Telegram Web Link
https://www.facebook.com/share/p/15Z9jRs3JB/

ኢትዮጵያ ለአፍሪካ አባል ሀገራት በኒኩለር ኢንጂነሪግ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም እንድትሰጥ በአለም አቀፍ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ (IAEA) ተመረጠች።
===================
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ አለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ (IAEA)፣ በቻይና መንግስት የ Tsingua University፣ ኦንዲሁም የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ (AASTU) ባደረጉት የተለያየ ጊዜ የምክክር መድረክ ለሀገር ውስጥና ለአፍሪካ አባል ሀገራት በኢትዮጵያ የኒኩለር ሳይንስና ቴክኖሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም እንዲሰጥ ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡

ስምምነቱ በኢትዮጵያ የኑክሌር ሳይንስና ቴክኖሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም በመክፈት ፤ በኢትዮጵያ የኑክሌር ሳይንስና ምርምርን በማስፋትና በዘርፉም ኢትዮጵያዊ ኢንጂነሮችን በማፎራት ብሎም ለአፍሪካ አባል ሀገራት የትምህርትና ስልጠና ማዕከል እንዲሆን በማሰብ በኢንዱስትሪ፣ በጤና፣ በግብርና፣ በአካባቢ ሳይንስ፣ በማዕድን፣ በማኑፋክቸሪንግና በሌሎችም ዘርፎች ላይ አቅም በመፍጠር ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ያለመ ነው ተብሏል፡፡

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር በለጠ ሞላ ሀገራችን እያከናወነች ያለውን የኢኮኖሚ እድገት ለማሳለጥ በኒኩለር ሳይንስና ቴክኖሎጂ ብቁ ዜጋን መፍጠር ወሳኝ ሚና እንዳለው ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ የአፍሪካ መግቢያ በር ናት ያሉት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የኒኩለር ሳይንስና ቴክኖሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም ለአፍሪካ IAEA አባል ሀገራት እንዲሰጥ ኢትዮጵያ የተመረጠችው ዘርፈ ብዙ ድርድሮች ተደርገውና የማስተናገድና አቅሟ ከግምት ውስጥ ገብቶ እንደሆ ገልፀዋል፡፡

ሀገራችን የኒኩለር ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዘርፉን ለሰላማዊ ህልውና ኢኮኖሚ ማበልፀጊያነት ለመጠቀም በሰው ሀይል ልማት ላይ በመስራትና ከፖሊሲዎቻችን ጋር በማናበብ ዘርፉን ለሀገራዊ ኢኮኖሚ እድገት ለመጠቀም በትብብር አውድ ላይ በትኩረት እየሰራች ነው ብለዋል፡፡

የአለም አቀፍ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ የቴክኒክ ትብብር ም/ዋና ዳይሬክተር Hua Liu ለአፍሪካ አባል ሀገራት በኢትዮጵያ የኒኩለር ሳይንስና ቴክኖሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም መሰጠቱ ኢኮሚውን ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ከአሁን ቀደም ከሚኒስትሩ ጋር ባደረጓቸው ተከታታይ ውይይቶች የገለጹት ነበር።

አክለውም በኢትዮጵያ የኑኩሌር ሳይንስና ቴክኖሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም ለመስጠት የሚያስችሉ ላብራቶሪና አስፈላጊ ግብዓቶች በአለም አቀፍ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲና በቻይና መንግስት በኩል ድጋፍ እንደሚደረግ መግባባት ላይ ተደርሷል።

በዘርፉ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራሙን ለመስጠት የአዲስ አበባ የሳይንስና ቴክኖለጂ ዩኒቨርስቲና የቻይና Tsinghua ዩኒቨርስቲ በጋራ በመስራት እስከ 10 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን ለ6 ወር በቻይና Tsinghua ዩኒቨርስቲ ሰልጥነው በሀገራች ለአፍሪካ IAEA አባል ሀገራት በኢትዮጵያ የኒኩለር ሳይንስና ቴክኖሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም እንደሚሰጡ ተገልጿል፡፡

በመጨረሻም በቀጣይ ወደስራ የሚያስገባ የሶስትዮሽ የስምምነት ሰነድ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ በአለም አቀፍ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲና በቻይና መንግስት ለመፈራረም የሚያስችል የጋራ አቅጣጫ ተወስዷል፡፡
Happening now at OGH
AASTU CHARITY
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🚀 FINAL CLASS ALERT!
Mechatronics Engineering Students' Association - AASTU
Arduino & Proteus Course
🌟 Big Day Today!
Time to Test, shine and showcase what you’ve learned!

📅 Date: Today May 1
New Time: 12:00pm local time
📍 Venue Block 64, Room 201

✔️ Review all past lessons

Let’s end this course with a BANG! 💥

MESA - AASTU

#FinalShowdown #AASTU #MESA #Mechatronics #Electronics #Arduino #Proteus #On_Hands_Training
🙏A Heartfelt Thank You to the AASTU Family🙏

Yesterday was a day to remember filled with joy, laughter, purpose, and unity. Through your support and generosity, we raised an incredible 42,295 ETB!😊

Town every single person who showed up, contributed, volunteered, or simply spread the word thank you🙏. Your presence made all the difference. The energy we felt wasn’t just excitement it was love, community, and commitment to something greater than ourselves.

We especially want to thank the AASTU community. You showed up in the most beautiful way, and I can't express how proud I am to be part of this family. You proved once again that when we come together, there’s nothing we can’t achieve.

This isn't just about the amount we raised it's about the bond we strengthened😇, the impact we’re about to make, and the memories we created together.

Thank you again for believing, for giving, and for being part of this journey🙏.

https://www.tg-me.com/AASTU_Charity

#AASTU_CHARITY_CLUB
#AASTU_STUDENT_UNION
Our trip is being rescheduled, like you guys have asked out.
          🎉 Don't miss out! 🎉
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
2025/07/07 12:33:18
Back to Top
HTML Embed Code: