Telegram Web Link
መልአክ ይመለካልን?

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

7፥206 እነዚያ እጌታህ ዘንድ ያሉት መላእክት እርሱን ከማምለክ አይኮሩም። ያወድሱታልም፥ ለእርሱ ይሰግዳሉ፡፡ إِنَّ الَّذِينَ عِندَ رَبِّكَ لَا يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِهِ وَيُسَبِّحُونَهُ وَلَهُ يَسْجُدُونَ

ሰዎች የማይሉትን እና የማያምኑትን እንደሚሉ እና እንደሚያምኑ አርጎ ሙግትን አዋቅሮ እና አደራጅቶ መሞገት ቁልመማዊ ሕፀፅ"strawman fallacy" ነው፥ አንድ ሰው ሰዎች የማይሉትን እና የማያምኑትን እንደሚሉ እና እንደሚያምኑ አርጎ ቁልመማዊ ሕፀፅ ማፀፅ የአጠይቆትን እሳቤ በቅጡ ያልተረዳ ሰው ነው። አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ "እንዚራ ስብሐት" በሚል መድብሉ "የአምልኮ መሥዋዕትንም ለአንቺ እሠዋለሁ" "የአምልኮ መሥዋዕትን ለአንቺ አቀርብልሻለሁ" በማለት በግልጽ እና በማያሻማ መልኩ ማርያምን እንደሚያመልክ ይናገራል፦
እንዚራ ስብሐት ምዕራፍ 12 ቁጥር 98 "ለአንቺም የምስጋና እጅ መንሻን አቀርባለሁ፣ በመፍራት እገዛልሻለሁ፣ በመስገድም እጅ እነሣሻለሁ። "የአምልኮ መሥዋዕትንም ለአንቺ እሠዋለሁ"።
እንዚራ ስብሐት ምዕራፍ 13 ቁጥር 113
"ማርያም ሆይ! ያማረ ፍጹም ምስጋና አቀርብልሻለሁ። የሚጣፍጥ "የአምልኮ መሥዋዕትን ለአንቺ አቀርብልሻለሁ"።

"ለአንቺ" የሚለው ይሰመርበት! ለዚህ ጥያቄ መልስ ቀጥታ መመለስ ያቃተው ዲያቆን ዘማርያም(ቴዲ) "በባይብልም እኮ መልአክ እንደሚመለክ ይናገራል፥ ያ ትርጉም ከገባችሁ ይህንን መረዳት ቀላል ነው" በማለት ተቃራኒ አጸፋ ከመስጠት ይልቅ ከትካች አጸፋ በመስጠት አግባባዊ ሕፀፅ"Relevance fallacy" ሲያፅፅ ነበር። አንዱ ቀዳዳን ለመድፈን ሌላው ሲቦተረፍ የታየበትን ጥቅስ እንመልከት፦
የሐዋርያት ሥራ 27፥23 የእርሱ የምሆን እና ደግሞ የማመልከው የአምላክ መልአክ በዚች ሌሊት በአጠገቤ ቆሞ ነበርና። παρέστη γάρ μοι ταύτῃ τῇ νυκτὶ τοῦ Θεοῦ, οὗ εἰμι, ᾧ καὶ λατρεύω, ἄγγελος

"ላትሬኦ" λατρεύω ማለት "አምልኮ" ማለት ሲሆን "የማመልከው" የሚለው የሚጠጋው "አምላክ" ወደሚለው እንጂ "መልአክ" ወደሚለው አይደለም፥ ይህ ሰው እንግሊዝኛ፣ ግዕዝ እና ግሪክ ቢያንስ እንዲያጠና ምከሩት! "የአስቀሪዬ የኡሥታዝ ልጅ ሰላም አለኝ" ብል "የአስቀሪዬ" የሚለው የሚጠጋው "ኡሥታዝ" ወደሚለው እንጂ "ልጅ" ወደሚለው አይደለም። አንድ ተመሳሳይ የሰዋስው አወቃቀር እስቲ እንመልከት፦
ራእይ 6፥9 የታረዱትን የሰዎች ነፍሳት ከመሠዊያ በታች አየሁ። εἶδον ὑποκάτω τοῦ θυσιαστηρίου τὰς ψυχὰς τῶν ἐσφαγμένων

ሰው እንጂ ነፍስ እንደማይታረድ እሙን እና ቅቡል ነው፥ ቅሉ እና ጥቅሉ ግን "የታረዱትን" የሚለው የሚጠጋው "ሰዎች" ወደሚለው እንጂ "ነፍሳት" ወደሚለው አይደለም። "የ" የሚል አገናዛቢ ዘርፍ ያለበት "ሰዎች" የሚለው ቃል ባለቤትን ስለሚያሳይ "የታረዱትን" የሚለው የሚጠጋው "ሰዎች" ወደሚለው እንደሆነ ሁሉ "የ" የሚል አገናዛቢ ዘርፍ ያለበት "አምላክ" የሚለው ቃል ባለቤትን ስለሚያሳይ "የማመልከው" የሚለው የሚጠጋው "አምላክ" ወደሚለው ነው፥ ጳውሎስ የማመልከው የሚለው አምላክን እንጂ መልአክን በፍጹም አይደለም፦
2ኛ ጢሞቴዎስ 1፥3 ሌሊት እና ቀን በልመናዬ ሳላቋርጥ ስለማስብህ እንደ አባቶቼ አድርጌ በንጹሕ ሕሊና የማመልከውን አምላክን አመሰግናለሁ። Χάριν ἔχω τῷ Θεῷ, ᾧ λατρεύω ἀπὸ προγόνων ἐν καθαρᾷ συνειδήσει, ὡς ἀδιάλειπτον ἔχω τὴν περὶ σοῦ μνείαν ἐν ταῖς δεήσεσίν μου νυκτὸς καὶ ἡμέρας,

"የማመልከውን አምላክን" የሚለው ኃይለ ቃል የሚመለከው አምላክ መሆኑን ቁልጭ እና ፍንትው አድርጎ ያሳያል። "እንደ አባቶቼ አድርጌ" የሚለው ቃል ከጥንት ጀምሮ አባቶች ሲያመልኩት የነበረው መልአክን ሳይሆን አምላክን ነው፥ የኦርቶዶክስን አምልኮተ ማርያም ስህተት ለመሸፈን ባይብል ውስጥ ገብቶ መደበቅ አግባብ አይደለም።

ይህንን መጣጥፍ መልስ ለመስጠት የተነሳሁበት ዓላማ ኦርቶዶክሳውያን "እኛ ማርያምን አናመልክም፥ ቁርኣን ቁልመማዊ ሕፀፅ ሐፅፆአል" ብለው ለከሰሱት የሐሰት ክስ ምላሽ ከአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ "እንዚራ ስብሐት" መድብል ላይ አንብበን ያቀረብነው እኛ ሙሥሊሞች ነን፥ ይህንን ሙግት ፕሮቴስታንቱ ከእኛ ተቀብለው ሲያራግቡ ዲያቆን ዘማርያም መልስ ብሎ የመለሰው ገለባ መልስ እኛ ስለሚመለከት ብቻ ነው እንጂ በሰው ጉዳይ ለመፈትፈት አይደለም።

አሳብ መሞገት የሚበረታታ ጉዳይ ነው፥ በአሳብ ሉዓላዊነት፣ ልዕልና፣ ገዢነት እና ዘውግ የሚያምን ሰው ረብጣ የሆነ አሳብ ሲመጣለት በተሻለ አሳብ ማረቅ እና ማሳለጥ እንጂ እርር እና ምርር ብሎ መንጨርጨር እና መንተክተክ አግባብ አይደለም።

ከአንዱ አምላክ በቀር ለአንዳች ነገር የአምልኮ መሥዋዕት መሠዋት በገሃነም ሊያስጠፋ የሚችል ወንጀል ነውና ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፈርታችሁ ከዚህ ድርጊት ተቆጠቡ፦
ዘጸአት 22፥20 ከያህዌህ በቀር ለአንዳች አምላክ የሚሠዋ ፈጽሞ ይጥፋ።
ማቴዎስ 10፥28 ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ።

ከአምልኮተ ማርያም ወጥታችሁ አሏህን በብቸኝነት እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://www.tg-me.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ትንቅንቅ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

40፥41 «ወገኖቼም ሆይ! ወደ መዳን የምጠራችሁ ስኾን ወደ እሳትም የምትጠሩኝ ስትኾኑ ለእኔ ምን አለኝ? وَيَا قَوْمِ مَا لِي أَدْعُوكُمْ إِلَى النَّجَاةِ وَتَدْعُونَنِي إِلَى النَّارِ

“ኢሥላም” إِسْلَٰم ማለት "አምላክ አንድ አምላክ ብቻ ነው" ብሎ ለእርሱ ብቻ መገዛት ነው፦
22፥34 አምላካችሁም አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ ለእርሱም ብቻ ታዘዙ፡፡ ለአላህ ተዋራጆችንም አብስራቸው፡፡ فَإِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ فَلَهُ أَسْلِمُوا ۗ وَبَشِّرِ الْمُخْبِتِين

እዚህ አንቀጽ ላይ “ታዘዙ” ለሚለው ቃል የተቀመጠው “አሥሊሙ” أَسْلِمُوا ሲሆን “አሥለመ” أَسْلَمَ ማለትም “ታዘዘ”፣ “ተገዛ”፣ ” አመለከ” ከሚል ግስ የመጣ ነው፥ “አሥሊሙ” የሚለው ቃል “ሙሥሊም” مُسْلِم ለሚለው ቃል ትእዛዛዊ ግሥ ነው። ሙሥሊም ወደ አሏህ በመጥራት ቃሉ ያማረ ነው፦
41፥33 *ወደ አሏህ ከጠራ እና መልካምንም ከሠራ፦ «እኔ ከሙሥሊሞች ነኝ» ካለም ሰው ይበልጥ ቃሉ ያማረ ማን ነው?* وَمَنْ أَحْسَنُ قَوْلًا مِّمَّن دَعَا إِلَى اللَّهِ وَعَمِلَ صَالِحًا وَقَالَ إِنَّنِي مِنَ الْمُسْلِمِينَ

ሙሥሊም ሰዎችን የሚጠራው ወደ መዳን ነው፥ ሰዎች ከእሳት እንዲያመልጡ ነው። ሙሽሪክ ደግሞ ወደ እሳት ነው የሚጠራው፦
40፥41 «ወገኖቼም ሆይ! ወደ መዳን የምጠራችሁ ስኾን ወደ እሳትም የምትጠሩኝ ስትኾኑ ለእኔ ምን አለኝ? وَيَا قَوْمِ مَا لِي أَدْعُوكُمْ إِلَى النَّجَاةِ وَتَدْعُونَنِي إِلَى النَّارِ

ሙሽሪክ ጥሪው በአልምህ ለማስካድ እና በእርሱም ዕውቀት የሌለንን ነገር በእርሱ እንዳጋራ እንድናጋራ ነው፥ ሙሥሊም ግን ወደ አሸናፊው መሓሪው አሏህ ነው፦
40፥42 «በአሏህ ልክድ እና በእርሱም ለእኔ ዕውቀት የሌለኝን ነገር በእርሱ እንዳጋራ ትጠሩኛላችሁ፡፡ እኔም ወደ አሸናፊው መሓሪው አሏህ እጠራችኋለሁ፡፡ تَدْعُونَنِي لِأَكْفُرَ بِاللَّهِ وَأُشْرِكَ بِهِ مَا لَيْسَ لِي بِهِ عِلْمٌ وَأَنَا أَدْعُوكُمْ إِلَى الْعَزِيزِ الْغَفَّارِ

እንግዲህ በሙሥሊም እና በሙሽሪክ መካከል ያለው ትንቅንቅ ይህ ነው፥ ወደ አሏህ መጣራት ይህ መንገዳችን ነው። ከአጋሪዎች አይደለንም፥ ይህም ቀጥተኛ  መንገድ ነው። ሌሎች የጥመት መንገዶችንም አትከተል፥ ከቀጥተኛው መንገድ እኛን ለመለየት ነው ጥሪው፦
12፥108 «ይህች መንገዴ ናት፡፡ ወደ አላህ እጠራለሁ፡፡ እኔም የተከተለኝም ሰው በግልጽ ማስረጃ ላይ ነን፡፡ ጥራትም ለአሏህ ይገባው፡፡ እኔም ከአጋሪዎቹ አይደለሁም» በል፡፡ قُلْ هَـٰذِهِ سَبِيلِي أَدْعُو إِلَى اللَّهِ ۚ عَلَىٰ بَصِيرَةٍ أَنَا وَمَنِ اتَّبَعَنِي ۖ وَسُبْحَانَ اللَّهِ وَمَا أَنَا مِنَ الْمُشْرِكِينَ
6፥153 «ይህም ቀጥተኛ ሲኾን መንገዴ ነው፤ ተከተሉትም፡፡ የጥመት መንገዶችንም አትከተሉ፡፡ ከቀጥተኛው መንገዱ እናንተን ይለያዩዋችኋልና፡፡ እነሆ ትጠነቀቁ ዘንድ በእርሱ አዘዛችሁ፡፡» وَأَنَّ هَـٰذَا صِرَاطِي مُسْتَقِيمًا فَاتَّبِعُوهُ ۖ وَلَا تَتَّبِعُوا السُّبُلَ فَتَفَرَّقَ بِكُمْ عَن سَبِيلِهِ ۚ ذَٰلِكُمْ وَصَّاكُم بِهِ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ

አምላካችን አሏህ ይህንን እውነተኛ የተውሒድ መንገድ አመጣልን፥ ግን አብዛኛዎቹ ሰዎች እውነቱን ጠይዎች ናቸዉ፦
43፥78 እውነተኛውን መንገድ በእርግጥ አመጣንላችሁ፡፡ ግን አብዛኞቻችሁ እውነቱን ጠይዎች ናችሁ፡፡ لَقَدْ جِئْنَاكُم بِالْحَقِّ وَلَـٰكِنَّ أَكْثَرَكُمْ لِلْحَقِّ كَارِهُونَ

ሙስሊም ወደ አንድ አምላክ መንገድ  ሲጣራ መጣራት ያለበት “ስሙር ሙግት”valid argument”  ተጠቅሞ ነው፤ ይህ ሙግት በእማኝነትና በአስረጂነት ጠቅሶና አጣቅሶ መሟገት ነው፤ በትክክለኛው የአስተላለፍ ስልትና አወቃቀር ስለተዋቀረ የራሱ የሆነ መንደርደሪ፣ የሙግት ነጥብ”premise” እና መደምደሚያ ያለው ነው፤ ዕውቀት ላይ የተመሰረተ ማስረጃ በአጽንኦትና በአንክሮት ለማዳመጥ ጥልና ጥንፍፍ ያለ መረዳት ነው፤ ይህን ሙግት አምላካችን አላህ መልካም ክርክር ይለዋል፤ ይህ ዘዴ ርቱዕ አካሄድ”optimistic approach” ነው፦
16፥125 ወደ ጌታህ መንገድ በብልሃትና በመልካም ግሣጼ በለዘብታ ቃል ጥራ”፤ በዚያችም እርሷ መልካም በሆነችው “ዘዴ ተከራከራቸው”። ٱدْعُ إِلَىٰ سَبِيلِ رَبِّكَ بِٱلْحِكْمَةِ وَٱلْمَوْعِظَةِ ٱلْحَسَنَةِ ۖ وَجَٰدِلْهُم بِٱلَّتِى هِىَ أَحْسَنُ ۚ إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعْلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ ۖ وَهُوَ أَعْلَمُ بِٱلْمُهْتَدِينَ

“ሙሽሪክ” مُشْرِك የሚለው ቃል “አሽረከ” أَشْرَكَ ማለትም “አጋራ” ከሚል ግስ የመጣ ሲሆን በአንድ አምላክ ላይ ሌሎች ማንነቶችንና ምንነቶችን "አጋሪ" ማለት ነው፥ ድርጊቱ  “ሺርክ” شِرْك ማለትም  “ማጋራት” ይባላል፤ በአላህ ላይ የሚያጋሩት ማንነትና ምንነት “ሸሪክ” شَرِيك ማለትም “ተጋሪ” ይባላሉ።    
ይህ ትንቅንቅ ይቀጥላል፤ ሙሽሪክ፦
1ኛ  ሦስት ማንነቶችን ማለትም ሥላሴን እንድናመልክ ይጠሩናል፥ ግን መመለክ ያለበት አንድ ማንነት ብቻ ነው።
2ኛ  ሰው እንድናመልክ ይጠሩናል፤ ኢየሱስ ሰውነቱ ይመለካል፥ በሰውነቱ ፍጡር ነው ይላሉና።
3ኛ ፍጡራንን እንድናመልክ ይጠሩናል፥ ፍጡራንን በሌሉበት ወደ እነርሱ መጎባደድ፣ መተናነስ፣ ማሸርገድ፣ መለማመን፣ መጸለይ፣ ስለት መሳል፣ መስዋዕት ማቅረብ፣ ስማቸውን መጥራት የአምልኮ ክፍል ነው፤ ሁሉን የሚሰማ፣ የሚያይ፣ የሚያውቅ አንድ መለኮት ብቻ ሆኖ ሳለ ወደ መላእክትና ቅዱሳን ይህንን ማድረግ ሺርክ ነው።
4ኛ. ለተቀረጸ ምስል እንድንሰግድ ይጠሩናል፤ ለተቀረጸ ምስል አትስገድ ተብሎ ነገር ግን በተቃራኒው ከእንጨት፣ ከብር፣ ከወርቅ፣ ከብረት፣ ከድንጋይ ለተቀረጹ መስቀል፣ ስዕል እና ሃውልት ይሰግዳሉ። ወገኖቼም ሆይ! ወደ መዳን የምጠራችሁ ስኾን ወደ እሳትም የምትጠሩኝ ስትኾኑ ለእኔ ምን አለኝ? እሳት መግባት አልፈልግም፦
40፥41 «ወገኖቼም ሆይ! ወደ መዳን የምጠራችሁ ስኾን ወደ እሳትም የምትጠሩኝ ስትኾኑ ለእኔ ምን አለኝ? وَيَا قَوْمِ مَا لِي أَدْعُوكُمْ إِلَى النَّجَاةِ وَتَدْعُونَنِي إِلَى النَّارِ

ወደ ዲኑል ኢሥላም እንድትመጡ ጥሪያችን ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://www.tg-me.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
መንበርከክ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

3፥51 «አሏህ ጌታዬ እና ጌታችሁ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» አላቸው፡፡ إِنَّ اللَّهَ رَبِّي وَرَبُّكُمْ فَاعْبُدُوهُ ۗ هَـٰذَا صِرَاطٌ مُّسْتَقِيمٌ

ፈጣሪ በመጀመሪያ መደብ "ጕልበት ሁሉ “ለ”-እኔ ይንበረከካል" በማለት ይናገራል፦
ኢሳይያስ 45፥23 ጕልበት ሁሉ “ለ”-እኔ ይንበረከካል። כִּי־לִי֙ תִּכְרַ֣ע כָּל־בֶּ֔רֶךְ

"ሊ" לִי֙ ማለት "ለእኔ" ማለት ሲሆን "እኔ" በሚል ተውላጠ ስም መነሻ ላይ ያለው "ለ" የሚል መስተዋድድ መንበርከክ ለእርሱ እንደሆነ ቁልጭ አርጎ ያሳያል፥ "ለ" ቀጥታ የሚንበረከኩለት ማንነት እና ምንነት ነው፦
ሮሜ 14፥11 "ጉልበት ሁሉ "ለ"-እኔ ይንበረከካል"። ὅτι ἐμοὶ κάμψει πᾶν γόνυ, 

"ኩርዮስ" Κύριος ከቀኝ ወደ ግራ የሚነበቡት ቴትራግራማቶን ስለሚያመለክት እና ከኢሳይያስ 45፥23 ላይ ስለተጠቀሰ "ዮድ ሔ ቫቭ ሔ" יְהוָה֮ የተባለውን አብን አመላካች ነው፦
ኤፌሶን 3፥15 ስለዚህ ምክንያት በሰማይ እና በምድር ያለ አባትነት ሁሉ ከሚሰየምበት ከአብ ፊት እንበረከካለሁ። ἐξ οὗ πᾶσα πατριὰ ἐν οὐρανοῖς καὶ ἐπὶ γῆς ὀνομάζεται,

"ከአብ ፊት እንበረከካለሁ" የሚለውን አስምረህ በሰማይ እና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ ለአብ የሚንበረከከው "በ"-ኢየሱስ ስም እንደሆነ ጳውሎስ ተናግሯል፦
ፊልጵስዩስ 2፥10 ይህም በሰማይ እና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ "በ"-ኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ ነው። ἵνα ἐν τῷ ὀνόματι Ἰησοῦ πᾶν γόνυ κάμψῃ ἐπουρανίων καὶ ἐπιγείων καὶ καταχθονίων,

እዚህ አንቀጽ "በ" ለሚለው መስተዋድድ የገባው ቃል "ኤን" ἐν ሲሆን "በኩል" ማለት ነው፥ "ዲይ" δἰ ወይም "ዲያ" διά ከሚል ቃል ጋር ተለዋዋጭ ነው። "ኤን ቱ ኦኖማቲ የሱ" ἐν τῷ ὀνόματι Ἰησοῦ ማለት "በኢየሱስ ስም" ማለት ስለሆነ የተለያዩ ዕትማት በትክክሉ "በኢየሱስ ስም"in the name of Jesus" በማለት አስቀምጠዋል፦
1. American Standard Version
Philippians 2፥10 "in the name of Jesus"
2. Aramaic Bible in Plain English
Philippians 2፥10 "in the name of Jesus"
3. English Revised Version
Philippians 2፥10 "in the name of Jesus"
4. Literal Standard Version
Philippians 2፥10 "in the name of Jesus"
5. Young's Literal Translation
Philippians 2፥10 "in the name of Jesus"

ብዙ ክርስቲያን ሚሽነሪዎች "በኢየሱስ ስም" የሚለው "ለኢየሱስ ስም" በማለት እያጠናገሩ ስለሆነ ትኩረት ሰቶ ማንበብ ያሻል፦
ኤፌሶን 5፥20 ሁልጊዜ ስለ ሁሉ "በ"-ጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንን እና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ። εὐχαριστοῦντες πάντοτε ὑπὲρ πάντων ἐν ὀνόματι τοῦ Κυρίου ἡμῶν Ἰησοῦ Χριστοῦ τῷ Θεῷ καὶ Πατρί,

አሁንም "በ" ለሚለው መስተዋድድ የገባው ቃል "ኤን" ἐν ሲሆን "በኩል" ማለት ነው፥ ጳውሎስ "አምላካችንን እና አባታችንን" ያለው አብን በኢየሱስ ስም ስለማመስገን ብዙ ቦታ ይናገራል፦
ሮሜ 1፥8 አምላኬን “በ”-ኢየሱስ ክርስቶስ አመሰግናለሁ። εὐχαριστῶ τῷ Θεῷ μου διὰ Ἰησοῦ Χριστοῦ 
ሮሜ 7፥25 “በ”-ኢየሱስ ክርስቶስ በጌታችን “ለ”-እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን።χάρις τῷ Θεῷ διὰ Ἰησοῦ Χριστοῦ τοῦ Κυρίου ἡμῶν. 
ሮሜ 16፥27 ብቻውን ጥበብ ላለው ለእግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ እስከ ዘላለም ድረስ ክብር ይሁን! አሜን። μόνῳ σοφῷ Θεῷ, διὰ Ἰησοῦ Χριστοῦ, ᾧ ἡ δόξα εἰς τοὺς αἰῶνας τῶν αἰώνων· ἀμήν.

ሦስቱም አናቅጽ ላይ "በ" ለሚለው የገባው ቃል "ዲያ" διά ሲሆን ምስጋናው "አምላኬ" ለሚለው ብቻውን ጥበብ ላለው ለእግዚአብሔር አብ ነው፦
ቆላስይስ 3፥17 እግዚአብሔር አብን “በ”-እርሱ እያመሰገናችሁ። εὐχαριστοῦντες τῷ Θεῷ Πατρὶ δι’ αὐτοῦ.
ዕብራውያን 13፥15 እንግዲህ ዘወትር “ለ”-እግዚአብሔር የምስጋናን መሥዋዕት ማለት ለስሙ የሚመሰክሩ የከንፈሮችን ፍሬ፥ “በ”-እርሱ እናቅርብለት። δι’ αὐτοῦ οὖν ἀναφέρωμεν θυσίαν αἰνέσεως διὰ παντὸς τῷ Θεῷ, τοῦτ’ ἔστιν καρπὸν χειλέων ὁμολογούντων τῷ ὀνόματι αὐτοῦ.

ሁለቱም አናቅጽ ላይ "በ" ለሚለው የገባው ቃል "ዲይ" δἰ ሲሆን ምስጋናው “ለ”-እግዚአብሔር አብ" ነው፥ "ለ" መስተዋድዱ የሚጠጋው ብቻውን ለሆነ አምላክ እና መድኃኒት ነው፦
ይሁዳ 1፥25 ብቻውን "ለ"-ሆነ አምላክ እና መድኃኒታችን ከዘመን ሁሉ በፊት አሁንም እስከ ዘላለምም ድረስ "በ"-ጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ክብርና ግርማ ኃይልም ሥልጣንም ይሁን! አሜን። μόνῳ Θεῷ Σωτῆρι ἡμῶν διὰ Ἰησοῦ Χριστοῦ τοῦ Κυρίου ἡμῶν δόξα μεγαλωσύνη κράτος καὶ ἐξουσία πρὸ παντὸς τοῦ αἰῶνος καὶ νῦν καὶ εἰς πάντας τοὺς αἰῶνας· ἀμήν.
እዚህ አንቀጽ "በ" ለሚለው የገባው ቃል "ዲያ" διά ሲሆን "በኩል" ማለት ነው፥ ክብርና ግርማ ኃይልም ሥልጣንም ለአብ በክርስቶስ በኩል መሆንን ያሳያል። ይህንን ከተረዳን ዘንድ ኢየሱስ መንበርከኪያ መሣሪያ"Instrument" እንጂ የሚንበረከኩለት ማንነት እና ምንነት አይደለም፥ "ፊልጵስዩስ 2፥10 ላይ መንበርከክ ለኢየሱስ እንደሆነ ያሳያል" የሚለው ሙግት ውኃ የማያነሳ እና የማይቋጥር ሙግት ነው። “በ” አስመላኪ ሲሆን “ለ” ደግሞ ተመላኪ ነው፥ “በ” የሚለውን “ለ” ብሎ ከተረዱት እንግዲያውስ “በ”-ጽዮን” የሚለውን “ለ”-ጽዮን” ብለው መረዳት ይኖርባቸዋል፦
መዝሙር 65፥1 አቤቱ “በ”-ጽዮን ለአንተ ምስጋና ይገባል።  לַמְנַצֵּ֥חַ מִזְמֹ֗ור לְדָוִ֥ד שִֽׁיר׃ לְךָ֤ דֻֽמִיָּ֬ה תְהִלָּ֓ה אֱלֹ֘הִ֥ים בְּצִיֹּ֑ון

ዋናው ነጥብ ጉልበት ሁሉ የሚንበረከክ ለኢየሱስ ስም ሳይሆን በኢየሱስ ስም ለፈጣሪ ነው። ስለዚህ ኢየሱስ አስመላኪ እንጂ ተመላኪ አይደለም፥ ለፈጣሪው ተንበርክኮ የሚያመልክ አካል ተመልሶ ተመላኪ አይሆንም። ኢየሱስ እራሱ በጉልበቱ ተንበርክኮ እና በፊቱ ተደፍቶ ወደ ፈጣሪ ይጸልይ ነበር፦
ማቴዎስ 26፥39 ጥቂትም ወደ ፊት እልፍ ብሎ በፊቱ ወደቀ እና ሲጸልይ። καὶ προελθὼν μικρὸν ἔπεσεν ἐπὶ πρόσωπον αὐτοῦ προσευχόμενος
ሉቃስ 22፥41 ከእነርሱም የድንጋይ ውርወራ የሚያህል ራቀ፥ "ተንበርክኮም" ጸለየ። καὶ αὐτὸς ἀπεσπάσθη ἀπ’ αὐτῶν ὡσεὶ λίθου βολήν, καὶ θεὶς τὰ γόνατα προσηύχετο

ሸብረክ እና ብርክክ ብሎ ለፈጣሪው ሡጁድ የሚወርድ ኢየሱስ እራሱ አምላኪ መሆኑን ይህ ጥቅስ ጉልኅ ማሳያ ነው፥ እንደው ለኢየሱስ ቢንበረከኩለት እንኳን መንበርከክ በእስራኤል ባህል አክብሮትን ለማሳየት ይመጣል፦
2ኛ ነገሥት 1፥13 በኤልያስ ፊት በጒልበቱ "ተንበረከከ"። וַיִּכְרַ֥ע עַל־ בִּרְכָּ֣יו לְנֶ֣גֶד אֵלִיָּ֗הוּ

"ዪክራ" כְרַ֥ע የሚለው የግሥ መደብ "ካራ" כָּרַע ለሚለው አሁናዊ ግሥ ነው፥ ታዲያ አምሳ አለቃው ለኤልያስ በጒልበቱ ስለተንበረከከ ኤልያስን እያመለከው ነበርን? እረ በፍጹም። ዳዊት ለልጁ ለሰሎሞን የምድረ በዳ ዘላኖች እንደሚንበረከኩለት ተናግሯል፦
መዝሙር 72፥9 የምድረ በዳ ዘላኖች በፊቱ ይንበረከካሉ። לְ֭פָנָיו יִכְרְע֣וּ צִיִּ֑ים

"ጺዪ" צִיִּי ማለት "የምድረ በዳ ዘላን" ማለት ሲሆን የጺዪ ብዙ ቁጥር ደግሞ "ጺዪም" צִיִּ֑ים ነው፥ ይህም ቃል የበረሃ ሰውን ወይም የዱር አውሬን ለማመልከት ይመጣል። እዚህ አንቀጽ ላይ "ይንበረከካሉ" ለሚለው የገባው ቃል "ይክራዩ" יִכְרְע֣וּ ሲሆን "ካራ" כָּרַע ማለትም "ተንበረከከ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ነው፥ ስለዚህ መንበርከክ በራሱ አምልኮ አይደለም። ዋናው ነጥባችን "ፊልጵስዩስ 2፥10 ላይ በሰማይ እና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ "በ"-ኢየሱስ ስም የሚንበረከኩት ለአብ እንደሆነ የሚናገር ክፍል ነው" የሚል ሰፊ ሙግት ነው፥ በእርግጥ ለእኛ ለሙሥሊሞች የጳውሎስ ንግግር መረጃ"Information" እንጂ ማስረጃ"Evidence" አይደለም። የአምላካችን የአሏህ ንግግር ማስረጃችን ሲሆን ኢየሱስ የመልእክቱ ጭብጥ «አሏህ ጌታዬ እና ጌታችሁ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» የሚል እንደነበር አሏህ በቅዱስ ቃሉ ነግሮናል፦
3፥51 «አሏህ ጌታዬ እና ጌታችሁ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» አላቸው፡፡ إِنَّ اللَّهَ رَبِّي وَرَبُّكُمْ فَاعْبُدُوهُ ۗ هَـٰذَا صِرَاطٌ مُّسْتَقِيمٌ

ፍጡር ከማምልከ ነጻ ወጥታችሁ አሏህን በብቸኝነት እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://www.tg-me.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ቃቢል

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

5፥27 በእነርሱም ላይ የአደምን ሁለት ልጆች ወሬ ቁርባንን ባቀረቡ እና አሏህ ከአንደኛቸው ተቀብሎ ከሌላው ባልተቀበለ ጊዜ የኾነውን በእውነት አንብብላቸው፡፡ وَاتْلُ عَلَيْهِمْ نَبَأَ ابْنَيْ آدَمَ بِالْحَقِّ إِذْ قَرَّبَا قُرْبَانًا فَتُقُبِّلَ مِنْ أَحَدِهِمَا وَلَمْ يُتَقَبَّلْ مِنَ الْآخَرِ

በባይብል በግልጽ እና በማያሻማ መልኩ አዳም ከሚስቱ ከሔዋን ጋር ተራክቦ በመፈጸም የበኵር ልጅ ቃየን ፀንሳ ወለደች፦
ዘፍጥረት 4፥1 አዳምም ሚስቱን ሔዋንን አወቀ፤ ፀነሰችም፥ ቃየንንም ወለደች። እርስዋም፦ “ወንድ ልጅ ከያህዌህ አገኘሁ” አለች። וְהָ֣אָדָ֔ם יָדַ֖ע אֶת־חַוָּ֣ה אִשְׁתֹּ֑ו וַתַּ֙הַר֙ וַתֵּ֣לֶד אֶת־קַ֔יִן וַתֹּ֕אמֶר קָנִ֥יתִי אִ֖ישׁ אֶת־יְהוָֽה׃

እዚህ አንቀጽ "ቃየን" ለሚለው የገባው ቃል "ካዬን" קַיִן ሲሆን "የተገኘ" ማለት ነው፥ "አገኘሁ" ለሚለው የገባው ቃል "ካኒቲ" קָנִ֥יתִי ሲሆን "ካዬን" קַיִן የሚለው የስም መደብ ሆነ "ካኒቲ" קָנִ֥יתִי የሚለው የሥም መደብ ሥርወ ቃሉ "ካና" קָנָה ነው።

ይህ ሆኖ ሳለ “ወንድ ልጅ ከያህዌህ አገኘሁ” ያለችውን በታርገም ዮናታን ላይ "ወንድ ልጅ ከጌታ መልአክ አገኘሁ” በማለት ያስቀምጣል፦
ታርገም ዮናታን ዘፍጥረት 4፥1 አዳምም መልአኩን የፈለገችው ሚስቱን ሔዋንን አወቀ፤ ፀነሰችም፥ ቃየንንም ወለደች። እርስዋም፦ “ወንድ ልጅ ከጌታ መልአክ አገኘሁ” አለች። וְאָדָם יְדַע יַת חַוָה אִיתְּתֵיהּ דַהֲוָה חֲמֵידַת לְמַלְאָכָא וְאַעֲדִיאַת וִילֵידַת יַת קַיִן וַאֲמָרַת קָנִיתִי לְגַבְרָא יַת מַלְאָכָא דַיְיָ

"መልአኩን የፈለገችው ሚስቱን" የሚለውን አስምርበት! ሔዋን ልጁን ያገኘችው ከአዳም ሳይሆን ከምትፈልገው ከመልአኩ ሰለሆነ "ወንድ ልጅ ከጌታ መልአክ አገኘሁ" አለች። ሳጥናኤል የተባለው የጌታ መልአክ ሥጋ ሆኖ ያ ሥጋ እባብ ሲሆን በዔድን ገነት ውስጥ የሔዋንን ክብረ ንጽሕና ወስዶ አስረገዛት፦
ታርገም ዮናታን ዘፍጥረት 3፥6 የሞት መልአክን ሳማኤልን አየችው እና ፈራች፥ እሷ ግን ዛፉ ለመብላት ጥሩ እንደ ሆነ አውቃለች። וְחָמַת אִתְּתָא יַת סַמָאֵל מַלְאָךְ מוֹתָא וּדְחִילַת וְיַדְעַת אֲרוּם טַב אִילָנָא לְמֵיכַל וַאֲרוּם אָסוּ הוּא

"ሳማኤል" סַמָּאֵל ማለት "የአምላክ መርዝ" ማለት ሲሆን ይህ የሞት መልአክ ሳማኤልን ሔዋንን ያፀነሰ የቃየን አባት ተብሎ የሚታመን በእባብ ሥጋ የተሠገወ መልአክ ነው። ሔዋን ከእባቡ ጋር ማግጣ ቃየንን የወለደችውን የሚሉት ይህንን ዳራ ይዘው ነው፦
1ኛ ዮሐንስ 3፥12 ከክፉው እንደ ነበረ ወንድሙንም እንደ ገደለ እንደ ቃየል አይደለም።

"ቃየል ከክፉው ሰይጣን ነበረ" ማለት አንዳንድ በኋላ የአይሁድ መጻሕፍት "የቃየን አባት ራሱ ዲያብሎስ ነው" ይላሉ፦
"የቃየንን ኃጢአተኛነት የአይሁድ ትውፊት በሰፊው አብራርቷል አስምሮበታል፥ እርሱ ከክፉው ነበረ። ነፍሰ ገዳይ የዲያብሎስ ልጅ ነበር(ቁ. 10)፥ ከዲያብሎስ የመጀመሪያ ሥራዎቹ አንዱ ለአዳም ሞት ማምጣት ነበር(ዮሐ 8፥44 ላይ ያለውን ማስታወሻ ተመልከት!)። አንዳንድ በኋላ የአይሁድ መጻሕፍት "የቃየን አባት ራሱ ዲያብሎስ ነው" ይላሉ"።
The NIV Cultural Backgrounds Study Bible 1st John 3፥12

"የተወለደው ልጅ ቃየን የእባቡ ልጅ ነው" የሚል ትርክት ከጥንት ጀምሮ የመጣው በዚህ ምክንያት ነው፦
"ነገር ግን ሔዋን ከወደቀች በኋላ ሰይጣን በእባቡ ተመስሎ ወደ እርስዋ ቀረበ፥ እናም የአንድነታቸው ፍሬ ቃየን ነበር። በአምላክ ፊት ያመፁ የክፉ ትውልድ ሁሉ አባት ሲሆን በአምላክ ላይ ተነሳ። ቃየን በሱራፌል መገለጡ የተገለጠ የመልአኩ ሳማኤል ዘር ነው፥ በተወለደ ጊዜ ከሔዋን፦ "ወንድ ልጅ ከጌታ መልአክ አገኘሁ" የሚል ድምፅ ተሰምቷል፥ ቃየንን ሔዋን ባረገዘች ጊዜ አዳም ከእርሷ ጋር አልነበረም"።
Legends of the Jews 1:3

የፊሊጶስ ወንጌል ይህንን ዳራ እና ፍሰት ይዞ "ቃየን በዝሙት ተወለደ፥ የእባቡ ልጅ ነበረ" ይለናል፦
የፊሊጶስ ወንጌል 61፥5 ዝሙት መጀመርያው ተጀመረ፥ ከዚያ ግዲያ ቀጠለ። ቃየን በዝሙት ተወለደ፥ የእባቡ ልጅ ነበረ። እርሱ ልክ እንደ አባቱ ነፍሰ ገዳይ ሆነ።

በሁለተኛ ክፍለ ዘመን የተገኘው የፊሊጶስ ወንጌል ቅጂ በቫሊንቲንዮስ የተዘጋጀ ሲሆን "ቃየልን ሔዋን ከእባቡ የፀነሳችውን በዝሙት ነው" የሚለውን እሳቤ ኢራኒየስ ዘሊዮን"Irenaeus of Lyon" በማውገዝ ቫሊንቲንዮስ የሚለውን እንዲህ ያቀርብልናል፦
"ቀድሞ ራሱን እባብ አባት ብሎ የሚጠራው ውሸታም ነበረ፥ እናም ወንድ እና የመጀመሪያዋ ሴት ከዚህ በፊት ሲኖሩ ይህቺ ሴት ሔዋን ዝሙት በመፈጸም ኃጢአት ሠርታለች"።
Against Heresies (St. Irenaeus) Book I(1) Chapter 30 Number 7

በቫሊንቲንዮሳውያን ዘንድ ዲያብሎስ ከመጀመሪያ ከሔዋን ጋር ኃጢአትን አድርጓል ተብሎ ይታመናል፦
1ኛ ዮሐንስ 3፥8 ኃጢአትን የሚያደርግ ከዲያብሎስ ነው፥ ዲያብሎስ ከመጀመሪያ ኃጢአትን ያደርጋልና።

በክርስትና እና በአይሁድ እሳቤ የመላእክት ጋብቻ የሚባል ቅሰጣዊ ትምህርት አለ። ይህንን ሊንክ ያስፈንጥሩ፦ https://www.tg-me.com/Wahidcom/1849

ወደ ዲኑል ኢሥላም ስንመጣ "ቃቢል" قَابِيْل ማለት "ቃየን"Cain" ማለት ሲሆን የአደም እና የሐዋእ የበኵር ልጅ ነው፥ "ሃቢል" هَابِيل ማለት "አቤል"Abel" ማለት ሲሆን ሁለተኛው የአደም እና የሐዋእ ልጅ ነው። "ነበእ" نَبَأ ማለት "ወሬ" ማለት ሲሆን ለነቢይ የሚወርድለት "ግልጠተ መለኮት ነው፥ "ነቢይ" نَبِيّ አሏህ የሩቅ ወሬ የሚተርክለት ሰው ነው። አምላካችን አሏህ አላፊ የሆነውን የአደምን ሁለት ልጆች የሩቅ ወሬ በተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" ላይ እንዲህ ሲል ይተርካል፦
5፥27 በእነርሱም ላይ የአደምን ሁለት ልጆች ወሬ ቁርባንን ባቀረቡ እና አሏህ ከአንደኛቸው ተቀብሎ ከሌላው ባልተቀበለ ጊዜ የኾነውን በእውነት አንብብላቸው፡፡ وَاتْلُ عَلَيْهِمْ نَبَأَ ابْنَيْ آدَمَ بِالْحَقِّ إِذْ قَرَّبَا قُرْبَانًا فَتُقُبِّلَ مِنْ أَحَدِهِمَا وَلَمْ يُتَقَبَّلْ مِنَ الْآخَرِ

"የአደምን ሁለት ልጆች" የሚለው ይሰመርበት! ይህ አንቀጽ ቃቢል የአደም ልጅ መሆኑን ፍንትው እና ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፥ ስለዚህ ቃቢል የኢብሊሥ ልጅ ሳይሆን የአደም ልጅ ነው። በእናታችን ሐዋእ ላይ የቀጠፉትን ቀጣፊዎች አምላካችን አሏህ የእጃቸውን ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://www.tg-me.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ዲኑል ኢሥላም ከአሏህ ዘንድ ሰዎች የሚድኑበት ምርጫ እንጂ ከባጢል ውስጥ የምናማርጠው አማራጭ በፍጹም አይደለም።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
ወደ ቻናሉ የምትገቡ አዳዲስ አንባቢያን ከላይ ጀምሩ፦ https://www.tg-me.com/Wahidcom/18
ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
Video
የኦርቶዶክስ ትርምስ

በልጅነታችን "ታቦት በውስቴታ ኦሪት በውስቴታ
ውቱረ ይከድንዋ በወርቅ" ወይም "ውስቴታ ታቦት በውስቴታ ኦሪት በውስቴታ ይኬልልዋ በወርቅ ይኬልልዋ" ሲባል ያደግንበትን ነገር መምህር ብርሃኑ አድማስ "የብሉይ ኪዳን ታቦት የለንም" ሲሉ የነበረው ወይስ እኛ ሳናውቅ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ እድሳት አረገች? በተቃራኒው መምህር ዘበነ ለማ ደግሞ "የብሉይ ኪዳን እና የአዲስ ኪዳን ታቦት ልዩነት እንደሌለው እና የብሉይ ኪዳን ታቦት በአዲስ ኪዳን የቀጠለ ነው" ብለዋል።

በእርግጥ ታቦት በብሉይ ኪዳን ነበረ፥ ያ ታቦት መሠዊያ ወይም ጠረጴዛው ሳይሆን እራሱን የቻለ የጽላት ማስቀመጫ ሳጥን ነው፦
ዘጸአት 26፥34 በቅድስተ ቅዱሳኑም ውስጥ የስርየት መክደኛውን በምስክሩ ታቦት ላይ አድርግ።
ዘዳግም 10፥5 ጽላቶችንም በሠራሁት ታቦት ውስጥ አደረግኋቸው።

ታቦት መቀመጫው በቅድስተ ቅዱሳኑ ውስጥ ነው፥ ጠረጴዛ ደግሞ በቅድስት ውስጥ ሲሆን የሚቃጠል መሥዋዕት መሠዊያ ደግሞ በአደባባይ ላይ አሊያም ከሰፈር ውጪ ያለ ነበር፦
ዕብራውያን 9፥2 ቅድስት በምትባለው ውስጥ መቅረዙ እና "ጠረጴዛው" የመስዋዕቱም ኅብስት ነበረባት።
ዘጸአት 17፥15 ሙሴም መሠዊያ ሠራ፥ ስሙንም፡ ይህዌህ ንሲ፡ ብሎ ጠራው።
ዕብራውያን 13፥11 ሊቀ ካህናት ስለ ኃጢአት ወደ ቅድስት የእንስሶችን ደም ያቀርባልና፤ ሥጋቸው ግን ከሰፈሩ ውጭ ይቃጠላል።

ስለዚህ አዲስ ኪዳን ላይ ታቦት የሚባል በጉባኤ መካከል ያለ የለም፥ ጠረጴዛ እና መሠዊያ ደግሞ ለየቅል የሆኑ ነገሮች ሲሆኑ "ታቦት" ተብለው እንደተጠሩ የሚያሳይ ምንም ዓይነት የአዲስ ኪዳን ፍንጭ የለም። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ የወከለችው መምህር ማንን ነው? "የብሉይ ኪዳን ታቦት የለንም" የሚለውን መምህር ብርሃኑ አድማስን ወይስ "የብሉይ ኪዳን እና የአዲስ ኪዳን ታቦት ልዩነት እንደሌለው እና የብሉይ ኪዳን ታቦት በአዲስ ኪዳን የቀጠለ ነው" የሚለውን መምህር ዘበነ ለማ?
የጌቶች ጌታ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

6፥164 በላቸው «እርሱ አላህ የሁሉ ነገር ጌታ ሲሆን ከአላህ በቀር ሌላን ጌታ እፈልጋለሁን? ነፍስም ሁሉ በራሷ ላይ እንጅ ክፉን አትሠራም፡፡ قُلْ أَغَيْرَ ٱللَّهِ أَبْغِى رَبًّۭا وَهُوَ رَبُّ كُلِّ شَىْءٍۢ ۚ وَلَا تَكْسِبُ كُلُّ نَفْسٍ إِلَّا عَلَيْهَا

ባይብል ሴት ለባሏ እንድትገዛ ይናገራል፥ ሕግ ደግሞ "ፈቃድሽም ወደ ባልሽ ይሆናል፥ እርሱም "ገዥሽ" ይሆናል" ይላልና፦
1ኛ ቆሮንቶስ 14፥34 ሴቶች በማኅበር ዝም ይበሉ፥ ሕግ ደግሞ እንደሚል እንዲገዙ እንጂ እንዲናገሩ አልተፈቀደላቸውምና።
ዘፍጥረት 3፥16 ፈቃድሽም ወደ ባልሽ ይሆናል፥ እርሱም "ገዥሽ" ይሆናል።

ወንድ የሴት "ራስ" ነው፥ ሴት ባሏን "ጌታ" እያለች ከታዘዘች ትሸለማለች፦
1ኛ ጴጥሮስ 3፥5 ቅዱሳት ሴቶች ደግሞ ለባሎቻቸው ሲገዙ ተሸልመው ነበርና፥ እንዲሁም ሣራ ለአብርሃም፦ ጌታ" ብላ እየጠራችው ታዘዘችለት።
1 ቆሮንቶስ 11፥3 ነገር ግን የወንድ ሁሉ ራስ ክርስቶስ፥ የሴትም ራስ ወንድ፥ የክርስቶስ ራስ አምላክ እንደ ሆነ ልታውቁ እወዳለሁ። Θέλω δὲ ὑμᾶς εἰδέναι ὅτι παντὸς ἀνδρὸς ἡ κεφαλὴ ὁ Χριστός ἐστιν, κεφαλὴ δὲ γυναικὸς ὁ ἀνήρ, κεφαλὴ δὲ τοῦ Χριστοῦ ὁ Θεός.

"የወንድ ሁሉ ራስ ክርስቶስ" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! ወንዶች ሁሉ የሴቶች ራሶች ከሆኑ የወንዶች ሁሉ ራስ ክርስቶስ ነው፥ "ራስ" እና "ጌታ" ተለዋዋጭ ቃላት ናቸው፦
የሐዋርያት ሥራ 5፥31 ይህን አምላክ ለእስራኤል ንስሐን የኃጢአትንም ስርየት ይሰጥ ዘንድ "ራስ" እና መድኃኒትም "አድርጎ" በቀኙ ከፍ ከፍ አደረገው። τοῦτον ὁ Θεὸς Ἀρχηγὸν καὶ Σωτῆρα ὕψωσεν τῇ δεξιᾷ αὐτοῦ τοῦ δοῦναι μετάνοιαν τῷ Ἰσραὴλ καὶ ἄφεσιν ἁμαρτιῶν.
የሐዋርያት ሥራ 2፥36 ኢየሱስን አምላክ ጌታም ክርስቶስም እንዳደረገው የእስራኤል ወገን ሁሉ በእርግጥ ይወቅ። ἀσφαλῶς οὖν γινωσκέτω πᾶς οἶκος Ἰσραὴλ ὅτι καὶ Κύριον αὐτὸν καὶ Χριστὸν ἐποίησεν ὁ Θεός, τοῦτον τὸν Ἰησοῦν.

አንዱ አምላክ ኢየሱስን "ራስ" እና "ጌታ" ካደረገው ኢየሱስ "የራሶች ራስ" "የጌቶች ጌታ" ነው። ክርስቶስ "የጌቶች ጌታ" የተባለው በአንጻራዊ ደረጃ ስለሆነ እርሱ እራሱ ከእርሱ በላይ ራስ አለው፥ ይህም ኢየሱስን ራስ ያደረገው አንዱ አምላክ ነው፦
1 ቆሮንቶስ 11፥3 ነገር ግን የወንድ ሁሉ ራስ ክርስቶስ፥ የሴትም ራስ ወንድ፥ የክርስቶስ ራስ አምላክ እንደ ሆነ ልታውቁ እወዳለሁ። Θέλω δὲ ὑμᾶς εἰδέναι ὅτι παντὸς ἀνδρὸς ἡ κεφαλὴ ὁ Χριστός ἐστιν, κεφαλὴ δὲ γυναικὸς ὁ ἀνήρ, κεφαλὴ δὲ τοῦ Χριστοῦ ὁ Θεός.

"የክርስቶስ ራስ አምላክ እንደ ሆነ ልታውቁ እወዳለሁ" ከተባለ የኢየሱስ ራስነት በመደረግ ላይ የተመሠረተ ነው፥ ምክንያቱም "ራስ" አድርጎ በቀኙ ከፍ ከፍ አደረገው" ስለሚል ነው። "ራስ" ተብሎ የገባው ቃል "አርኬጎስ" ἀρχηγός ሲሆን "አለቃ" "ገዥ" ማለት ነው፦
ራእይ 1፥5 የምድርም ነገሥታት "ገዥ" ከሆነ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ እና ሰላም ለእናንተ ይሁን። καὶ ὁ ἄρχων τῶν βασιλέων τῆς γῆς. Τῷ ἀγαπῶντι ἡμᾶς 

"የምድርም ነገሥታት ገዥ" ማለት "የጌቶች ጌታ" ማለት ነው፥ ሁሉንም ከእግሩ በታች ያስገዛለት አንዱ አምላክ ሲሆን ኢየሱስ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ለአንድ አምላክ ይገዛል፦
ኤፌሶን 1፥22 ሁሉንም ከእግሩ በታች አስገዛለት።
1 ቆሮንቶስ 15፥27 ሁሉን ከእግሩ በታች አስገዝቶአልና። ነገር ግን፦ "ሁሉ ተገዝቶአል" ሲል፥ ሁሉን ካስገዛለት በቀር መሆኑ ግልጥ ነው።
1 ቆሮንቶስ 15፥28 ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት ይገዛል።

ኢየሱስን "ራስ" "ገዥ" "ጌታ" ያደረገው አንዱ አምላክ ጌትነቱ የባሕርይ ሲሆን ኢየሱስ ግን "የጌቶች ጌታ" የተባለው "የነገሥታት ንጉሥ" በተባለበት ሒሣብ ነው፦
ራእይ 17፥14 በጉ "የጌቶች ጌታ እና "የነገሥታት ንጉሥ" ስለ ሆነ እነርሱን ድል ይነሣል።
ሉቃስ 1፥32 ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል።

ጌታ አምላክ የአባቱን የዳዊትን ንግሥና ከሰጠው እርሱ "የነገሥታት ንጉሥ" የተባለው በአንጻራዊ ደረጃ እና በሥዩም ሢመት ነው። በባይብል "የነገሥታት ንጉሥ" የተባለው ኢየሱስ ብቻ ሳይሆን አርጤክስስ እና ናቡከደነጾርም ጭምር ናቸው፦
ዕዝራ 7፥12 "ከ-"ነገሥታት ንጉሥ" ከአርጤክስስ ለሰማይ አምላክ ሕግ ጸሐፊ ለካህኑ ለዕዝራ ሙሉ ሰላም ይሁን።
ዳንኤል 2፥37 አንተ ንጉሥ ሆይ! የሰማይ አምላክ መንግሥትን፣ ኃይልን፣ ብርታትንና ክብርን የሰጠህ "የነገሥታት ንጉሥ" አንተ ነህ።

ሰው ሰውን የሚገዛው መገዛዛት የግብር መገዛዛት ሲሆን አምላክ ሰውን የሚገዛበት መገዛዛት የባሕርይ መገዛዛት ነው። የኢየሱስ ጌታ የሰማይና የምድር ጌታ ነው፦
ማቴዎስ 11፥25 በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መልሶ እንዲህ አለ፦ አባት ሆይ! የሰማይና የምድር ጌታ።
የሐዋርያት ሥራ 17፥24 ዓለሙንና በእርሱ ያለውን ሁሉ የፈጠረ አምላክ እርሱ የሰማይና የምድር ጌታ ነውና እጅ በሠራው መቅደስ አይኖርም።
የሐዋርያት ሥራ 2፥36 ኢየሱስን አምላክ ጌታም ክርስቶስም እንዳደረገው የእስራኤል ወገን ሁሉ በእርግጥ ይወቅ። ἀσφαλῶς οὖν γινωσκέτω πᾶς οἶκος Ἰσραὴλ ὅτι καὶ Κύριον αὐτὸν καὶ Χριστὸν ἐποίησεν ὁ Θεός, τοῦτον τὸν Ἰησοῦν.
እዚህ አንቀጽ ላይ "አምላክ" ባለቤት ሲሆን "ኢየሱስ" ተሳቢ ነው፥ በባለቤት እና በተሳቢ መካከል "እንዳደረገው" የሚል ተሻጋሪ ግሥ አለ። ጌታ አድራጊው አንዱ አምላክ ሲሆን ጌታ ተደራጊው ኢየሱስ ነው፥ አምላክ ኢየሱስን ጌታ ካረደገው የኢየሱስ ጌትነት መነሾ እና ጅማሮ ያለው ነው። ጌታ ከመደረጉ በፊት በባዶነት ስለሚቀደም ጌትነቱ ሥልጣን እና ሹመት ያሳያል፥ አንዱ አምላክ ኢየሱስን የጌቶች ጌታ ካደረገው ዘንዳ የመሢሑ ጌትነት የማዕረግ ነው። "አዶናይ" אֲדֹנָ֥י ማለት "ጌታዬ" ማለት ነው፥ መሢሑ በትንቢት መነጽር ያህዌህን "ጌታዬ" ብሎታል፦
ኢሳይያስ 61፥1 "የ-"ጌታዬ" የያህዌህ መንፈስ በእኔ ላይ ነው፥ ለድሆች የምሥራችን እሰብክ ዘንድ ያህዌህ ቀብቶኛልና። ר֛וּחַ אֲדֹנָ֥י יְהוִ֖ה עָלָ֑י יַ֡עַן מָשַׁח֩ יְהוָ֨ה אֹתִ֜י לְבַשֵּׂ֣ר עֲנָוִ֗ים

እዚህ አንቀጽ ላይ "አዶናይ" אֲדֹנָ֥י ማለት "ጌታዬ" ማለት ከሆነ ኢየሱስ አምላኩን "ጌታዬ" ማለቱ በራሱ የሚገዛለት ጌታ እንዳለው አመላካች ነው። ኢየሱስ በትንቢት መነጽር የፈጠረው ጌታ እንዳለው ተናግሯል፦
ምሳሌ 8፥22 "ጌታ" በቀድሞ ተግባሩ "ፈጠረኝ"። κύριος ἔκτισέν με ἀρχὴν ὁδῶν αὐτοῦ εἰς ἔργα αὐτοῦ

በግሪክ ሰፕቱአጀንት እዚህ አንቀጽ ላይ "ፈጠረኝ" ለሚለው የገባው ቃል "ኤክቲሴን ሜ" ἔκτισέν με ሲሆን፣ በዕብራይስጥ ማሶሬት "ቃናኒ" קָ֭נָנִי ሲሆን፣ በግዕዝ ደግሞ "ፈጠረኒ" ነው፥ ቀደምት የቤተክርስቲያን አበው ምሳሌ 8፥22 ላይ "ፈጠረኝ" የሚለው ኢየሱስ እንደሆነ ያለምንም ልዩነት በወጥ ፍሰት አብራርተዋል።
ኢየሱስን የፈጠረ ጌታ ጌትነቱ የባሕርይ ሲሆን የዓለማቱ ጌታ ነው፥ በጌትነቱ ላይ ባርነት የሌለበት ይህ ጌታ ኢየሱስን "ባሪያዬ" ይለዋል፦
ኢሳይያስ 42፥1 እነሆ ደግፌ የያዝሁት ባሪያዬ፤ ነፍሴ ደስ የተሰኘችበት ምርጤ፤ በእርሱ ላይ መንፈሴን አድርጌአለሁ፥ እርሱም ለአሕዛብ ፍርድን ያወጣል። הֵ֤ן עַבְדִּי֙ אֶתְמָךְ־בֹּ֔ו בְּחִירִ֖י רָצְתָ֣ה נַפְשִׁ֑י נָתַ֤תִּי רוּחִי֙ עָלָ֔יו מִשְׁפָּ֖ט לַגֹּויִ֥ם יֹוצִֽיא׃

በጌትነቱ ላይ ባርነት ያለበት ኢየሱስ የባሕርይ ጌታ አለመሆኑን ይህ ጥቅስ በቂ አስረጅ ነበር። ማርያም እና ዮሴፍ ኢየሱስ በጌታው ፊት ሊያቆሙት ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት፦
ሉቃስ 2፥24 "በጌታ ፊት ሊያቆሙት"፥ በጌታም ሕግ፦ “ሁለት ዋሊያ ወይም ሁለት የርግብ ጫጩቶች፡” እንደ ተባለ፥ መሥዋዕት ሊያቀርቡ ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት።

"በጌታ ፊት ሊያቆሙት" የሚለው ይሰመርበት! የተወሰደው ኢየሱስ እና ጌታው በማንነት ሆነ በምንነት ሁለት ለየቅል የሆኑ ሃልዎት ናቸው።
ኢየሱስ ከአሏህ የተሰጠው ተልእኮ "ጌታዬን እና ጌታችሁን አሏህን አምልኩ" የሚል ነበር፦
5፥117 በእርሱ ያዘዝከኝን ቃል "ጌታዬን እና ጌታችሁን አሏህን አምልኩ" ማለትን እንጂ ለእነርሱ ሌላ አላልኩም፡፡ مَا قُلْتُ لَهُمْ إِلَّا مَا أَمَرْتَنِي بِهِ أَنِ اعْبُدُوا اللَّهَ رَبِّي وَرَبَّكُمْ

"የባሕርይ ጌታ" ማለት "በራሱ የተብቃቃ እና ጌትነቱ ከማንም ያላገኘው የባሕርይ ገንዘቡ የሆነ ጌታ" ማለት ነው፥ አሏህ የሁሉ ነገር ጌታ ሲሆን ጌትነቱ የባሕርይ ነው፦
6፥164 በላቸው «እርሱ አሏህ የሁሉ ነገር ጌታ ሲሆን ከአሏህ በቀር ሌላን ጌታ እፈልጋለሁን? ነፍስም ሁሉ በራሷ ላይ እንጅ ክፉን አትሠራም፡፡ قُلْ أَغَيْرَ ٱللَّهِ أَبْغِى رَبًّۭا وَهُوَ رَبُّ كُلِّ شَىْءٍۢ ۚ وَلَا تَكْسِبُ كُلُّ نَفْسٍ إِلَّا عَلَيْهَا

አምላካችን አሏህ "ጌታ" የተባለበት ቃል "ረብ" رَّبّ ሲሆን አሏህ ብቻውን ፍጥረትን ፈጥሮ፣ ብቻውን ሙሐከማትን አውጥቶ፣ ብቻውን በፍርዱ ቀን ባወጣው ሙሐከማት የሚፈርድ ነው። እንግዲህ ኢየሱስ ጌታ ካለው፣ ለጌታው ባሪያ ከሆነ፣ ጌትነቱ በመደረግ ላይ የተመሠረተ መነሻ እና ጅማሮ ካለው እንግዲያውስ በጌትነቱ ባርነት የሌለበትን የባሕርይ ጌታ አሏህን በብቸኝነት አምልኩ! እንደ ኢየሱስ ለጌታችን ባሪያ መሆን ምንኛ መታደል ነው? ስለዚህ የኢየሱስን ጌታ እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። ጌታችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://www.tg-me.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኢየሱስ አምላክን በማወቅ እና በመስገድ ያመልከው ነበር፦
ዮሐንስ 4፥22 እናንተስ ማታውቁትን ታመልካላችሁ፥ እኛ መዳን ከአይሁድ ነውና የምናውቀውን "እናመልካለን"። ὑμεῖς προσκυνεῖτε ὃ οὐκ οἴδατε, ἡμεῖς προσκυνοῦμεν ὃ οἴδαμεν, ὅτι ἡ σωτηρία ἐκ τῶν Ἰουδαίων ἐστίν·

"እናመልካለን" የሚለው ይሰመርበት! የሚመለከውም ዐውዱ ላይ አብ ብቻ ነው። የእስክንድርያው ቄርሎስ ዮሐንስ 2፥22 በፈሠረው ተፍሢሩ ላይ፦
"ስለዚህም ሰው ሆኖ አምልኳል"therefore He worshippeth as man"
በማለት እንቅጩን ፍርጥ አርጎ አምላኪ መሆኑን ተናግሯል። የሚያመልከው ልክ እንደ እኛ ሡጁድ በግባሩ በመደፋት ነው። ማቴዎስ 26፥39 ላይ "በፊቱ ወደቀ" የሚለውን ግዕዙ "ሰገደ በገጹ" ይለዋል፦
ማቴዎስ 26፥39 ወተአተተ ሕቀ እምኔሆሙ ወ-"ሰገደ በገጹ" ወጸለየ ወይቤ፦ “አቡየ፡ እመሰ ይትከሀል ይኅልፍ እምኔየ ዝንቱ ጽዋዕ፡ ወባሕቱ ፈቃደ ዚኣከ ይኩን፡ ወአኮ ፈቃደ ዚኣየ።”

"ሰገደ" በግዕዝ አላልታችሁ "ገ" ፊደልን ስታነቡት በዐማርኛ "ሰገደ" አጥብቃችሁ "ገ" ፊደልን ስታነቡት ማለት ነው፥ አንድምታውም፦ "ግንባሩን ምድር አስነክቶ ሰገደ" ይለናል፦
የማቴዎስ ወንጌል 26፥39 አንድምታ
"ከዚያ ጥቂት እልፍ ብሎ ግንባሩን ምድር አስነክቶ ሰገደ"።

ግንባሩን ምድር አስነክቶ ከሰገደ አምላኪ እንጂ ተመላኪ መሆን የለበትም። በተመሳሳይ ማርቆስ 14፥35 እና ሉቃል 22፥41 ግዕዙን እና አንድምታውን ተመልከት! ከምድር ከሰገደ ሰጋጅ እንጂ ተሰጋጅ መሆን የለበትም። ርኩዕ በማድረግ ሸብረክ እና ብርክክ ብሎ ማጎንበሱ ለአንድ አምላክ የሚቀርብ መጎባደድ፣ ማሸርገድ፣ ማጎብደድ ነው፥ ይህ በውጥን የሚቀርብ አምልኮ ነው።
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ቅድሚያ ከዚህ በፊት ስለ መገዛዛት የጻፉትኩትን አንብቡት፦
የባሕርይ መገዛዛት
የግብር መገዛዛት

ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 120 ቁጥር 13
"ሥጋ ለቃል ይታዘዛል" የሚል ቢኖር ውጉዝ ይሁን"።

ሥጋ ለቃል የማይገዛ ከሆነ ክርስቶስ ገዥ እና ተገዥ እንዴት ይሆናል?
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 124 ቁጥር 18
"እኛስ ይህን አንድ ወልድን አምላክ ሰው፣ ገዥ ተገዥ፣ ሠዋዒ ተሠዋዒ፣ ፍጡር ፈጣሪ ሆኖ እናገኘዋለን"።

"ገዥ ተገዥ" ከሆነ የሚገዛው ለአብ ብቻ ከሆነ ወልድ ለራሱ አምላክነት የማይገዛ ከሆነ ወልድን የማያካትት መገዛት ምን ዓይነት ነው? ወልድ ለራሱ አምላክነት ከተገዛ እራሱን ያምልካል ማለት ነውና ይህም ከድጡ ወደ ማጡ ነው።
ከዚህ ሁሉ ጣጣ ወደ ኢሥላም ኑ ና አንዱን አምላክ አሏህን አምልኩ! አሏህ በአምላክነቱ ሰውነት የሌለበት ነው።
በሲዳሚኛ ደርሥ ተለቋም። ሲዳማዎች አንብቡ፦ https://www.tg-me.com/wahidcomsidamo/77
ሰው አምላክ ሆነ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

5፥17 እነዚያ "አሏህ እርሱ የመርየም ልጅ አል መሢሕ ነው" ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ

ዐበይት አበው "አምላክ ሰው ሆነ" ብቻ ሳይሆን "ሰው አምላክ ሆነ" ብለው ያምናሉ፥ በጣም ሥመ ጥር እና ገናና የቤተክርስቲያን አባት ዮሐንስ አፈ ወርቅ"John Chrysostom" እንዲህ ይለናል፦
"አምላክ ሰው ሆነ ሰውም አምላክ ሆነ"።
St.John Chrysostom homily 11 on first Timothy 1 Timothy Chapter 3 Number 16

ድንግል ማርያም ማኅፀን ውስጥ የተፈጠረው ሰው "አምላክ ሆነ" የሚለው ትምህርት በሰፊው በአበው የሚነገር ነው፥ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ"Gregory of Nazianzus" እራሱ "ሰብእ ዘኮነ አምላክ" በማለት "ሰው አምላክ ሆነ" ይለናል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 61 ቁጥር 23
"ሰው አምላክ ሆነ"

አንድምታ ላይም "አምላክ ሰው ሆነ" የሚሉ ምንባባት በሰፊው አሉ፦
ዮሐንስ 2፥14 አንድምታ፦ "አምላክ ሰው ሆነ፥ ሰው አምላክ ሆነ" እያሉ ርደቱን እና ዕርገቱን ለመንገር።
ሉቃስ 2፥14 አንድምታ፦ "አምላክ ለሆነ ሥጋ ከሥላሴ ጋር በአንድነት ምስጋና ይገባዋል፥ ወሰላም በምድር "ሰው አምላክ ሆነ" እያሉ።

የሚገርመው ቄርሎስ ዘእስክንንድርያ"Cyril of Alexandria" በድንግል ማርያም ማኅፀን ውስጥ የተፈጠረው ሥጋ "አምላክ ነው" በማለት ተናግሯል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 78 ቁጥር 31
"ዳግመኛ የጌታችን የክርስቶስ ሥጋ አምላክ እንደሆነ እንናገራለን"።

ከፍጡር የሚገኝ ሥጋ ፍጡር ሆኖ ሳለ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ"Athanasius of Alexandria" ሳያቅማማ "የባሕርይ አምላክ ነው" በማለት ይናገራል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 29 ቁጥር 19
"ከእመቤታችን ከቅድስት ከድንግል ማርያም የነሳው ይህ ሥጋም እውነተኛ የባሕርይ አምላክ ነው"።

ከአምላክ የማይገኝ ፍጡር ሥጋ በተቃራኒ ከፍጡር የተገኘ ሥጋ "የባሕርይ አምላክ ነው" ማለት የጤና ነውን? ፈጣሪ ድንግል ማርያም ማኅፀን ውስጥ ከፈጠረው ፍጡር ጋር አምላክነቱን አንድ ቢያደርግ ኖሮ እራሱ የራሱን ባሕርይ እያጋራ ነው፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 31 ቁጥር 18
"ሥጋ አምላክነትን የማይመረመር ጌትነትን አገኘ"
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 66፥ ቁጥር 15
"ሥጋ የፈጣሪ አካል ባሕርይ በሆነ ጊዜ ፍጹም አምላክነትን አገኘ"

ሰውን ወደ አምላክነት ከፍ ማድረግ እና እግዚአብሔር ወደ መሆን ከፍ ማድረግ ጣዖት ማስመለክ ነው፦
መጽሐፈ ምሥጢር ምዕራፍ 21 ቁጥር 14
"ሰውነት በመለኮት አምላክ ሆነ"
መጽሐፈ ምሥጢር ምዕራፍ 29 ቁጥር 53
"እግዚአብሔር ሰው ሆነ ሰውን ወደ አምላክነት ከፍ አደረገው"
መጽሐፈ ምሥጢር ምዕራፍ 11 ቁጥር 10
"ከዳዊት ሴት ልጅ የነሳውን ሥጋ ግን በአንድ አካል ከሆነው ከመለኮት ጋር አዋሐደው፥ እንዳይለይ እግዚአብሔር ወደ መሆን ከፍ አደረገው"

ሰው አምላክ ሆነ ማለት ሁሉን ዐላዋቂ ሁሉን ዐዋቂ ሆነ፣ ሁሉን የማይችል ሁሉን ቻይ ሆነ፣ የሚሞት የማይሞት ሆነ፣ የሚተኛ የማይተኛ ሆነ፣ ግዙፍ ረቂቅ ሆነ፣ ስሉጥ ምጡቅ ሆነ እያላችሁን ነው። ሥጋን እግዚአብሔር ማድረግ እና ማስመለክ ባዕድ አምልኮ ነው፦
መጽሐፈ ምሥጢር ምዕራፍ 17 ቁጥር 12
"መለኮት ትስብእትን ባማረ "አምልኮ" ባሕሪያዊ ምስጋና አሳተፈው"

ፍጡሩ ትስብእት አምልኮን ሲሳተፍ አይታያችሁምን? ፍጡሩ ትስብእት አምላክነት እና አምልኮ ያገኘው፦
፨ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ "ከአምላክ ጋር በመዋሐድ ነው" ሲሉ፣
፨ ኦርቶዶክስ ቅብዓት "በአብ ቀቢነት በመቀባት ነው" ሲሉ፣
፨ ኦርቶዶክስ ጸጋ ደግሞ "በአብ ጸጋ ነው" ሲሉ፣
፨ ኦርቶዶክስ ካራ "በሦስተኛ ልደት ከአብ በመወለድ እና በራሱ ቀቢነት በመቀባት ነው" ይላሉ።

ምን አለፋችሁ ድንግል ማርያም ማኅፀን ውስጥ የተፈጠረው ፍጡር "ከሦስቱ የሥላሴ አካላት አንዱ ሆነ" እያሉን ነው፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 77 ቁጥር 2
"በኃለ የተገኘን ሥጋ ሊዋሐደው ከዳዊት ባሕርይ እርሱ ፈጠረ እንደ ተጻፈ ከሦስቱ አካላት አንዱን አደረገው"።

"ኮሊሪዲያን"Collyridian" የሚባሉት ማርያማውያን "ማርያም አምላክ ሆነች" ብለው ማርያምን ማምለክ የጀመሩበት ምክንያት "የማርያምን ሥጋ እና ደም አምላክ ሆነ" በሚል ትምህርት ነው፥ "የሰው እናት ሰው ናት፥ የአምላክ እናት አምላክ ናት" በሚል ብሒል ማርያምን ያመልኳት ነበር።
በምሥራቅ ነገረ መለኮት በስፋት የሚነገር "ቴዎሲስ" የሚባል እሳቤ አለ፥ "ቴዎሲስ" θέωσις ማለት "ሱታፌ አምላክ"divinization" ማለት ነው። ሰው አምላክነትን በመሳተፍ አምላክ መሆን የሚለው እሳቤ ጠንሳሾቹ አበው ናቸው፥ ለምሳሌ፦ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ"Basil of Caesarea" በአንድ ጽሑፉ ላይ "አምላክ መሆን የሁሉም ከፍተኛ ግብ ነው" ብሏል፦
"አምላክ መሆን የሁሉም ከፍተኛ ግብ ነው"።
Basil of Caesarea On the Spirit Chapter 9 Number 23

እንደ ባይብሉ ኢየሱስ ድንግል ማርያም ማኅፀን ውስጥ የተፈጠረ ሰው ነው፥ እርሱም በትንቢት መነጽር "ከማኅፀን ጀምሮ የሠራኝ" በማለት ይናገራል፦
ኢሳይያስ 49፥5 ያዕቆብን ወደ እርሱ እንድመልስ እስራኤልንም ወደ እርሱ እንድሰበስብ ባሪያ እሆነው ዘንድ "ከማኅፀን ጀምሮ የሠራኝ" ያህዌህ እንዲህ ይላል፦

“ከማኅፀን ጀምሮ የሠራኝ” የሚለው ስለ ኢየሱስ መሆኑ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ ተናግሯል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 76 ቁጥር 19
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 76 ቁጥር 21
ተመልከት!

አንድ ሰው ከተፈጠረ አምላክ አይሆንም፥ ምክንያቱም አምላክ አይሠራምና፦
ኢሳይያስ 43፥10 ከእኔ በፊት አምላክ አልተሠራም ከእኔም በኋላ አይሆንም።

"አምላክ አልተሠራም" ካለ ከማኅፀን ኢየሱስን የሠራ ብቻውን ሰማያትን እና ምድርን የፈጠረ ሲሆን ይህ አምላክ ኢየሱስን በሁለተኛ መደብ ሲያናግረው እናያለን፦
ኢሳይያስ 44፥24 ከማኅፀን የሠራህ፥ የሚቤዥህ ያህዌህ እንዲህ ይላል፦ ሁሉን የፈጠርሁ፥ ሰማያትን ለብቻዬ የዘረጋሁ ምድርንም ያጸናሁ ያህዌህ እኔ ነኝ፤ ከእኔ ጋር ማን ነበረ?
ኢሳይያስ 42፥5-6 ሰማያትን የፈጠረ የዘረጋቸውም፥ ምድርንና በውስጥዋ ያለውን ያጸና፥ በእርስዋ ላይ ለሚኖሩ ሕዝብ እስትንፋስን፥ ለሚሄዱባትም መንፈስን የሚሰጥ አምላክ ያህዌህ እንዲህ ይላል፦ እኔ ያህዌህ በጽድቅ ጠርቼሃለሁ፥ እጅህንም እይዛለሁ እጠብቅህማለሁ፥ የዕውሩንም ዓይን ትከፍት ዘንድ የተጋዘውንም ከግዞት ቤት በጨለማም የተቀመጡትን ከወህኒ ቤት ታወጣ ዘንድ ለሕዝብ ቃል ኪዳን ለአሕዛብም ብርሃን አድርጌ እሰጥሃለሁ።

"እኔ ያህዌህ በጽድቅ ጠርቼሃለሁ፥ እጅህንም እይዛለሁ እጠብቅህማለሁ" እያለ ኢየሱስ የሚያናግረው አንዱን አምላክ ኢየሱስን ሰው እንዲሆን አረገ እንጂ እራሱ ሰው አይደለም። አንዱ አምላክ ለዳዊት ቃል የገባለት "ከሆድህ ፍሬ በዙፋንህ ላይ አስቀምጣለሁ" በማለት ነው፦
መዝሙር 132፥11 ያህዌህ ለዳዊት በእውነት ማለ አይጸጸትምም፥ እንዲህ ብሎ፦ "ከሆድህ ፍሬ በዙፋንህ ላይ አስቀምጣለሁ"።

አንዱ አምላክ ያህዌህ ከዳዊት ሆድ ፍሬ የሚፈጥር እንጂ ከዳዊት የሚፈጠር አይደለም፥ መሢሑ ከዳዊት ሥርወ አብራክ የሚፈጠር ሰው ነው። ከድንግል ማርያም የተፈጠረውን የማርያምን ልጅ መሢሑን "አምላክ ነው" ያሉ በእርግጥ ካዱ፦
5፥17 እነዚያ "አሏህ እርሱ የመርየም ልጅ አል መሢሕ ነው" ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ

ሴት ማኅፀን ውስጥ የተፈጠረን ፍጥረታዊ ሰው "አምላክ ሆነ" ብሎ ከማምለክ ይልቅ ያንን ፍጥረታዊ ሰው የፈጠረውን አንዱን አምላክ አሏህን እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። በአምላክነቱ ሰውነት የሌለበት አምላካችን አሏህ ሂዳያ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://www.tg-me.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
በዳዒ ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም የተጻፈው "አልገደሉትም አልሰቀሉትም" የሚለው መጽሐፍ በገበያ ላይ ዋለ።

ድሮ ድሮ ክርስቲያኖች "ክርስቶስ አልተገደለም አልተሰቀለም" የሚል ከቁርኣን በፊት ምንም የታሪክ ማስረጃ እና መረጃ የለም" የሚል ሙግት ነበራቸው፥ ዛሬ ላይ እኛ በተራችን "ክርስቶስ አልተገደለም አልተሰቀለም" የሚል ወንጌል እና አማኞች ከቁርኣን መወረድ በፊት በመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን የታሪክ ማስረጃ እና መረጃ ስናቀርብ ወንጌሉን "ኑፋቄ" አማኞቹን "መናፍቅ" በማለት ያነውራሉ። ለመሆኑ አሥራ ሁለቱ የክርስቶስ ሐዋርያት በዚህ ነጥብ ላይ ያላቸው አቋም ምንድን ነው? በመጽሐፉ ተዳሷል።

መጽሐፉን የምትፈልጉ አገር ውስጥ ያላችሁ ሆነ ከአገር ውጪ ያላችሁ በ +251928444408 ዐብዱ መርካቶ ብላችሁ በቀጥታ አሊያም በዋትሳፕ ታገኙታላችሁ፥ እንዲሁ በቴሌ ግራም ይህንን ዩዘር ኔም በመጠቀም http://www.tg-me.com/merkatozon ማግኘት ትችላላችሁ።

ለብዙዎች ሠበቡል ሂዳያህ ለመሆን ሁሉም ቦታ ሼር አርጉት!
ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!
በአፋን ኦሮምኛ ደርሥ ተለቋም። የአፋን ኦሮሞ አንባቢያን አንብቡ፦ https://www.tg-me.com/Wahidomar1/90
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
መምህር ያረጋል አበጋዝ በመጀመሪያ መቶ ክፍለ ዘመን ማለትም ከሐዋርያት ዘመን ጀምሮ ብዙ ወንጌላት ነበሩ፥ ከእነዚያ ውስጥ በአጥቢያ ጉባኤ(local chuch) የተመጠሩት አራት ብቻ ሲሆኑ ሌሎቹ ግን ስለ ክርስቶስ ህማማት(ስቅለት፣ ግድለት እና ሞት) አይናገሩም ነበር። ጉባኤው እምነቱን በሚገልጥ መልኩ ተገሏል ተሰቅሏል የሚሉትን አጽድቋል።

በስቅለት ዙሪያ የነበረውን ውዝግብ "አልገደሉትም አልሰቀሉትም" የሚለው ስንክሳሩን በአንድ ንዑስ መግቢያ በመሰነድ፣ በአምስት ዐበይት አርዕስት በመሰደር እና በአንድ ጉልኅ ማጠቃለያ በመሰነግ ረብጣ እይታ አቅርቤአለውና እናንተም ውድ አንባቢያን ሆይ! ይህንን መጽሐፌን ለማሳለጥ እና ለማረቅ ልባችሁን ክፍት እንደምታረጉ ተስፋ አለኝ።

መጽሐፉን የምትፈልጉ አገር ውስጥ ያላችሁ ሆነ ከአገር ውጪ ያላችሁ በ +251928444408 ዐብዱ መርካቶ ብላችሁ በቀጥታ አሊያም በዋትሳፕ ታገኙታላችሁ፥ እንዲሁ በቴሌ ግራም ይህንን ዩዘር ኔም በመጠቀም http://www.tg-me.com/merkatozon ማግኘት ትችላላችሁ።

እንዲሁ ቤተል ተቅዋ መሥጂድ ሥር ስለሚገኝ ኩብራ ብላችሁ በመደወል ማግኘት ይችላሉ፦ +251911663699
አየር ጤና አንሷር መሥጂድ ሥር፦ 0963796354

ለብዙዎች ሠበቡል ሂዳያህ ለመሆን ሁሉም ቦታ ሼር አርጉት!
ወጀዛኩሙላህ ኸይራ!
ግዝረተ ኢየሱስ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

21፥22 የዐርሹ ጌታ አሏህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ። فَسُبْحَانَ اللَّهِ رَبِّ الْعَرْشِ عَمَّا يَصِفُونَ

ፈጣሪ ጾታ የለውም፥ ሴትም ወንድም አይደለም። ፈጣሪ የሴትም የወንድም ሩካቤ ሥጋ የሌለው ሲሆን ወንድ ልጅ ግን ሩካቤ ሥጋ"sex organ" አለው፥ ይህ ሩካቤ ሥጋ ሽንት ለመሽናት እና ከሴት ጋር ተራክቦ"intercourse" ለማድረግ ያገለግላል። ኢየሱስ ከሴት የተወለደ ወንድ ልጅ ነው፦
ሉቃስ 1፥31 እነሆም፥ ትፀንሻለሽ "ወንድ" ልጅም ትወልጃለሽ፥ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ።

"ወንድ" የሚለው ቃል የሥጋ መደብ እና አንቀጽ እንደሆነ ልብ አድርግ! እንደሚታወቀው ወንድ ሩካቤ ሥጋው ላይ ያለውን ሸለፈት በስምንተኛ ቀን ይገረዛል፦
ዘፍጥረት 17፥12 የስምንት ቀን ልጅ ይገረዝ፤ በቤት የተወለደ ወይም ከዘራችሁ ያይደለ በብርም ከእንግዳ ሰው የተገዛ፥ ወንድ ሁሉ በትውልዳችሁ ይገረዝ።

ኢየሱስም ስምንት ቀን ሲሞላው ተገርዟል፥ በማኅፀን ከመረገዙ ማለትም ከመፀነሱ በፊት ስም እንደወጣለት ስሙ ኢየሱስ ተብሎ ተጠራ፦
ሉቃስ 2፥21 ሊገርዙት ስምንት ቀን በሞላ ጊዜ፥ በማኅፀን ሳይጸነስ በመልአኩ እንደ ተባለ፥ ስሙ ኢየሱስ ተብሎ ተጠራ።
ሮሜ 15፥9 ክርስቶስ ስለ አምላክ እውነት የመገረዝ አገልጋይ ሆነ እላለሁ። λέγω γὰρ Χριστὸν διάκονον γεγενῆσθαι περιτομῆς ὑπὲρ ἀληθείας Θεοῦ,

አምላክ በሥጋ ሊገረዝ ይቅርና ክርስቶስ እራሱ ስለ አምላክ እውነት የተገረዘ አገልጋይ እንደሆነ በመግለጽ በአምላክ እና በክርስቶስ መካከል የምንነት ልዩነት እንዳለ ቁልጭ እና ፍንትው አርጎ ያሳያል። ይህ የተገረዘውን ሕፃን በጌታ ፊት ያቆሙት ዘንድ ዮሴፍ እና ማርያም ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት፦
ሉቃስ 2፥24 እንደ ሙሴም ሕግ የመንጻታቸው ወራት በተፈጸመ ጊዜ፥ በጌታ ሕግ፦ የእናቱን ማኅፀን የሚከፍት ወንድ ሁሉ ለጌታ የተቀደሰ ይባላል ተብሎ እንደ ተጻፈ "በጌታ ፊት ሊያቆሙት፥ በጌታም ሕግ፦ ሁለት ዋሊያ ወይም ሁለት የርግብ ጫጩቶች እንደ ተባለ፥ መሥዋዕት ሊያቀርቡ ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት"።

የሁሉ ጌታ እና ሕፃኑ ሁለት የተለያዩ ኑባሬ እንደሆኑ አያችሁን? ፈጣሪ ፆታ ኖሮት፣ ወንድ ሆኖ፣ ተገርዞ፣ ሕፃን ሆኖ በጌታ ፊት ሊያቆሙት ሲወስዱት አስቡት! የተገረዘው ወንድን ልጅ ወደ ጌታ አምላክ ከወሰዱት ዘንዳ የተገረዘው ወንድ ልጅ እንጂ ጌታ አምላክ አይደለም።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ጥር 6 ቀን በዓመት አንዴ "ግዝረተ ኢየሱስ" ተብሎ የተገዘረበትን ዓመታዊ ክብረ በዓል ይዘከራል፥ "ግዝረት" ማለት የግዕዝ ቃል ሲሆን "ግርዘት"circumcision" ማለት ነው። ቄርሎስ ዘእስክንድርያ ስለ ኢየሱስ መገረዝ እንዲህ ይለናል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 70 ቁጥር 24
"ሰውም እንደ መሆኑ ለሥጋ እንደሚገባ ተገዘረ"።

ኢየሱስ መገረዙን ከተረዳን ዘንዳ ይህ ተቆርጦ የተገዘረው ሸለፈት ሥጋ አምላክ እንደሆነ እራሱ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ እና አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ ይናገራሉ፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 78 ቁጥር 31
"ዳግመኛ የጌታችን የክርስቶስ ሥጋ አምላክ እንደሆነ እንናገራለን"።
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 29 ቁጥር 19
"ከእመቤታችን ከቅድስት ከድንግል ማርያም የነሳው ይህ ሥጋም እውነተኛ የባሕርይ አምላክ ነው"።

ተቆርጦ የተገረዘው ሸለፈታዊ ሥጋ እውነተኛ የባሕርይ አምላክ ተሸልቶ አፈር ሆኖ ታመልኩታላችሁን? "ያ ፍጥረትን የፈጠረውን አሏህን ማርያም የወለደችው ወንድ ልጅ ነው" ብለው ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ የዐርሹ ጌታ አሏህም ከሚሉት ሁሉ ጠራ፦
5፥17 እነዚያ "አሏህ እርሱ የመርየም ልጅ አል መሢሕ ነው" ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ
21፥22 *የዐርሹ ጌታ አሏህም ከሚሉት ሁሉ ጠራ*። فَسُبْحَانَ اللَّهِ رَبِّ الْعَرْشِ عَمَّا يَصِفُونَ

"ከሚሉት" ለሚለው ቃል የገባው "የሲፉን" يَصِفُون ሲሆን "ባሕርይ ካደረጉለት"They attribute” ማለት ነው። አምላካችን አሏህ አባጣ እና ጎርባጣ ከሆነ የሺርክ ሕይወት አውጥቶ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://www.tg-me.com/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
2025/07/08 16:32:47

❌Photos not found?❌Click here to update cache.


Back to Top
HTML Embed Code: