Telegram Web Link
ኢትዮጵያና የዓለም ባንክ የአንድ ቢሊየን ዶላር የፋይናንስ ስምምነት ተፈራረሙ!

ኢትዮጵያ እና የዓለም ባንክ የአንድ ቢሊየን ዶላር የፋይናንስ ስምምነት ተፈራርመዋል።ስምምነቱ ሀገሪቱ እያካሄደች ላለው የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና ሁሉን አቀፍ እድገትን ለመደገፍ የተደረገ ነው ተብሏል።

ስምምነቱ የዓለም ባንክ የኢትዮጵያን የሪፎርም አጀንዳ ለመደገፍ ያለውን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ የገንዘብ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።የድጋፍ ስምምነቱ የኢትዮጵያን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አካታች የኢኮኖሚ እድገትን ለማገዝ እንደሚውል ተገልጿል፡፡

ስምምነቱ የፋይናንስ ሴክተሩ መረጋጋትን ለማረጋገጥ፣ የንግድ ተወዳዳሪነትን ለማጎልበት፣ የሀገር ውስጥ ሃብት ማሰባሰብን ለማጠናከር፣ ግልፅ እና ውጤታማ የመንግስት ሴክተር አስተዳደርን ለማስፈን እና የማህበራዊ አገልግሎቶችን ዘላቂነት ለማረጋገጥ እንደሚያግዝ ተነግሯል።

@YeneTube @FikerAssefa
#TemerProperties
ከዚህ በፊት 7 ሳይቶችን ጥንቅቅ አርጎ ያስረከበዉ ቴምር ፕሮፐርቲስ አሁን

📌  በሳርቤት
📌 በፒያሳ መኖሪያ እና የንግድ ሱቆች


10% ቅድመ ክፍያ
ሰፊ የጋራ መገልገያ
ቢያከራዩት,ቢሸጡት ወይም ቢኖሩበት አዋጭ
ተመጣጣኝ ዋጋ

🏡  ሊሴ ገ/ማርያም አጠገብ
       👉1 መኝታ 63ካሬ=
     10% ቅድመ ክፍያ 693,000 ብር
        ሙሉ ክፍያ 6,930,000 ብር

         👉2 መኝታ 86 ካሬ
        10%ቅድመ ክፍያ 946,000 ብር
        ሙሉ ክፍያ 9,460,000 ብር

        👉3 መኝታ 114 ካሬ
      10%ቅድመ ክፍያ 1,219,800 ብር
      ሙሉ ክፍያ 12,198,000 ብር
       
👉ቀሪውን 90% በ16ዙር ብር ያለምንም
ጭማሪ በብር ከፍለው የሚጨርሱት

👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% ደረስ የሚደርስ ቅናሽ

⚠️በተጨማሪም ሱቅ በ900ሺ ብር ቅድመ ክፍያ እዛው ፒያሳ ሚኒሊክ አደባባይእየሸጥን እንገኛለን::

ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251976195835

WhatsApp
Message Temer properties on WhatsApp. https://wa.me/251976195835

Telegram user
@Ruthtemersales

TEMER PROPERTIES
Create | Construct | Deliver
#TemerProperties #Temerrealestate
አቅመ ደካማወችን ሀረጋውያኖችን በነፃ

https://vm.tiktok.com/ZMSayMdXa
በተለያየ የጤና ችግር የሚሰቃዩትን እየ ፈወሰ
ደስታቸውን እየመለሰ የሚገኘውን የህክምና ተቋም https://vm.tiktok.com/ZMSay8eV2/
ሰወች እንዴት እንደተፈወሱ ሲመሰክሩ እንስማ እንይ ቻናሉን እንቀላቀል
https://vm.tiktok.com/ZMSaDEhoN

በስጋውይም ሆነ በመንፈስ ደውየ ከተቸገሩ መተው በመመርመር ይታከሙ ይፈወሱ
  44ት አይነት በሽታወችን እየፈወስን እንገኛለን
  አድራሻ አዲስ አበባ አየርጤና ወደካራ ናትራን ኩፓንያ ፊት ለፊት
ቁጥር ሁለት ባህርዳር ዲያስፖራ በአሮጌው አስፓልት መስጊዱ ፊት ለፊት
☎️ 0917040506
☎️0912718883
ይደውሉ ይምጡ ይታከሙ ይፈወሱ ይመስክሩ
ዜና: "የኃይሌ ኃይሎች" የተሰኘና በአንጋፋው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ የስኬት ሚስጥሮች ዙርያ የሚያጠነጥን መጽሐፍ ለምርቃት ሊበቃ ነው

"የኃይሌ ኃይሎች" ወይም 'Dissecting Haile' የተሰኘና በአንጋፋው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ የህይወት ስኬት ሚስጥሮች ዙርያ የሚያጠነጥን መጽሐፍ ለምርቃት ሊበቃ መሆኑ ተገለጸ።

የመጽሐፉን ምረቃ ቅድመ ዝግጅት አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ መርሀግብር ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 28 ቀን 2017 ዓ.ም በኃይሌ ግራንድ ሆቴል ተካሄዷል።

በመርሀግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የመጽሐፉ ደራሲ እና የአትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ልጅ ሜላት ኃይሌ መጽሐፉ ስለ አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ የህይወት ፍልስፍናዎች የሚዳስስ መሆኑን አንስተዋል።

አክለውም መከራን ወደ ተጽዕኖ ለመለወጥ ለሚፈልጉ ሰዎች ምሳሌ የሚሆን እና ከሀይሌ ገብረስላሴ የህይወት ስኬቶች ጀርባ ያሉ ሚስጥሮችን ያካተተ መጽሐፍ መሆኑን ተናግረዋል።

አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ በመርሀግብሩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉ ሲሆን "ብቻን ሆኖ ጀግና መሆን አይቻልም: እኔም ከቤተሰብ ጀምሮ የማህበረሰቤ ውጤት ነኝ" ብለዋል።

አክለውም በመጽሐፉ ላይ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሰዎች ምስጋና አቅርበዋል።

"የኃይሌ ኃይሎች" /Dissecting Haile/ በ12 ምዕራፎች ተከፋፍሎ በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች እንዲሁም በብሬል የተሰናዳ እንደሆነም ተገልጿል።

መጽሐፉ የፊታችን ነሐሴ 2017 ዓ.ም በኤሌክትሮኒክስ እና በሀርድ ኮፒ አማራጮች በይፋ ለአንባቢያን ይቀርባል ተብሏል።
ኦፌኮ ከተመድ የውጭ መረጃ አሰባሳቢ ልዑክ ጋር በ2018 ሀገራዊ ምርጫ ዙሪያ ተወያየ፤ የምርጫ ቦርድ እንደገና ማዋቀርን ጨምሮ ቁልፍ ጥያቄዎችን አቀረበ!

የኦሮሞ ፌዴራላሲት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ጋር በ2018 ዓ.ም. በሚካሄደው 7ኛው ዙር አጠቃላይ ምርጫ ዙርያ ውይይት ማድረጉን አስታወቀ።

በኦፌኮ ዋና ጽ/ቤት በተካሄደው ስብሰባ ላይ የፓርቲው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና እና የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሱልጣን ቃሲም የተገኙ ሲሆን በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ህብረት ቢሮ (UNOAU) የምርጫ ድጋፍ ክፍል ዋና ኦፊሰር የሆኑት አኪንየሚ ኦ. አዴግባላን ጨምሮ አራት አባላትን የያዘ ልዑክ መገኘቱን ከፓርቲው ይፋዊ የፌስቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ኦፌኮ በስብሰባው ላይ ነጻ፣ ፍትሃዊ እና ተአማኒነት ያለው የምርጫ ሂደት እንዲረጋገጥ መንግስት ሊያሟላቸው የሚገቡ "መሰረታዊ" ጥያቄዎችን ማቅረቡ ተጠቁሟል።

የፓርቲው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ኦፌኮ በ2018 ምርጫ ላይ መሳተፉ ሙሉ በሙሉ "በመሠረታዊ እና በተጨባጭ ለውጦች" ላይ የተመሰረተ መሆኑን ለልዑካን ቡድኑ አስረድተዋል።

"ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ድምፅ የመስጠት ቴክኒካዊ ሂደት ብቻ አይደለም፤ የዲሞክራሲያዊ ሂደት ውጤት ነው" ያሉት ፕሮፌሰር መረራ፣ "ይህ ሂደት ዛሬ በኢትዮጵያ የለም። በጦርነት እና በፖለቲካ ስደት ውስጥ ተአማኒነት ያለው ምርጫ ማካሄድ አይቻልም" ሲሉ አክለዋል።

ኦፌኮ በ2018 ዓ.ም አጠቃላይ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ መሠረታዊ ተቋማዊ እና ህጋዊ ማሻሻያዎች እንዲደረጉ የጠየቀ ሲሆን የምርጫ ቦርድን እንደገና ማዋቀርን ጨምሮ የምርጫ ስርዓት ማሻሸያ እንዲደረግ እና ከምርጫ በፊት በገዢው ፓርቲ እና በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል ግልጽ የሆነ ፍኖተ ካርታ ላይ ለመስማማት የሚያስችል ውይይት እንዲካሄድ ጥሪ አቅርቧል።

በተጨማሪም በኦሮሚያና በመላ ኢትዮጵያ ያለው ግጭት እንዲቆም፣ የኦፌኮ አባላት፣ አመራሮችንና ደጋፊዎችን ጨምሮ በመላ አገሪቱ የታሰሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች፣ ጋዜጠኞችና አክቲቪስቶች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ፣ በተቃዋሚዎች ላይ የሚደርሰው ማስፈራራት፣ ወከባና እስራት እንዲቆም እና የጸጥታ ሀይሎች በፖለቲካው ሂደት ውስጥ ገለልተኛ የሚሆኑበት ስምምነት እንዲፈረም ጠይቋል።

@YeneTube @FikerAssefa
የሀጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን ለአርቲስት አንዱአለም ጎሳ ሰጥቶት የነበረውን ሽልማት ሰረዘ፤ ይቅርታም ጠይቋል!

የሀጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን ስሞኑን በተካሄደው አራተኛው የሀጫሉ ሁንዴሳ የሽልማት ፕሮግራም ላይ ለአርቲስት አንዱአለም ጎሳ ሽልማት መስጠቱ "ስህተት" እንደሆነ ገልፆ ሽልማቱን በይፋ መሰረዙን አስታወቀ።

በእጮኛው ቃናኒ አዱኛ ሞት ጋር በተያያዘ ተጠርጥሮ ለሶስት ወራት ታስሮ ከቆየ በኃላ በዋስ የተለቀቀው አርቲስት አንዱአለም ጎሳ ሰሞኑን የሀጫሉ ሁንዴሳ ሽልማት መሸለሙን ተከትለው የተለያዩ አካላት በማህበራዊ ሚድያ ተቃውሞዋቸውን ሲያሰሙ ቆይተዋል።

በተለይም ከሽልማት ፕሮግራሙ በኃላ በቀኔኒ አዱኛ ላይ የደረሱ አካላዊ ጉዳቶችን የሚያሳዩ ምስሎች በማህበራዊ ሚድያ በስፋት መሰራጨታቸውን ተከትሎ ፋውንዴሽኑ የሰጠውን ሽልማት እንዲሰርዝ የማህበራዊ ሚድያ ዘመቻ ሲደረግ ነበር።

ይህንን ተከትሎ የሀጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን ዛሬ ሰኔ 28 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ሽልማቱን ከማበርከቱ በፊት ጉዳዩን ሲከታተል መቆየቱን ገልፆ፤ ሽልማቱ ምርመራ እያደረገ ካለው የሚመለከተው አካል ባገኘው ደብዳቤ ላይ በመመስረት የተበረከተ መሆኑን ገልጿል።

ይሁን እንጂ "ሽልማቱን ተከትሎ ከህዝብ በደረሰን ሀሳብ እና ቅሬታ ላይ በመመስረት ውሳኔያችን ስህተት እንደ ነበር በፋውንዴሽኑ ቦርድ ተረጋግጧል "ብሏል። ፋውንዴሽኑ ለተፈጠረው ስህተት ህዝቡን ይቅርታ እየጠየቀ ለአርቲስት አንዱአለም ጎሳ ተሰጥቶ የነበረው ሽልማት መሰረዙን ገልጿል። ፋውንዴሽኑ የሰውን ልጅ መብት ከሚጥሱ እና ፍትህ ከሚያዛቡ አካላት ጋር አብሮ እንደማይቆም አረጋግጧል።

@YeneTube @FikerAssefa
ህወኃት ጠ/ሚኒስትሩ በፓርላማ ለሰጡት ሃሳብ ምን አለ?

ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ተገኝተው ትግራይን በተለይም የተከፋፈሉትን የህወሓት አመራሮች አስመልክቶ ለሰጡት ሃሳብ ህወኃት ባለ 3 ነጥብ መግለጫ አውጥቷል፡፡ በመግለጫው ምን አለ?

@YeneTube @FikerAssefa
2025/07/06 01:51:55
Back to Top
HTML Embed Code: