Forwarded from YeneTube
በሩን ይክፈቱ ችግረወን
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
👎6❤2
በኦሮሚያ ክልል በውጪ ዜጎች አንድ የደጋ አጋዘን በ15 ሺህ ዶላር እየታደነ መሆኑን ባለስልጣኑ ገለፀ!
በኦሮሚያ ክልል የውጪ ዜጎች በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኘውን የደጋ አጋዘንን በ15 ሺህ ዶላር እያደኑ መሆኑን ክልሉ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ።የኦሮሚያ ክልል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ቦና ያዴሳ፤ “የውጪ ዜጎች አንድ አጋዘን ለማደን 15 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ይከፍላሉ፤ ያደኑትንም አጋዘን ከአንገት በላይ ያለው አካል ይዘው መሄድ ይችላሉ” ብለዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ፤ የደጋ አጋዘን በአርሲ እና ባሌ ተራራማ ስፍራዎች እንዲሁም በምዕራብ ሀረርጌ በስፋት የሚገኝ መሆኑን ጠቅሰው የውጪ ሀገር ዜጎችም ለስፖርታዊ አደን የሚመርጡት ብርቅዬ እንስሳ መሆኑን ተናግረዋል።አሁን ላይ በአዳባ እና ዶዶላ አካባቢዎች ኢንተርፕራይዞች ተደራጅተው ለውጪ ዜጎች የደጋ አጋዘንን ለአደንነት እንዲያቀርቡ መደረጉን ገልጸዋል፡፡
አደኑን የሚያደርጉት የውጪ ዜጎች ፈቃድ የሚሰጣቸው ሲሆን፤ በአካባቢው ከተደራጁ ኢንተርፕራይዞች ጋር በመሆን ያረጀ ወንድ የደጋ አጋዘን ተመርጦ እንዲያድኑ ይደረጋል ሲሉ ለኢፕድ ተናግረዋል። ማንኛውንም የደጋ አጋዘን ማደን ፈጽሞ የተከለከለ መሆኑንም አክለዋል፡፡ከአደኑ የሚገኘው ገቢ 70 በመቶ ለኢንተርፕራዞች የሚገባ መሆኑና 30 በመቶውን መንግስት እንደሚወሰድም አቶ ቦና ተናግረዋል፡፡
በዚህም ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኘውን የደጋ አጋዘን ለውጪ ሀገር ዜጎች ለሕጋዊ አደን በማቅረብ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከፍ ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡
Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
በኦሮሚያ ክልል የውጪ ዜጎች በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኘውን የደጋ አጋዘንን በ15 ሺህ ዶላር እያደኑ መሆኑን ክልሉ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ።የኦሮሚያ ክልል አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ቦና ያዴሳ፤ “የውጪ ዜጎች አንድ አጋዘን ለማደን 15 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ይከፍላሉ፤ ያደኑትንም አጋዘን ከአንገት በላይ ያለው አካል ይዘው መሄድ ይችላሉ” ብለዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ፤ የደጋ አጋዘን በአርሲ እና ባሌ ተራራማ ስፍራዎች እንዲሁም በምዕራብ ሀረርጌ በስፋት የሚገኝ መሆኑን ጠቅሰው የውጪ ሀገር ዜጎችም ለስፖርታዊ አደን የሚመርጡት ብርቅዬ እንስሳ መሆኑን ተናግረዋል።አሁን ላይ በአዳባ እና ዶዶላ አካባቢዎች ኢንተርፕራይዞች ተደራጅተው ለውጪ ዜጎች የደጋ አጋዘንን ለአደንነት እንዲያቀርቡ መደረጉን ገልጸዋል፡፡
አደኑን የሚያደርጉት የውጪ ዜጎች ፈቃድ የሚሰጣቸው ሲሆን፤ በአካባቢው ከተደራጁ ኢንተርፕራይዞች ጋር በመሆን ያረጀ ወንድ የደጋ አጋዘን ተመርጦ እንዲያድኑ ይደረጋል ሲሉ ለኢፕድ ተናግረዋል። ማንኛውንም የደጋ አጋዘን ማደን ፈጽሞ የተከለከለ መሆኑንም አክለዋል፡፡ከአደኑ የሚገኘው ገቢ 70 በመቶ ለኢንተርፕራዞች የሚገባ መሆኑና 30 በመቶውን መንግስት እንደሚወሰድም አቶ ቦና ተናግረዋል፡፡
በዚህም ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኘውን የደጋ አጋዘን ለውጪ ሀገር ዜጎች ለሕጋዊ አደን በማቅረብ የህብረተሰቡን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ከፍ ማድረግ ተችሏል ብለዋል፡፡
Via AS
@YeneTube @FikerAssefa
😭62❤34😁10👍2👀2
የአሜሪካ አየር ማረፊያዎች በደህንነት ፍተሻዎች ወቅት ጫማ ማውለቅን ሊያስቀሩ ነው!
የዩናይትድ ስቴትስ አየር ማረፊያዎች በትራንስፖርት ደህንነት አስተዳደር (TSA) በሚካሄዱ የደህንነት ፍተሻዎች ወቅት ተሳፋሪዎች ጫማቸውን እንዲያወልቁ የሚያስገድደውን እና ከ20 ዓመታት በፊት ገደማ የተጀመረውን ብዙም ተቀባይነት የሌለውን ፖሊሲ ሊያስቆሙ ነው።
የሃገር ውስጥ ደህንነት ኃላፊ ክሪስቲ ኖውም ምንም እንኳን "ተከታታይ" የፍትሻ ሂደቱ እንዳለ ቢቆይም ለውጡ በመላው የአሜሪካ አየር ማረፊያዎች ላይ ወዲያውኑ ተግባራዊ ሆኗል ብለዋል ።
መንገደኞች አሁንም ቀበቶዎችን እና ካፖርቶችን ማውለቅ እንዲሁም ላፕቶፖችን እና ፈሳሾችን ከቦርሳ ማውጣት አለባቸው፣ ነገር ግን እነዚህም ሂደቶች እየተገመገሙ ናቸው ሲሉ ኖውም ተናግረዋል።
አየር መንገድ ተሳፋሪዎች ለምርመራ ጫማ እንዲያወልቁ የሚጠይቀው መስፈርት በአገር አቀፍ ደረጃ ተግባራዊ መሆን የጀመረው እ.አ.አ ከ2006 ጀምሮ አንድ እንግሊዛዊ ወደ ማያሚ በሚጓዝ በረራ ላይ በአንዱ ጫማው ውስጥ ቦምብ ከደበቀ በኋላ ነበር።
ኖውም ማክሰኞ ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ "የእኛ የደህንነት ቴክኖሎጂ በከፍተኛ ሁኔታ ተቀይሯል፣ ተሻሽሏል። የትራንስፖርት ደህንነት አስተዳደር ተለውጧል" ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
የዩናይትድ ስቴትስ አየር ማረፊያዎች በትራንስፖርት ደህንነት አስተዳደር (TSA) በሚካሄዱ የደህንነት ፍተሻዎች ወቅት ተሳፋሪዎች ጫማቸውን እንዲያወልቁ የሚያስገድደውን እና ከ20 ዓመታት በፊት ገደማ የተጀመረውን ብዙም ተቀባይነት የሌለውን ፖሊሲ ሊያስቆሙ ነው።
የሃገር ውስጥ ደህንነት ኃላፊ ክሪስቲ ኖውም ምንም እንኳን "ተከታታይ" የፍትሻ ሂደቱ እንዳለ ቢቆይም ለውጡ በመላው የአሜሪካ አየር ማረፊያዎች ላይ ወዲያውኑ ተግባራዊ ሆኗል ብለዋል ።
መንገደኞች አሁንም ቀበቶዎችን እና ካፖርቶችን ማውለቅ እንዲሁም ላፕቶፖችን እና ፈሳሾችን ከቦርሳ ማውጣት አለባቸው፣ ነገር ግን እነዚህም ሂደቶች እየተገመገሙ ናቸው ሲሉ ኖውም ተናግረዋል።
አየር መንገድ ተሳፋሪዎች ለምርመራ ጫማ እንዲያወልቁ የሚጠይቀው መስፈርት በአገር አቀፍ ደረጃ ተግባራዊ መሆን የጀመረው እ.አ.አ ከ2006 ጀምሮ አንድ እንግሊዛዊ ወደ ማያሚ በሚጓዝ በረራ ላይ በአንዱ ጫማው ውስጥ ቦምብ ከደበቀ በኋላ ነበር።
ኖውም ማክሰኞ ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ "የእኛ የደህንነት ቴክኖሎጂ በከፍተኛ ሁኔታ ተቀይሯል፣ ተሻሽሏል። የትራንስፖርት ደህንነት አስተዳደር ተለውጧል" ብለዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
❤21👍6😁1
ስኳር በእርግጥ ልጆችን ሃይፐርአክቲቭ(ከመጠን በላይ የነቁ) ረባሾች ያደርጋል?
https://www.tiktok.com/@sociosaga/video/7524997823616584965
https://www.tiktok.com/@sociosaga/video/7524997823616584965
❤2😁2
የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ የኢትዮጵያ ብር ከሩብል ጋር ያለውን ይፋዊ የምንዛሪ ተመን ሊወስን መሆኑ ታወቀ!
ባንኩ በተጨማሪ የ11 ሀገራት ገንዘቦች ከሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ጋር ያላቸውን ይፋዊ የምንዛሪ ተመን ለማስቀመጥ ውሳኔ ላይ መድረሱ ታውቋል።
እነርሱም የባንግላዴሽ ታካ፣ የባህሬን ዲናር፣ የቦሊቪያ ቦሊቪያኖ፣ የኩባ ፔሶ፣ የአልጄሪያ ዲናር፣የኢራን ሪያል፣ የሚያንማር ኪያት፣ የሞንጎሊያ ቱግሪክ፣ የናይጄሪያ ናይራ፣ የኦማን ሪያል እናየሳዑዲ ሪያል ናቸው።ባንኩ የምንዛሪ ተመኑን ከሀምሌ 3 ጀምሮ ይፋ እንደሚያደርግ ኢንተርፋክስ ዘግቧል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
ባንኩ በተጨማሪ የ11 ሀገራት ገንዘቦች ከሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ጋር ያላቸውን ይፋዊ የምንዛሪ ተመን ለማስቀመጥ ውሳኔ ላይ መድረሱ ታውቋል።
እነርሱም የባንግላዴሽ ታካ፣ የባህሬን ዲናር፣ የቦሊቪያ ቦሊቪያኖ፣ የኩባ ፔሶ፣ የአልጄሪያ ዲናር፣የኢራን ሪያል፣ የሚያንማር ኪያት፣ የሞንጎሊያ ቱግሪክ፣ የናይጄሪያ ናይራ፣ የኦማን ሪያል እናየሳዑዲ ሪያል ናቸው።ባንኩ የምንዛሪ ተመኑን ከሀምሌ 3 ጀምሮ ይፋ እንደሚያደርግ ኢንተርፋክስ ዘግቧል፡፡
@YeneTube @FikerAssefa
❤35😁14🔥2
ቡስትግራም - የሶሻል ሚዲያ ገፅታዎን መገንባት አሁን በጣም ቀላል ሆኗል!`
LINK -
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤5
የኬንያዊ ፕረዝዳምት ዊሊያም ሩቶ ፖሊስ የተቃዋሚዎችን እግር ተኩሶ እንዲሰብር ትዕዛዝ ሰጡ።
*
ተቃውሞ የበረታባቸው የኬንያው ፕረዝዳንት ዊሊያም ሩቶ የንግድ ድርጅቶችን ኢላማ የሚያደርጉ ተቃዋሚዎችን ፖሊስ እግራቸው ላይ ተኩሶ እንዲመታ መመሪያ ሰጥቷል። ፕረዝዳንቱ ተቃዋሚዎች እግራቸው ላይ ተመትተው አቅማቸው እንድዳከም፣ ግን ደግሞ እንዳይገደሉ አዟል።
“የሌላ ሰው ንግድ ወይም ንብረት ሲያቃጥል የተያዘ ማንኛውም ሰው እግሩ ላይ በጥይት ተመትቶ ሆስፒታል ይግባ፤ ኋላም ፍርድ ቤት መቅረብ አለበት፤ አትግደሏቸው ነገር ግን እግሮቹ መሰባበራቸውን ያረጋግጡ” ብለዋል ፕሬዝዳንቱ ለፖሊስ ባስተላለፉት ትዕዛዝ። ዘገባው የቢቢሲ አፍሪካ ነው።
@Yenetube @Fikerassefa
*
ተቃውሞ የበረታባቸው የኬንያው ፕረዝዳንት ዊሊያም ሩቶ የንግድ ድርጅቶችን ኢላማ የሚያደርጉ ተቃዋሚዎችን ፖሊስ እግራቸው ላይ ተኩሶ እንዲመታ መመሪያ ሰጥቷል። ፕረዝዳንቱ ተቃዋሚዎች እግራቸው ላይ ተመትተው አቅማቸው እንድዳከም፣ ግን ደግሞ እንዳይገደሉ አዟል።
“የሌላ ሰው ንግድ ወይም ንብረት ሲያቃጥል የተያዘ ማንኛውም ሰው እግሩ ላይ በጥይት ተመትቶ ሆስፒታል ይግባ፤ ኋላም ፍርድ ቤት መቅረብ አለበት፤ አትግደሏቸው ነገር ግን እግሮቹ መሰባበራቸውን ያረጋግጡ” ብለዋል ፕሬዝዳንቱ ለፖሊስ ባስተላለፉት ትዕዛዝ። ዘገባው የቢቢሲ አፍሪካ ነው።
@Yenetube @Fikerassefa
😁28😭16❤15👍10👀3👎1🔥1
ዩናይትድ ተጨዋቾቹ ማልያ መቀየር ያቆማሉ !
ማንችስተር ዩናይትድ በቀጣይ በሚያደርጋቸው የወዳጅነት ጨዋታዎች የተለመዱትን ባህላዊ መርሐግብሮች እንደሚሰርዝ ተገልጿል።
ይህንንም ተከትሎ ማንችስተር ዩናይትድ በቀጣይ በወዳጅነት ጨዋታዎች የተለመደውን አርማ እና ስጦታ እንደማይቀያየር ተነግሯል።
በተጨማሪም ተጨዋቾቹ ከወዳጅነት ጨዋታው በፊትም ሆነ በኋላ ማልያቸውን እንዳይቀያየሩ እንደሚያደርግ ተነግሯል።
ክለቡ ውሳኔውን ያሳለፈው በጀመረው የወጪ ቅነሳ መርሐግብር ምክንያት እንደሆነ ቶክ ስፖርት ዘግቧል።
ይሁን እንጂ ማንችስተር ዩናይትድ ውሳኔው አላስፈላጊ ባህላዊ ስነስርዓቶችን ለማስቀረት በማሰብ መሆኑን መግለፁ ተነግሯል።
Via:- Talk Sport
@Yenetube @Fikerassefa
ማንችስተር ዩናይትድ በቀጣይ በሚያደርጋቸው የወዳጅነት ጨዋታዎች የተለመዱትን ባህላዊ መርሐግብሮች እንደሚሰርዝ ተገልጿል።
ይህንንም ተከትሎ ማንችስተር ዩናይትድ በቀጣይ በወዳጅነት ጨዋታዎች የተለመደውን አርማ እና ስጦታ እንደማይቀያየር ተነግሯል።
በተጨማሪም ተጨዋቾቹ ከወዳጅነት ጨዋታው በፊትም ሆነ በኋላ ማልያቸውን እንዳይቀያየሩ እንደሚያደርግ ተነግሯል።
ክለቡ ውሳኔውን ያሳለፈው በጀመረው የወጪ ቅነሳ መርሐግብር ምክንያት እንደሆነ ቶክ ስፖርት ዘግቧል።
ይሁን እንጂ ማንችስተር ዩናይትድ ውሳኔው አላስፈላጊ ባህላዊ ስነስርዓቶችን ለማስቀረት በማሰብ መሆኑን መግለፁ ተነግሯል።
Via:- Talk Sport
@Yenetube @Fikerassefa
😁56❤23
"የኤርትራ ድርጊት በኢትዮጵያ ላይ የጦርነት ስጋት የሚደቅን ነው" -ኢትዮጵያ
በጀኔቫ የተመድ ጽሕፈት ቤት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ጸጋአብ ክበበው፣ የኤርትራ ድርጊት በኢትዮጵያ ላይ ቀጥተኛ የጦርነት ስጋት የሚደቅን ነው በማለት ከሰዋል።
የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት፣ በኤርትራ የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ተቆጣጣሪ ልዩ ራፖርተር የጊዜ ቆይታን ለማራዘም ባለፈው ሳምንት መገባደጃ ላይ በተሰበሰበበት ወቅት፣ አምባሳደር ጸጋአብ የኤርትራ ወታደሮች በተቆጣጠሯቸው የትግራይ አካባቢዎች የከፉ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን እየፈጸሙ ይገኛሉ ብለዋል።
አምባሳደሩ ኤርትራ በኢትዮጵያ ላይ ደቅነዋለች ላሉት ስጋት፣ የኤርትራ ወታደሮች የትግራይ አንዳንድ አካባቢዎችን ተቆጣጥረው እንደሚገኙ የተመድ ልዩ ራፖርተር ለምክር ቤቱ ያቀረቡትን ሪፖርት በአስረጅነት ጠቅሰዋል።
በተመድ የጀኔቫ ቋሚ ጽሕፈት ቤት የኤርትራ ልዑክ አቶ ሃብቶም ዘርዓይ በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ ውንጀላ ካለፉት ድርጊቶቿና አቋሞቿ ጋር የማቃረንና ወጥነት የሌለው መኾኑን በመጥቀስ፣ በምክር ቤቱ ውስጥ ምላሽ ሠጥተዋል።
የኤርትራ ጦር በዓለማቀፍ ሕግ በሚታወቀው የኤርትራ ግዛት ብቻ እንደሚገኝ የጠቀሱት አቶ ሃብቶም፣ የኤርትራ ጦር የኢትዮጵያን ግዛቶችን ይዟል የሚባለው ትርክት "ጦርነት ለመቀስቀስ" እና "ለጦርነት ሽፋን ለመፍጠር ያለመ ሴራ" ነው በማለት ውድቅ አድርገውታል።
ኢትዮጵያ ባኹኑ ወቅት በይፋ ዛቻዎችን መሠንዘር፣ ጦር መሳሪያ ማከማቸትና ቀጠናዊ ሰላምና ጸጥታን የሚያደፈርሱ ድርጊቶችን መፈጸም ቀጥላለች ያሉት አቶ ሃብቶም፤ ኢትዮጵያ ይህን የምታደርገው ውስጣዊ ችግሮቿን ለመሸፋፈን መኾኑን ምክር ቤቱ መረዳት አለበት ብለዋል።
(ዋዜማ)
@YeneTube @FikerAssefa
በጀኔቫ የተመድ ጽሕፈት ቤት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ጸጋአብ ክበበው፣ የኤርትራ ድርጊት በኢትዮጵያ ላይ ቀጥተኛ የጦርነት ስጋት የሚደቅን ነው በማለት ከሰዋል።
የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት፣ በኤርትራ የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ተቆጣጣሪ ልዩ ራፖርተር የጊዜ ቆይታን ለማራዘም ባለፈው ሳምንት መገባደጃ ላይ በተሰበሰበበት ወቅት፣ አምባሳደር ጸጋአብ የኤርትራ ወታደሮች በተቆጣጠሯቸው የትግራይ አካባቢዎች የከፉ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን እየፈጸሙ ይገኛሉ ብለዋል።
አምባሳደሩ ኤርትራ በኢትዮጵያ ላይ ደቅነዋለች ላሉት ስጋት፣ የኤርትራ ወታደሮች የትግራይ አንዳንድ አካባቢዎችን ተቆጣጥረው እንደሚገኙ የተመድ ልዩ ራፖርተር ለምክር ቤቱ ያቀረቡትን ሪፖርት በአስረጅነት ጠቅሰዋል።
በተመድ የጀኔቫ ቋሚ ጽሕፈት ቤት የኤርትራ ልዑክ አቶ ሃብቶም ዘርዓይ በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ ውንጀላ ካለፉት ድርጊቶቿና አቋሞቿ ጋር የማቃረንና ወጥነት የሌለው መኾኑን በመጥቀስ፣ በምክር ቤቱ ውስጥ ምላሽ ሠጥተዋል።
የኤርትራ ጦር በዓለማቀፍ ሕግ በሚታወቀው የኤርትራ ግዛት ብቻ እንደሚገኝ የጠቀሱት አቶ ሃብቶም፣ የኤርትራ ጦር የኢትዮጵያን ግዛቶችን ይዟል የሚባለው ትርክት "ጦርነት ለመቀስቀስ" እና "ለጦርነት ሽፋን ለመፍጠር ያለመ ሴራ" ነው በማለት ውድቅ አድርገውታል።
ኢትዮጵያ ባኹኑ ወቅት በይፋ ዛቻዎችን መሠንዘር፣ ጦር መሳሪያ ማከማቸትና ቀጠናዊ ሰላምና ጸጥታን የሚያደፈርሱ ድርጊቶችን መፈጸም ቀጥላለች ያሉት አቶ ሃብቶም፤ ኢትዮጵያ ይህን የምታደርገው ውስጣዊ ችግሮቿን ለመሸፋፈን መኾኑን ምክር ቤቱ መረዳት አለበት ብለዋል።
(ዋዜማ)
@YeneTube @FikerAssefa
❤48🔥5
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ለንግድ ሱቅ ፈላጊዎች በሙሉ
📍 ፒያሳ ከሚኒልክ አደባባይ ወደ ሀገር ፍቅር ቲያትር የሚወስደው መንገድ ላይ የንግድ ሱቆችን መሸጥ ጀምረናል።
👉 2 ቤዝመንት ያለው
👉ከ 900,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
👉በ1 ዓመት ተኩል የምትረከቡት
👉ምድር ቤት
20 ካሬ= 7ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 2.8ሚሊዮን ብር
👉1ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 5.5 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 2 ሚሊዮን ብር
👉2ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 4.8 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 1.5 ሚሊዮን ብር
👉3ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 4.2 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 1.2 ሚሊዮን ብር
👉4ኛ እና 5ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 3.9 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 900 ሺ ብር
👉ቀሪው በግንባታ ሂደት የሚከፈል።
ለበለጠ መረጃ
09-76-19-58-35
Telegram username
@Ruthtemersales
Whats app
Message Temer properties on WhatsApp. https://wa.me/251976195835
📍 ፒያሳ ከሚኒልክ አደባባይ ወደ ሀገር ፍቅር ቲያትር የሚወስደው መንገድ ላይ የንግድ ሱቆችን መሸጥ ጀምረናል።
👉 2 ቤዝመንት ያለው
👉ከ 900,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
👉በ1 ዓመት ተኩል የምትረከቡት
👉ምድር ቤት
20 ካሬ= 7ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 2.8ሚሊዮን ብር
👉1ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 5.5 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 2 ሚሊዮን ብር
👉2ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 4.8 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 1.5 ሚሊዮን ብር
👉3ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 4.2 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 1.2 ሚሊዮን ብር
👉4ኛ እና 5ኛ ፎቅ
20 ካሬ= 3.9 ሚሊዮን ብር
ቅድመ ክፍያ= 900 ሺ ብር
👉ቀሪው በግንባታ ሂደት የሚከፈል።
ለበለጠ መረጃ
09-76-19-58-35
Telegram username
@Ruthtemersales
Whats app
Message Temer properties on WhatsApp. https://wa.me/251976195835
❤6
በሩን ይክፈቱ ችግረወን
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
ይፍቱ ህመምወን ይዳኑ
ዐሊንኩን ይጫኑ ይቀላቀሉ
https://vm.tiktok.com/ZMSqDLvo7/
https://vm.tiktok.com/ZMSqD4rLk/
ሙሉ አድራሻ አዲስ አበባ ባሕርዳር
0912718883
0917040506
❤1
📌 Minoxidil የወንዶች ፀጉርና ፂም ማሳደግያ
📌 ፀጉሮት እየሳሳ አስቸግሮታል አልያም ፂም ማብቀል ይፈልጋሉ ? መፍትሔውን ይዘንሎት መተናል
⚡ከቆዳችን ስር የሚገኘውን የፀጉር ጉጥ በማንቃት የሳሳን ፀጉር ወደ ቀድሞው የሚመልስ
📌📌 በ"FDA" እውቅናና ማረጋገጫ የተሰጠው ደግሞም በebay ፣ amazon እና በመሳሰሉት የ online መገበያያዎች ላይ "5" ★★★★★ ኮኮብ ያገኘ ነው
⚡በቀን 2 ጊዜ ለሚጠቀሙ ሰዎች በ 1 ወር ውስጥ ውጤት የሚያሳይ
📞 0993944661
Telegram channel link
https://www.tg-me.com/Ethiopiaminoxidil
📌 ፀጉሮት እየሳሳ አስቸግሮታል አልያም ፂም ማብቀል ይፈልጋሉ ? መፍትሔውን ይዘንሎት መተናል
⚡ከቆዳችን ስር የሚገኘውን የፀጉር ጉጥ በማንቃት የሳሳን ፀጉር ወደ ቀድሞው የሚመልስ
📌📌 በ"FDA" እውቅናና ማረጋገጫ የተሰጠው ደግሞም በebay ፣ amazon እና በመሳሰሉት የ online መገበያያዎች ላይ "5" ★★★★★ ኮኮብ ያገኘ ነው
⚡በቀን 2 ጊዜ ለሚጠቀሙ ሰዎች በ 1 ወር ውስጥ ውጤት የሚያሳይ
📞 0993944661
Telegram channel link
https://www.tg-me.com/Ethiopiaminoxidil
❤7
በአንካራ ስምምነት ከስድስት ወራት በኋላ በኢትዮጵያና በሶማሊያ መካከል የነበረው የቴክኒክ ድርድር ቆመ!
በአንካራ ስምምነት ከተፈረመ ከስድስት ወራት በኋላ፣ በኢትዮጵያና በሶማሊያ መካከል በባሕር በር ጉዳይ ላይ ሲካሄድ የነበረው የቴክኒክ ድርድር መቋረጡ ታውቋል። ይህ ድርድር የተጀመረው ባለፈው ዓመት ሁለቱ መንግስታት በቱርክ ሽምግልና የውይይት ጠረጴዛ ላይ ከቀረቡ በኋላ ነበር።
የውዝግቡ መንስኤ እና የሽምግልናው ጅማሬ
ባሕር በር የሌላት ኢትዮጵያ በጥር 1፣ 2024 ከሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ሰነድ በመፈረሟ ውጥረቱ ተባብሶ ነበር።
ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ 20 ኪሎ ሜትር የባሕር ኃይል እና የንግድ መስመር በአደን ባሕረ ሰላጤ እንድትጠቀም የሚያስችል ሲሆን፣ በምላሹም ራሷን የቻለችውን ሶማሌላንድ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እውቅና የማግኘት ዕድል ይሰጣታል። ሶማሊያ ይህንን ስምምነት "ሉዓላዊነቷን የጣሰ ግልጽ ጥሰት" በማለት አውግዛ፣ ስምምነቱ እንዳይጸድቅ ኃይለኛ የዲፕሎማሲ ዘመቻ ጀምራ ነበር። ይህን ውጥረት ለማርገብ ነበር ቱርክ በየካቲት 2024 በአንካራ ሽምግልና የጀመረችው።
በአንካራ በተደረጉ ሦስት ዙር ንግግሮች፣ ታህሳስ 11፣ 2024 ላይ ጊዜያዊ "የአንካራ መግለጫ" ላይ ተደርሷል። በዚህም ሁለቱም ወገኖች በቴክኒካዊ ንግግሮች ለመሳተፍ እና እርስ በእርስ የየብስ ወሰን ክብርን ለመጠበቅ ቃል ገብተው ነበር።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
በአንካራ ስምምነት ከተፈረመ ከስድስት ወራት በኋላ፣ በኢትዮጵያና በሶማሊያ መካከል በባሕር በር ጉዳይ ላይ ሲካሄድ የነበረው የቴክኒክ ድርድር መቋረጡ ታውቋል። ይህ ድርድር የተጀመረው ባለፈው ዓመት ሁለቱ መንግስታት በቱርክ ሽምግልና የውይይት ጠረጴዛ ላይ ከቀረቡ በኋላ ነበር።
የውዝግቡ መንስኤ እና የሽምግልናው ጅማሬ
ባሕር በር የሌላት ኢትዮጵያ በጥር 1፣ 2024 ከሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ሰነድ በመፈረሟ ውጥረቱ ተባብሶ ነበር።
ይህ ስምምነት ኢትዮጵያ 20 ኪሎ ሜትር የባሕር ኃይል እና የንግድ መስመር በአደን ባሕረ ሰላጤ እንድትጠቀም የሚያስችል ሲሆን፣ በምላሹም ራሷን የቻለችውን ሶማሌላንድ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እውቅና የማግኘት ዕድል ይሰጣታል። ሶማሊያ ይህንን ስምምነት "ሉዓላዊነቷን የጣሰ ግልጽ ጥሰት" በማለት አውግዛ፣ ስምምነቱ እንዳይጸድቅ ኃይለኛ የዲፕሎማሲ ዘመቻ ጀምራ ነበር። ይህን ውጥረት ለማርገብ ነበር ቱርክ በየካቲት 2024 በአንካራ ሽምግልና የጀመረችው።
በአንካራ በተደረጉ ሦስት ዙር ንግግሮች፣ ታህሳስ 11፣ 2024 ላይ ጊዜያዊ "የአንካራ መግለጫ" ላይ ተደርሷል። በዚህም ሁለቱም ወገኖች በቴክኒካዊ ንግግሮች ለመሳተፍ እና እርስ በእርስ የየብስ ወሰን ክብርን ለመጠበቅ ቃል ገብተው ነበር።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
❤20😁4
አሜሪካ ለኢትዮጵያውያን የምትሰጠውን ቪዛ ቆይታ ወደ ሦስት ወር አሳጠረች!
በኢትዮጵያ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ለኢትዮጵያውያን የሚሰጠው ቪዛ የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር ማጠሩን አስታወቀ።ኤምባሲው ዛሬ ሐሙስ ሐምሌ 3/2017 ዓ.ም. በኤክስ ገፁ ባሰፈረው መረጃ፤ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስደተኛ ባልሆኑ የቪዛ አመልካቾች ላይ ባደረገው የፖሊሲ ለውጥ ምክንያት ውሳኔው መተላለፉን ገልጿል።
በአዲሱ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፖሊሲ መሠረት፤ "ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም. ጀምሮ ለኢትዮጵውያን የሚሰጠው ቪዛ ለአንድ ጊዜ ብቻ የሚያገለግል እና የሦስት ወር ቆይታ" እንደሚኖረው አስታውቋል።ኤምባሲው በዚሁ የኤክስ ገጽ ልጥፉ ላይ ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም. በፊት የተሰጡ ቪዛዎች ባሉበት እንደሚቀጥሉ ገልጿል።
ለንግድ እና ለጉብኝት ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን የሚያገኙት ቪዛ "B1" እና "B2" በሚለው ምድብ ውድብ ውስጥ ይካተታል።እስካሁን በነበረው አሰራር በዚህ ምድብ ውስጥ የሚገቡ ተጓዦች የሚያገኙት ቪዛ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ነበር። በተጨማሪም የቪዛው የቆይታ ጊዜ እስከሚጠናቀቅ ድረስ በተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ እንዲገቡ ያስችል ነበር።
አሁን ይፋ የተደረገው ፖሊሲ የቪዛውን የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር ከማሳጠር በተጨማሪ በአንድ ቪዛ ተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ መግባትን ከልክሏል።በአዲሱ ፖሊሲ ቪዛ የሚያገኙ ተጓዦች የቆይታ ጊዜ ባይጠናቀቅም እንኳ ከአሜሪካ ከወጡ በኋላ በዚያው ቪዛ ተመልሰው መግባት አይችሉም።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተለያዩ አፍሪካ አገራትን ቪዛ የቆይታ ጊዜን ወደ ሦስት ወራት ማሳጠሩን ይፋ ያደረገው በትናንትናው ዕለት ነበር። ይህ ውሳኔ ከተላለፈባቸው ሀገራት መካከል ናይጄርያ እና ጋና ይገኙበታል።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ለኢትዮጵያውያን የሚሰጠው ቪዛ የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር ማጠሩን አስታወቀ።ኤምባሲው ዛሬ ሐሙስ ሐምሌ 3/2017 ዓ.ም. በኤክስ ገፁ ባሰፈረው መረጃ፤ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስደተኛ ባልሆኑ የቪዛ አመልካቾች ላይ ባደረገው የፖሊሲ ለውጥ ምክንያት ውሳኔው መተላለፉን ገልጿል።
በአዲሱ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፖሊሲ መሠረት፤ "ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም. ጀምሮ ለኢትዮጵውያን የሚሰጠው ቪዛ ለአንድ ጊዜ ብቻ የሚያገለግል እና የሦስት ወር ቆይታ" እንደሚኖረው አስታውቋል።ኤምባሲው በዚሁ የኤክስ ገጽ ልጥፉ ላይ ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም. በፊት የተሰጡ ቪዛዎች ባሉበት እንደሚቀጥሉ ገልጿል።
ለንግድ እና ለጉብኝት ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን የሚያገኙት ቪዛ "B1" እና "B2" በሚለው ምድብ ውድብ ውስጥ ይካተታል።እስካሁን በነበረው አሰራር በዚህ ምድብ ውስጥ የሚገቡ ተጓዦች የሚያገኙት ቪዛ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ነበር። በተጨማሪም የቪዛው የቆይታ ጊዜ እስከሚጠናቀቅ ድረስ በተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ እንዲገቡ ያስችል ነበር።
አሁን ይፋ የተደረገው ፖሊሲ የቪዛውን የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር ከማሳጠር በተጨማሪ በአንድ ቪዛ ተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ መግባትን ከልክሏል።በአዲሱ ፖሊሲ ቪዛ የሚያገኙ ተጓዦች የቆይታ ጊዜ ባይጠናቀቅም እንኳ ከአሜሪካ ከወጡ በኋላ በዚያው ቪዛ ተመልሰው መግባት አይችሉም።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተለያዩ አፍሪካ አገራትን ቪዛ የቆይታ ጊዜን ወደ ሦስት ወራት ማሳጠሩን ይፋ ያደረገው በትናንትናው ዕለት ነበር። ይህ ውሳኔ ከተላለፈባቸው ሀገራት መካከል ናይጄርያ እና ጋና ይገኙበታል።
Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
❤24👎11😁3😭2🔥1
"ኢትዮጵያ በማንኛውም ሁኔታ ከኤርትራ ጋር ወደ ጦርነት የመግባት ፍላጎት የላትም" -የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዛሬው ዕለት ሐምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም በወቅታዊ የስራ ክንውኖቹ ዙሪያ ለሀገር ውስጥና መቀመጫውን አዲስ አበባ ላደረጉ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል። መግለጫውን የሰጡት የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነበያት ጌታቸው የኤርትራና የኢትዮጵያ አሁናዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እና ወቅታዊ እንቅስቃሴዎችን በተመለከተ ከጋዜጠኞች ጥያቄ ቀርቦላቸዋል።
ቃል አቀባዩ ለዚሁ ለቀረበላቸው ጥያቄ <<ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር በማንኛውም ሁኔታ ጦርነት ውስጥ የመግባት ፍላጎት የላትም>>ሲሉ አጭር ምላሽ በመስጠት ተጨማሪ ማብራሪያ ከመስጠት መታቀባቸውን አሻም በታደመችበት ታዝባለች።
በተመሳሳይ ከሰሞኑ በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ የተካሄደውና ኢትዮጵያ አባል የሆነችበት የብሪክስ ጉባኤ መካሄዱን ያስታወሱት ነብያት ፤ ብሪክስ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍ ያደረገና ያስተዋወቀ መድረክ ነውም ብለዋል።
በሌላ በኩል በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ ከ131ሺህ በላይ የሚሆኑና በተለያዩ ሀገራት በተለይም በመካከለኛው እና ሩቅ ምስራቅ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ዜጎች ወደ ሀገር ቤት መንግስት መመለሱን አምባሳደር ነብያት አስታውቀዋል።
Via Asham
@YeneTube @FikerAssefa
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዛሬው ዕለት ሐምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም በወቅታዊ የስራ ክንውኖቹ ዙሪያ ለሀገር ውስጥና መቀመጫውን አዲስ አበባ ላደረጉ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል። መግለጫውን የሰጡት የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነበያት ጌታቸው የኤርትራና የኢትዮጵያ አሁናዊ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እና ወቅታዊ እንቅስቃሴዎችን በተመለከተ ከጋዜጠኞች ጥያቄ ቀርቦላቸዋል።
ቃል አቀባዩ ለዚሁ ለቀረበላቸው ጥያቄ <<ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር በማንኛውም ሁኔታ ጦርነት ውስጥ የመግባት ፍላጎት የላትም>>ሲሉ አጭር ምላሽ በመስጠት ተጨማሪ ማብራሪያ ከመስጠት መታቀባቸውን አሻም በታደመችበት ታዝባለች።
በተመሳሳይ ከሰሞኑ በብራዚል ሪዮ ዴጄኔሮ የተካሄደውና ኢትዮጵያ አባል የሆነችበት የብሪክስ ጉባኤ መካሄዱን ያስታወሱት ነብያት ፤ ብሪክስ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍ ያደረገና ያስተዋወቀ መድረክ ነውም ብለዋል።
በሌላ በኩል በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ ከ131ሺህ በላይ የሚሆኑና በተለያዩ ሀገራት በተለይም በመካከለኛው እና ሩቅ ምስራቅ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ዜጎች ወደ ሀገር ቤት መንግስት መመለሱን አምባሳደር ነብያት አስታውቀዋል።
Via Asham
@YeneTube @FikerAssefa
😁22❤13🔥2👍1
የሁቲ አማጽያን በአንድ ሳምንት ውስጥ ሁለተኛውን የቀይ ባህር የጭነት መርከብ አሰጠሙ!
የየመን ሁቲዎች በጉዞ ላይ የነበረ የጭነት መርከብ ላይ ጥቃት ከፈጸሙ እና መርከቡ ቀይ ባህር ውስጥ ከሰጠመ በኋላ ስድስት መርከበኞች መትረፋቸውን እና ቢያንስ ሦስት ሌሎች ሰዎች መሞታቸውን የአውሮፓ የባህር ኃይል ተልዕኮ አስታወቀ።የላይቤሪያን ባንዲራ የሚያውለበልበው እና በግሪክ የሚንቀሳቀሰው 'ኤተርኒቲ ሲ' የተባለው የጭነት መርከብ 25 ሠራተኞችን ይዞ እየተጓዘ ነበር።
መርከቡ ሰኞ ዕለት ከትንሽ ጀልባዎች በተተኮሱ የሮኬት ቦምቦች ከተመታ በኋላ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን በዚህም የመንቀሳቀስ አቅሙን እንዳጣ የእንግሊዝ የባሕር ንግድ ሥራዎች ኤጀንሲ (UKMTO) ገልጿል።ጥቃቱ ማክሰኞ ዕለትም ቀጥሎ የዋለ ሲሆን መርከበኞቹን የማዳን ሥራ የተጀመረው ሌሊት ላይ ነው።
በኢራን የሚደገፉት ሁቲዎች፤ ኤተርኒቲ ሲ ላይ ጥቃት የፈጸሙት ወደ እስራኤል እየተጓዘ ስለነበረ እንደሆነ አስታውቀዋል።ቁጥራቸው ያልታወቀ ሠራተኞችንም "ደህንነቱ ወደ የተጠበቀ ቦታ" እንደወሰዱ ተናግረዋል።በየመን የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ሁቲዎች "በሕይወት የተረፉ የቡድን አባላትን አፍነው መውሰዳቸውን" ገልጾ፤ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ጥሪ አቅርቧል።
የፊሊፒንስ ባለስልጣናት ከቡድኑ አባላት ውስጥ 21 ያህሉ ዜጎቻቸው እንደሆኑ ተናግረዋል።ከቀሪዎቹ መካከል አንዱ የሩስያ ዜግነት ያለው እንደሆነ እና በጥቃቱ በደረሰበት ከፍተኛ ጉዳት እግሩን እንዳጣም ተገልጿል።ሁቲዎች በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ይህንን ዓይነቱን ጥቃት ሲፈጽሙ ይህ ሁለተኛቸው ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
የየመን ሁቲዎች በጉዞ ላይ የነበረ የጭነት መርከብ ላይ ጥቃት ከፈጸሙ እና መርከቡ ቀይ ባህር ውስጥ ከሰጠመ በኋላ ስድስት መርከበኞች መትረፋቸውን እና ቢያንስ ሦስት ሌሎች ሰዎች መሞታቸውን የአውሮፓ የባህር ኃይል ተልዕኮ አስታወቀ።የላይቤሪያን ባንዲራ የሚያውለበልበው እና በግሪክ የሚንቀሳቀሰው 'ኤተርኒቲ ሲ' የተባለው የጭነት መርከብ 25 ሠራተኞችን ይዞ እየተጓዘ ነበር።
መርከቡ ሰኞ ዕለት ከትንሽ ጀልባዎች በተተኮሱ የሮኬት ቦምቦች ከተመታ በኋላ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን በዚህም የመንቀሳቀስ አቅሙን እንዳጣ የእንግሊዝ የባሕር ንግድ ሥራዎች ኤጀንሲ (UKMTO) ገልጿል።ጥቃቱ ማክሰኞ ዕለትም ቀጥሎ የዋለ ሲሆን መርከበኞቹን የማዳን ሥራ የተጀመረው ሌሊት ላይ ነው።
በኢራን የሚደገፉት ሁቲዎች፤ ኤተርኒቲ ሲ ላይ ጥቃት የፈጸሙት ወደ እስራኤል እየተጓዘ ስለነበረ እንደሆነ አስታውቀዋል።ቁጥራቸው ያልታወቀ ሠራተኞችንም "ደህንነቱ ወደ የተጠበቀ ቦታ" እንደወሰዱ ተናግረዋል።በየመን የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ሁቲዎች "በሕይወት የተረፉ የቡድን አባላትን አፍነው መውሰዳቸውን" ገልጾ፤ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ጥሪ አቅርቧል።
የፊሊፒንስ ባለስልጣናት ከቡድኑ አባላት ውስጥ 21 ያህሉ ዜጎቻቸው እንደሆኑ ተናግረዋል።ከቀሪዎቹ መካከል አንዱ የሩስያ ዜግነት ያለው እንደሆነ እና በጥቃቱ በደረሰበት ከፍተኛ ጉዳት እግሩን እንዳጣም ተገልጿል።ሁቲዎች በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ይህንን ዓይነቱን ጥቃት ሲፈጽሙ ይህ ሁለተኛቸው ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
❤24😭10👍2
1.7 ሚሊዮን ሱዳናውያን ስደተኞች ወደ አገራቸው ተመልሰዋል ተባለ!
የሱዳን ጦር ማዕከላዊ ግዛቶችን ከተቆጣጠረ በወዲህ 1.7 ሚሊዮን ሱዳናውያን ወደ አገራቸው ተመልሰዋል ሲል የተባበሩት መንግስታት አስታውቋል።ወደ ቀያቸው ከተመለሱት 1.7 ሚሊዮን ሱዳናውያን ውስጥ፤- 1.5 ሚሊዮን የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ሲሆኑ፤ 200,000 የሚሆኑት ደግሞ ወደ ሌሎች ሀገራት የተሰደዱ ናቸው።
ስደተኞቹ የተመለሱት የሱዳን ጦር ሴናር ፣ ገዚራ እና ካርቱም ግዛቶችን ከተቆጣጠረ ወዲህ መሆኑን ከፓሪስ ሱዳን ትሪቡን ድረ-ገጽ ትናንት ዘግቧል።"አለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (አይኦኤም) እና UNHCR ትናንት እንዳስታወቁት ከ1.5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ሲሆኑ200,000 የሚጠጉ ስደተኞች ደግሞ ከግብፅ እና ደቡብ ሱዳን ወደ ሀገራቸው ሱዳን ተመልሰዋል" ሲል ድረ-ገጹ ዘግቧል።
በሀገሪቱ ያለው የተፈናቃዮች ቁጥር ጦር ሠራዊቱ ሴናር፣ ገዚራ እና ካርቱም ግዛቶችን ከተቆጣጠረ በኋላ በ13 በመቶ ቀንሷል ተብሏል።በጎርጎሪያኑ ሚያዚያ 2023 ዓ/ም በፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ እና በሱዳን ጦር መካከል የተቀሰቀሰው ግጭት ከ12 ሚሊዮን በላይ ሱዳናውያን ቤት ንብረታቸውን ጥለው እንዲሰደዱ አድርጓል።ከነዚህ መካከል ዘጠኝ ሚሊዮን የሚሆኑት በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ጠቅሶ ዘገባው አመልክቷል።
@YeneTube @FikerAssefa
የሱዳን ጦር ማዕከላዊ ግዛቶችን ከተቆጣጠረ በወዲህ 1.7 ሚሊዮን ሱዳናውያን ወደ አገራቸው ተመልሰዋል ሲል የተባበሩት መንግስታት አስታውቋል።ወደ ቀያቸው ከተመለሱት 1.7 ሚሊዮን ሱዳናውያን ውስጥ፤- 1.5 ሚሊዮን የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ሲሆኑ፤ 200,000 የሚሆኑት ደግሞ ወደ ሌሎች ሀገራት የተሰደዱ ናቸው።
ስደተኞቹ የተመለሱት የሱዳን ጦር ሴናር ፣ ገዚራ እና ካርቱም ግዛቶችን ከተቆጣጠረ ወዲህ መሆኑን ከፓሪስ ሱዳን ትሪቡን ድረ-ገጽ ትናንት ዘግቧል።"አለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (አይኦኤም) እና UNHCR ትናንት እንዳስታወቁት ከ1.5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ሲሆኑ200,000 የሚጠጉ ስደተኞች ደግሞ ከግብፅ እና ደቡብ ሱዳን ወደ ሀገራቸው ሱዳን ተመልሰዋል" ሲል ድረ-ገጹ ዘግቧል።
በሀገሪቱ ያለው የተፈናቃዮች ቁጥር ጦር ሠራዊቱ ሴናር፣ ገዚራ እና ካርቱም ግዛቶችን ከተቆጣጠረ በኋላ በ13 በመቶ ቀንሷል ተብሏል።በጎርጎሪያኑ ሚያዚያ 2023 ዓ/ም በፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ እና በሱዳን ጦር መካከል የተቀሰቀሰው ግጭት ከ12 ሚሊዮን በላይ ሱዳናውያን ቤት ንብረታቸውን ጥለው እንዲሰደዱ አድርጓል።ከነዚህ መካከል ዘጠኝ ሚሊዮን የሚሆኑት በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ጠቅሶ ዘገባው አመልክቷል።
@YeneTube @FikerAssefa
❤22
የትግራይ ኦርቶዶክስ አባቶች የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፓርላማ ንግግር እና በትግራይ ህዝብ ሁኔታ ላይ ያላቸው ግምገማ እንዳሳሰባቸው ገለጹ!
የትግራይ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የሃይማኖት መሪዎች ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በፓርላማ ተገኝተው ያደረጉት ንግግር እንዳሳሰባቸው ገለጹ። የጠ/ሚኒስትሩ ንግግር በጦርነት በተጎዳው ክልሉ ውስጥ ያለውን የሰላም ሂደት ሊያዳክም እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
የሃይማኖት መሪዎቹ፤ “የጠቅላይ ሚኒስትሩ የትግራይ ሁኔታ ግምገማ ከሕዝቡ የኑሮ ሁኔታ ጋር የሚገናኝ አይደለም” ሲሉ ገልጸው፣ እንዲህ ያለው አለመጣጣም ያለውን ሰብአዊ ቀውስ ሊያባብሰው እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
የሃይማኖት መሪዎቹ ረቡዕ ባወጡት መግለጫ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቦታው ያለውን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እውነታዎች መረዳትን በተመለከተ በትግራይ ህዝብ ዘንድ ስጋት እየጨመረ መምጣቱንም ገልጸዋል።
ቤተክርስቲያኗ የሽማግሌዎች ልዑክ በቀጥታ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር እንዲገናኝ እንደምትልክ አስታውቃለች። መግለጫው እንደገለጸው፤ የስብሰባው ዓላማ የትግራይን ሕዝብ ስጋት ለማሳየት እና ለሰላም ሂደቱ የበለጠ ምላሽ ሰጪ እና ውጤታማ አቀራረብን ለመደገፍ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
የትግራይ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የሃይማኖት መሪዎች ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በፓርላማ ተገኝተው ያደረጉት ንግግር እንዳሳሰባቸው ገለጹ። የጠ/ሚኒስትሩ ንግግር በጦርነት በተጎዳው ክልሉ ውስጥ ያለውን የሰላም ሂደት ሊያዳክም እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
የሃይማኖት መሪዎቹ፤ “የጠቅላይ ሚኒስትሩ የትግራይ ሁኔታ ግምገማ ከሕዝቡ የኑሮ ሁኔታ ጋር የሚገናኝ አይደለም” ሲሉ ገልጸው፣ እንዲህ ያለው አለመጣጣም ያለውን ሰብአዊ ቀውስ ሊያባብሰው እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
የሃይማኖት መሪዎቹ ረቡዕ ባወጡት መግለጫ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቦታው ያለውን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እውነታዎች መረዳትን በተመለከተ በትግራይ ህዝብ ዘንድ ስጋት እየጨመረ መምጣቱንም ገልጸዋል።
ቤተክርስቲያኗ የሽማግሌዎች ልዑክ በቀጥታ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር እንዲገናኝ እንደምትልክ አስታውቃለች። መግለጫው እንደገለጸው፤ የስብሰባው ዓላማ የትግራይን ሕዝብ ስጋት ለማሳየት እና ለሰላም ሂደቱ የበለጠ ምላሽ ሰጪ እና ውጤታማ አቀራረብን ለመደገፍ ነው።
@YeneTube @FikerAssefa
❤27👎21👀2