በህወሓት እና ሻዕቢያ መካከል የተፈጠረው ጥምረትና ግንኙነት በፌደራል መንግሥቱ መቋረጥ አለበት ሲሉ የቀድሞ የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ!
በቅርቡ ህወሓትና ሻዕቢያ ጥመረት እየፈጠረ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ይህ የሁለቱ አካላት ጥምረት በመንግሥት ጣልቃ ገብነት ሊቋረጥ ይገባል ሲሉ የቀድሞ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች አሳስበዋል፡፡የቀድሞዋ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም፤ "ይህንን ለጦርነት የተደረገ ጥምረት መንግሥት ሊያቋርጠው ይገባል" ሲሉ ገልጸዋል።
ሌላው የቀድሞ የድርጅቱ አባልና ከፍተኛ አመራር እንዲሁም የዲሞክራሲ ስምረት ትግራይ ፖርቲ መስራች ውስጥ አንዱ የሆኑት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት በበኩላቸው፤ "የሁለቱ አካላት ጥምረት ዓላማ ግልፅ አይደለም" ሲሉ ተናግረዋል።በምርጫ ቦርድ የተሰረዘው ህወሐትና የኤርትራ መንግሥት ጥምረት መፍጠር ለጦርነት ዓላማ የተደረገ መሆኑ እየተገለጸ ይገኛል።
በተጨማሪም በትግርኛ "ፅምዶ" ወይንም "ጥምረት ለሀቀኛ ሰላም ለትግራይ እና ኤርትራ" በሚል የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት እየተደረገ መሆኑንም መመልከት ተችሏል።ይህንን ጥምረት በሚመለከት ሀሳባቸውን የሰጡት የቀድሞ የህወሓት ከፍተኛ አመራር ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም "በግልፅ ለጦርነት የተደረገ ጥምረት ነው" ብለዋል።
"ሕዝብን ከተደቀነበት ጦርነት ማዳን ላይ መስራት አለብን" ያሉ ሲሆን፤ ጦርነቱ የማይቀር እንኳን ቢሆን ዱላው ሕዝብ ላይ እንዳያርፍ መስራት አለብን" ሲሉም ገልጸዋል።"አሁን ላይ በግልፅም ይሁን በድብቅ ጥምረቱ ይታያል" ያሉት ወይዘሮ ኬሪያ፤ "ይህንን ማስቆምና መቁረጥ ያለበት የትግራይ ሊሂቃንና ፌደራል መንግሥት ነው በማለት ሀሳባቸውን" ሰጥተዋል።
ሌላው ሀሳባቸውን ለአሐዱ የሰጡት የቀድሞ የህወሕት አባልና ከፍተኛ አመራር ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት፤ "በአንድ ሉዓላዊት ሀገር ውስጥ ከሌላ ሀገር ጋር ማን ግንኙነት መፍጠር እንዳለበት ይታወቃል" ብለዋል፡፡"ሕገ-ወጥ ግነኙነት ሲኖር ደግሞ ማስቆም ያለበት ማን እንደሆነም ግልፅ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።"ይሁን እንጂ ከኤርትራ ጋር ያለው ግንኙነት ያልጠራ ነው፤ ነገር ግን ግንኙነቱ በመርህ ላይ ካልተመሰረተ ትክክል አይለም" ሲሉም ለአሐዱ ገልጸዋል።
በዚህ ጥምረት ዙሪያ የፌደራል መንግሥት በግልፅ ያስታወቀው ነገር ባይኖርም፤ ባለፈው ሳምንት አርብ በትግራይ ሰላም፣ ልማትና ዲሞክራሲ የሚጠይቅ ወይይት ተካሂዶ ነበር።የፌደራል መንግሥት የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከልን በመወከል የተገኙት አቶ መለሰ አለሙ፤ "የፌደራል መንግሥት ኃላፊነት እንዳለ ሆኖ የትግራይ ፖለቲከኞችም ለሰላም ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል" ሲሉ ተደምጠዋል።"የድንበር ጉዳይን በተመለከተ መንግሥት ሉዓላዊነቱን በፍፁም አሳልፎ አይሰጥም" ያሉም ሲሆን፤ የውስጥ ችግሮች ከተፈቱ ሌላውን ማስተካከል እንደሚቻል ተናግረዋል።
Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
በቅርቡ ህወሓትና ሻዕቢያ ጥመረት እየፈጠረ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ይህ የሁለቱ አካላት ጥምረት በመንግሥት ጣልቃ ገብነት ሊቋረጥ ይገባል ሲሉ የቀድሞ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች አሳስበዋል፡፡የቀድሞዋ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም፤ "ይህንን ለጦርነት የተደረገ ጥምረት መንግሥት ሊያቋርጠው ይገባል" ሲሉ ገልጸዋል።
ሌላው የቀድሞ የድርጅቱ አባልና ከፍተኛ አመራር እንዲሁም የዲሞክራሲ ስምረት ትግራይ ፖርቲ መስራች ውስጥ አንዱ የሆኑት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት በበኩላቸው፤ "የሁለቱ አካላት ጥምረት ዓላማ ግልፅ አይደለም" ሲሉ ተናግረዋል።በምርጫ ቦርድ የተሰረዘው ህወሐትና የኤርትራ መንግሥት ጥምረት መፍጠር ለጦርነት ዓላማ የተደረገ መሆኑ እየተገለጸ ይገኛል።
በተጨማሪም በትግርኛ "ፅምዶ" ወይንም "ጥምረት ለሀቀኛ ሰላም ለትግራይ እና ኤርትራ" በሚል የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት እየተደረገ መሆኑንም መመልከት ተችሏል።ይህንን ጥምረት በሚመለከት ሀሳባቸውን የሰጡት የቀድሞ የህወሓት ከፍተኛ አመራር ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም "በግልፅ ለጦርነት የተደረገ ጥምረት ነው" ብለዋል።
"ሕዝብን ከተደቀነበት ጦርነት ማዳን ላይ መስራት አለብን" ያሉ ሲሆን፤ ጦርነቱ የማይቀር እንኳን ቢሆን ዱላው ሕዝብ ላይ እንዳያርፍ መስራት አለብን" ሲሉም ገልጸዋል።"አሁን ላይ በግልፅም ይሁን በድብቅ ጥምረቱ ይታያል" ያሉት ወይዘሮ ኬሪያ፤ "ይህንን ማስቆምና መቁረጥ ያለበት የትግራይ ሊሂቃንና ፌደራል መንግሥት ነው በማለት ሀሳባቸውን" ሰጥተዋል።
ሌላው ሀሳባቸውን ለአሐዱ የሰጡት የቀድሞ የህወሕት አባልና ከፍተኛ አመራር ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት፤ "በአንድ ሉዓላዊት ሀገር ውስጥ ከሌላ ሀገር ጋር ማን ግንኙነት መፍጠር እንዳለበት ይታወቃል" ብለዋል፡፡"ሕገ-ወጥ ግነኙነት ሲኖር ደግሞ ማስቆም ያለበት ማን እንደሆነም ግልፅ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።"ይሁን እንጂ ከኤርትራ ጋር ያለው ግንኙነት ያልጠራ ነው፤ ነገር ግን ግንኙነቱ በመርህ ላይ ካልተመሰረተ ትክክል አይለም" ሲሉም ለአሐዱ ገልጸዋል።
በዚህ ጥምረት ዙሪያ የፌደራል መንግሥት በግልፅ ያስታወቀው ነገር ባይኖርም፤ ባለፈው ሳምንት አርብ በትግራይ ሰላም፣ ልማትና ዲሞክራሲ የሚጠይቅ ወይይት ተካሂዶ ነበር።የፌደራል መንግሥት የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከልን በመወከል የተገኙት አቶ መለሰ አለሙ፤ "የፌደራል መንግሥት ኃላፊነት እንዳለ ሆኖ የትግራይ ፖለቲከኞችም ለሰላም ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል" ሲሉ ተደምጠዋል።"የድንበር ጉዳይን በተመለከተ መንግሥት ሉዓላዊነቱን በፍፁም አሳልፎ አይሰጥም" ያሉም ሲሆን፤ የውስጥ ችግሮች ከተፈቱ ሌላውን ማስተካከል እንደሚቻል ተናግረዋል።
Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from YeneTube
🎨 Graphic Design Course Registration Now Open!
Unlock your creativity and learn the skills to design stunning visuals for social media, branding, and more.
✅ Beginner-friendly
✅ Hands-on projects
✅ Certificate included
📅 Limited seats – Register today!
Call us:
☎️
0989747878
0799331774
@merahyan
Unlock your creativity and learn the skills to design stunning visuals for social media, branding, and more.
✅ Beginner-friendly
✅ Hands-on projects
✅ Certificate included
📅 Limited seats – Register today!
Call us:
☎️
0989747878
0799331774
@merahyan
Forwarded from YeneTube
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ምሽት አይበግረንም!
ለሱቅ ፈላጊዎች በሙሉ
📍 ፒያሳ ከሚኒልክ አደባባይ ወደ ሀገር ፍቅር ቲያትር የሚወስደው መንገድ ላይ የንግድ ሱቆችን መሸጥ ጀምረናል።
👉 2 ቤዝመንት ያለው
👉ከ 900,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
👉በ1 ዓመት ተኩል የምትረከቡት
👉ምድር ቤት
20 ካሬ= 7ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 2.8ሚሊዮን ብር
👉1ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 5.5 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 2 ሚሊዮን ብር
👉2ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 4.8 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 1.5 ሚሊዮን ብር
👉3ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 4.2 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 1.2 ሚሊዮን ብር
👉4ኛ እና 5ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 3.9 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 900 ሺ ብር
👉ቀሪው በግንባታ ሂደት የሚከፈል።
ለበለጠ መረጃ
09-76-19-58-35
Telegram username
@Ruthtemersales
Whats app
Message Temer properties on WhatsApp. https://wa.me/251976195835
ለሱቅ ፈላጊዎች በሙሉ
📍 ፒያሳ ከሚኒልክ አደባባይ ወደ ሀገር ፍቅር ቲያትር የሚወስደው መንገድ ላይ የንግድ ሱቆችን መሸጥ ጀምረናል።
👉 2 ቤዝመንት ያለው
👉ከ 900,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
👉በ1 ዓመት ተኩል የምትረከቡት
👉ምድር ቤት
20 ካሬ= 7ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 2.8ሚሊዮን ብር
👉1ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 5.5 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 2 ሚሊዮን ብር
👉2ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 4.8 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 1.5 ሚሊዮን ብር
👉3ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 4.2 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 1.2 ሚሊዮን ብር
👉4ኛ እና 5ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 3.9 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 900 ሺ ብር
👉ቀሪው በግንባታ ሂደት የሚከፈል።
ለበለጠ መረጃ
09-76-19-58-35
Telegram username
@Ruthtemersales
Whats app
Message Temer properties on WhatsApp. https://wa.me/251976195835
Forwarded from YeneTube
አቅመ ደካማወችን ሀረጋውያኖችን በነፃ
https://vm.tiktok.com/ZMSayMdXa
በተለያየ የጤና ችግር የሚሰቃዩትን እየ ፈወሰ
ደስታቸውን እየመለሰ የሚገኘውን የህክምና ተቋም https://vm.tiktok.com/ZMSay8eV2/
ሰወች እንዴት እንደተፈወሱ ሲመሰክሩ እንስማ እንይ ቻናሉን እንቀላቀል
https://vm.tiktok.com/ZMSaDEhoN
በስጋውይም ሆነ በመንፈስ ደውየ ከተቸገሩ መተው በመመርመር ይታከሙ ይፈወሱ
44ት አይነት በሽታወችን እየፈወስን እንገኛለን
አድራሻ አዲስ አበባ አየርጤና ወደካራ ናትራን ኩፓንያ ፊት ለፊት
ቁጥር ሁለት ባህርዳር ዲያስፖራ በአሮጌው አስፓልት መስጊዱ ፊት ለፊት
☎️ 0917040506
☎️0912718883
ይደውሉ ይምጡ ይታከሙ ይፈወሱ ይመስክሩ
https://vm.tiktok.com/ZMSayMdXa
በተለያየ የጤና ችግር የሚሰቃዩትን እየ ፈወሰ
ደስታቸውን እየመለሰ የሚገኘውን የህክምና ተቋም https://vm.tiktok.com/ZMSay8eV2/
ሰወች እንዴት እንደተፈወሱ ሲመሰክሩ እንስማ እንይ ቻናሉን እንቀላቀል
https://vm.tiktok.com/ZMSaDEhoN
በስጋውይም ሆነ በመንፈስ ደውየ ከተቸገሩ መተው በመመርመር ይታከሙ ይፈወሱ
44ት አይነት በሽታወችን እየፈወስን እንገኛለን
አድራሻ አዲስ አበባ አየርጤና ወደካራ ናትራን ኩፓንያ ፊት ለፊት
ቁጥር ሁለት ባህርዳር ዲያስፖራ በአሮጌው አስፓልት መስጊዱ ፊት ለፊት
☎️ 0917040506
☎️0912718883
ይደውሉ ይምጡ ይታከሙ ይፈወሱ ይመስክሩ
Forwarded from YeneTube
Ethiopian Building Code Standards
Private Sector Engagement in Code Revision: Final Week – Week 4 Sessions
We're closing out our 14-part expert-led workshop series with two crucial technical sessions in Week 4:
🧱 Concrete Design & Specifications
📏 Technical Specs & Measurement Methods
📅 Tuesday, June 24, 2025
📍 The Urban Center, Addis Ababa
🖥 Live on TUC Facebook page & Google Meet (link shared 30 min before each session)
☕️ Free sessions with refreshments
📲 Register now: https://forms.gle/NewtRdbnasiUFW6r7
🔗 Let’s finish strong, join the conversation, contribute your perspective, and help shape Ethiopia’s future building code.
Many thanks to all our incredible partners for making this journey possible!
#EBCS #CodeRevision #BuiltEnvironment #ECA #CoTBE #TUC #EngineeringEthiopia #ConstructionStandards #UrbanDevelopment #ProfessionalEngagement
Private Sector Engagement in Code Revision: Final Week – Week 4 Sessions
We're closing out our 14-part expert-led workshop series with two crucial technical sessions in Week 4:
🧱 Concrete Design & Specifications
📏 Technical Specs & Measurement Methods
📅 Tuesday, June 24, 2025
📍 The Urban Center, Addis Ababa
🖥 Live on TUC Facebook page & Google Meet (link shared 30 min before each session)
☕️ Free sessions with refreshments
📲 Register now: https://forms.gle/NewtRdbnasiUFW6r7
🔗 Let’s finish strong, join the conversation, contribute your perspective, and help shape Ethiopia’s future building code.
Many thanks to all our incredible partners for making this journey possible!
#EBCS #CodeRevision #BuiltEnvironment #ECA #CoTBE #TUC #EngineeringEthiopia #ConstructionStandards #UrbanDevelopment #ProfessionalEngagement
በአሜሪካ እርዳታ ስረዛ ምክንያት በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የ14 ሚሊዮን ሰዎች ሕይወት ሊያልፍ እንደሚችል ተጠቆመ!
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ ለውጭ ሰብዓዊ እርዳታ ትሰጥ የነበረውን የገንዘብ ድጋፍ መሰረዛቸው በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ተጨማሪ 14 ሚሊዮን ሰዎች ሕይወት እንዲያልፍ ሊያደርግ እንደሚችል ዘ ላንሴት የተባለው ተቋም የሕክምና ሪፖርት ጠቆመ።ካለ እድሜያቸው ሕይወታቸው ከሚያልፉት ውስጥ ሲሶ ያህል ሕፃናት መሆናቸውን የጥናቱ ግኝት አሳይቷል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ባለፈው መጋቢት የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር በአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) የሚሰጡ 80 በመቶ መርሐ ግብሮችን መሰረዙን ተናግረዋል።ከጥናቱ ፀሐፊዎች መካከል አንዱ የሆኑት ዴቪድ ራሰላ "ለበርካታ ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ላላቸው አገራት ውጤቱ ከዓለም አቀፍ ወረርሽኝ አሊያም ከግዙፍ ግጭት ጋር የሚነፃፀር ነው" ብለዋል።
የረድኤት ድጋፉ "ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት በተጋላጭ ሕዝቦች ጤና ላይ የታየው እድገት በአፋጣኝ እንዲገታ ወይም ወደነበረበት እንዲመለስ አደጋ ደቅኗል" ሲሉ በባርሴሎና ዓለም አቀፍ ጤና ኢንስቲትዩት ተመራማሪ የሆኑት ዴቪድ ራሰላ አክለው ተናግረዋል።ሪፖርቱ የወጣው የዓለም መሪዎች በስፔን ሰቪል ከተማ በዚህ ሳምንት በመንግሥታቱ ድርጅት የተመራ እና ከአስር ዓመታት በኋላ ግዝፉ የሆነው ጉባኤ ከመካሄዱ አስቀድሞ ነው።
ከ133 አገራት የተገኘ መረጃን የተመለከተው የተመራማሪዎች ቡድን በግመታው እ.አ.አ ከ2001 እስከ 2021 ድረስ በማደግ ላይ ባሉ አገራት የዩኤስኤአይዲ ድጋፍ 91 ሚሊዮን ሰዎችን ከሞት የታደገ ነው።ተመራማሪዎች ከወራት በፊት በአሜሪካ መንግሥት ይፋ የተደረገው 83 በመቶ ድጋፍ መቀነስ የሞት ምጣኔን ከፍ እንደሚያደርግም ግመታቸውን አስቀምጠዋል።
በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የእርዳታ መሰረዙ ሕይወታቸውን መታደግ እየተቻለ 14 ሚሊዮን ሰዎችን ወደ ሞት ይመራል ብለዋል።ይህ አኃዝ ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ 4.5 ሚሊዮን ሕፃናትን ጨምሮ ሲሆን ይህም ማለት 700 ሺህ ሕፃናት በየዓመቱ ሕይወታቸው ያልፋል ማለት ነው።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ ለውጭ ሰብዓዊ እርዳታ ትሰጥ የነበረውን የገንዘብ ድጋፍ መሰረዛቸው በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ተጨማሪ 14 ሚሊዮን ሰዎች ሕይወት እንዲያልፍ ሊያደርግ እንደሚችል ዘ ላንሴት የተባለው ተቋም የሕክምና ሪፖርት ጠቆመ።ካለ እድሜያቸው ሕይወታቸው ከሚያልፉት ውስጥ ሲሶ ያህል ሕፃናት መሆናቸውን የጥናቱ ግኝት አሳይቷል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ባለፈው መጋቢት የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር በአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) የሚሰጡ 80 በመቶ መርሐ ግብሮችን መሰረዙን ተናግረዋል።ከጥናቱ ፀሐፊዎች መካከል አንዱ የሆኑት ዴቪድ ራሰላ "ለበርካታ ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ላላቸው አገራት ውጤቱ ከዓለም አቀፍ ወረርሽኝ አሊያም ከግዙፍ ግጭት ጋር የሚነፃፀር ነው" ብለዋል።
የረድኤት ድጋፉ "ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት በተጋላጭ ሕዝቦች ጤና ላይ የታየው እድገት በአፋጣኝ እንዲገታ ወይም ወደነበረበት እንዲመለስ አደጋ ደቅኗል" ሲሉ በባርሴሎና ዓለም አቀፍ ጤና ኢንስቲትዩት ተመራማሪ የሆኑት ዴቪድ ራሰላ አክለው ተናግረዋል።ሪፖርቱ የወጣው የዓለም መሪዎች በስፔን ሰቪል ከተማ በዚህ ሳምንት በመንግሥታቱ ድርጅት የተመራ እና ከአስር ዓመታት በኋላ ግዝፉ የሆነው ጉባኤ ከመካሄዱ አስቀድሞ ነው።
ከ133 አገራት የተገኘ መረጃን የተመለከተው የተመራማሪዎች ቡድን በግመታው እ.አ.አ ከ2001 እስከ 2021 ድረስ በማደግ ላይ ባሉ አገራት የዩኤስኤአይዲ ድጋፍ 91 ሚሊዮን ሰዎችን ከሞት የታደገ ነው።ተመራማሪዎች ከወራት በፊት በአሜሪካ መንግሥት ይፋ የተደረገው 83 በመቶ ድጋፍ መቀነስ የሞት ምጣኔን ከፍ እንደሚያደርግም ግመታቸውን አስቀምጠዋል።
በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የእርዳታ መሰረዙ ሕይወታቸውን መታደግ እየተቻለ 14 ሚሊዮን ሰዎችን ወደ ሞት ይመራል ብለዋል።ይህ አኃዝ ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ 4.5 ሚሊዮን ሕፃናትን ጨምሮ ሲሆን ይህም ማለት 700 ሺህ ሕፃናት በየዓመቱ ሕይወታቸው ያልፋል ማለት ነው።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ በአንድ ማዕከል ብቻ 7 ሺህ 500 የሚሆኑ የልብ ህሙማን ወረፋ እየጠበቁ እንደሚገኙ ተገለጸ!
የኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህፃናት መርጃ ማዕከል 7 ሺህ 500 የሚሆኑ የልብ ህሙማን ወረፋ እየጠበቁ እንደሚገኙ አስታወቀ።ወረፋ እየጠበቁ ከሚገኙት ውስጥ ከ2 ሺህ በላይ የሚሆኑት ከተወለዱ ጀምሮ በሚከሰት የልብ ህመም ተጠቂ ህፃናት መሆናቸውን የማዕከሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ኤልኤዘር ሃይሌ ገልጸዋል።
የልብ ህሙማኑን ለመርዳት ለማዕከሉ የሚበረከቱ ግብአቶች ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱ አስታውቀው፤ ለማዕከሉ አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶች ሙሉ በሙሉ ከውጪ የሚገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡በተለይ አላቂ የህክምና ግብዓቶች በየህፃናቱ የክብደት መጠን ልክ እንደሚገዙ የገለጹት ዳይሬክተሩ፤ በድጋሚ መጠቀም የማይቻሉ ግብዓቶች በመሆናቸው የህክምናውን ሂደት አደገኛ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ግብአቶቹ ዋጋቸው እጅግ በጣም ውድ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
የልብ ቫልቮች፣ ልዩ ልዩ ማሽኖች፣ ልዩ ልዩ መድሀኒቶች እንዲሁም ልብን በማቆም ለሚሰሩ ቀዶ ጥገናዎች የሚውሉ የተለያዩ ግብአቶች ለማዕከሉ ወሳኝ መሆናቸውንም አስረድተዋል፡፡ድጋፍ ማድረግ የሚፈልጉ ሰዎች 6710ን በመጠቀም፤ በግልም ሆነ በቡድን ታማሚዎችን በመጎብኘት፣ ታማሚዎችን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ስፖንሰር በማድረግ እንዲሁም ከማዕከሉ በሚያገኙት ዝርዝር መሰረት በግብዓት አቅርቦት መደገፍ እንደሚችሉ መጠቆማቸውን ከፕሬስ ድርጅት ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡
Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህፃናት መርጃ ማዕከል 7 ሺህ 500 የሚሆኑ የልብ ህሙማን ወረፋ እየጠበቁ እንደሚገኙ አስታወቀ።ወረፋ እየጠበቁ ከሚገኙት ውስጥ ከ2 ሺህ በላይ የሚሆኑት ከተወለዱ ጀምሮ በሚከሰት የልብ ህመም ተጠቂ ህፃናት መሆናቸውን የማዕከሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ኤልኤዘር ሃይሌ ገልጸዋል።
የልብ ህሙማኑን ለመርዳት ለማዕከሉ የሚበረከቱ ግብአቶች ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱ አስታውቀው፤ ለማዕከሉ አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶች ሙሉ በሙሉ ከውጪ የሚገቡ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡በተለይ አላቂ የህክምና ግብዓቶች በየህፃናቱ የክብደት መጠን ልክ እንደሚገዙ የገለጹት ዳይሬክተሩ፤ በድጋሚ መጠቀም የማይቻሉ ግብዓቶች በመሆናቸው የህክምናውን ሂደት አደገኛ ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ግብአቶቹ ዋጋቸው እጅግ በጣም ውድ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
የልብ ቫልቮች፣ ልዩ ልዩ ማሽኖች፣ ልዩ ልዩ መድሀኒቶች እንዲሁም ልብን በማቆም ለሚሰሩ ቀዶ ጥገናዎች የሚውሉ የተለያዩ ግብአቶች ለማዕከሉ ወሳኝ መሆናቸውንም አስረድተዋል፡፡ድጋፍ ማድረግ የሚፈልጉ ሰዎች 6710ን በመጠቀም፤ በግልም ሆነ በቡድን ታማሚዎችን በመጎብኘት፣ ታማሚዎችን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ስፖንሰር በማድረግ እንዲሁም ከማዕከሉ በሚያገኙት ዝርዝር መሰረት በግብዓት አቅርቦት መደገፍ እንደሚችሉ መጠቆማቸውን ከፕሬስ ድርጅት ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡
Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
“በአዲስ አበባ የትግራይ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ የዘፈቀደ እስራት እየተፈጸመ ነው” - ሂዩማን ራይት ፈርስት
ሂዩማን ራይትስ ፈርስት የተሰኘ የሃገር ውስጥ መብት ተሟጋች ድርጅት “በአዲስ አበባ የሚገኙ የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ወጣቶች በከተማዋ ባለስለጣናት ኢላማ ተደርገው፣ ያለምንም መደበኛ ክስ እና ፍርድ ሂደት በማንነታቸው ምክንያት “የዘፈቀደ እስራት” እየተፈጸመባቸው ነው” ሲል ክስ አቀረበ።
በተመሳሳይ በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሰው ሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳወት) ትላንት ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ነዋሪነታቸው በአዲስ አበባ የሆኑ የትግራይ ተወላጆች በፀጥታ ሃይሎች በዘፈቀደ እየታፈሱ እና በህገወጥ መንገድ እየታሰሩ እንደሚገኙ ሪፖርት እንደደረሰው አስታውቋል።
ለእስር ተዳርገው በኋላ ላይ መፈታታቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ ያስታወቁ አንድ በከተማዋ ነዋሪ የሆኑ የትግራይ ተወላጅ ለምን እንደታሰርን ስንጠይቃቸው ምንም አይነት ማብራሪያ አልሰጡንም ብለዋል፤ “ከበላይ አካል የመጣ ትዕዛዝ ነው” የሚል ምላሽ ነው የሰጡን፤ ክስ አልተመሰረተብንም፣ ፍርድ ቤትም አለቀረብንም” ብለዋል።
ሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳወት) እንዲሁም ሂዩማን ራይት ፈርስት “ዜጎችን ስማቸውን ወይም ብሄራቸውን መሰረት በማድረግ ለእስር መዳረግ ሀገር አቀፍ እና አለም አቀፍ ህግጋትን የሚጻረር እና መጣስ ነው” ሲል በመኮነን “ያለ ፍርድ ሂደት ለእስር የታዳረጉት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ” ሲሉ በተናጠል ባወጡት መግለጫ ጠይቀዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ሂዩማን ራይትስ ፈርስት የተሰኘ የሃገር ውስጥ መብት ተሟጋች ድርጅት “በአዲስ አበባ የሚገኙ የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ወጣቶች በከተማዋ ባለስለጣናት ኢላማ ተደርገው፣ ያለምንም መደበኛ ክስ እና ፍርድ ሂደት በማንነታቸው ምክንያት “የዘፈቀደ እስራት” እየተፈጸመባቸው ነው” ሲል ክስ አቀረበ።
በተመሳሳይ በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሰው ሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳወት) ትላንት ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ነዋሪነታቸው በአዲስ አበባ የሆኑ የትግራይ ተወላጆች በፀጥታ ሃይሎች በዘፈቀደ እየታፈሱ እና በህገወጥ መንገድ እየታሰሩ እንደሚገኙ ሪፖርት እንደደረሰው አስታውቋል።
ለእስር ተዳርገው በኋላ ላይ መፈታታቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ ያስታወቁ አንድ በከተማዋ ነዋሪ የሆኑ የትግራይ ተወላጅ ለምን እንደታሰርን ስንጠይቃቸው ምንም አይነት ማብራሪያ አልሰጡንም ብለዋል፤ “ከበላይ አካል የመጣ ትዕዛዝ ነው” የሚል ምላሽ ነው የሰጡን፤ ክስ አልተመሰረተብንም፣ ፍርድ ቤትም አለቀረብንም” ብለዋል።
ሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳወት) እንዲሁም ሂዩማን ራይት ፈርስት “ዜጎችን ስማቸውን ወይም ብሄራቸውን መሰረት በማድረግ ለእስር መዳረግ ሀገር አቀፍ እና አለም አቀፍ ህግጋትን የሚጻረር እና መጣስ ነው” ሲል በመኮነን “ያለ ፍርድ ሂደት ለእስር የታዳረጉት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ” ሲሉ በተናጠል ባወጡት መግለጫ ጠይቀዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
ኢባትሎ አዳዲስ መርከቦችን በሀገር ውስጥ ባንኮች ድጋፍ ሊገዛ ነው!
የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ (ኢባትሎ) የአስር መርከቦች ባለቤት የመሆን ግቡን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት፣ አዳዲስ መርከቦችን ለመግዛት ማቀዱን እና ለዚህም ከሀገር ውስጥ ባንኮች የገንዘብ ድጋፍ ማግኘቱን አስታውቋል።የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ አዋሽ ባንክ እና ዳሽን ባንክ ይህንን ግዙፍ ግዢ በጋራ ለመደጎም መስማማታቸው ተገልጿል።
ኢባትሎ አዲስ ሁለት የአልትራማክስ ሁለገብ የደረቅ ጭነት መርከቦችን ለመግዛት ጨረታ ያወጣ ሲሆን፣ በተጨማሪም አራት ያገለገሉ መካከለኛ መጠን ያላቸው መርከቦችን በመርከብ ደላሎች በኩል ለመግዛት ማቀዱን ካፒታል ሰምቷል።
የፋይናንስ ስምምነቱ ዝርዝር እንደሚያሳየው፣ አዋሽ ባንክ እና ዳሽን ባንክ ለአንድ ሁለገብ መርከብ እና ለአንድ የአልትራማክስ ደረቅ ጭነት መርከብ የገንዘብ ድጋፍ ያደርጋሉ።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሌላ በኩል አዲስ የአልትራማክስ ሁለገብ እና ሁለቱን ያገለገሉ ኮንቴይነር መርከቦችን ጨምሮ የሦስት ተጨማሪ መርከቦችን ግዥ ለመደገፍ ተስማምቷል።
በአጠቃላይ፣ ኢባትሎ ለአምስቱ መርከቦች ጠቅላላ ወጪ 30% የሚሆነውን በራሱ የሚሸፍን ሲሆን፣ ቀሪው 70% በባንኮቹ ይሸፈናል። ከዚህም ባሻገር፣ አንድ መርከብ በሙሉ በተቋሙ ፋይናንስ እንደሚደረግ ተገልጿል።
ኢባትሎ ያገለገሉትን አራት መርከቦችን በቅርብ ጊዜ ውስጥ ለመረከብ ሲጠብቅ፣ የአዲሶቹ ሁለት ሁለገብ መርከቦች ግንባታ ግን የጨረታ ሂደቱ ከተጠናቀቀ በኋላ ቢያንስ ሁለት ዓመታትን ይወስዳል ተብሎ ይገመታል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ (ኢባትሎ) የአስር መርከቦች ባለቤት የመሆን ግቡን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት፣ አዳዲስ መርከቦችን ለመግዛት ማቀዱን እና ለዚህም ከሀገር ውስጥ ባንኮች የገንዘብ ድጋፍ ማግኘቱን አስታውቋል።የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ አዋሽ ባንክ እና ዳሽን ባንክ ይህንን ግዙፍ ግዢ በጋራ ለመደጎም መስማማታቸው ተገልጿል።
ኢባትሎ አዲስ ሁለት የአልትራማክስ ሁለገብ የደረቅ ጭነት መርከቦችን ለመግዛት ጨረታ ያወጣ ሲሆን፣ በተጨማሪም አራት ያገለገሉ መካከለኛ መጠን ያላቸው መርከቦችን በመርከብ ደላሎች በኩል ለመግዛት ማቀዱን ካፒታል ሰምቷል።
የፋይናንስ ስምምነቱ ዝርዝር እንደሚያሳየው፣ አዋሽ ባንክ እና ዳሽን ባንክ ለአንድ ሁለገብ መርከብ እና ለአንድ የአልትራማክስ ደረቅ ጭነት መርከብ የገንዘብ ድጋፍ ያደርጋሉ።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሌላ በኩል አዲስ የአልትራማክስ ሁለገብ እና ሁለቱን ያገለገሉ ኮንቴይነር መርከቦችን ጨምሮ የሦስት ተጨማሪ መርከቦችን ግዥ ለመደገፍ ተስማምቷል።
በአጠቃላይ፣ ኢባትሎ ለአምስቱ መርከቦች ጠቅላላ ወጪ 30% የሚሆነውን በራሱ የሚሸፍን ሲሆን፣ ቀሪው 70% በባንኮቹ ይሸፈናል። ከዚህም ባሻገር፣ አንድ መርከብ በሙሉ በተቋሙ ፋይናንስ እንደሚደረግ ተገልጿል።
ኢባትሎ ያገለገሉትን አራት መርከቦችን በቅርብ ጊዜ ውስጥ ለመረከብ ሲጠብቅ፣ የአዲሶቹ ሁለት ሁለገብ መርከቦች ግንባታ ግን የጨረታ ሂደቱ ከተጠናቀቀ በኋላ ቢያንስ ሁለት ዓመታትን ይወስዳል ተብሎ ይገመታል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
ጫጫታን የማያስተላልፉ(Noise Canceling የጆሮ ማዳመጫዎች አእምሯችንን ሚያታልሉት እንዴት ነው?
https://www.tiktok.com/@sociosaga/video/7522058529646202117
https://www.tiktok.com/@sociosaga/video/7522058529646202117
TikTok
TikTok · sociosaga
Check out sociosaga’s video.
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ደንበኞች ቁጥር 10 ሚሊዮን መድረሱ ተገለጸ!
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የአገልግሎት ፍቃዱን ከተረከበ በአራት ዓመታት ውስጥ፤ በሀገሪቱ ዙሪያ ያሉ የ90 ቀናት ንቁ ደንበኞቹ ቁጥር 10 ሚሊዮን መድረሱን ገልጿል።የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዊም ቫንሄለፑት እንደተናገሩት፤ የቴሌኮም ኩባያው በኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎት መስጠት ከጀመረ አራት ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን፤ በእነዚህ አራት ዓመታት ውስጥ 300 ቢሊየን ብር በላይ ሙዓለ ንዋይ ወጪ አድርጓል፡፡
የ90 ቀናት ንቁ ደንበኞቻችን ቁጥር 10 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን፤ 7 ነጥብ 1 ሚሊዮን የሞባይል ዳታ አገልግሎት ተጠቃሚዎች መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡አክለውም አሁን ላይ ኩባንያው 900 ሠራተኞች ሲኖሩት ከእነዚህ ውስጥ 97 በመቶ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን በመግለጽ፤ በተጨማሪም ከ20 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች ተዘዋዋሪ የሥራ ዕድል መፍጠሩ ገልጸዋል።
ሳፊሪኮም ኢትዮጵያ በየቀኑ 31 ሺሕ አዳዲስ የአገልግሎት ተጠቃሚዎች ደንበኞችን እየተቀላቀ መሆኑን ተናግረዋል፡፡በአሁኑ ሰዓት ካሉት ደንበኞች 75 በመቶዎቹ በቋሚነት አገልግሎቱን እየተጠቀሙ መሆኑንም ዋና ሥራ አስፈጻሚው ጨምረው ተናግረዋል፡፡
አክለውም "በዚህ አራት ዓመት ውሰጥ ችግር ሆኖብን ነበረው፤ ተፎካካሪያችን በመንግሥት ባለቤትነት ያለ መሆኑ ነው" ብለዋል።ሳፊሪኮም ኢትዮጵያ 3 ሚሊዮን ዶላር ለኢትዮ ቴሌኮም ለመሠረተ ልማት ኪራይ እንደሚከፈል የገለጹት ዋና ሥራ አስኪያጁ፤ ኩባንያው የሚጠበቅነትን ግብር እስካሁኑ ሰዓት ድረስ በቴሌብር እንሚከፍል ተናግረዋል፡፡
Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የአገልግሎት ፍቃዱን ከተረከበ በአራት ዓመታት ውስጥ፤ በሀገሪቱ ዙሪያ ያሉ የ90 ቀናት ንቁ ደንበኞቹ ቁጥር 10 ሚሊዮን መድረሱን ገልጿል።የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዊም ቫንሄለፑት እንደተናገሩት፤ የቴሌኮም ኩባያው በኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎት መስጠት ከጀመረ አራት ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን፤ በእነዚህ አራት ዓመታት ውስጥ 300 ቢሊየን ብር በላይ ሙዓለ ንዋይ ወጪ አድርጓል፡፡
የ90 ቀናት ንቁ ደንበኞቻችን ቁጥር 10 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን፤ 7 ነጥብ 1 ሚሊዮን የሞባይል ዳታ አገልግሎት ተጠቃሚዎች መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡አክለውም አሁን ላይ ኩባንያው 900 ሠራተኞች ሲኖሩት ከእነዚህ ውስጥ 97 በመቶ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን በመግለጽ፤ በተጨማሪም ከ20 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች ተዘዋዋሪ የሥራ ዕድል መፍጠሩ ገልጸዋል።
ሳፊሪኮም ኢትዮጵያ በየቀኑ 31 ሺሕ አዳዲስ የአገልግሎት ተጠቃሚዎች ደንበኞችን እየተቀላቀ መሆኑን ተናግረዋል፡፡በአሁኑ ሰዓት ካሉት ደንበኞች 75 በመቶዎቹ በቋሚነት አገልግሎቱን እየተጠቀሙ መሆኑንም ዋና ሥራ አስፈጻሚው ጨምረው ተናግረዋል፡፡
አክለውም "በዚህ አራት ዓመት ውሰጥ ችግር ሆኖብን ነበረው፤ ተፎካካሪያችን በመንግሥት ባለቤትነት ያለ መሆኑ ነው" ብለዋል።ሳፊሪኮም ኢትዮጵያ 3 ሚሊዮን ዶላር ለኢትዮ ቴሌኮም ለመሠረተ ልማት ኪራይ እንደሚከፈል የገለጹት ዋና ሥራ አስኪያጁ፤ ኩባንያው የሚጠበቅነትን ግብር እስካሁኑ ሰዓት ድረስ በቴሌብር እንሚከፍል ተናግረዋል፡፡
Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
የውጭ ሀገር ዜጎች በትንሹ 150 ሺህ ዶላር በመውጣት የማይንቀሳቀስ የመኖሪያ ቤት ባለቤት እንዲሆኑ የሚፈቅደው አዋጅ ፀደቀ!
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ሀገር ዜጎች የማይንቀሳቀስ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የመሆን መብት አዋጅን አጸደቀ። ከአዲስ አበባ ውጪ መስራት ቢፈልጉ በወጣው መመሪያ መሰረት ክልሎች ተፈፃሚ እንደሚያደርጉም ተገልጿል።የውጭ ሀገር ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በመኖሪያ ቤት ባለቤትነት ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የተቀመጠው አነስተኛ የገንዘብ መጠን 150 ሺህ ዶላር ነው ተብሏል።
“አንድ የውጭ ሀገር ዜጋ የሊዝ ዋጋውን ጨምሮ ለአንድ መኖሪያ ቤት ግንባታ ሙሉ ዋጋ ወይንም ለመኖሪያ ቤት ግዢ የሚመድበው አነስተኛ የገንዘብ መጠን ከ150 ሺ ዶላር ያነሰ ሊሆን አይችልም” ተብሏል።150 ሺህ ዶላር ሁኖ የተቀመጠው አነስተኛ የገንዘብ መጠን በጊዜ ሂደት እየተሻሻለ እንደሚሄድም ተመላክቷል።
"ማንኛው የውጭ ዜጋ በማናቸውም ጊዜ፣ በአንድ ግዜ የሚኖረው የመኖሪያ ቤት ቁጥር አንድ ብቻ" መሆኑ የተቆመ ሲሆን ሚኒስቴሩ "ከአገር ጥቅም አንጻር አስፈላጊ ሁኖ ሲያገኘው ይህን ቁጥር በመመሪያ ማሻሻል ይችላል" ተብሏል።የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሆነ የውጭ ሀገር ዜጋ “ለግለሰብ ወይም ለቤተሰብ የማከራየት መብቱ እንደተጠበቀ ሁኖ መኖሪያ ቤቱን ለንግድ አላማ ማዋል የተከለከለ መሆኑ” በአዋጁ ተቀምጧል።
ይህ የተገለጸው በምክር ቤቱ የከተማ፣ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በአዋጁ ዙሪያ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡለት ጥያቄ ምላሽ እና ማብራሪያ በሰጠበት ወቅት ነው።መሬት የመንግስት እና የህዝብ እንደመሆኑ ለኢንቨስትመንት የሚመጡ ዜጎች መሬቱን የመሸጥ እና የመለወጥ መብት የላቸውም ተብሏል።
የውጭ ሀገር ዜጎች በመኖሪያ ቤት ባለቤትነት ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የቀረበው የገንዘብ መጠን ዝቅተኛ በመሆኑ ወደ ኢትዮጵያ በብዛት ሊገቡ ስለሚችሉ የሰው ቁጥሩ በሀገራችን እንዲጨምር ሊያደርግ ይችላል የሚል ጥያቄ ከአባላቱ ተነስቷል።
@YeneTube @FikerAssefa
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ሀገር ዜጎች የማይንቀሳቀስ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የመሆን መብት አዋጅን አጸደቀ። ከአዲስ አበባ ውጪ መስራት ቢፈልጉ በወጣው መመሪያ መሰረት ክልሎች ተፈፃሚ እንደሚያደርጉም ተገልጿል።የውጭ ሀገር ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በመኖሪያ ቤት ባለቤትነት ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የተቀመጠው አነስተኛ የገንዘብ መጠን 150 ሺህ ዶላር ነው ተብሏል።
“አንድ የውጭ ሀገር ዜጋ የሊዝ ዋጋውን ጨምሮ ለአንድ መኖሪያ ቤት ግንባታ ሙሉ ዋጋ ወይንም ለመኖሪያ ቤት ግዢ የሚመድበው አነስተኛ የገንዘብ መጠን ከ150 ሺ ዶላር ያነሰ ሊሆን አይችልም” ተብሏል።150 ሺህ ዶላር ሁኖ የተቀመጠው አነስተኛ የገንዘብ መጠን በጊዜ ሂደት እየተሻሻለ እንደሚሄድም ተመላክቷል።
"ማንኛው የውጭ ዜጋ በማናቸውም ጊዜ፣ በአንድ ግዜ የሚኖረው የመኖሪያ ቤት ቁጥር አንድ ብቻ" መሆኑ የተቆመ ሲሆን ሚኒስቴሩ "ከአገር ጥቅም አንጻር አስፈላጊ ሁኖ ሲያገኘው ይህን ቁጥር በመመሪያ ማሻሻል ይችላል" ተብሏል።የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሆነ የውጭ ሀገር ዜጋ “ለግለሰብ ወይም ለቤተሰብ የማከራየት መብቱ እንደተጠበቀ ሁኖ መኖሪያ ቤቱን ለንግድ አላማ ማዋል የተከለከለ መሆኑ” በአዋጁ ተቀምጧል።
ይህ የተገለጸው በምክር ቤቱ የከተማ፣ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በአዋጁ ዙሪያ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡለት ጥያቄ ምላሽ እና ማብራሪያ በሰጠበት ወቅት ነው።መሬት የመንግስት እና የህዝብ እንደመሆኑ ለኢንቨስትመንት የሚመጡ ዜጎች መሬቱን የመሸጥ እና የመለወጥ መብት የላቸውም ተብሏል።
የውጭ ሀገር ዜጎች በመኖሪያ ቤት ባለቤትነት ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የቀረበው የገንዘብ መጠን ዝቅተኛ በመሆኑ ወደ ኢትዮጵያ በብዛት ሊገቡ ስለሚችሉ የሰው ቁጥሩ በሀገራችን እንዲጨምር ሊያደርግ ይችላል የሚል ጥያቄ ከአባላቱ ተነስቷል።
@YeneTube @FikerAssefa
የመንግስት ገቢን “በከፍተኛ ደረጃ” ማሳደግ “የሞት የሽረት ጉዳይ ነው” ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ ተናገሩ!
የፌደራል መንግስት የሚሰብሰበውን ገቢ በሚቀጥለው ዓመት “በከፍተኛ ደረጃ” ለማሳደግ ማቀዱ “የሞት የሽረት ጉዳይ ነው” ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ተናገሩ። በኢትዮጵያ ያለውን የልማት ፍላጎት ከአሁን በኋላ ማሳካት የሚቻለው ገቢን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ እንደሆነ የገለጹት ሚኒስትሩ፤ “አዲስ የልማት ጥያቄ ለመፍታት ብለን ከብሔራዊ ባንክ የምንበደርበት ሁኔታ አብቅቶለታል” ብለዋል።
የገንዘብ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 24፤ 2017 በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው። የዛሬው መደበኛ ስብሰባ ዋነኛ ትኩረቱን ያደረገው፤ የፌደራል መንግስት ለ2018 ባዘጋጀው በጀት ዝርዝር ጉዳዮች ላይ ነበር።
የፌደራል መንግስት በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ለፓርላማ ያቀረበው የበጀት መጠን 1.93 ትሪሊዮን ብር ሲሆን ከሀገር ውስጥ ምንጮች ለመሰብሰብ ያቀደው የገንዘብ መጠን 1.23 ትሪሊዮን ብር ነው። በቀጣዩ በጀት ዓመት ከታክስ ይገኛል ተብሎ የሚጠበቀው 1.1 ትሪሊዮን ብር ገቢ፤ ለዘንድሮ በእቅድ ከተያዘው በ200 ቢሊዮን ብር ገደማ ጭማሪ አለው።
የ2018 በጀትን አስመልክቶ በዛሬው የፓርላማ ውይይት ላይ ማብራሪያ ያቀረቡት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ፤ የፌደራል መንግስት የሀገር ውስጥ ገቢን “በከፍተኛ ደረጃ” የማሳደግ ዓላማ እንዳለው ገልጸዋል። መንግስት በአገልግሎት ታሪፍ ማሻሻያ የሚያገኘውን የገቢ መጠን በተመሳሳይ ሁኔታ ከፍ የማድረግ እቅድ እንዳለውም ጠቁመዋል።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
የፌደራል መንግስት የሚሰብሰበውን ገቢ በሚቀጥለው ዓመት “በከፍተኛ ደረጃ” ለማሳደግ ማቀዱ “የሞት የሽረት ጉዳይ ነው” ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ተናገሩ። በኢትዮጵያ ያለውን የልማት ፍላጎት ከአሁን በኋላ ማሳካት የሚቻለው ገቢን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ እንደሆነ የገለጹት ሚኒስትሩ፤ “አዲስ የልማት ጥያቄ ለመፍታት ብለን ከብሔራዊ ባንክ የምንበደርበት ሁኔታ አብቅቶለታል” ብለዋል።
የገንዘብ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 24፤ 2017 በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው። የዛሬው መደበኛ ስብሰባ ዋነኛ ትኩረቱን ያደረገው፤ የፌደራል መንግስት ለ2018 ባዘጋጀው በጀት ዝርዝር ጉዳዮች ላይ ነበር።
የፌደራል መንግስት በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ለፓርላማ ያቀረበው የበጀት መጠን 1.93 ትሪሊዮን ብር ሲሆን ከሀገር ውስጥ ምንጮች ለመሰብሰብ ያቀደው የገንዘብ መጠን 1.23 ትሪሊዮን ብር ነው። በቀጣዩ በጀት ዓመት ከታክስ ይገኛል ተብሎ የሚጠበቀው 1.1 ትሪሊዮን ብር ገቢ፤ ለዘንድሮ በእቅድ ከተያዘው በ200 ቢሊዮን ብር ገደማ ጭማሪ አለው።
የ2018 በጀትን አስመልክቶ በዛሬው የፓርላማ ውይይት ላይ ማብራሪያ ያቀረቡት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ፤ የፌደራል መንግስት የሀገር ውስጥ ገቢን “በከፍተኛ ደረጃ” የማሳደግ ዓላማ እንዳለው ገልጸዋል። መንግስት በአገልግሎት ታሪፍ ማሻሻያ የሚያገኘውን የገቢ መጠን በተመሳሳይ ሁኔታ ከፍ የማድረግ እቅድ እንዳለውም ጠቁመዋል።
Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
ክልሎች ለወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር በሚል፤ ህግ ወጥ ኬላዎችን እንደሚያቋቁሙ ሁለት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በጋራ ያስጠኑት ጥናት አመላከተ!
በኢትዮጵያ በክልል ፖሊሶች፣ የሚሊሻ መዋቅሮችና ለወጣቶች የስራ እድል በሚል 237 ህገወጥ ኬላዎች መቋቋማቸውን የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶቹ ጥናት አመላከተ።ንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና ከትራንስፖርት እና ሎጂስቲከስ ሚኒስቴር በጋራ በመሆን በሚያዚያ ወር 2017 ዓ.ም ባጠናቀቁት ጥናት መሰረት በሀገሪቱ 237 ህገ ወጥ ኬላዎች መኖራቸው መረጋገጡ ተገለጸ።
ክልሎች ለወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር በሚል፤ ህግ ወጥ ኬላዎችን እንደሚያቋቁሙ በጥናቱ መረጋገጡም የጉምሩክ ኮሚሽን ጠቁሟል።የጉምሩክ ኮሚሽን ይህን የተናገረው የ11 ወር የስራ ክንውን ሪፖርቱን ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት መሆኑ ተገልጿል።
ባለፉት 11 ወራት 19 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የተናገረው የጉምሩክ ኮሚሽን፤ በየክልሎች ገመድ እየተወጠረ ገቢ የሚሰበስብባቸው ህገ ወጥ ኬላዎች በሀገሪቱ ንግድ ሥርዓት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደሩ እንደሆነ ተናግሯል፡፡ኬላዎችን ዘርግተው ግብር የሚሰበስቡት የክልለ ፖሊሶች፣ የሚሊሻ መዋቅሮች እንዳንድ ቦታ ደግሞ ለወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ እና በወረዳ ግብረ ሃይል ተብሎም ጭምር የተቋቋሙ ኬላዎች እንዳሉ ምክትል ኮሚሽነሩ አቶ አዘዘው ጫኔ መናገራቸውን ከሸገር ሬድዮ ያገኘነው መረጃ ያሰያል።
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ በክልል ፖሊሶች፣ የሚሊሻ መዋቅሮችና ለወጣቶች የስራ እድል በሚል 237 ህገወጥ ኬላዎች መቋቋማቸውን የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶቹ ጥናት አመላከተ።ንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና ከትራንስፖርት እና ሎጂስቲከስ ሚኒስቴር በጋራ በመሆን በሚያዚያ ወር 2017 ዓ.ም ባጠናቀቁት ጥናት መሰረት በሀገሪቱ 237 ህገ ወጥ ኬላዎች መኖራቸው መረጋገጡ ተገለጸ።
ክልሎች ለወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር በሚል፤ ህግ ወጥ ኬላዎችን እንደሚያቋቁሙ በጥናቱ መረጋገጡም የጉምሩክ ኮሚሽን ጠቁሟል።የጉምሩክ ኮሚሽን ይህን የተናገረው የ11 ወር የስራ ክንውን ሪፖርቱን ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት መሆኑ ተገልጿል።
ባለፉት 11 ወራት 19 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የተናገረው የጉምሩክ ኮሚሽን፤ በየክልሎች ገመድ እየተወጠረ ገቢ የሚሰበስብባቸው ህገ ወጥ ኬላዎች በሀገሪቱ ንግድ ሥርዓት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደሩ እንደሆነ ተናግሯል፡፡ኬላዎችን ዘርግተው ግብር የሚሰበስቡት የክልለ ፖሊሶች፣ የሚሊሻ መዋቅሮች እንዳንድ ቦታ ደግሞ ለወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ እና በወረዳ ግብረ ሃይል ተብሎም ጭምር የተቋቋሙ ኬላዎች እንዳሉ ምክትል ኮሚሽነሩ አቶ አዘዘው ጫኔ መናገራቸውን ከሸገር ሬድዮ ያገኘነው መረጃ ያሰያል።
@YeneTube @FikerAssefa
የህወሓት ክፍፍልን ተከትሎ ለሁለት የተከፈሉት የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ወደ እርስ በርስ ግጭት ሊያመሩ ነዉ የሚል ከፍተኛ ስጋት መፈጠሩን በትግራይ በተቃዋሚነት የሚንቀሳቀሰው «ሳልሳይ ወያነ ትግራይ» አሳሰበ።
ሊፈጠር የሚችለዉን ቀውስ ለማስቀረትም በትግራይ ሁሉን አካታች ብሔራዊ ውይይት እንዲደረግ ፓርቲው ጥሪ አቅርቧል።የትግራይ ሐይሎች ወታደራዊ መኮንኖች ባለፈው ጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም «ለአንዱ የህወሓት ክንፍ ያጋደለ» የተባለለትን የአቋም መግለጫ በማንፀባረቃቸው፣ በትግራይ ሐይሎች መካከል መከፋፈሎች መፈጠራቸው ይነሳል።
ይህ ደግሞ የትግራይ ሐይሎች ከፍተኛ አዛዦች ያሉበት ሌላ ታጣቂ ሐይል እንዲፈጠር ምክንያት መሆኑ ተነግሯል። በአፋር እና ትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎች ለወራት የቆየው ይህ አዲስ ሐይል ወደ ትግራይ ክልል መንቀሳቀሱን መረጃዎች ያመለክታሉ።አዲሱ ታይል እዚያዉ ትግራይ ከሚገኘዉ ነባሩ ኃይል ጋር የእርስ በርስ ግጭት እንዳይገጥም የሚል ስጋት በበርካቶች ዘንድ ተፈጥሯል ሲል የዘገበው ዶይቼ ቬለ ነው፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ሊፈጠር የሚችለዉን ቀውስ ለማስቀረትም በትግራይ ሁሉን አካታች ብሔራዊ ውይይት እንዲደረግ ፓርቲው ጥሪ አቅርቧል።የትግራይ ሐይሎች ወታደራዊ መኮንኖች ባለፈው ጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም «ለአንዱ የህወሓት ክንፍ ያጋደለ» የተባለለትን የአቋም መግለጫ በማንፀባረቃቸው፣ በትግራይ ሐይሎች መካከል መከፋፈሎች መፈጠራቸው ይነሳል።
ይህ ደግሞ የትግራይ ሐይሎች ከፍተኛ አዛዦች ያሉበት ሌላ ታጣቂ ሐይል እንዲፈጠር ምክንያት መሆኑ ተነግሯል። በአፋር እና ትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎች ለወራት የቆየው ይህ አዲስ ሐይል ወደ ትግራይ ክልል መንቀሳቀሱን መረጃዎች ያመለክታሉ።አዲሱ ታይል እዚያዉ ትግራይ ከሚገኘዉ ነባሩ ኃይል ጋር የእርስ በርስ ግጭት እንዳይገጥም የሚል ስጋት በበርካቶች ዘንድ ተፈጥሯል ሲል የዘገበው ዶይቼ ቬለ ነው፡፡
@YeneTube @FikerAssefa