተው ከወሰዷቸው በኋላ በአካባቢው ጫካ አስክሬናቸው ወድቆ ተገኝቷል።

- ጥር 13 ቀን 2016 ዓ/ም ከጠዋት 2 ሰዓት ጀምሮ ማንነታቸው ያልታወቀ ታጣቂዎች በምዕራብ ጉጂ ዞን፣ ገላና አባያ ወረዳ ኤርገንሳ ቀበሌ ለሚኖሩ ነዋሪዎች የኩፍኝ በሽታ ክትባት ለመስጠት በመጓዝ ላይ በነበሩ ሠራተኞች ላይ በፈጸሙት ጥቃት የገላና አባያ ወረዳ አስተዳደር ጤና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊን ጨምሮ ሁለት ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል። እንዲሁም 3 ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

- ከየካቲት 28 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ በአማራ ክልል ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ #የአማራ_ታጣቂ_ቡድኖች የኦሮሚያ ክልል ፤ በሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ በሚገኙ አዋሳኝ ቀበሌዎች በሲቪል ሰዎች ላይ #በተከታታይ በፈጸሟቸው ጥቃቶች ፦
➡️ 25 ሲቪል ሰዎችን ገድለዋል ፤ 
➡️ 4 ሲቪል ሰዎች ላይ የአካል ጉዳትን አድርሰዋል
➡️ ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ ሲቪል (ሰላማዊ) ሰዎችን #አግተው ወስደዋል። በታጣቂዎቹ በተፈጸመ ጥቃት በርካታ የመኖሪያ ቤቶች ተቃጥለዋል።

- በሰሜን ሸዋ ዞን ፤ ደራ ወረዳ የሚንቀሳቀሱ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (በተለምዶው “ ኦነግ ሸኔ ”) ታጣቂዎች ከኅዳር ወር 2016 ዓ/ም ጀምሮ በወረዳው በሚገኙ የተለያዩ ቀበሌዎች በሲቪል ሰዎች ላይ በፈጸሟቸው ጥቃቶች ፦
➡️ 15 ሲቪል (ሰላማዊ) ሰዎች #ተገድለዋል
➡️ ቁጥራቸው ለጊዜው በትክክል ያልታወቀ በርካታ ነዋሪዎችን #አግተው_ወስደዋል
➡️ በርካታ የቀንድ ከብቶችን ዘርፈዋል
➡️ መኖሪያ ቤቶችን አቃጥለዋል።

- መጋቢት 1/2016 ዓ.ም. በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ ስልካምባ ከተማ ላይ የኦሮሞ ነጸነት ሰራዊት (በተለምዶ “ #ኦነግ_ሸኔ ”) ታጣቂዎች በከፈቱት ጥቃት የወረዳው አበዪ ሄቤን ቀበሌ ነዋሪ የነበሩ አቶ ሹመቴ ፋርስ እና ወ/ሮ ተቀባ አበጋዝ የተባሉ አረጋዊያን በመኖሪያ ቤቶቻቸው ፊት ለፊት ተገድለዋል።

- መጋቢት 16/2016 ዓ/ም ከምሽቱ 3፡00 እስከ 5፡00 ባሉት ሰዓታት ማንነታቸው ያልታወቀ የታጠቁ ቡድኖች በምዕራብ አርሲ ዞን ዶዶላ ከተማ 02 ቀበሌ ውስጥ 7 ሰዎችን ተኩሰው መግደላቸውን ለማወቅ ተችሏል። በዕለቱ በተፈጸመ ጥቃት የቀበሌው ነዋሪ የሆነ እና የምዕራብ አርሲ ሃገረ ስብከት የዶዶላ ደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የሆነ ግለሰብ ፣ ከባለቤቱ እና #ከ2_ልጆቹ ጋር በመኖሪያ ቤታቸው እያሉ እንዲሁም ሌላ አንድ ዲያቆን ከባለቤቱ እና ከእህቱ ጋር በመኖሪያ ቤታቸው መገደላቸውን ለማወቅ ተችሏል። 

- መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ/ም በዶዶላ ወረዳ በደነባ ቀበሌ በግምት ከምሽቱ 5፡00 ሰዓት አካባቢ ላይ 4 የቀበሌው ነዋሪዎች ማንነታቸው ባልታወቀ የታጠቁ ሰዎች/ቡድኖች በጥይት ተመተው ሲገደሉ 5 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን ለማወቅ ተችሏል።

- የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ( በተለምዶ “ #ኦነግ_ሸኔ ” ) በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን፣ አመያ ወረዳ ውስጥ “ የመንግሥት ሠራተኞች እና የመንግሥት ጸጥታ ኃይል አባላት ቤተሰቦች ናችሁ ” በሚል ወይም “ለመንግሥት አካላት ትብብር አድርጋችኋል” በሚል ምክንያት በወረዳው በተለያዩ ቀበሌዎች በየካቲት እና ሚያዝያ ወራት በፈጸማቸው ተከታታይ ጥቃቶች በሲቪል ሰዎች ላይ ግድያ፣ አካል ጉዳት፣ እገታ፣ ንብረት ውድመት እና ዘረፋ ፈጽሟል።

ለምሳሌ ፦

👉 በወረዳው አቡዬ ጀብላል ቀበሌ የካቲት 7/ 2016 ዓ.ም. በፈጸመው ጥቃት 11 ሲቪል ሰዎችን ገድሏል፤ መኖሪያ ቤቶችንና ሞተር ብስክሌቶችን አቃጥሏል፤ የቀንድ ከብቶችን ዘርፏል።

👉 መጋቢት 27/2016 ዓ.ም. በወረዳው ቆታ ከተማ ላይ በፈጸመው ጥቃት 31 ሲቪል ሰዎችን ገድሏል፣ 3 ሲቪል ሰዎችን አቁስሏል፣ የቀንድ ከብቶችንና ሌሎች ንብረቶችን ዘርፏል እንዲሁም ንብረቶችን አቃጥሏል።

👉 ሚያዝያ 8/2016 ዓ/ም በደራ ቲርቲሪ ቀበሌ ላይ ታጣቂ ቡድኑ በፈጸመው ጥቃት 2 ሲቪል ሰዎችን ገድሏል ፣ ከ100 በላይ የተለያዩ የቀንድ ከብቶች ዘርፏል።

👉 በሚያዝያ 13/2016 ዓ/ም በጎምንቦሬ አሊይ ቀበሌ 36 የቀንድ ከብቶችንና 3 የሞቶር ብስክሌት ዘርፏል።

#Oromia #Ethiopia #EHRC

@tikvahethiopia
🇪🇹 #NationalDialogue 🇪🇹

የመጅሊሱ ቅሬታ ምንድነው ?

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ህዝበ ሙስሊሙ ሀገራዊ ምክክሩን እጅግ እንደሚደግፈው ነገር ግን ከምክክሩ ተሳታፊዎች ጋር በተያያዘ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ እንዳልተሰጠው በዚህም ምክንያት ቅሬታ እንዳደረበት ገልጿል።

ም/ቤቱ ያደረበት ቅሬታ " በምክክሩ ላይ የሙስሊሞች ውክልና አነስተኛ ነው ፤ ይህ ደግሞ በምክክር ውጤቱ ላይ ተጽእኖ እንዳያሳድር ስጋት አለኝ " የሚል ነው።

" #ከወረዳ እስከ #ክልል ድረስ የሚሳተፉት ተወካይ ሙስሊሞች ቁጥር እጅግ አነስተኛ ነው " የሚለው ም/ቤቱ ፥ " እንደ ሙስሊም በጋራ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ መግባባት ላይ ለመድረስ በቂ ተወካዮች አልተወከሉም " ብሏል።

የምክር ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ከማል ሀሩን ምን አሉ ? (ለሃሩን ሚዲያ)

- ሙስሊሙ ከምንም በላይ ምክክሩን ይፈልገዋል።

- ሙስሊሙ የቆዩ ችግሮች ስላሉበት ይሄን ምክክር እንዲሳካ በጣም ከሚደግፉት ማህበረሰብ ክፍሎች ዋነኛው ነው።

- ከሌሎች እምነቶች ሲነጻጸር ሙስሊሙ ማህበረሰብ ለዚህ ምክክር ያለው ድጋፍ ፈጽሞ ሊወዳደር የሚችል አይደለም። ሙስሊሙ ይህንን ምክክር የሚፈልገው ያልተመለሱለት ጥያቄዎቹ እንዲመለሱለት ነው።

- ተወካዮች ከታች ሲመረጡ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ተሳታፊ እንዲሆን ያስፈልጋል። ኮሚሽኑም check and balance ማድረግ አለበት ፤ በትክክልም የዚህን ማህበረሰብ ጥያቄዎች የሚያነሱ ተወካዮች ተወክለዋል የሚለውን።

- የተሳታፊዎች ልየታ ከታች ጀምሮ ሲመጣ በትክክል ሁሉም ማህበረሰብ መወከሉን ማረጋገጥ ይገባል። ኮሚሽኑም ከሌሎች እምነቶች ጋር balance የማድረግ ስራ ይጠበቅበታል።

- ተሳትፎ ላይ ቁጥሩ የተዛባ ከሆነ፣ በጣም አነስተኛ ከሆነ ቅሬታ ስለሚያስከትል ጥንቃቄ ያስፈልጋል።

- ኮሚሽኑ አካሄድ የነበረው ሲቪል ማህበራት፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ መምህራን ፣ አርብቶ አደሮች፣ እድሮች፣ የፍትህ አካላት፣ የመንግሥት ሰራተኞች፣ ፖለቲከኞች የያዘ ነው በሃይማኖት መልክ ግን የቀረበ ነገር የለም። እነዚህ አደረጃጀቶች ምን ያህል ሙስሊሙ ተሳትፎ አለው ? የሚለው ያሳስበናል፤ ስጋትም አድሮብናል።

- የተነሱ ጥያቄዎችን እና ያሉትን ስጋቶች በተደጋጋሚ ለኮሚሽኑ ቀርበው የጋራ ኮሚቴ ጭምር እንዲቋቋም መረጃዎችም እንዲሰጡ ተጠይቆ በተለያየ ምክንያት ሊሳካ አልቻለም።

- ውይይቶች አድርገናል በተደጋጋሚ ፤ በውጤቱ ላይ የሙስሊሙን ተሳትፎ የሚያሳዩ መረጃዎች (ዳታ) ማግኘት አልተቻለንም።

- እንደ አጀንዳ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ጥያቄዎች በ9 አጀንዳዎች ተካተው ፣ በ47 ጥያቄ ቀርቦ የካቲት 2 ላይ ለኮሚሽኑ ቀርቧል። መጨረሻ ላይ ኮሚሽኑ ያንን የማስፈጸም ኃላፊት አለበት።

- ታች ያለው የማህበረሰቡ ውክልና በተሻለ ሁኔታ ሁሉ የሃይማኖት ተቋማት ባገናዘበ፣ ሃይማኖት ተቋማትን balanced ባደረገ ሁኔታ መታየት አለበት ቁጥሩ። ለምሳሌ ፦ ከ12 ሺህ ምን ያህል ሙስሊም ተካቷል ፤ ከአዲስ አበባም ከ2500 ተሳታፊ ካለ ምን ያህል ሙስሊም ተሳታፊ ነው ? የሚለው ነው የማህበረሰቡ ጥያቄ።

- እኛ በቂ መረጃዎች የሉንም ለማህበረሰቡ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት አስቸጋሪ ነው። በአንዳንድ ሁኔታ ስናጣራ በጣም አነስተኛ ቁጥር ያለበት ስለሆነ የተሻለ ውጤት እንዲገኝ ጥያቄ በማያስነሳ መንገድ እንዲሄድ ማድረግ ይገባል።

- የሙስሊሙ ማህበረሰብ ተሳታፊ ቁጥር አነስተኛ ከሆነ የሚቀርበው አጀንዳ ይቀራል ፤ ያ ደግሞ እጅጉን ያሳስበናል።

- በእኛ በኩል አሁንም ምላሽ እየጠበቅን ነው።

#EthiopianMuslims
#HarunMedia
#NationalDialogue

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🇪🇹 #NationalDialogue 🇪🇹 የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከግንቦት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ የምክክር ምዕራፉን ይጀምራል። ለ7 ቀናት ያህል በሚቆየው የአዲስ አበባው ምክክር ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከ2 ሺህ በላይ ሰዎች እንደሚሳተፉ ኮሚሽኑ ገልጿል። በምክክሩ የውይይት የአጀንዳ ሀሳቦችን የሚያመጡ ለምክክሩ የሚቀርቡ ተሳታፊዎች ሲሆኑ ፤ እነዚሁ ተሳታፊዎች በተስማሙባቸው…
🇪🇹 #NationalDialogue 🇪🇹

ከነገ ግንቦት 21 ጀምሮ ለ7 ቀናት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ የምክክር ምዕራፉን ይጀምራል። ከ2 ሺህ በላይ ሰዎችም ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃን።

የስብሰባው ሥርዓቶች ምንድናቸው ?

1. ማንኛውም ተሳታፊ #በነጻነት ሀሳቡን የመግለጽ መብት አለው። ሆኖም ተሳታፊዎች ከጥላቻ፣ ከአዋራጅ እና ከተንኳሽ ንግግሮችመቆጠብ፤

2. በምክክሩ ጊዜ መደማመጥን ከሚያውኩ፣ ሁከትን ከሚፈጥሩ እና መረጋጋትን ከሚነፍጉ ድርጊቶች እና ንግግሮች መቆጠብ፤

3. በጽሁፍ፣ ምልክት ወይም ድምጽ የጎንዮሽ ንግግር አለማድረግ እና ከተሳታፊዎች የሚቀርበውን ሃሳብ በአክብሮትና በጥሞና ማዳመጥ፤

4. እያንዳንዱ የምክክሩ ተሳታፊ የሚሰጠውን ሃሳብና የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ማክበር፣ በቅንነትና በታጋሽነት ማዳመጥ ፤

5. ሌላው ተሳታፊ ያቀረበውን ሃሳብ የመደገፍ ወይም የመቃወም ሁኔታ ሲኖር የሌሎች ተሳታፊዎችን መብት በሚያከብር መልኩ ማቅረብ፣

6. ተሳታፊው እድል ተሰጥቶት ሃሳቡን በመግለጽ ሂደት ላይ እያለ በማንኛውም ሁኔታ ያለማቋረጥ፤

7. የሰውን ክብር ከሚነኩ ነቀፌታዎች ፣ ዘለፋዎች ፣ ስብዕናን ከሚነኩ ንግግሮችና ድርጊቶች መቆጠብ፤

8. ሰዎች በሚያቀርቡት ሃሳብ እንዲሁም አስተሳሰብ ባይስማሙ እንኳ ሃሳባቸውን እና አስተሳሰባቸውን ማክበር፤

9. የሚሰጠውን ሀሳብ በቅን ልቦና ላይ የተመሠረተ ሆኖ ከውይይቱ  አጀንዳ ጋር አግባብነት ያለው አጭር፣ ግልጽ ያልተደጋገመ እና የተፈቀደውን ጊዜ ባከበረ መልኩ መግለጽ፤

10. በሂደቱ ላይ ግልጽ ያልሆኑ ጉዳዮች ሲያጋጥሙ ማብራሪያ እንዲሰጥ መጠየቅ ናቸው፡፡

#የኢትዮጵያ_ሀገራዊ_ምክክር_ኮሚሽን
#NationalDialogue

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

ከሰሞኑን በአዲስ አበባ ከተማ መኪና ይዘው የነበሩ ሁለት ወጣቶች ከቤት እንደወጡ እስካሁን አልተመለሱም።

የመጀመሪያው ዳዊት አስናቀ ይባላል። 

ተወልዶ ያደገዉ አዲስ አበባ ከተማ ነው። ከ4 ቀናት በፊት የጠፋ እሰካሁን ድረስ እንዳልተመለሰ ታውቋል።

ዳዊት ኮድ 2-B65248 ኮሮላ መኪና እያሽከረከረ ነበር።

ስልኩም አይሰራም ፤ በምን ሁኔታ ላይም እንዳለ አይታወቅም ብለዋል ቤተሰቦች።

ዳዊት ያለበትን የምታውቁ ወይም ደግሞ ያያችሁት ካላችሁ ቤተሠቦቹ  ጭንቀት ላይ ናቸውና በስልክ ቁጥር 0918706526 / 0913412564 / 0911609294 በመደወል አሳውቋቸው።

ሌላኛው ፥ እዮብ አንዳርጌ ይባላል።

እዮብ በ14/9/2016 ከቤት እንደወጣ እስካሁን አልተመለሰም።

በወቅቱ ኮድ 1 አ/አ 30805 ታርጋ ያላት ቢጫ ያሪስ ይዞ ነበር።

ፈላጊ ቤተሰቦች እዮብን ያየ ወይም ያለበትን የሚያውቅ በስልክ ቁጥር  0913577424 / 0911116275 / 0910479302 / 0945576477 በመደወል እንዲያሳውቃቸው ተማጽነዋል።

@tikvahethiopia
2024/05/29 00:36:22
Back to Top
HTML Embed Code: