Telegram Web Link
👉‹ግብረ አውናን» ምንድር ነው?

ከዚህ በላይ ወጣቶች በጠለቀ እንቅልፍ ላይ ሳሉ በሚያልሙበት ጊዜ ስለሚከሰት የ«ፈሳሽ ነገር» ከሰውነት መውጣት በሚገባ ተብራርቷል፡፡ ነገር ግን በወጣትነት ወራት ስለ አባለ ዘር ሥራና ውጤት ለማውቅ ካለ ጉጉትና ለተቃራኒ ፆታ የሚኖር ዝንባሌ
መጨመሩ የተነሣ ከእንቅልፍ ውጭ ንቁ በሆኑበትም ሰዓት በስሜት እስኪረኩ ድረስ የፆታ ብልቶቻቸውን በመነካካትና በማሽሽት ለመደሰት የሚሞክሩ ወጣቶች እሉ፡፡ ይህ ድርጊት በአብዛኛው በስውርና በግል ስለሚፈጸም በዚህ መጥፎ ልማድ የተለከፉት ወጣቶች መካሪ ሳያገኙ ልማዳቸው እብሮኣቸው ያድግና ለወደፊት ኑሮኣቸው ክባድ እንቅፋት ይሆናል፡፡
እግዚኣብሔር ለምሕረትና ለመቅሠፍት ያዘጋጃቸው ልዩ ልዩ ግዳጆችን የሚፈጽሙ መላእክት እንዳሉት ሁሉ ሰይጣንም ሰውን በልዩ ልዩ መንገድ እንዲፈትኑ ድርሻ ሰጥቶ ያዘጋጃቸው አጋንንት እሉት፡፡ ሮሜ9 ፡ 22 ከእነርሱም ውስጥ አንዱ «ሰይጣነ ዝሙት» ነው::
ሰይጣነ ዝሙት የሰው ልጆችን የሚፈትንበት መንገድ ረቂቅና ልዩ ልዩ ነው:: ኣንዳንዶቹ የፈተና ስልቶች ፈጽሞ ከዝሙት ጋር ምንም ግንኙነት ያላቸው አይመስሉም:: ፍጻሜያቸውን ከልብ ያስተዋል ሰው ግን ረቂቅና ቀጥተኛ ዝምድና እንዳላቸው ለመረዳት ይችላል፡፡ ዖር የለመዱ (የሰይጣንን የፈተና ስልት በደንብ ለይተው ያውቁ፡) አበው ቅዱሳን ግን ሽንገላ የሃሞላበትን የሰይጣንን የፈተና አሸንነላ ምን እንደሚመስል መጪ ትውልድ እንዲያውቀው በሕይወታቸው ያዮትንና መንፈስ ቅዱስ ያቀበላቸውን ጽፈው አስቀምጠዋል፡፡

( ለምሳሌ፡- ሰይጣነ ዝሙት የሰውን ልጅ ወደ ዝሙት ተግባር ከሚስብባቸው መንገዶች አንዱና ዋነኛው ሂሥ ነው:: ጓሂረሥ ማለት ማሻሽት፣ መነካካት፣ መዳበስ ማለት ነው::

· ነቢዩ ሕዝቅኤል «ወከዐዉ ዝንየቶሙ ዲቤሃ» ማለትም «ግልሙትናቸውንም አፍስሰውባት ነበር» በማለት እንደተናገረው ለዘር የደረሱ ወንዶች ከሴቶች ጋር ሲላፉና ሲዳሩ ሩካቤ ሳይፈጽሙ ዘራቸው የሚፈስበት ጊዜ አለ፡፡ ሕዝ23፥8

ይህንን ድርጊት እንደ ተድላ በመቁጠር ብዙ ወጣቶች ሆን ብለው ያደርጉታል፡፡
በቅዱስ መጽሐፍ «የድንግልናዋንም ጡቶች ዳብሰው ነበር» እንደ ተባለው ቦታ ( ሳይመርጡና ሰው ሳይለዩ የሴት ልጅን ገላ በመዳበስ «ግልሙትናን ማፍሰስ» እንዴት ያሳፍራል? ሕዝ23: 3፤ 23 ፥8

ይህ መጥፎ ልማድ የተጣባቸው ሰዎች ግርግርና በሰው ብዛት የታጨናነቀ ስፍሪ የሴቶችን ገላ እንደ ሐሳባቸው ለመነካካት ምቹ ሁኔታን ይፈጥርላቸዋል፡፡ ከእነዚህ ሰዎች መካከል አንዳንዶቹ የሥራቸውን አስነዋሪነት ስለሚያውቁ እንዳይነቀፉ ልዩ ልዩ ዘዴ በመፍጠር የተካኑ ናቸው፡፡

👉 ለምሳሌ፡- አንዳንዶቹ ምንም ሳያውቁና በእንቅልፍ ልባቸው ያደረጉት ለማስመሰል እንደ ታኛ ሰው እየተገላበጡና እያንኳረፉ በልዩ ልዩ አጋጣማ. አወገባቸው ለመተኛት የተገደደችውን ሴት ጎላ ሰደባብሱ ያድራሉ፡፡ ይህ ድርጊት ያለ ሩካቤ - የወንድ ዘር የትም ከሚፈስባቸው ሕገ ወጥ መንገዶች መካከል አንዱ ነው፡፡

👉ሌሎች ደግሞ በአድካሚ ጉዞ ወቅት ደጋፊ፣ በሕመም ጊዜ | ደግዓሞ አስታማሚ፣ ... ወዘተ እየመሰለ ከወልድ ጋራ ተዛምዶ ያላቸውን እካላት ለመደባበስ የሚሞክሩ ሰዎች ናቸው::

እነዚህ ሰዎች ውጫቸውን ላየ አዛኝን ሌላውን ለመርዳት የሚፋጠኑ ይመስላሉ። ሰውን መርዳት ባልከፋ ነበር፡፡ ነገር ግን ችግሩ ወንዶቹ ይህን በሚያደርጉበት ጊዜ ልባቸው በፍትወት እሳት እንደ ሰም እየቀለጠና አባለ በራቸው እየታለበ መሆኑ ነው:: ሰውን ለማርዳት የሚፋጠኑትም ፍትወታቸው እስክትሟላላቸው ድረስ ብቻ ይሆናል፡፡

_👉አንዳንዶች ደግሞ እነርሱ ለመነካካት ፈጸሞ እንዳላሰቡ ነገር ግን የተፈጠረው ችግር እንዲጋፉ ወይም እንዲገፋፉ እንዳደረጋቸው ለማስመሰል ይጥራሉ:: ይህም የሚሆነው በአብዛኛው ሕዝባዊ ስብሰባዎች በሚደረጉባቸው ዕለታትና መጨናነቅ ሰሚኖርባቸው ስፍራዎች ነው::

👉ለምሳሌ፡- እንደ ጥምቀትና መስቀል ያሉ ሕዝብ የሚበዛባቸውን ዕለታት መጥቀስ ይቻላል፡፡ ያለ አግባብ በርካታ ሰዎችን የሚጭኑ የሀገራችንን የሕዝብ ማመላለሻዎችንም (አውቶና ሚኒ ባስስ) እንደ ተጨማሪ ማስረጃ መጥቀስ ይቻላል፡፡
ስለዚህ ጉዳይ በሕዝብ ማመላለሻ መኪና ውስጥ ሳለ አጠገባቸው በቆመ ጎረምሳ እንደ ቆዳ የለፉ ሴቶች ምስክርነት በሰጠ የተሻለ ነበር፡፡ ለካ በመኪና ውስጥና በተጨናነቀ ቦታ ሁሉ መጠንቀቅ የሚገባው ኪስን ከማበረብር ሌባ ብቻ አይደለም:: ታዲያ ሌላ ምን እንጠንቀቅ የሚል ጠያቂ ካለም መልሱ ሕዋሳትን የሚያባብስ ሴሰኛ ነዋ የሚል ነው!
ሌሉች ደግሞ ውጫዊ ይዘታቸው ሲታይ በዚህ ዓይነት ዘርን በማፍሰስ የመርካት ተግባር የማይጠረጠሩ ዓይነት ናቸው::

👉 ለምሳሌ.፡ ዕድሜያቸው በጣም የገፋ፣ በአስተሳሰብ የበሰሉ፣ በአለባበስና በምጣኔ ህብት የተከበሩ የሚመስሉ ወይም እስተማሪ የሆነ መንፈሳዊ አቋምና
መልካም ስም የያዙ ናቸው:: እንደዚህ ያሉ ሰዎች የሌሉችን ሕዋሳት ለመነካካት የሚያደርጉት ጥረት «ይህን አስበው እይደለም! » እየተባለ ብዙ ጊዜ በበጎ ይተረጎምላቸዋል፡፡ ይህም እነርሱን ወደ ባሰ የጥፋት ዐዘቅት ይመራቸዋል፡፡

ስለዚህ ክርስቲያኖች ሁሉ ይህን ተገንዝበው አጥፊዎች እንዲታረሙ ከማድረግ ጋራ የራሳቸውን ሕይወት በንጽሕና መጠበቅ አለባቸው:: .

ዘርን በማፍሰስ የመርካት ልማድ ሩካቤን ከመፈጸም በላይ የሚያስደስታቸው ስዎች ሌላው ዝንባሌያቸው ታዳጊ ሕጻናትን ማባለግ ነው:: በቅጡ ጡት ያላጎጠጎጡ ሕጻናትም እንኳን የእነዚህ ሰዎች የጥቃት ሰለባ ናቸው:: ሕጻናቱ እነዚህ ሰዎች ምን እያደረጉ እንደሆነ አያስተውሉትም፣ አያውቁትም፣ ቢያውቁትም አይቃወሟቸውም እይከሷቸውምም:: ወይም በትንሽ ነገር በቀላሉ ሊባበሉና ሊታለሉላቸው ይችላሉ፡፡ ስለዚህ እንደዚህ ያሉ ሰዎች እንደ መላእክት ንጹሐን የሆኑ ሕጻናትን ሕይወት ያበላሻሉ፡፡ ሕጻናቱን ያጫወቱና ያሳሳቁ በመምሰል ሲታገሉና ሲላፉ በፍትወት እየተቃጠሉ : ልብሳቸውን በዘር ጭቃ የሚለውሱትን ወንዶች ቁጥር ቤት ይቁጠረው::

· ከላይ የተሰጠት ማስገንዘቢያዎች በማንም ሰው ቢሆን ያለ ኣግባብ እንዳንተማመን የሚረዱ ናቸው:: በተጨማሪም የምንውልበትን፣ የምንጓዝበትንና የምናድርበትን ቦታ ዙሪያውን እየቃኘን ወደ ዝሙት የሚያመሩ ምክንያቶችን ከወዲሁ አውቀን እንድንሽሽ ያግዙናል፡፡ ሌላው ደግሞ ሕጻናቶቻችንን በጥንቃቄ እንድንይዝ የሚያደርገን ሲሆኑ በዚህ መጥፎ ተግባር የተመረዙትን ሰዎች ደግሞ ሥራቸው በብዙዎች ዘንድ መገለጡን አውቀው አደብ እንዲገዙ ሊያደርጓቸው ይችላሉ፡፡
ሰይጣነ ዝሙት እንድን ሰው ያልተፈቀደለትን........

ይቀጥላል .......

@Tserezmut
@Tserezmut
@Tserezmut
ከአንድ ወዳጄ የተላከልኝ ትምህርት አዘል ፅሁፍ ነው። ሀይማኖትን መሠረት ያደረገ ትምህርት ነው ለሁላችንም ይጠቅመናል በማለት ልለቅላችሁ ወድጃለሁ...!


ሥርዐት አልባ ሩካቤ የሚባሉት የትኞቹ ናቸው?

/በሩካቤ ወቅት የማይፈጸሙ ድርጊቶች/

/ይህን ጽሑፍ ስታነቡ ‹‹ወይ ቄሱ ጉድ ነው›› እያላችሁ በመገረም ሳይሆን እራስን ከማረም እና ትውልድን ከማዳንና ሥርዓትን ከማሳወቅ አንጻር ተገንዝባችሁ አንብቡ፡፡ ነገሮችን በመንፈሳዊ ጨዋነት በግልጽ ባለማስተማራችን ዛሬ ዋጋ እያስከፈለን ነው/

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ሼር በማድረግ ትውልድና ይታደጉ ሥርዓትን አሳውቁ

ተወዳጆች ሆይ መንፈሳዊ ሰው ማንኛውንም ነገር ሥርዐትና አግባብ ባለው መልኩ ነው የሚከውነው፡፡ ሥርዐቱም በራስ ላይ ቀንበር ከመጫን አንጻር ሳይሆን ከመንፈሳዊ ሥነ-ምግባር ውጤት አንጻር ነው፡ ስለዚህ መንፈሳዊ ሰው እንኳን ለከበረው ለሩካቤ ሥጋ ቀርቶ ለአለባበሱ፣ ለአመጋገቡ፣ ለአነጋገሩ ሥርዐትና መንፈሳዊ መልክ ይኖረዋል፡፡

በተለይ ምንም መንፈሳዊ ብንሆንም በዘመናዊው ዓለም በመኖራችን የሩካቤ ሥጋ አፈጻጸም መልክና ይዘቱም እየተቀየረ ለሥጋ እርካታም እየተባለ ዘመን አመጣሹንና የምዕራባውያንን ሥርዐት አልበኝነትን በመመልከትና በመከተል እንዲሁም የዘመንን እየመሰለን ሩካቤ ሥጋችን ሥርዐት አጥቷል፡፡ ሩካቤን ሥርዐት ባለው መልኩ መፈጸም ማለት ለተጣማሪያችን ክብራችንን የመግለጽ ሒደት ነው፡፡ ዛሬ ዛሬ በዓለማዊ እሳቤ ማኅበረሰብን ለማነጽ ሳይሆን ገንዘብን ለማግኘት ሲባል የታተሙት ወሲብ ነክ መጻሕፍት የሰውን ቀልብ እየገዙ፣ ትውልድን እያደነዘዙ ናቸው፡፡ እነዚህ መጻሕፍት በብዙ የሚቆጠሩ የሩካቤ አፈጻጸም ዓይነቶችን በመያዛቸው፣ የተፈቀደና ያልተፈቀደን ባለመለየታቸው፣ ሰዉ ግራ እየተጋባ ያልለመደውንና ያላወቀውን የሩካቤ ዓይነት እንዲያውቅና እንዲተገብር እየተገደደ ስለሆነ የዚህ ገዳፋ ለመንፈሳዊያንም እንዳይተርፍ፣ ከተረፈም ሕጋዊ ያልሆነውን ለማሳወቅ እና ሕጋዊውን ለማስጠበቅ ስንል እንመለከታለን፡፡

ሴቶች በተለይም በወንዶች አላስፈላጊ ፍላጐት ሩካቤው በማፈንገጡ የአፈጻጸም ሥርዐቱ ወጣ በማለቱ ሩካቤ ሥጋ ክብሩንና ንጽሕናውን እንዳያጣ፣ እንደ እንስሳም እንዳንሆን ከመንፈሳዊነት አንጻር እንዴትና በምን መልኩ መፈጸም አለብን የሚለውን ዘርዘር አድርገን እናያለን፡፡ በተለይ በአልጋ የምንፈጽመው እግዚአብሔር ስለሚያየው ራሳችንን ከማስተካከልና አዲስ ተጋቢዎችን ሥርዐተ ሩካቤን ከማሳወቅ አንጻር ያለ ምንተ እፍረት አቀርበዋለሁ፡፡ ምክንያቱም እኛ ካህናት በተለይ ለወጣት ንስሐ ስንሰጥ ደጋግመን የምንሰማው አንዱ ይህ ያፈነገጠ ተራክቦ ነውና፡፡

ሥርዐት አልባ ሩካቤ የሚባሉት የትኞቹ ናቸው?
/በሩካቤ ወቅት የማይፈጸሙ ድርጊቶች/

1/ በኋላ የሚፈጸም ሩካቤ፦ ሩካቤን በኋላ በኩል መፈጸም እንስሳነት ከመሆኑ ባሻገር ለተጣማሪ ክብርን ሳይሆን ውርደትና ንቀትን የምንገልጽበት ነው፡፡ ሰውን እንደ አንስሳ አድርጐ ሩካቤ የመፈጸም መንፈሳዊ ሥርዐት አልበኝነት ከመሆኑም ባሻገር ከእግዚአብሔር ዘንድም ቁጣን ያመጣል፣ ያልተባረከ ትውልድን ይፈጥራል፡፡ እንስሳት በኋላ በኩል የሚፈጽሙት አራት እግር ስላላቸውና ተፈጥሮአቸው በኋላ በኩል ስለሚያመቻቸው ነው፡፡ እኛ የሰው ልጆች ሩካቤ ሥጋን በኋላ በኩል ፈጸምን ማለት ባለ ሁለት እግር እንስሳት ሆንን ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ይህ ተግባር ጸያፍ ስለሆነ ልንፈጽመው ሳይሆን ልናስበው አይገባም፡፡

2/ በቁም የሚፈጸም ሩካቤ ፦ የሰው ልጅ ብዙ ነገሮችን ከተፈጥሮ፣ ከእንስሳት ከአዕዋፋት፣ ከዱር አራዊት ወዘተ የተማራቸው፣ በሕይወቱ የተገበራቸው መልካም ነገሮች ቢኖሩትም እንደ ሩካቤ ያሉትን ማለትም ሩካቤን ቆሞ መፈጸምን ከእንስሳት የተመለከተው ሥርዐት አልባ ሩካቤ ነው፡፡ እንስሳት ሩካቤን በቁም የሚፈጽሙት ተፈጥሮአቸው ተኝተው መፈጸም ስለማያስችላቸው ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ሩካቤን በቁም ስለመፈጸም የተጻፈበት ቦታ የለም፡፡ ይህ ሥርዐት አልባ ወረርሽን ምዕራባውያን እንደ ሸቀጥ በየፊልሙና በማኅበራዊ ድረ ገጽ እያስተማሩን ከተፈጥሮ እንድናፈነግጥ ያደረጉት ነው፡፡ የሰውና የእንስሳን የሩካቤን ሥርዐት በውልደታቸው ብናይ መልካም ነው፡፡ ሰው እንደ ተወለደ መቆም አይችልም፡፡ እንስሳት አንደ ተወለዱ መተኛት ሳይሆን ከደቂቃዎች በኋላ መቆም ይጀምራሉ፡፡ ይህ ተፈጥሮአቸው ሩካቤያቸውንም ያሳየናል፡፡ እንስሳት ሩካቤያቸው በቁም ስለሆነ ሲወለዱ መቆም ይጀምራሉ፡፡ ሰዎች ሩካቤያቸው ተኝተው ስለሆነ ሲወለዱ ወድያው መቆም ሳይሆን ለወራት ይተኛሉ፡፡ ይህ የተፈጥሮ ሥርዐታቸው ሩካቤያቸውን ያሳየናል፡፡ ስለዚህ ተፈጥሮአችን ባልሆነ መንገድ ሩካቤን መፈጸም ትርፉ እርግማንን የራስ ለማድረግ ማሳደድ እና የእርግማንን ትውልድ መውለድ ነው፡፡

እግዚአብሔር ከአዳም አንዲት አጥንት ክብርት ሔዋንን ሲፈጥራት አዳምን አቁሞት ሳይሆን በክቡድ እንቅልፍ አስተኝቶት ነው፡፡ የእርሷም መፈጠር ከቆመ ሰውነት ሳይሆን መሬት ከተኛው አዳም መገኘቷ ወደ ፊት ሥርዐተ ሩካቤያቸው በመቆም ሳይሆን በመተኛት የሚፈጸም መሆኑን እንደ ሥርዐት ጭምር ሊሠራላቸው መሆኑን ሊያሳውቃቸው ፈልጐ ነው፡፡ ስለዚህ ሩካቤን በቁም መፈጸም ማለት ከእንስሳ ጋር በጸያፍ ምግባር መወዳጀት ስለሚሆን በሥርዐት መፈጸሙ መባረክን ያተርፋል፡፡

3/ ልቅ ወሲብ ፦ መቼም ልቅ ወሲብ ብዬ ስጽፍ አንባቢዎቼ ትረዱኛላችሁ ብዬ አስባለሁ፡፡ በተለይ በፊልሞች የታዩትን፣ በልብ ወለድ የተነበቡትን፣ ከሰው የሰሙትን ሁሉ በትዳር ለመሞከር ከዛም ባለፈ መፈጸም እንስሳ መሆንና ከእንስሳም ማነስ ነው፡፡ በየትኛውም መንገድ ሩካቤያችን መንፈሳዊ ጨዋነትን የተላበሰ፣ የተፈጥሮ ሥርዓታችንን ያልጣሰ መሆን አለበት፡፡ ልቅ ወሲብን በትዳር ሕይወት ለመፈጸም መሞከር የከበረውን፣ የተቀደሰውን ሩካቤ ሥጋ መናቅና ማቃለል ነው፡፡ ስለዚህ በትዳራችን ልቅ ወሲብ በመፈጸም እግዚአብሔርን ብናስቆጣው እግዚአብሔር በቀጥታ ባይቀጣንም በልጅ ሊቀጣን ይችላል፡፡ ይህም የልቅ ወሲብ ተግባራችን፣ውጤታችን የሆኑ ልቅ እና ልብ አውልቅ እንዲሁም ጤናቸው፣ተፈጥሯቸው የተዛባ ልጆች ሊሰጠን ይችላል፡፡ እርግማንን በሚያመጣ ልቅ ወሲብ ተፀንሰው የሚወለዱት ልጆች ደዌ የያዛቸው፣በሽታ የተጫናቸው እና አጋንንት የተጣባቸው ልጆች ሊሆኑ ስለሚችሉ ለራሳችንና ለሚወለዱት ልጆች ስንል ሩካቤ ሥጋችን ሥርዐት ሊኖረው ይገባል፡፡

4/ በአፍ የሚፈጸም /Oral Sex/ ፦ ይህ ለመንፈሳዊ ሰው ብቻ ሳይሆን ሰው ለተባለው ሁሉ ጸያፍ ተግባር ነው፡፡ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም የከበረው አፍ ጸያፍ ተግባር መፈጸምያ መሆን የለበትም፡፡ ይህ ጸያፍ ተግባር ከሃይማኖት ብቻ ሳይሆን ከባሕልና ከትውፊት አንጻር አስነዋሪ ተግባር ነው፡፡ በተለይም የሴትን ልጅ ክብር የሚያጐድፍ ነው፡፡ አንዳንዶች በተለይ ወንዶች ከስንፈት ጋር በተያያዘ ኃፍረታቸው ለተረክቦ ዝግጁ ባለመሆኑ ለማነቃቂያነት፣ ስሜትን ለመቀስቀስ እንደዚህ ዓይነት ኢ-ሩካቤ መንገድን ይጠቀማሉ፡፡

ሌሎችም እርግዝናን ለመከላከልና እላፊና አስከፊ ደስታን ለማግኘት ሲሉ የስሜታቸውን ፍጻሜ በአፍ ወሲብ ለማግኘት ይሞክራሉ፡፡ እንኳን ለኃፍረታችን በቤታችን ያለው ድስት የራሱ የሆነ ግጣም አለው፡፡ እኛም ኃፍረታችንን ያለ ግጣሙ፣ እርስ በእርስ በማይስማሙ ቦታ ደስታ ለማግኘት መጣር፣ በራስ ላይ እርግማንን መከመር ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹ስለዚህ እግዚአብሔር ለሚያስነውር ምኞት አሳልፎ ሰጣቸው፤ ሴቶቻቸውም ለባሕርያቸ
ው የማይገባውን ሥራ ለባሕርያቸው በማይገባው ለወጡ›› ብሎ በግልጽ አስቀምጦልናል፡፡ /ሮሜ 1÷26/

በአፍ የሚፈጸም ስንል ወንዶቹ ቢያተገብሩትም ወንዶቹም በአ

ጸፋው የሴትን ልጅ ኃፍረት በመግለጥ አልባሌ ተግባር ይፈጽማሉ፡፡ የሴት ልጅ ኃፍረት እግዚአብሔር በማይታይ ቦታ ያስቀመጠው የምስጢር ገላ ስለሆነ ነው፡፡ አፈጣጠሩ ማንም በቀላሉ የማያይበት ቦታ መሆኑን ልብ ካልን የተደበቀን ገላ በነውር እንግለጠው ማለት አይቻልም፡፡ የምስጢር ገላ ባይሆን በቀላሉ ማንም የሚያይበት ቦታ ይሆን ነበር፡፡

ወዳጆቼ የሴትን ልጅ ክቡር ኃፍረት ቅዱስ ዮሐንስ ‹‹አፈ ወርቅ›› የተባለበት እና ክብርና ጸጋን ያገኘበት ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ‹‹አፈ ወርቅ›› የሚል ልዩ የክብር ስም ከእመቤታችን ያገኘው፤ ሰው የተጠየፈውን የናቀውን በተለይም የምስኪኗን ሴት ኃፍረት ለመዘባበት ሰዎች ባሰቡበት ሰዓት እርሱ አክብሮ በመሳሙ ነው፡፡

የሴት ልጅ ማሕፀን ጌታ የተወለደበት ቅዱሳን የተገኙበት ስለሆነ ለፍትወት ተብሎ ማነወር ሳይሆን ማክበር ነው የሚገባን፡፡ እኅቴ የአባትሽን ኃፍረት ለማየት እንደምታፍሪ ሁሉ የባልሽንም እፈሪ፡፡ ወንድሜ የእናትህን ኃፍረት ለማየት እንደምታፍር ሁሉ የሚስትህን ኃፍረት ለማየት እፈር፡፡ ወዳጆቼ የትኛውም ዓይነት የስንፈት ችግር ቢገጥመን ጸያፍ ተግባር ውስጥ በመግባት ከፈጣሪ ጋር መጋጨት የለብንም፡፡

5/ በእጅ የሚፈጸም ፦ ይህ ግለ ወሲብ ከልጅነት እስከ ወጣትነት ባለ እድሜ ውስጥ የሚጠናወት አስከፊ ተግባር ነው፡፡ ልዩ ልክፍትም ነው፡፡ ምክንያቱም ግለ ወሲብን ወንዶቹም ሴቶቹም ከለመዱት በቀላሉ ለመላቀቅ ይቸገራሉ፡፡ መንፈሳዊ ነን የሚሉትም በዚህ ችግር ክፉኛ ይጠቃሉ፡፡ ይህ ድርጊት እግዚአብሔር በኪነ ጥበቡ ካላስተወን በስተቀር ለመተው እንቸገራለን፡፡ አንዳንዱማ በምክር፣ በንስሐ፣ በጠበል መተው ይቸገራል፡፡ ድርጊቱም እንደ ኮሶ ሲጣባ፣ ግራ የሚያጋባ ሕይወት ውስጥ ይከተናል፡፡ ሌላ ችግሩ ግለ ወሲብን በእጁ መፈጸም የጀመረ ሰው ምናልባት ትቶት ወደ ትዳር ዓለም ውስጥ ሲገባ ትልቅ ችግር ይገጥመዋል፡፡ ኢ-ሩካቤን ለምዶ የተፈጥሮ የሆነው ሕጋዊ ሩካቤ እምብዛም ላያስደስተው ይችላል፡፡

ብዙ ወንዶችና ሴቶች በእጅ የሚፈጸም ግለ ወሲብን ከትዳር በፊት ይፈጽሙታል፡፡ ይህም በተግባር የሚፈጸመውን ሩካቤ በመፍራት በራሳቸው ሕይወት የግላቸውን ይፈጽማሉ፡፡ የግለ ወሲብ አንዱ ችግር ዘርን ያለ አግባብ ያለቦታው በማፍሰስ በኀጢአት ላይ ኀጢአትን መጨመር ነው፡፡ ወዳጄ ስንት ለሀገርና ለወገን ለቤተ ክርስቲያን የሚጠቅሙ ዘሮች ያለ ቦታቸው ወድቀዋል፡፡ አንተ ያለ ቦታው የምታፈሰው ዘር ምናልባት መካን ባለ ትዳሮች ልጃቸው እንዲሆን የሚመኙት ነው፡፡

ሴቶችም ደንግልናቸውን ከመጠበቅና ደፍረውም ተፈጥሮአዊ ሩካቤን ለመፈጸም ዝሙትን ከመፍራት አንጻር ግለ ወሲብን በአልጋቸው ላይ ይፈጽማሉ፡፡ ግን በእነዚህ ሁሉ ድርጊቶች የዝሙት መንፈስ ትልቅ ሚና ይኖረዋል፡፡ ዝሙትን አልፈጽምም ብለን የሥጋ ንጽሕናችንን ብንጠብቅም በግለ ወሲብ በመፈተን ንጽሕናችንን እናጐድላለን፡፡ ‹‹ሴቶቻቸውም ለባሕርያቸው የሚገባውን ሥራ ለባሕርያቸው በማይገባው ለወጡ›› የተባለው ይሄ ነው፡፡ /ሮሜ 1÷26/ ሰይጣን ምናልባትም ኀጢአት እስከ ማይመስል ድረስ እየመከረ በግለ ወሲብ እያሰከረ ትውልዱን ይጫወትበታል፡፡ ይህንን ድርጊት የሚፈጽሙትን ቅዱስ ዮሐንስ ‹‹እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ›› ብሎዋል፡፡ /ዮሐ 8÷44/ ስለዚህ ባል እና ሚስት ምንም እንኳን ሩካቤያቸው ሕጋዊ ቢሆንም በሕጋዊ ሩካቤያቸው ላይ ኢ-ሩካቤ የሆነው ግለ ወሲብ ደስታ ለማግኘት ብለው በፍጹም መፈጸም የለባቸውም፡፡ ባል እና ሚስት ያለ ሩካቤ ሥጋ አንዱ የአንዱን ኃፍረት በእጅ በመነካካት ደስታ ለማግኘት ቢጥሩ ይህ ግለ ወሲብ ነው፡፡ ይህን ድርጊት አንዳንዶች በእርግዝና ወራት እና በአራሥነት ወቅት ከሚስቶቻቸው ጋር ይፈጽሙታል፡፡ በተለይ ሩካቤ ሥጋን በሚከለክሉ ቀናት እና ምክንያት ለምሳሌ በአፅዋማት፣በእርግዝናና በአራሥነት ጊዜ በመሳሳም በሚመጣ ምርዐት በእጅ ወደ ሚፈፀም ግለ ወሲብ ሊገቡ ይችላሉ፡፡ ስለዚህ ከዚህ ድርጊት መጠንቀቅ ይገባቸዋል፡፡

6/ በግብረ ሰዶማዊ የሚፈጸም፡- ይህ በእግዚአብሔር የተጠላ ተግባርና ጸያፍ ሥራን ባለትዳሮች ‹‹ባልና ሚስት ነን፣ የራሴ ናት፣ የራሴ ነው›› በማለት መፈጸም አይገባቸውም፡፡ ተፈጥሮ ባልሆነና ባልተፈቀደልን መንገድ ሩካቤን መፈጸም በራሳችን ላይ መርገምን ከማምጣታችን በላይ በነፍሳችን ያስፈርድብናል፡፡ እግዚአብሔር አስቀድሞ ለሩካቤ ምቹና አስደሳች አካልን ፈጥሮልን ባላዘዘን መልኩ ብናደርገው ጣጣው ብዙ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚነግረን አንድ ትውልድ የጠፋው በግብረ ሰዶም ምክንያት ነው፡፡ በሎጥ ዘመን በዛ ግብረ ሰዶማዊ ትውልድ ላይ ከሰማይ እሳት የዘነበው፣ ትውልድንም የቀሰፈው ግብረ ሰዶም ነው፡፡

ሀገራት ግብረ ሰዶምን ፈቅደው፣ የእነሱ ርዝራዥ እኛም ሀገር እየታየ ነው፡፡ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሚባለው በሃይማኖት ሀገራችን የዝሙት መስፋፋት፣ የትውልድ የኀጢአት እድፈት ሲገርመን ግብረ ሰዶም መስፋፋቱ በተፈጥሮ ሩካቤ ላይ ያለው አሉታዊ ተጽዕኖ ከባድ ነው፡፡ እንስሳት እንኳን በደመ ነፍሳቸው የማይፈጽሙትን ድርጊት የሰው ልጅ በብሩህ አእምሮው አስቦ መፈጸሙን ስናስብ አጋንንት እንዴት እንዳደረብን፣ እንዴት እንደተቆጣጠረን ትልቅ ማሳያ ነው፡፡ ይህ ጸያፍ ተግባር ከእግዚአብሔር መቅሠፍት ነው የሚያተርፍብን፡፡ ስለዚህ ከዚህ ድርጊት መታቀብ ብቻ ሳይሆን በየትኛውም ፈተና ብንወጠር ማሰብ የለብንም፡፡

7/ ዘርን ከማሕፀን ውጭ ማፍሰስ ፦ ይህ ምናልባት ብዙዎች እርግዝናን ከመከላከል ጋር በማያያዝ የሚፈጽሙት ተግባር ነው፡፡ ነገር ግን ግብረ አውናን በመሆኑ ያስቀጣል፡፡ የከበረውን የወንድ ዘር ያለ ቦታው ማፍሰስ ተገቢ ስላልሆነ፡፡ ዘርን በሩካቤ ሥጋ ጊዜ ከማሕፀን ውጪ ማፍሰስ በወገባችን ያለን ልጅ በሜዳ ላይ እንደመጣል ነው፡፡ ሆን ተብሎ ታስቦበት፣ ተነጋግረው ዘርን ከማሕፀን ውጪ ማፍሰስ ትልቅ ኀጢአት ነው፡፡ በሩካቤ ሥጋ ጊዜ ዘርን ማፍሰስ የእርካታ ምልክት ቢሆንም በእኛ ደስታ ውስጥ ማለትም በሚፈሰው ዘር ውስጥ ነገ ልጆች የሚሆኑ ናቸው፡፡ የሚሳዝነው ወልደን ካሳደግናቸው ልጆች ይልቅ ዘርን ከማሕፀን ውጪ በማፍሰሳችን የማናውቃቸው የበተንናቸው ልጆች ይበልጣሉ፡፡

ወዳጆቼ የሰው ልጅ ዘር በእግዚአብሔር ዘንድ ክቡር ነው፡፡ እግዚአብሔር ልጆችን በማሕፀን ለመፍጠር የሚጠቀምበት አንዱ የሰው ልጅ ዘር ነው፡፡ ይህ የእግዚአብሔር መለኮታዊ ጥበብ የሚገለጥበትን የሰው ዘር ያለ ቦታው ማፍሰስ ተገቢ አይደለም፡፡ አባቶቻችን ይህን ድርጊት ‹‹ኃጢአተ አውናን›› በማለት ይገልጹታል፡፡ ይሁዳ ‘‘ኤር’’ የሚባል ልጅ ነበረው፡፡ እሱም ትእማር የምትባል ልጅ አግብቶ ይኖር ነበር፡፡ የይሁዳ ልጅ ኤር ግን በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ ክፉ ነበር፡፡ እግዚአብሔርም ኤርን ቀሠፈው ሞተም፡፡ ይሁዳም የኤርን ወንድም ልጁ አውናንን ‹‹ወደ ወንድምህ ሚስት ግባ፣ አግባትም፣ ለወንድህም ዘር አቁምለት›› አለው፡፡ አውናንም እንደ ወንድሙ ኤር ክፉ ነበርና ለወንድሙ ዘር እንዳይተካለት ከትእማር ጋር ሩካቤ ሥጋ ሲፈጽም ዘሩን ከማሕፀንዋ ውጪ በምድር ላይ ያፈሰው ነበር፡፡ በማሕፀን ፅንስን የሚጠቀልለው እግዚአብሔር የአውናንን ተንኮልና ግፍ ተመለከተ፡፡ በአስጸያፊ ድርጊቱ እግዚአብሔር አውናንን ቀሠፈው እንደ ወንድሙ ኤር ሞተ፡፡ /ዘፍ 38÷6-1
0/

እግዚአብሔር በሐዲስ ኪዳን ንስሐን ባይሰጠን፣ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ባይታረቀን ኖሮ ዘርን ከማሕፀን ውጪ እያፈሰስን፣ ዘርን በኮንዶም እየቋጠርን ያለ ቦታው

ስናውለው፣ ስንጥለው እንደ አውናን በተቀሠፍን ነበር፡፡ ምሕረቱ እና ቸርነቱ ይዞን ይኸው ከነበደላችን አለን፡፡ በዓለማችን ላይ በሕይወት ካሉት የሰው ልጆች ይልቅ የመፈጠር ዕድል እያላቸው ግን ባልባሌ ቦታ በሚፈስ ዘር ልጆች የመሆናቸው ዕድል የተጨናገፉ ይበልጣሉ፡፡ ስለዚህ ስንት ጳጳሳት፣ ሀገር መሪዎች፣ ለወገንና ለሀገር የሚጠቅሙ ሰዎች የሚሆኑትን ዘርን ያለ ቦታው በማፍሰስ ምክንያት እያጠፋን ስለሆነ በትዳራችን ከዚህ ድርጊት ልንታቀብ ይገባል፡፡

ፍትሐ ነገሥትም በአንቀጽ 24 ቁ.928 ላይ ዘርን ከማሕፀን ውጪ ስለማፍሰስ ‹‹ከሴት ጋር የተኛ ዘሩንም ከእርሷ ያራቀ ቢኖር ከሞት አይዳን፡፡ የይሁዳ ልጅ አውናን ከወንድሙ ሚስት ጋር በተገናኘ ጊዜ ዘሩን ከእርሷ አውጥቶ በምድር ያፈስሰው እንደነበረ ይህን ሥራውን መሥራቱም በእግዚአብሔር ፊት በጸና ጊዜ እንደ ገደለው መጽሐፍ ይናገራል›› በማለት ያስቀምጥልናል፡፡ እዛው ላይ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ የማቴዎስን ወንጌል የተረጐመውን በማምጣት ‹‹ለተፈጥሯቸው ልጅ እንዳይገኝ እነሆ ይጥራሉ፡፡ ይህስ ካሉት መታጣት ይከፋል፡፡ ይህም ክፋት ያሉት ይታጡ ዘንድ ነው፡፡ ይህም ዘርን አውጥቶ በማይሆን ቦታ ስለማፍሰስ ይሆናል፡፡ ፅንስን ስለመከልከል ሥራይ በማድረግ ይሆናል›› በማለት ዘርን ከማሕፀን ውጪ ማፍሰስ ትልቅ ኀጢአት መሆኑን ይናገራል፡፡

https://www.tg-me.com/Tserezmut
ወደዳችሁት ተማራችሁበት?
@ይነበብ
👇👇👇

#የተጨማለቀው_ህይወቴ"


ለመጀመሪያ ጊዜ ልቅ የወሲብ ፊልም ወይም ፖርኖግራፊ ያየሁት የ13 ዓመት ልጅ ሆኜ የትምህርት ቤት ጉዞ ባደረግንበት ወቅት ነበር፡፡ አንዱ ጓደኛዬ ብዙ ልቅ የሆኑ ለወሲብ የሚያነሳሱ ፎቶ ግራፎች ያሉበትን መፅሔት ከቦርሳው ሲያወጣ በጣም ነበር የደነገጥኩት፡ ፡(በእርግጥ ይህ የሆነው ኢንተርኔት ከመጀመሩ ከብዙ አመታት በፊት ነው፡፡) ጓደኛዬም ወደፊት ማወቄ ስለማይቀር አሁን አስቀድሜ ማወቄ ጥሩ እንደሆነ ነገረኝ፡፡ በእርግጥ ምስሎቹ በጣም ማራኪ ናቸው የሚገርመው ነገር ደግሞ ያየሁት ምስል ሁሉ መርሳት እስኪያቅተኝ ድረስ በህሊናዬ ታትሞብኝ ነበር፡፡

ከዚህ ጊዜ ብዙም ሳይቆይ በቴሌቨዥን አልፎ አልፎ ፖርኖግራፊን የሚያካትቱ አንዳንድ ፊልሞች ቅዳሜ ቅዳሜ ማታ ይታዩ ጀመር፡፡ ታዲያ በዚህ ጊዜ በጊዜ ወደቤት ገብቼ እተኛ እና ልክ ሁሉም ሲተኙ ቀስ ብዬ ተነሰቼ የቲቪውን ድምፅ ቀንሼ ቁጭ ብዬ እከታተል ነበር፡፡ በዚህም ጭንቅላቴ በፖርኖግራፊ እየተበከለ መጣ፡፡ በጣም ትንሽ ልጅ ሆኜ እንኳን ፖርኖግራፊ ካየሁ በኃላ እራሴን በራሴ ሳላረካ እንቅልፍ እስካይወስደኝ ድረስ ተጠናወተኝ፤ ይህም ለብዙ አመታት የለት ተዕለት ተግባሬ ሆነ፡፡ ሁሌ ይህንን ድርጊት ስፈፅም የጥፋተኝነት ሰሜት ይሰማኝ እና ሁለተኛ አልደግመውም ብዬ ማላከብረውን ቃል ለእግዚአብሔር እገባለታለሁ፡፡ እውነት ለመናገር ግን ይህንን ማቆምበት የምችልበት ምንም አቅም አልነበረኝም፡፡

ሰዎች ይህንን ቢያውቁ ስለእኔ ምን ያስባሉ የሚለው ሁሌ ያስፈራኛል፡፡

የኢንተርኔት አገልግሎት ሲስፋፋ እኔ በሀያዎቹ መጀመሪያ እድሜ ላይ ነበርኩኝ፡፡ በኢንተርኔት ምክንያት ሁሉም አይነት ፖርኖግራፊዎችን ለማግኘት በጣም ቀላል ሆነ፡፡ በቀላሉ ሁሉንም አይነት ፖርኖግራፊ ማለትም ምስል፣ ቪዲዩ፣ ሙዚቃ ሁሉንም በትንሿ ስልኬ ማየት ጀመርኩኝ፡፡ ይህንን ተግባር ለማቆም ሁልጊዜ ለራሴ ቃል ብገባም አንድም ቀን ተሳክቶልኝ አያውቅም፡፡ መቋቋም ከምችለው በላይ ይሆንብኛል፡፡ ይህ የህይወት ኡደት፡ ፖርኖግራፊ ማየት፣ እራስን በራስ ማርካት፣ ከዛ መፀፀት ፣ ከዛ ድጋሚ ላለማድረግ ቃል መግባት ከዛ፣ ከዛ ደግሞ ማየት…..ይህ ከህይወቴ መቼ እንደሚቆም አላውቅም፡፡ በውጪ ለሚያየኝ በጣም ጥሩ ሰው ነው የምመስለው እንደውም በማመልክበት የሀይማኖት ተቋም መሪ ነበርኩኝ፡፡ ነገር ግን በውስጤ ያለውን ጨለማ የማውቀው እኔ ብቻ ነበርኩኝ፡፡ ሰዎች ይህንን ቢያውቁ ስለእኔ ምን ያስባሉ የሚለው ሁሌ ያስፈራኛል፡፡ ሚስት ባገባ ይህ ችግሬ ይፈታል ብዬ አስቤ ነበር፤ አገባሁ ነገር ግን የፖርኖግራፊ እና እራሴን በራሴ የማርካት ሱሴ በጋብቻ ውስጥ ሆኜም ቀጥሎ ነበር፡፡

የመጀመሪያው ትክክለኛው ነፃ የመውጣቴ አንድ ብሎ የጀመረው ፖርግራፊ ስለወሲብ ወይም ስለውበት ወይም ተፈጥሮ አለመሆኑን በተረዳሁኝ ቀን ነበር፡፡ በእርግጥ ፖርኖግራፊን ማየት የምፈልገው እራሴን መቆጣጠር እስካልችል ድረስ ቆንጆ የሆነች ሴት ስለማገኝ አይደለም ነገር ግን ሁሉም የራሴ ችግር ነው፡፡ ተቀባይነት፣ ተደናቂነትን፣ ፍቅርን እና ስልጣንን ለማግኘት ካለኝ ረሃብ የተነሳ ነው፡፡ የምጓጓበት ትክክለኛ ምክንያት ፖርኖግራፊ አለማችን ስለእኔ ማየት ያልቻለችውን አማላይነቴን ማየት ባትችልም እነዛ በፖርኖግራፊው አለም ያሉ ውብ ሴቶች ግን በፈጠርኩት የምናብ አለም በውበቴ ማልለው እጅግ ያፈቅሩኛል፡፡ ፖርኖግራፊ የጭንቅላቴ እና የልቤ ልምምዴ ውጤት ስለሆነ ከዚህ ሱስ መላቀቅ ካለብኝ መጀመሪያ መበጠስ ያለበት አስተሳሰቤ ነው፡፡ የፖርኖግራፊ ባሪያነቴን ለማስቆም ለራሴ የምነግራቸውን ውሸቶች በእውነት በመተካት በእውቀት ነፃ ለመውጣት መታገል ጀመርኩኝ፡፡

ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ይህንን ሱስ ሰብሬ እንድወጣ የረዳኝ ባለቤቴ ለእኔ ያላት ፍቅር ነበር፡፡

ፖርኖግራፊን አሸንፌ እንድወጣ ከረዱኝ ነገሮች ውስጥ ወሳኙ መልካም ጓደኞቼ ነበሩ፡፡ ላምናቸው የምችላቸው ጓደኞች ነበሩኝ፤ ሁሉንም ነገር የማካፍላቸው ጓደኞች፤ ተመሳሳይ ጥፋት ለአንድ ሺህኛ ጊዜ ባጠፋ እንኳን ለእኔ መፀለይ ያላቆሙ ጓደኞች ነበሩኝ፡፡ በፖርኖግራፊ እና ዝሙት ላይ የተቀናጀሁት የመጨረሻው ድሌ የተከሰተውን ሁሉ፤ የቀድሞውንም የአሁኑንም ትግሌን ለምርጧ ጓደኛዬ ለውዷ ባለቤቴ በነገርኳት ቀን ነበር፡፡ ሁሉንም ስነግራት በድጋሚ በዚህ ነገር ከወደኩኝ ጭምር እንደምነግራት ነበር የነገርኳት፡፡ ምንም ሳላስቀር ሁሉም ነገርኳት፡፡ በጣም የምትናደድ እና የምትቆጣ መስሎኝ ነበር፡፡ ነገር ግን ከሆነው ሁሉ ግራ መጋባቴ ነበር በጣም ያሳዘናት እና ከጎኔ ለመቆም፣ ልትረዳኝ እና ልትፀልይልኝ ቃል ገባችልኝ፡፡ ለእርሷ ከተናዘዝኩ ጊዜ ጀምሮ ግን ፖርኖረግራፊ በእኔ ላይ የነበረው ሀይል በተለያየ መንገድ ተሰብሮ ነበር እና ባለቤቴ ለእኔ ያላት ታላቅ ፍቅር ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ይህንን ልምምድ ሰብሬ እድወጣ አገዘኝ፡፡ ከዛ በኃላ ምንም አልደብቅም እናም ለእርሷ ታመኝ ሳልሆን መቀጠል አልፈለኩም፡፡ (በምናብ አለሜም ቢሆን)

ምንም እንኳን ለአመታት በፖርኖግራፊ ብሰቃይም አሁን ነፃ ነኝ ብዬ መናገር በመቻሌ በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡ ፖርኖግራፊ በአለም ላይ ያሉ ጥሩ ነገሮችን ይዞ እንደሚመጣ ቃል የሚገባ ቢሆንም የሚሰጠን ግን የተጨማለቀ ህይወት ብቻ ነው፡፡ ይህ ነፃ መውጣት ግን በአንድ ለሊት የሆነ ነገር አይደለም፡፡ ከአስር አመት በላይ በፈጀ የለውጥ ሂደት የመጣ ነው፡፡

ያ ሁሉ ትግል አልፎ እኔ አሁን ነፃ እና ደስታ ነኝ፡፡ እናንተም ይህንን የነፃነት መንገድ እንድትጀምሩ እጋብዛችሀለሁ፡፡

ይህንን ብቻውን መጋፈጥ የለብዎትም ፡፡ ከአማካሪ ጋር ይነጋገሩ ፣ ሚስጥራዊ ነው ፡፡



Pornography (ፓርኖግራፊ) = የወሲብ ምስል እንዲሁም ተንቀሳቃሽ ምስል ማለት ነው።
#ሀሳብ_አስተያየታችሁን_ፃፉልን

@Men_lerdawo_Bot
@Men_lerdawo_Bot


ለመተንፈስ
ከሱስ ለመውጣት
ታሪክ ለማጋራት

እርዳታ ከፈለጉ

@Men_lerdawo_Bot

ሚስጥርዎ 100% የተጠበቀ ነው።
ፀረ ዝሙት via @like
ጾታዊ ፍቅር.pdf
ፍቅር ምንድነው ?

መልሱን ከመፅሐፉ ይውሰዱ ።
👆👆ይህን ለመፃፍ ብዙ ሰአት ወስዶብኛል እና በደንብ አንቡት አደራ አደራራራራ

ክፍል ሁለት

ከላይ ባለው ተማራችሁ? Like በማድረግ ግለፁ 👍

በቀጣይ የምናብራራው ጥያቄ

👉 ''''''''ግብ አውናን ''''' ተገቢ ነውን

የምናብራራ ይሆናል ተፅፎ አልቋል like 👍 አይቼ እፓስተዋለው።

Like 👍like👍like👍

አበረታቱን ቢያንስ በlike
👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍


የሚለውን ጥያቄ ይብራራ? በlike ግለፁልን ፍላጎታችሁን ። የላይኩን ብዛት አይቼ የማብራራ ይሆናል ።

ሼርርርር

https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAFgp28OdrgPlpf4dag

ይብራራ👍
ይቅር 👎


ሼርርርርርር
አንተንም/ቺንም ይመለከታል

Pornography
🔞🔞🔞🔞🔞

🔍ሊነበብ የሚገባ አንገብጋቢ ጉዳይ‼️

💦"ዘመን" አፈራሹ ፀረ~ሰብአዊ ጠንቅ !


🔞Pornography
(ፖርኖግራፌ)

#ፖርኖግራፊ በተለያዩ መንገዶች የሚገለጥ ሲሆን እነዚያም፡
#ጽሑፎች_ፎቶዎች_ስእሎች_ተንቀሳቃሽ_ምስሎች_ድምጾች_ያጠቃልላል፡፡

☞የፖርኖግራፊ 🔞ፊልሞች ተንቀሳቃሽ ምስሎችና የወሲብ ቃላትን የያዘ ሲሆን ፣ መጽሄቶች ደግሞ የጽሑፍ መልእክቶችንና ስእሎችን በጣምራነት ይዘዋል፡፡

📚ልብወለዶችና አጫጭር ታሪኮች የጽሑፍ መልእክቶችን በተብራራ ሁኔታ ያቀርባሉ፡፡
የሚገርመዉ ከላይ የተጠቀሱት ሁሉ በኢንተርኔት ላይ ይገኛሉ፡፡ 🌐☞ዊኪፒዲያ
🌐☞ፈሪ ኢንሳይክሎፒድያ

🙇🙇🙇🙇‍♀እንዴት ሰዎች ለፖርኖግራፊ ሱስ ተጋላጭ ይሆናሉ ?

እንዲሁ እንደ አጋጣሚ ሌሎች ሰዎች ሲመለከቱ በማየት
- በሚያዩት ፊልሞችና
- የቴሌቪዥን የኮመርሻል ማስታወቂያ
♨️ በጓደኞቻቸው/ ወዳጆች/
♨️ሳይፈልጉ ወደ ኢሜላቸው በሚላኩ መልዕክቶች
♨️ማሕበራዊ ድህረ-ገጾች ( ፌስ ቡክ፣ ቲውተር፣...)
♨️ የግብረ ስጋ ግንኙነት ፍላጎት/ የፍትዎት ፍላጎት/

🐲🐉የፖርኖግራፊ ክፉ ተጽዕኖ

♨️ መደበቂያና ማምለጫ መንገድ አድርገው መጠቀማቸው
ፖርኖግራፊ ጥልቅ ስሜቱ የተጎዳ ሰው ምልክት ነው
➡️ስለራሳቸው ዝቅተኛ የሆነ አመለካከት ያላቸው
ብቸኝነት የሚያጠቃቸው
➡️ከአሁን በፊት ግብረ ስጋዊ የሆነ ጥቃት የገጠማቸ
♨️ በፖርኖግራፊ ሱስ የተጠመዱ ሰዎች ለሌሎች ነገሮች ተጋላጭም ናቸው።


➡️Hunger (መራብ፣ ከፍተኛ የሆነ ፍላጎት...)
➡️ Angry( ቁጣ፣ ንዴት፣ ጥላቻ)
➡️ Lonely ( ብቸኝነት፣ ጓደኛ አልባ መሆን...)
➡️ Tired ( መድከም፣ እንቅልፍ እንቅልፍ ማለት፣ አለመንቃት)
➡️ የበደለኝነት፣ የኃፍረትና የጭንቀት ስሜት🤦‍♂🙇🙇🙇
➡️🔞ፖርኖግራፊ ሴትና ወንዶችን እንደ ዕቃ እንዲታዩ ያበረታታል
➡️ ከማግባት በፊት ይለማመዳሉ ከዚያም አግብተው ይቀጥላሉ
➡️ከአግቡ በኃላ በዚህ ነገር መጠመድ( መያዝ ይጀምራሉ)

የፖርኖ ግራፊ መስፋፋት
🔞ፖርኖግራፊ 🌐ዌብ ሳይት ብዛት #4.2. million, #12% of the total website🌐🌐🌐

©አንድ 🔞የፖርኖግራፊ ዌብ ሳይት የሚጎበኙት #40 ሚሊየን ሰዎች ይጎበኙታል
>68 million ከአጠቃላይ 🌐ዌብ ሳይቶች ከሚፈልጉት ውስጥ ሲሆን ይህም 25% ነው።
ቃል ገበተው እንደገና የተጠመዱ 53%
ለመጀመሪያ ጊዜ
ለፖርኖግራፊ የሚጋለጡ መካከለኛ እድሜ 11 አመት
8-16 አመት 90% ይመለከታሉ
( የቤት ስራቸውን ሲሰሩ)

🔞🔞🔞🔞🔞🔞🔞🔞🔞🔞
#የፖርኖግራፊ_የወሲብ_ፊልሞች_ግልፅ_እና_ድብቅ_ዓላማ_አንድ_ነው_ወሲብን_ያለ_ጊዜውና_ያለቦታው_መቀስቀስ_ነው.”
🔞🔞🔞🔞🔞🔞🔞🔞🔞🔞


🔞የፖርኖግራፊ ክፉው🐉 ተጽዕኖ!

☞ በግል ሕይወት
☞ በኑሮ
☞በመንፈሳዊ ሕይወት
☞በቤተሰብ
☞በማህበራዊ Lifeላይ ከባድ ቀውስ ያስከትላል።


ከእዚህ አደገኛ ችግር ለመውጣት የምክር አገልግሎት ይሰጣል እናም መተው ከችግርዎ ይውጡ ።

አስተያየት ጥያቄ ያናግሩን።
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
@Men_lerdawo_Bot
👍👍👍👍👍👍👍👍

🙏#ሼር🙏

በማድረግ የአንድ የወጣቶችን ህይወት እንታደግ።
👆👆👆👆👆🙏🙏
@Tserezmut 👍
@Tserezmut 👍
@Tserezmut 👍
👆👆👆👆👆👆👆

👉💙💚💜 Join ❤️💙💚🙏
👍👍👍ክፍል ሁለት👍👍?

?👉«ግብረ አውናን» ተገቢ ነውን????


ግብረ አውናንን በመጸሐፍ ቅዱስ ስንመዝነው ተገቢ ነገር አለመሆኑን እንረዳለን። አንድ ገበሬ ለዘር የሚያስቀረው ዘር ራሱ ከሚመገበው እንኳን የተሻለውን ምርጥ በር ነው:: ስለሆነም ዘር ወቅት በፊት ተጠንቅቆ ሰሪቅ (በጎተራ) ያስቀምጠዋል:: ዘር ወቅት ደግሞ አወጥቶ በመልካም ማሳ ላይ ይዘሪዋል እንጃ ያለ ቦታው እይበትነውም፡፡ እንደዚሁም ሁሉ የሰው ዘር አእህል በር ይከብራልና በመልካም ጎተራ ማለትም በሰውነት ተጠብቆ መቆየት አለበት፡፡
🙏 @Tserezmut 🙏
ከጋብቻ በኋላ ባልና ሚስት ሩካቤ ሲፈጽሙ ደግሞ በመልካሟ ማሳ በሚስት ማኅፀን መዝራት እንጂ በልዩ ልዩ ምክንያት ሆን ብሉ ዘርን እንደ ጉድፍ ከማኅፀን በአፍኣ ማፍሰስ ከባድ ኃጢአት ነው:: (ትዳርና ተላጽቆ ምዕ 7

የሰው ዘር ክቡር በመሆኑ ዘራቸውን በሜዳ ካሚያፈሱ ሰዎች ይልቅ ሰው የመሆን ዕድል የነበራቸው ነገር ግን በየሜዳው ፈሰው የቀሩት በሮች የተሻሉ ናቸው:: * ምክንያቱም አፍሳሾቹ ከሕገ እግዚአብሔር ወጥተው በኃጢኣት ሲኖሩ ፈሰው የቀሩት በሮች ግን ምንም ካለመበደላቸውም ባሻገር ሲወለዱ ኖሮ ፓትርሪርክ ጳጳስ መነኩሴ ቄስ ዲያቆን ዘማሪ ወዘተ ...ንጉሥ ንመሆን ዕድል ሊኖራቸው ስለሚችል ነው፡፡ እንዲህ ስለሆነ ዘራቸውን ያፈስሱ የነበሩ ሰዎችን ላፈሰሱት በር ራሳቸውን ቤዛ በማድረግ እግዚኣብሔር ጊዜ ሳይሰጥ ቀሥፏቸዋል፡፡ እግዚአብሔር እንዲህ በማድረጉ ዘርን ማፍሰስ እንደማይገባና የስው ዘር ክቡር መሆኑን አስረድቷል፡፡

ዘ538፡9-10 (ትዳርና ተላጽቆ ምዕ 7)
እውናን የተባው ሰው ነዘሩን ካማኀፀን ውጭ በማፍሰሱ ምክንያቱ የደረሰበትን መቅሠፍት መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይተርከዋል፡፡

‹‹አውናንም ዘሩ ለእርሱ እንዳይሆን ኣቀ ወደ ወንድሙ ሚስት በገባ ጊዜ ለወንድሙ ገtር እንዳይሰጥ ህሩን በምድር ያፈሰው ነበር፡፡ ይህም ሥራው በእግዚአብሔር ዘንድ ክፉ ሆነበት፡፡ እርሱንም ደግሞ ቀሠፈው::› በዘፍ፡38 ፡ 9-10 ይህ ታሪክ በማንኛውም ምክንያቱ ከዓዊ ዘርዕ ባር ኣፍሳሽ መሆን ሊያስቀረፍ የሚችል ክፉ ሥራ መሆንን ይገልጻል፡፡

_ ሰውነትን በመደባበስና በርን በማፍሰስ ለርካት መሞከር ተገቢ አለመሆኑን የሚያስረዱ በልዩ ልዩ አገባብ የታጠቀሱ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ይገኛሉ::
🙏 @Tserezmut 🙏

ለምሳሌ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በመንፈስቅዱስ ተቃኝቶ የጻፈው ክታብ እንዲህ ይላል፡፡ «እንግዲህ በምድር ያሉትን ብልቶቻችሁን ግደሉ እነዚህም ዝሙትና ርኩሰት፣ ፍትወትም ክፉ ምኞትም፣ ጣኦትንም ማምለክ የሆነ መጎምጀት ነው፡፡››
ቆላ3 5 እዚህ ላይ «ብልቶቻቸሁን ግደሉ» ሲል ቆርጣችሁ ጣሏቸው ማለቱ ሳይሆን ኣትቀስቅሱ ማለት ነው:: ታዲያ ዘርን በማፍሰስ ለመርካት ብልትን እየነካኩ ማነሣሣት «ብልቶቻችሁን ግደሉ» ከሚለው የሐዋርያው ትእዛዝ ጋር በቀጥታ የሚቃረን አይደለምን? ዘርን ማፍሰስ ከጣዖት ኣምልኮ፣ ከክፉ ምኞት፣ ከርኩሰት፣ ከመጐምጀት ጋር ተሰልፎ እየተቆጠረ እንዴት ተገቢ ሊሆን ይችላል?
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ «ደንዝዘውም ሰመመኘት ርኩሰትን ሁሉ ለማድረግ ራሳቸውን ወደ ሴሰኝነት አሳልፈው ሰጡ፡፡» በማለት የተናገረው ቃል ግብረ አውናንን ለሚፈጽሙ ሰዎች ሊጠቀስ ይችላል፡፡ ኤፌ4 ፥ 19 ምክንያቱም ሴጋ ዝሙትንና ርኩሰትን የመመኘ ት ዝንባሌ ዋና መገለጫ ነውና፡፡ ኣስቀድም እንደ ተገለጸውም የመጐምጀት፣ የስግብግብነት፣ የርኩሰት፣ የራስ ወዳድነትና ለሥጋ ማደርንም የሚያመለክት ነው::

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በፍትወት ለተቃጠሉ ሰዎች | መፍትሔ ሲስጥ «በምኞት ከመቃጠል መጋባት ይሻላልና ራሳቸውን መግዛት ባይችሉ ያግቡ» ብሏል፡፡ 1ቆሮ7 ፡ 9 ስለዚህ «በዝሙት ለሚቃጠሉ› መፍትሔው ማግባት እንጂ መሰንጋት (ሴጋ መፈጸም) - አይደለም:: መስንጋት በምንም መንገድ እንደ መፍትሔ ሊቆጠር አይችልም:: ሐዋርያው ማግባትን እንጂ ግብረ አውናንን እንደ መፍትሔ አድርጎ አልመከረምና፡፡
🙏 @Tserezmut 🙏
አምላካችን ሥጋ የፍትወቱን ያህል አግኝቶ እንዲረካ ጋብቻን ሲያሰናዳ ከጋብቻ ጋር አብረው የሚሄዱትንም ኃላፊነቶች ከመቀበልና ክመሸከም ጋር ነው፡፡ ነገር ግን በርን በማፍሰስ ራስን በራስ ለማርካት መሞከር ያለ ዋጋ ማለትም ምንም ዓይነት ኃላፊነት ሳይሸከሙ ያንን እርካታ ለማግኘት እንደመሞከር ይቆጠራል፡፡ ይህ ደግሞ የራስ ያልሆነን ነገር ለማግኘት መሞከር እንደመሆኑ መጠን የሚወገዝ እንጂ. እንደ ተገቢ ነገር ሊበረታታ አይገባውም፡፡

| ፣ የምኞት ቃጠሎን ዘርን በማፍሰስ ለማብረድ መሞከር ስሕተት ነው::

ምክንያቱም

አንድ ችግር ሲያጋጥም ተቋቁሞ በማለፍ ፈንታ በተሳሳተ ጐዳና በመጓዝ ችግሩን ለማምለጥ መካከር ሽንፈትንና ደካማነትን የሚያመለክት በመሆኑ ነው:: ይህን ዓይነት አካሄድ የተለማመደ አንድ ወጣት ችግሮችን እንደ አመጣጣቸው መመከት ይልቅ ሌላ የተሳሳተ አቋራጭ ሲማትር ይገኛል፡፡ በዚህ ምክንያት ብዙ : ወጣቶች ላለመማራቸውና ለሥራ ኣጥነታቸው ወይም በሕይወታቸው ለገጠማቸው እንድ ችግር ተገቢና ጤናማ መፍትሔ ከመፈለግ ይልቅ ዱርዬነትን፣ ሌብነትን፣ ሰካራምነትን፣ ሲጋራ ማጨስንና፣ ጫት መቃምን እንደ አማራጭ ይወስዳሉ፡፡

ታዲያ ይህ የሽንፈትና የደካማነት ምልክት አይደለምን? ፍትወት ሊያስቸግር ራስን በራስ ለማርካት መሞከርስ ከእነዚህ በምን ይለያል?

_ እንዳንድ ሰዎች «አንድ ሰው ጋብቻ ለመመሥረት ዕድሜው ያልደረሰ ወይም ሌሎች ችግሮች ያሉበት ክሆነ የጋብቻ ጊዜውን እየተጠባበቀ በዝሙትና በሰዶማዊ ተግባር ከሚሰነካኣል ራሱን በራሱ በማርካት ተግባር ቢቆይ ኣይሻልም?» እስከ ማለት ደርሰው ግብረ አውናንን ተገቢ ነገር ለማስመሰል ይጥራሉ:: እንደ እውነቱ ከሆነ ሕሊናችን ቢመስለውም ግብረ አውናንን ግብረ ሰዶምና ከዝሙት አሳንሶ የማየት ስልጣን የለንም:: ሁሉም የገመት ልዩ ልዩ ገጽታዎች ሲሆኑ የትኛውም ዓይነት ኃጢአት መሰነካክል የፈጣሪን ሕግ መሻር ነው:: ሕግጋት ደግሞ እንዱን ማሳነስ ሌላውን ማተለቅ ለሰው ኣልተሰጠውም:: ማቴ5 ፥ 19 ሰይጣንም ቢሆን ሐሳቡ እስኪፈጸምለት ድረስ በትንሽነቷ ንቀን እንድንፈጽማት ኣግብረ ሰዶምና ክዝሙት ታንሳለች በማለት ያሳስበናል እንጂ በዚሁ ኃጢአቱ የተያዙትን ሰዎች ደግሞ ያልሠሩትኝ ግብረ ሰዶምና ዝሙት እንዲሠሩለት ‹‹አንደኛውኑ ዝሙት ይሻላል፣ ይህን የመሰለ ኃጢአት እየፈጸምህ ዝሙት ኣልሠሪውም ለማለት ነውን?» እያለ ተስፋ ለማስቆረጥ እንደሚያምታታቸው መዘንጋት የለብንም፡፡ ትንሽ ናት ብለህ የምትንቃት ከሆነ መናቅህን ከእርሷ ስመለየት አሳይ! ልትለያት ወደህ ከእርሷ መራቅ ካቃተህ ትንሽ ናት ማለትህ የአፍ ብቻ አይሆንምን? በመጨረሻም ከላይ በተዘረዘሩት ጉሪያ ገብ ነጥቦች ግብረ አውናንን ስንመረምረው ክርስቲያኖች ሁሉ ሊጸየፉት የሚገባ እኩይ ምግባር መሆኑን እንረዳለን፡፡

#ይቀጥላል ....

በቀጣይ ክፍል ሦስት የምንመለከተው 👇

3 ስለ ግብረ አውናን #(ማስተርቤሽን) የተሳሳቱ አመለካከቶች ምን ምን ናቸው? እንመለከታለን ።

ይጠብቁን ።

ሼር ማረግ አትርሱ ቢያንስ 3 ሰው ብታስተምሩ ከእግዚአብሔር ዘንድ ዋጋ ታገኛላችሁ እና ሼር አርጉ ።



ዝሙት የኃጢአት ነው።
ዝሙት ከፈጣሪ ጋር መጣያ ነው።
ዝሙት ማንነትን የሚሸጥ ነው።
ዝሙት በሽታ ነው።
እባክዎ እራስዎን ይጠብቁ ።


https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAFgp28OdrgPlpf4dag
👆👆ይህን ለመፃፍ ብዙ ሰአት ወስዶብኛል እና በደንብ አንቡት አደራ አደራራራራ

ክፍል ሦስት ይቀጥላል

ከላይ ባለው ተማራችሁ? Like በማድረግ ግለፁ 👍

በቀጣይ የምናብራራው ጥያቄ

👉 ስለ''''''''ግብረአውናን''''' (ማስተርቤሽን)((እራስን በእራስ ማርካት)) የሣሣቱ አመለካከቶች ምን ምን ናቸው

የምናብራራ ይሆናል ተፅፎ አልቋል like 👍 አይቼ እፓስተዋለው።

Like 👍like👍like👍

አበረታቱን ቢያንስ በlike
👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍


የሚለውን ጥያቄ ይብራራ? በlike ግለፁልን ፍላጎታችሁን ። የላይኩን ብዛት አይቼ የማብራራ ይሆናል ።

ሼርርርር

https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAFgp28OdrgPlpf4dag

ይብራራ👍
ይቅር 👎


ሼርርርርርር
ክፍል ሦስት


👉«ግብረ አውናን» ማስተርቤሽን እራስን በእራስ ማርካትን በተመለከተ አሳሳች ሐሳቦች ምን ምን ናቸው?


ግብረ አውናንን በተመለከተ ከተለያየ አቅጣጫ የሚሰነዘሩ ሀሳቦች አሉ:: ከነዚህ ውስጥ አንዳንዶቹ ምንም እንኳን በቀጥታ ድርጊቱን ለማበረታታት የተነገሩ ባይመስሉም ብዘዎችን ከእዚህ ክፉ ልማደ እንዳይወጡ ለማሰር ኃይል ያላቸው ናቸው:: እነዚህም
ሳቦች መካከል ጥቂቶቹ ዚህ በታች ተዘርዝረዋል፡፡
👇👇👇👇

ህ) ብዙ ሰዎች «አውናን የተቀሠፈው Ilሩን በማፍሰሱ ሳይሆን ለወንድሙ ነበር ማቆምን ስላልወደደ በምቀኝነቱ፡ ነው›› በማለት መሠረት የሌለው ሐሳብ ይሰነዝራሉ:: በእርግጥ እውናን ለወንድሙ ዘር. ላለማቆም ማሰቡ ምቀኛ ያሰኘዋል:: ያስቀሠፈው ዋና ምክንያት "ምቀኝነቱ ነው ማለት ግን ስሕተት ነው:: ምቀኝነት ለያስቀስፍ፡ የሚችል ኃጢአት ቢሆንም እውናን የተቀሠፈው ግን ዘሩን በማፍሰሱ› እንጂ በምቀኝቱ አይደለም::
🙏 @Tserezmut 🙏
ሰው የራሱን የግል አስተያየት ወደ ጎን አደርጎ እግዚአብሔር በመጽሐፍ ቅዱስ ለሕገዝቡ የሚናገረውን ማድመጥ ከፈለገ አውናን የተቀሠፈበትን ዋና ምክንያት መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል፡፡ ምቀኝነትና በዘርን ማፍሰስ በጣም ይለያያሉ፡፡ ምቀኝነት የልቡና ሐሳብ ነው:: ነገርን ማፍሰስ ግን በግልጽ የሚታይ ተግባር ነው:: መጽሐፍ ቅዱስ ደግሞ አውናን የተቀሠፈበትን ምክንያት ሲገልጽ «ሥራውም በእግዚአብሔር ዘንድ ክፉ ሆነበት» ይላል እንጂ «ምቀኝነቱ» ኣይልም::ታዲያ የአውናን ክፉ ሥራው ምን ነበር ዘሩን በምድር ላይ ማፍሰሱ አልነበረምን? ምቀኝነት በሥራ የሚገለጥ የልቡና ክፋት እንጂ በራሱ «ሥራ» አይባልምና፡፡
| ከላይ እንደተብራራው አውናን የተቀሠፈው ዘሩን በማፍሰሱ ሳይሆን በምቀኝነት ብቻ እንደሆነ አድርጉ መናገር መሠረት የሌለው የሰይጣን ትርጓሜ ከመሆኑም ባሻገር «ዘርን ማፍሰስ› አያስቀጣም ወይም ሊያስቀፍ አይችልም እያሉ እንደማወጅ ነው፡፡ እንዲህ ማለት ደግሞ የእግዚአብሔርን ፍርድ ፈርቶ ከክፉ ሥራው ለመመለስ ያለውን ወጣት ለምን ትመለሳለህ ግፋበት እንጂ እያሉ እንደመምከር ይቆጠራል:: ክፉን ነገር እንደማያስቀጣ አድርጉ መተርጉም ተሳስቶ ማሳሳት ነውና ሊታረም ይገባል፡፡ በዚህ የተሳሳተ ሐሳብ ተወግተው ክፉውን ልማድ እንደ በጉ ይዘው የሚማቅቁትን ወጣቶች ቤት ይቁጠሪቸው::
🙏 @Tserezmut 🙏

👉ለ) በመሰንጋት ራስን በራስ ለማርካት የመሞክር ተግባር በብዙ ወጣቶች ከህንድ የተለመደ ሆኗል:: ይህ ድርጊት ፆታና ዕድሜ አይለይም:: በአጠቃላይ ሲታይ ወንዶች ከሴቶች ቀደም ባለ ዕድሜ ቢጀምሩም ሲቶችም ከዚህ ተግባር ውጭ አይደለም:: ጥናቱ፡ በኛ ሀገር እይካሄድ እንጂ አንደ በአሜሪካን ሀገር የተደረገ ጥናታዊ ጽሑፍ እንደሚያመለክተው ከሆነ በአጠቃላይ ወጣት ልጃገረዶች ሁለት ሦስተኛው እጅ በአጠቃላይ ወጣት ወንዶች ደግሞ ዘጠና አምስት በመቶ የሚሆኑ ወጣቶች የተለያየ ርዝማኔ ላላቸው ጊዜያት «በማስተርቤሽን» ልማድ ይያዛሉ:: ይህ አኀዝ ለወንዶች ሙሉ በሙሉ እንደማለት ነው:: ከሁሉ የሚያስደንቀው በሰባዎቹ ውስጥ ከሚገኙ አሮጊቶች ሠላሳ ሦስት እጅ ከሽማግሌዎች ደግሞ አርባ ሦስት እጅ የሚሆኑት አሁንም በዚሁ የመሰንጋት (ራስን በራስ ማርካት) ተግባር ውስጥ መገኘታቸው ነው፡፡ (ኢንካርታ ብሪታኒካ ኢንሳይክሎፒዲያ 2004 በኛ ም አገር ቁጥሩ ይህን ያህል አይጋነንን እንጂ ብዙ ወጣቶች በዚህ ክፉ ልማድ መመረዛቸው በተለያየ መንገድ ይሰማል፡፡ ካዚህ የተነሣ አንዳንድ ሰዎች «ይህ ድርጊት ጤናማነትን ስለሚያመለክት የሚያሳስበው በዚህ መንገድ የማይጓዙ ሰዎች ሕይወት ነው» እስከ ማለት ደርሰዋል፡፡ በዓለም ላይ ሴጋን መፈጸም በብዙኀኑ ዘንድ የተለመደ በመሆኑ ብቻ ድርጊቱ እንደ ተገቢና ጤናማ የሰውነት ተግባር ሊቆጠር እይችልም:: ወጣቶችም በዚህ ሐሳብ በመሳሳት በድርጊቱ የተለከፉ የሆነ ለመላቀቅ ካመጣጠር ይልቅ «ለካ እኔ ብቻ አይደለሁም!» እያሉ
መጽናናት አይገባቸውም:: ይህን ተግባር ሞክረውትም የማያውቁ ከሆነ ለመሞከር የማነሣሣት ይልቅ ጨርሶ የዚህን ክፉ ኃጢአት ጣዕም አለመቅመስ በሕይወታቸው ያለውን ፋይዳ ተረድተው ከመሞከር መታቀብ ይኖርባቸዋል፡፡

በዓለማችን መፋታት፣ ዝሙት፣ መግደል፣ ውርጃ፣ ባዕድ እምልኮ፣ ውሸትና መሥረቅ በብዙ ሰዎች ዘንድ የተለመዱ ናቸው:: :ታዲያ እነዚህ ተግባራት በብዙኀኑ ዘንድ መተግበራቸው ትክክል በሆነ ነው እንጂ ያሰኛቸዋልን? ሴጋ መፈጸምም እንደዚሁ ነው:: ከላይ በፊደል ሀ» እንደተጠቀሰው ሐሳብ ሁሉ ሰዎች ለክፉ ሥራቸው አጋር እንዳላቸው እያሰቡ እንዲጽናኑ ሰይጣን የዘረጋው የጥፋት ወጥመድ «ብዙዎች የሚፈጽሙት ከሆነ እንዴት ኃጢኣት ይሆናል?» የሚል ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ግን «ብዙዎች ኃጢአት ሲሠሩ አይተህ ከእነሱ ጋር አትተባበር ይላል፡፡» ዘፀ 23 * 2
🙏 @Tserezmut 🙏

👉ሐ) ብዙ የሕክምና ባለሙያዎችና የሥነ አእምሮ ጠበብቶች «ክዕወተ - ዘርዕ» ብዙ ዓይነት ሥነ ልቡናዊና አካላዊ የጤና ችግር እንደሚያስከትል በአንድ ልብ ይስማማሉ፡፡ እንዲያውም የብዙዎችን ጓዳ ከሚያንኳኳው ከ«ስንፈተ ወሲብ» ጀምሮ የኩላሊትና የልብ በሽታዎች ድረስ በሴጋ አማካኝነት ሊመጡ እንደሚችሉ በሰፊው ተዘግቧል። ሆኖም ግን የዓለም ጠቢባን ቃላቸው ወጥነት የሚጎድለውና ተለዋዋጭ ነው:: ስለዚህ ኣንዱ የካበውን ሌላው ሲንደው ይታያል፡፡ «የዓለም ጠቢባን ቃላቸው ወጥነት ይጎድለዋል» ለሚለው ሐሳብ ማስረጃ የሚሆነው ብዙ ምሁራን «ሴጋ» ወይም «ማስተርቤሽን» ለልዩ ልዩ በሽታ ያጋልጣል ሲሉ ሌሎች ደግሞ በጭራሽ ኣያጋልጥም ማለታቸው ነው፡ እንዲያውም ከእነዚህ መካከል ጥቂቶቹ «ሴጋ» ወይም ‹‹ማስተርቤሽን» ለኣንዳንድ በሽታዎች የመጋለጥ ዕድልን ይቀንሳል ሲሉ ይደመጣል፡፡ ለምሳሌ፡- በሀገራችን ከሚታተሙት በርካታ የግል ጋዜጦች እንዱ የሆነው ሜዲካል ጋዜጣ በ1995 በመጨረሻዎቹ ሁለት ወራት ውስጥ ካሳተማቸው ጋዜጦች በአንዱ ላይ ‹‹ማስተርቤሽን» በካንሠር የያገ፡ ዕድልን እንደሚቀንስ ጥናታዊ መረጃዎችንና የባለሙያዎችን አስተያየት ጠቅሶ አስፍራል፡፡ እንደ የሕክምና ባለሙያዎች ሁሉ የሥነ ኣእምሮ ጠበብቶችም «አንድ ሰው ሴጋ በመፈጸሙ ምክንያት ጉዳት ሊያገኘው የሚችለው የአእምሮና የስሜት መረበሽን የሚያስከትል የበደለኝነት ስሜት የሚሰማው ካሆነ ብቻ ነው» በማለት ይናገራሉ፡፡ ይሁን እንጂ ሐኪሞችና የሥነ አእምሮ ጠበብቶች እንደ ሌላው ሰው ሁሉ ለስሕተት የተጋለጡ፣ ደካማ ፍጡራንና ፍጽምና የሌላቸው በመሆናቸው አመለካከታቸው በየጊዜው ይለዋወጣል፡፡ ማን ያውቃል? ዛሬ ጉዳት አያስከትልም ያሉትን ድርጊት ነገ አንድ ያልደረሱበትን ዕውቀት ሲያገኙ ጉዳት የሞላበት ነው ይሉት ይሆናል፡፡ ያን ጊዜ የዛሬ ቃላታቸውን ተቀብለው በክፉ ልማዱ ጸንቶ የተገኘ ወጣት መጨረሻው ምን ይሆን? በዓለም ጠቢባን ቃል ልቡን ከሚያሳርፍ ይልቅ በእግዚአብሔር ሕግና ሥርዓት ጸንቶ የሚኖር ሰው እንዴት የተመሰገነ ነው? የዚህ መንፈሳዊ መጽሐፍ ዋና ዓላማ ዘርን በገዛ እጅ በማፍሰስ ስሜን ለማርካት መሞከር ምን ያህል ወይም ምን ዓይነት የጤና መታወክ ይፈጥራል? የሚለውን ማብራራት ሳይሆን ምን ያህል? መንፈሳዊ ጉዳት ያስከትላል ለሚለው ጥያቄ በቂ ግንዛቤ ማስጨበጥ ነው::
ምንም እንኳን ከዚህ በላይ «ምንም ዓይነት የጤና ጉዳት አያስከትልም፡ ጉዳት የሚያስከትለው ድርጊቱን የሚፈጽመው ሰው የበደለኘነት ስሜት የሚሰማው ከሆነ ብቻ ነው:: በሚል በባለሙያዎች የተሰነዘረው ሐሳብ አስተማማኝነት እንደሌለ
ው ቢገለጽም በዚህ ክፉ ልማደ የተመረዙትንና እየተሳበ ያሉትን ሰዎች ድርጊታቸው እንዳይላቀቁ የሚጫወተው ሚና ግን እጅግ የከፋ ነው::

👉ምክንያቱም ይህ ሥራዪዬ የጤና መታወክ የሚፈጥርብኝ ስጸጸት ብቻ ከሆነ ጉዳት እንዳያስከትልብኝ ራሴን እንደ ጥፋተኛ እየቆጠርኩ መቆርቆር የለብኝም እያሉ እንዲጽናኑ ስለሚያደርጋቸው ነው::
🙏 @Tserezmut 🙏

በዚህ መልኩ በክፉ ሥራቸው እንዳይጸጸቱና እግዚአብሔር የሚያመጣባቸውን የቅጣት ፍርድ እያሰቡ እንዳይፈሩ በጤና ባለሙያዎችና በሥነ አእምሮ ጠበብቶች የተሰጣቸው ምክር ምንም ዓይነት ፍርሃተ እግዚአብሔር በልቡናቸው እንዳይኖር ያደርጋል፡፡ ይህ ደግሞ «የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነውና» በእግዚአብሔር ዘንድ የተጣሉና ረድኤት የሌላቸው እንዲሆኑ ከማድረጉም በላይ ከክፉ ሥራቸው እንዳይመለሱ ያደርጋል፡፡


👉ምክንያቱም ሰው ከክፉ ሥራው የሚመለሰው በዋናነት ክፉ ሥራው የሚያስከትልበትን ፍርድ አስቦ ነውና:: ምንም ክፉ ነገር አያገኝኽም እየተባለ በባለ ሙያ የተመከረ ሰው ምን ፈርቶ ከክፉ ሥራው ይመለሳል?
በኃጢአት ተግባር ላይ ያለ ሰው ‹‹ምን ይመጣብኝ ይሆን?›› እያለ ማሰቡ በውስጠ እግዚአብሔርን መፍራት እንዳለ ያሳያል፡፡ : ምንም እንኳን ከኃጢኣት መላቀቅ ባይችል ይህ ፍርሃቱ እንደ ጽድቅ ' . ሊቆጠርለት ይችላል:: ያላየውን እግዚአብሔርን መፍራት የማመን
ምልክት ነውና:: እግዚአብሔር የሚያመጣውን ፍርድ አስቦ መፍራት ከሀጢኣት ኣንጽቶ እንደ ጻድቅ ሊያስቆጥር መቻሉን መጽሐፈ
መነኮሳት በዚህ መልኩ ገልጾታል:: «ፍሪህ እምእንታክቲ ምግባሪት እንተ ትኅበብ ከመ ባቲ መገጽ እስመ ዘካገ ግዕዝ ይትበልሃ ካመ ውእቱ፡ የሐውር በእፍኣ እምፍኖታ» ፡ «ቅጣትና ተግሣጽ እንደሚያስከትል ከጠረጠርከው ሥራ ሁሉ ተጠበቅ እንዲህ ሲፈራ የሚኖረው ሰው ነው ከሀጢአት ውጭ ነው ይባላልና» ማለት ነው:: ማር.ይስ.ኤን.16 ምዕ1

ሰው ሁሉ እግዚአብሔር ጋር አንድ መሆን የሚችለው እነዚህ ከሦስቱ መንገዶች ቢያንስ እንኳን በአንዱ መንገድ መሄድ ከቻለ ብቻ ነው::

1 አንደኛው ያለ ምንም ምክንያት በእራሱ ተነሳስቶ እንደ አብርሃም ፈጣሪሁን ፈልጎ ካመነ::

2 ሁለተኛው እንደ ቅዱስ ጳውሎስ በግርማ እግዚአብሔር ተገሥጾ ከተመለሰ::

3 ሦስታኛ ደግሞ በክፉ ሥራው ምክንያት የሚመጣበትን ቅጣት አስቦ ከፈራ ነው:: የሐዋ9 ፥ 6 ማር ይስ አን 3 ምዕ1

ለምሳሌ፡- እንደ ቅዱስ ወቅሪስ፡፡ ቅዱስ ወቅሪስ መልከ መልካም ነበረ፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ከሴት ጋር ተቃጠረ፡፡ በዚያችም ሌሊተ ራእይ እየ። ራእዩም «እርሱ ታሥሮ ካብሁ እሥረኞች ጋር በንጉሡ ፊት ቆሞ እሥረኞቹ እያንዳንዳቸው በተራ ሲመረመሩ እርሱ ግን የቀጠርኳት ሴት ባሏ እሥሮኝ ይሆን? እያለ ሲጨነቅና ሲፈራ በዚህ ጊዜ ጠባቂ መልዐኩ ከወዳጆቹ አንዱን መስሎ መጥቶ ይህን ሥራ ሠርተህ እንዳታሲዘኝ ማልልኝና እኔ ልዋስህ እያለ ሲያስምለው» ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ ሄሳኔ የምትባል ደግ ሴት ነበረች ወደ እርሷ ሄዶ ያየውን ራእይ ነገራት:: እርሷም ተርታ ልብስ ለብሰህ አልባሌ መስለህ ፈጣሪህን አገልግለው ይምርሐል አለችው:: እርሱም እንደነገረችው እድርጎ ከፈጣሪው ታርቋል፡፡ ማር ይስ እን3 ምዕ 1

እንዲህ ከሆነ ፍርድን ኣስቦ መፍራት ጻድቅ ያደርጋል ቢባል ምን ይደንቃል?

ከክፉ ሥራ ለመመለስና ንስሐ ለመግባት ጥርጊያ ጎዳናው እግዚአብሔርን መፍራት ነው:: እግዚአብሔርን መፍራት ከእግዚአብሔር ዘንድ ምሕረትንና ርኅራኄን እንደሚያስጎኝ ከዚህ በታች የተጻፈው ታሪክ ያስረዳል፡፡

የእግዚአብሔር ነቢይ ኤልያስ - እግዚአብሔር ፊት ክፉን ሥራ ለመሥራት ራሱን ለሽጠ» ለአክዓብ የሚደርስበትን ቅጣት ሁሉ በነገረው ጊዜ አክዓብ
«ልብሱን ቀዶ ገሳሁን ማቅ እለበሰ ፥ ጾመም፣ በማቅ ላይም ተኛ ቅስስ ብሉም ሄደ፡፡› ያላል:: በተለይ «ቅስስ ብሎ ሄደ» የሚለው ዐረፍተ ነገር የአክዓብን ባርሓና ድንጋጤ ያመለክታል::

በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር «ኤልያስ ሆይ አክዓብ እንደ ደነገጠ (እንደፈራ) ተክዞም እንደሄደ አየህን? በፊቴ የተዋረደ ስለሆነ በልጁ በመን በቤቱ፡ ላይ ክፉ ነገር ኣመጣለሁ እንጂ በእርሱ ዘመን ክፉ ነገር አላመጣም::» በማለት በይቅርታ ወደ አክዓብ መመለሱን ተናግራል፡፡ 2ነገ20 ፡ 27

| ሰው በክፉ ሥራው «ምን ይመጣብኝ ይሆን?» እያለ ሲፈራ እግዚኣብሐርን መፍራቱ እንጂ ሌላ አይደለም:: ከላይ የተጠቀሰው የአክዓብ . ታሪክ እግዚአብሔርን መፍራት የሚያስገኘውን ታላቅ ጥቅምና በእግዚአብሔርም ዘንድም ያለውን ተወዳጅነት ያስረዳል፡፡ ሰይጣን ደግሞ ሰው እግዚአብሔርን በመፍራቱ ብቻ እንኳን የሚያገኘ ውን ጥቅም ያውቃልና የዓለምን ምሁራንን አስነሥቶ በልዩ ልዩ ጉዳይ ፍርሐተ እግዚአብሔርን ከሰው ልብ የሚያርቅ ንግግር ያናግራቸዋል፡: . : አንድ ጊዜ ፍርሐትና የበደለኝነት ስሜት • ጤናን ሊያቃውስ እንደሚችል ሌላ ጊዜ ደግሞ ፍርሐት በራስ የመተማመን ጉድለትና : የብቃት ማነስ ምልክት እንደ ሆነ በማስረዳት ሰዎች በእግዚአብሔር ፊት በፍርሃት እንዳይመላለሱ ለማድረግ ይጥራሉ:: እኛ ክርስቲያኖች ግን ምንም ከበደል መራቅ ባይቻለን ፍርድን አስቦ መፍራታችን ብቻ እንኳን ዋጋ ያለው መሆኑን እንረዳለን፡፡ ሰይጣን በውጫዊ ማንነታችን ሰልጥኖ ኃጢአት ቢያሠራን ፍርድን አስበን በልባችን በውስጣችን የምንገዛው ለእግዚአብሔር መሆኑን ያመለክታል:: ውጫዊው ኃላፊና ፈራሽ ሲሆን ውስጣዊው ግን ዘለዓለማዊ ነው:: በውጫዊው ሰውነት ከመገዛት በውስጣዊው መገዛት በብዙ ይበልጣል፡፡ እንዲህም በእፍኣዊ ማንነታችን ኃጢአት እየሠራን ለሰይጣን ከምንገዛው ይልቅ በውስጣችን ለእግዚአብሔር የምንገዛው ይበልጣልና መጨረሻችን የእግዚአብሔር መሆን ነው:: ስለዚህ «ለእግዚኣብሔር በፍርሐት እንገዛ› መዝ 2:11 ብንበድልም ፍርሐትን ከልባችን አናርቃት::


#ይቀጥላል ....

በቀጣይ ክፍል አራት የምንመለከተው 👇

4 ግብረ አውናን #(ማስተርቤሽን) ሴጋ (እራስን በእራስ ማርካት) (ዘርን ማፍሰስን) መፈፀም ሰው መግደል ሊሆን ይችላልን በቀጣይ እንመለከታለን ።

#ይጠብቁን

ሼር ማረግ አትርሱ ቢያንስ 3 ሰው ብታስተምሩ ከእግዚአብሔር ዘንድ ዋጋ ታገኛላችሁ እና ሼር አርጉ ።



ዝሙት የኃጢአት ነው።
ዝሙት ከፈጣሪ ጋር መጣያ ነው።
ዝሙት ማንነትን የሚሸጥ ነው።
ዝሙት በሽታ ነው።
እባክዎ እራስዎን ይጠብቁ ።


https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAFgp28OdrgPlpf4dag
👆👆ይህን ለመፃፍ ብዙ ሰአት ወስዶብኛል እና በደንብ አንቡት አደራ አደራራራራ

ክፍል አራት ይቀጥላል

ከላይ ባለው ተማራችሁ? Like በማድረግ ግለፁ 👍

በቀጣይ የምናብራራው ጥያቄ

👉4ግብረ አውናን #(ማስተርቤሽን) ሴጋ (እራስን በእራስ ማርካት) (ዘርን ማፍሰስን) መፈፀም ሰው መግደል ሊሆን ይችላልን በቀጣይ እንመለከታለን ።

የምናብራራ ይሆናል ተፅፎ አልቋል like 👍 አይቼ እፓስተዋለው።

Like 👍like👍like👍

አበረታቱን ቢያንስ በlike
👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍


የሚለውን ጥያቄ ይብራራ? በlike ግለፁልን ፍላጎታችሁን ። የላይኩን ብዛት አይቼ የማብራራ ይሆናል ።

ሼርርርር

https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAFgp28OdrgPlpf4dag

ይብራራ👍
ይቅር 👎


ሼርርርርርር
ክፍል አራት

👉 ‹ግብረ አውናን» ማስተርቤሽን ሴጋ እራስን በእራስ ማርካትን መፈጸም ሰው መግደል ሊሆን ይችላል?



ብዙ ሰዎች ዘር ሲከፍሉ ወይም ሲፈሳቸው ይልቁኑም አውቀው ያደረጉት ከሆነ «ሰው እንደ መግደል ይቆጠርብኝ ይሆን?» እያሉ ራሳቸውን መጠየቃቸው አይቀርም:: በእርግጥ ግብረ አውናንን እየፈጸሙ ዘርን ማፍስስ ሰው እንደ መግደል ይቆጠር ይሆን?

በወንድና ሴት ሩካቤ ሲያደርጉ ከወንድ በር ሴት ደግሞ ደም ተከፍለው ተዋሕዶ ባደረጉ ጊዜ ተከፍሉዋ እንደ የብርሃን ፋና ይሁን እንጃ. በዚያው ጊዜ ነፍስም አብራ ትካፈላለች:: ነገር ግን ሴቶች በየወሩ ደም ሲያዩ ወንዶችም በዘር ሲወጣባቸው ነፍስ እንደ ማጥፋት እይቆጠርባቸውም:: እንዴት?

ምሥጢር

ምሥጢሩ እንዲህ ነው:- እነሆ እሳት በእንጨት ውስጥ መኖሩ የታወቀ ነው:: ሆኖም አንድ እንጨት ከሌላ ጋር ሳይሳበቅ ለብቻው እሳት መፍጠር አይችልም:: እሳት በእንጨት ወስጥ ይገኛል ቢባልም ቅሉ እንጨት መስበር እሳት እንደ ማጥፋት አይቆጠርም:: እንጨት ምሳሌነቱ፡ እንደ ሴት ደምና እንደ ወንድ ዘር ሲሆን እሳት ደግሞ እንደ ነብስ ነውና ፡ ሲቶች ለብቻቸው የሚያስገኘ፣ ደም ወንዶችም ለብቻቸው የሚከፍሉት ዘር ነፍስን ሊያስገኝ ስለማይችል ሰው እንደ መግደል ሊቆጠር አይችልም:: ሰው የሚባለው ራሱ አራቱ ባሕርያተ ሥጋ ሦስቱ ባሕርያተ ነፍስ ያሉት ፍጥረት ነውና፡፡
🙏 @Tserezmut 🙏


#ይቀጥላል ....

በቀጣይ ክፍል አምስት የምንመለከተው 👇

5 ግብረ አውናን #(ማስተርቤሽን) ሴጋ (እራስን በእራስ ማርካት) (ዘርን ማፍሰስ) የሚያስከትለው ጉዳት ምንድንነው? በቀጣይ እንመለከታለን ።

#ይጠብቁን

ሼር ማረግ አትርሱ ቢያንስ 3 ሰው ብታስተምሩ ከእግዚአብሔር ዘንድ ዋጋ ታገኛላችሁ እና ሼር አርጉ ።



ዝሙት የኃጢአት ነው።
ዝሙት ከፈጣሪ ጋር መጣያ ነው።
ዝሙት ማንነትን የሚሸጥ ነው።
ዝሙት በሽታ ነው።
እባክዎ እራስዎን ይጠብቁ ።


https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAFgp28OdrgPlpf4dag
👆👆ይህን ለመፃፍ ብዙ ሰአት ወስዶብኛል እና በደንብ አንቡት አደራ አደራራራራ

ክፍል አምስት ይቀጥላል

ከላይ ባለው ተማራችሁ? Like በማድረግ ግለፁ 👍

በቀጣይ የምናብራራው ጥያቄ

👉5 ግብረ አውናን #(ማስተርቤሽን) ሴጋ (እራስን በእራስ ማርካት) (ዘርን ማፍሰስ) የሚያስከትለው ጉዳት ምንድንነው? በቀጣይ እንመለከታለን ።

የምናብራራ ይሆናል ተፅፎ አልቋል like 👍 አይቼ እፓስተዋለው።

Like 👍like👍like👍

አበረታቱን ቢያንስ በlike
👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍


የሚለውን ጥያቄ ይብራራ? በlike ግለፁልን ፍላጎታችሁን ። የላይኩን ብዛት አይቼ የማብራራ ይሆናል ።

ሼርርርር

https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAFgp28OdrgPlpf4dag

ይብራራ👍
ይቅር 👎


ሼርርርርርር
ክፍል አምስት

«ግብረ አውናን (ሴጋ )((ማስተርቤሽን)) (((እራስን በእራስ ማርካት)))

የሚያስከትለው ጉዳት
🙏 @Tserezmut 🙏

ግብረ አውናን (ሴጋ) ውጥረትን ለፈጠረ አንድ ችግር , የተሳሳተ አማራጭን መጠቀም እንደመሆኑ መጠን በሕይወት ዘመናችን ሁሉ ብርታትና ጥንካሬን የሚጠይቁ መንገዶችን እንድንሸሽ ያለማምዳል፡፡ ይህ ማለት ደግሞ እጅግ ሲበዛ ሰነፍ እንድንሆን ያደርጋል ማለት ነው።
🙏 @Tserezmut 🙏

ግብረ አውናን ኃጢኣት እንደ መሆኑ መጠን በዚህ ዓለምና በወዲያኛው ዓለም ቅጣትን ያስከትላል፡፡ በዚህ ዓለም ቅጣቱ፡ እንደ አውናን ከመቀሠፍ ሊጀምር ይችላል፡፡ ዘፍ:38 ፡ 9 ሰላም ማጣት፣ ቁጥያት፣ ጸጸት፣ ጭንቀት፣ መረበሽ፣ ንጹሕ ያለ መሆን ስሜትና የመሳሰሉት የግብረ አውናን ኣንጻሪዊ ጉዳዩች ተደርገው ሊጠቀሱ ! ይችላሉ።
🙏 @Tserezmut 🙏
ክዕወቱ ዘርዕ /ሥር እየሰደደ ሲሄድ ባለበት እያወሰንም:: «እንደኛውኑ ዝሙት ይሻላል›› በማሰኘት ወደ ዝሙትና ግብረ ሰዶም ሊያመራ ይችላል፡: ገለልተኝነት፣ ብቸኝነትን መሻትና የሥራ ተነሣሽነትን ማጣት ደግሞ ለላው የዚህ ክፉ ልማደ ጉጂ ገጽታ ነው::
🙏 @Tserezmut 🙏


- የመሰንጋት ሌላው አደገኛና ጐጂ ገጽታው ደግሞ ተስፋ መቁረጥና አጉል ጸጸት እንዲሁም ከንቱ ትሕትናን ማሳደሩ ነው። አጉል ጸጸቱ እንደ ይሁዳ ዓይነት ጸጸት በመሆኑ ኀፍረተ አካልን ተናዶ እስካ መቁረጥ ሊያደርስ ይችላል፡፡ ይሁዳ ራሱን እስከ መግደል የደረሰው በአጉል ጸጸት ነውና፡፡ የሐዋ1 ፥ 16-20፤ ማቴ27 ፥ 3-5
ኣጉል ትሕትና ማለት ደግሞ በዚህ ክፉ ልማድ የተመረዙ ሰዎች ዘማርያን፣ ሰባክያን፣ መነኮሳትና በልዩ ልዩ አገልግሉትና መንፈሳዊ ሙያ የተሰማሩ ሰዎች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ መንፈሳዊ አገልግሉት ንጽሕናን የሚፈልግ በመሆኑ ኑሮአቸውና መንፈሳዊ አገልግሎታቸው ሳይጣጣም ሲቀር «ማገልግል አይገባኝም!» በማለት ከትሩፋትና ከበጉ ሥራ ራሳቸውን የሚያሽሹ አሉ፡፡ ነገር ግን ክፉ ሥራን እንጂ የትሩፋት ሥራን መሽሽ በምንም መልኩ አይበጅም፡፡
🙏 @Tserezmut 🙏

ከአገልግሎት ጋር ሆነን ያላራቅነውን ክፉ ሥራ ኣረድኤተ እግዚኣብሔር ተለይተን ልናርቀው ኣንችልም:: ውሣኔያችንን እየመረመርን ከበላዮቻችን ማለትም ከመንፈሳዊ እባቶች ጋር እየመከርን በምክረ ካሀን በፈቃደ ካህን መኖርን መፍትሔ እናድርግ:: ይኸውም ለጊዜው ነው እንጂ አማራጭ የሌለው መፍትሔ ከዚህ ልማድ መለየት ብቻ ነው::
በጋብቻ ሕይወት ውስጥ አንዱ ለሌላው ወገን ደስታና እርካታ ማሰቡ እጅግ አስፈላጊ ነው:: ይህ ካልሆነ ግን የጋብቻ ግንኙነቶች ይበላሻሉ፡፡ በጋብቻ መሃል ጭንቀትና ቅሬታም ይፈጠራል፡፡ ወጣቶች
.ጋብቻ በፊት ያዘወትሩት የነበረው የፆታ ብልትን በመነካካትና በማሻሸት ለመርካት የመሞክር ተግባር ወይም ሴጋ ማስተርቤሽን ስለ ራስ ደስታና እርካታ ብቻ የማሰብ ልምድን ያሳድግባቸዋል፡፡ ይህ ልምድ ደግሞ በጋብቻ ውስጥ የሚገኘውን ደስታ አደጋ ላይ ይጥለዋል፡፡ ምክንያቱም ስለራስ እርካታ፡ ብቻ በማሰብ በባልና በሚስት መሃል መተሳሰብ እንዲጠፋ ስለሚያደርግ ነው:: ይህ ችግር ትክክለኛውን መፍትሔ አያግኙለት እንጂ በዓለማዊያኑ ዘንድ በስፋት ለውይይት ይቀርባል፡፡ በመንፈሳዊያን ሰዎች ዘንድ ደግሞ ምንም በሰፊው ባይወያዩበት በጋብቻ ውስጥ ለሚፈጠሩ የግጭት መነሻዎች ዋነኛ ሲሆን የሚመነጨውም ከትዳር በፊት ይዘወተር የነበረ ክዕወተ ዘርዕ (ሴጋ) እማካኝነት ነው:: አንተ ወጣት ይህ ክፉ ልማድ እስካ ጋብቻ ዘልቆ እንዴት ሊጉዳ እንደሚችል ተረዳህን?

ለንተ/ላንቺ መልሱን ተውኩ።

🙏 @Tserezmut 🙏


#ይቀጥላል ....

በቀጣይ ክፍል ስድስት የምንመለከተው 👇

6 ግብረ አውናን #(ማስተርቤሽን) ሴጋ (እራስን በእራስ ማርካት) (ዘርን ማፍሰስ) ከሚያስከትለው ጉዳት እንዴት መላቀቅ እንችላለን በቀጣይ እንመለከታለን ።

#ይጠብቁን

ሼር ማረግ አትርሱ ቢያንስ 3 ሰው ብታስተምሩ ከእግዚአብሔር ዘንድ ዋጋ ታገኛላችሁ እና ሼር አርጉ ።



ዝሙት የኃጢአት ነው።
ዝሙት ከፈጣሪ ጋር መጣያ ነው።
ዝሙት ማንነትን የሚሸጥ ነው።
ዝሙት በሽታ ነው።
እባክዎ እራስዎን ይጠብቁ ።


https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAFgp28OdrgPlpf4dag
👆👆ይህን ለመፃፍ ብዙ ሰአት ወስዶብኛል እና በደንብ አንቡት አደራ አደራራራራ

ክፍል ስድስት ይቀጥላል

ከላይ ባለው ተማራችሁ? Like በማድረግ ግለፁ 👍

በቀጣይ የምናብራራው ጥያቄ

👉6 ግብረ አውናን #(ማስተርቤሽን) ሴጋ (እራስን በእራስ ማርካት) (ዘርን ማፍሰስ) ከሚያስከትለው ጉዳት እንዴት መላቀቅ እንላለን? በቀጣይ እንመለከታለን ።

የምናብራራ ይሆናል ተፅፎ አልቋል like 👍 አይቼ እፓስተዋለው።

Like 👍like👍like👍

አበረታቱን ቢያንስ በlike
👍👍👍👍👍👍👍👍👍👍


የሚለውን ጥያቄ ይብራራ? በlike ግለፁልን ፍላጎታችሁን ። የላይኩን ብዛት አይቼ የማብራራ ይሆናል ።

ሼርርርር

https://www.tg-me.com/joinchat-AAAAAFgp28OdrgPlpf4dag

ይብራራ👍
ይቅር 👎


ሼርርርርርር
2024/05/15 17:03:09
Back to Top
HTML Embed Code: